Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.2K subscribers
40.8K photos
333 videos
7 files
5.8K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
“አፍሪካውያን ጂኦ-ፖለቲካዊ ጥቅማቸውን ለማስከበር ከዓድዋ ሊማሩ ይገባል”

- ፓን አፍሪካኒስቶች
+++++++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | አፍሪካውያን ጂኦ-ፖለቲካዊ ጥቅማቸውንና ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር የዓድዋን የአንድነትና የእኩልነት እሳቤ ሊቀስሙ እንደሚገባ የፓን አፍሪካኒስት ባለሙያዎች ገለጹ።

ባለሙያዎቹ ይህንን የገለጹት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ሲሆን፤ የአፍሪካ ሕዝቦች የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤን ማጎልበት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ፓን አፍሪካኒስት ሕይወት አዳነ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ዓድዋ ያለ አንድነትና ትብብር ድል እንደሌለ በተግባር ያሳየና የውጭ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ሥነ-ልቦናዊ ጫናዎችን ለመቋቋም ያስቻለ ታላቅ ድል ነው።

በአሁኑ ወቅት የምዕራቡ ዓለም ርዕዮተ ዓለምና የኃያላን ፉክክር በአፍሪካ ላይ ጫና እያስከተለ መሆኑን ጠቁመዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካና ኤዥያ ጥናት ተመራማሪ ዳዊት መዝገበጸጋዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በምዕራባውያን ተቋማትና መንግሥታት የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስና የቀጠናውን ጥቅም ለማስከበር ዓድዋ ዋነኛው መንገድ መሆኑን ገልጸዋል።

የአፍሪካ መሪዎችና አህጉራዊ ተቋማት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የወታደራዊ ጥንካሬን ለመገንባት በአንድነት ሊሠሩ እንደሚገባ መክረዋል።

ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ለመቋቋም አፍሪካውያን በዓድዋ የአንድነት መንፈስ በመመራት የጋራ ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ በጋራ መቆም እንዳለባቸውም ባለሙያዎቹ በአጽንኦት አሳስበዋል።

በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ዓድዋ #ፓን_አፍሪካኒዝም #አፍሪካ #ጂኦ_ፖለቲካ #ሉዓላዊነት #ሕይወት_አዳነ #ዳዊት_መዝገበጸጋዬ
1👍1
“የነበረው ጭቅጭቅ ይታወሳል፤ ነገር ግን ሰላም ነው ሚሻለው ብለን የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ ከፍለናል”

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ባደረጉት ቆይታ

#PMOEthiopia
👍32
“የካራማራ ድል የኢትዮጵያ ታላቅነት ማሳያ ነው”

- በኢትዮ- ሶማሊያ ጦርነት የፓራኮማንዶ ብርጌድ አዛዥ
+++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | የካራማራ ድል መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሀገሩ ነፃነት ያለውን ፍቅርና ታላቅነት በተግባር ያሳየበት የታሪክ ምዕራፍ መሆኑን በኢትዮ-ሶማሊያ ጦርነት የአንደኛ የፓራኮማንዶ ብርጌድ አዛዥ የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማሪያም ገለጹ።

ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ሀብተማሪያም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፣ በወቅቱ የነበረው የጦር ሁኔታ ተመጣጣኝ ባልነበረበትና ሀገሪቱ በውስጥ ችግሮች ተወጥራ በነበረችበት ወቅት ወራሪውን የሶማሊያ ኃይል በአጭር ጊዜ ዝግጅት ድል ማድረግ መቻሉ ተአምራዊ ነበር።

ሶማሊያ ጅግጅጋ ለመድረስ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ብትገሰግስም፣ የኢትዮጵያ ሠራዊት ካራማራ ላይ ባደረገው ተጋድሎና ምሽግ በመያዝ የጠላትን ጉዞ መግታት መቻሉን አውስተዋል።

የክተት አዋጁን ተከትሎ ከ120 ሺህ በላይ ሕዝብ በ48 ሰዓታት ውስጥ ታጠቅ ጦር ሰፈር በመክተት ያሳየው ወገንተኝነት የድሉ መሠረት መሆኑን ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ገልጸዋል።

በወቅቱ ሐረርና ድሬዳዋን ከመከላከል ባለፈ፣ የወገን ጦር ባደረገው ከፍተኛ ጥቃት ጠላት ተሸንፎ እስከ ሐርጌሳ እንዲገባ መደረጉንና በኦጋዴን አካባቢዎች የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ዳግም መውለብለቡን ተርከዋል።

ትውልዱ ከዚህ የታሪክ አጋጣሚ በመማር፣ ለሀገር ሉዓላዊነትና ሰላም ዘመናዊና በሚገባ የሠለጠነ የሰው ኃይል ያለው ሠራዊት የመገንባት አስፈላጊነትን ሊገነዘብ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በበኃይሉ አበራ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ካራማራ #ኢትዮጵያ #የካራማራ_ድል #ሶማሊያ #ታሪክ #ተስፋዬ_ሀብተማሪያም #ሉዓላዊነት
👍61
#ፕሬስ_መረጃ_ማጣሪያ - በመለያ የምርት ቁጥር 620 የተመረቱ የፋይን (Fine) የታሸጉ የውኃ ምርቶች ባዕድ ነገር የታየባቸው በመሆናቸው ምርቶችን ማህበረሰቡ እንዳይጠቀም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አሳስበ።
https://www.facebook.com/share/p/14WPmnaX475

#የጤናጥንቃቄ #PublicHealth #FoodSafety #የውኃጥራት #HealthAlertEthiopia #ፋይንውኃ #FineWater #የታሸገውኃ #ጥራትቁጥጥር #EFDA #የምግብናመድኃኒትባለስልጣን #ConsumerProtection #Ethiopia
1
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።

🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።

ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።

📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
5🔥1
“ህጋዊ የንግድ ስርዓትን የሚያቀጭጩ እና እንቅፋት የሚፈጥሩ ነገሮች በሙሉ ሊስተካከሉ ይገባል”

- አቶ ሙስጠፌ መሐመድ
የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር
+++++++++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | ህጋዊ የንግድ ስርዓትን የሚያቀጭጩ እና እንቅፋት የሚፈጥሩ ነገሮች በሙሉ ሊስተካከሉ ይገባል ሲሉ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሐመድ ገለጹ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በጂግጂጋ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘውን “ጉምሩክ ስለኢትዮጵያ” የውይይት መድረክ ላይ የመክፈቻ ንግግር ሲያደርጉ እንደገለጹት፤ ህገ-ወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድ ህጋዊ ነጋዴዎችን ከገበያ በማውጣት እና የሀገር ኢኮኖሚን በማቀጨጭ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል።

ኮንትሮባንድ የንግድ ስርዓቱን ከማዛባት ባሻገር የማህበረሰብ ጤና፣ ሰላም እና ደህንነት ላይ እክል የሚፈጥር የሀገር እክል ነው ብለዋል።

የኮንትሮባንድ መረብ ውስብስብ እና በርካታ ተዋናዮች ያሉበት በመሆኑ በፀጥታ አካላት ብቻ በሚደረግ ጥረት እልባት ሊያገኝ አይችልም ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ይህንን የልማት ጠላት ለመከላከል እና ለማስወገድ ድርሻውን ሊወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል።

ህጋዊ ነጋዴዎች የንግድ ህግን አክብረው እና ለታክስ ህግ ተገዥ ሆነው በመስራት ለክልሉም ሆነ ለሀገሪቱ ገቢ እያስገኙ እንደሚገኙ አቶ ሙስጠፌ ገልጸዋል።

አክለውም፣ ክልሉ የሚሰራቸው የልማት ስራዎች ከግብር ከፋዩ በሚገኝ ገቢ የሚሰራ ነው፤ በዚህም ህጋዊ ነጋዴዎቻችን ሊኮሩ ይገባል ብለዋል።

ህጋዊ ነጋዴዎችን የንግድ ስራዎቻቸውን ለማስፋፋት ምቹ የንግድ ስነ-ምህዳር በመፍጠር እና አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ የክልሉ መንግስ እንደሚያበረታታቸውም አመልክተዋል።

በዮሐንስ መልካሙ (ጂግጂጋ)
8