Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25.2K subscribers
40.9K photos
333 videos
7 files
5.8K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
53ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው መደመር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአዋጅ ቁጥር 1294/2015 መሠረት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የሚቋቋም ሲሆን በዘርፉ ወጣቶችን ለማሰልጠንና ለሀገር ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ምሁራንን ለማፍራት የሚሰራ ነው፡፡ ደንቡ የዩኒቨርሲቲውን ተግባርና ሃላፊነት በመደንገግ ተቋሙ ለሀገር ዕድገት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው ለባለሃብቶች ካሳ ለመክፈል ግዴታ የሚገባበትን ሁኔታ ለመወሰን በቀረበ ደንብ ላይ ነው፡፡ ባለሀብቶች የሀገራችንን የኢኮኖሚ እድገት ሊያፋጥኑ በሚችሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው በሶስት የፋይናንስ ድጋፍ ሰምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪው ለብሄራዊ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል ከኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ የስልሳ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሃያ ሶስት ሺ /60,223,000/ የአሜሪካን ዶላር ብድር ሲሆን ከወለድ ነጻ፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች 0.1% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበት እና የ15 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡

ሁለተኛው ለታዳሽ፣ የተቀናጀ፣ ዘላቂ ኃይል እና ዲጂታላይዜሽን ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከፈረንሳይ የልማት ኤጄንሲ የሰማንያ ሚሊዮን /80,000,000/ ዩሮ ብድር ሲሆን አነስተኛ ወለድ 1.2% የሚከፈልበት፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች 0.5% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበት እና የ7 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ20 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡

ሶስተኛው ለከተማ ልማታዊ ሴፍትኔትና ሥራ ፈጠራ የሚውል ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር የአንድ መቶ ሰማንያ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ /184,100,000/ ኤስ ዲ አር ብድር ሲሆን ከወለድ ነጻ፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች እንዲሁም ጥቅም ላይ ላልዋለው ገንዘብ 1.25% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበትና የ6 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ30 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ሶስቱም የብድር ስምምነቶች ከአገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ ረቂቅ አዋጆቹ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርአት ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በሀገራችን የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዐትን ተግባራዊ ለማድረግ አዋጅ ቁጥር 372/1996 ወጥቶ በስራ ላይ የቆየ ቢሆንም ለአዋጁ ማስፈጸሚያ ደንብ ባለመውጣቱ በአፈጻጸም ሂደት ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶችን ለማረም፣ ለአዋጁ አፈጻጸም አስቻይ የሆኑ ዝርዝር ጉዳዮችን ለመደንገግና አስፈላጊውን የቁጥጥር ሥርዐትና መዋቅራዊ አደረጃጀት ለመፍጠር እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

5. በተጨማሪም የወርቅ ማዕድን እና የብረት ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ከማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ከመፍጠር፣ ለኢኮኖሚያችን አዎንታዊ ሚና ከመወጣት አንጻር ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡

6. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የቱሪዝም ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ የነበረው የቱሪዝም ልማት ፖሊሲ በዘርፉ የተከሰቱ ለውጦችን ከማስተናገድ፣ መልካም አጋጣሚዎችና የመልማት አቅሞችን ከመጠቀም እና ለአገራዊ ዕድገት ሚናውን ከመወጣት አንጻር ክፍተቶች የነበሩበት ነው፡፡ ዘርፉን በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከተቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ ጋር አጣጥሞ በመምራት እና በማልማት ለአገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ማስቻል አስፈላጊ በመሆኑ ረቀቂ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

#PMOEthiopia
3
"አርበኛን የሚያጀግን ባንዳን የሚፀየፍ ትውልድ ልንገነባ ይገባል"

- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
+++++++++++++++++

ጋዜጣ_ፕላስ | አርበኛን የሚያጀግንና ባንዳን የሚፀየፍ ትውልድ መገንባት እንደሚገባ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ይህንን የገለጹት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ነው።

በዓድዋ ዘመን ሀገርን በመካድ ለጠላት የተሰለፉ ባንዳዎች እንደነበሩ ሁሉ፣ ዛሬም የባንዳነት ርዝራዦች ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመሰለፍ ብሔራዊ ጥቅምን ለመሸጥ እየሠሩ መሆኑን ጠቁመዋል።

"ገመናን ለመሸፈን ተብሎ እውነታው ካልተገለጠ ባንዳነት በአደባባይ ወጥቶ የአርበኛ ማኅበረሰብ ግንባታን አደጋ ላይ ይጥላል" ሲሉም አሳስበዋል።

መምህራንንና የሕክምና ባለሙያዎችን የሚያግቱ፣ ተማሪዎችን የሚገድሉና የልማት ፕሮጀክቶችን ለማፍረስ የተላኩ ኃይሎች ሀገርን ለማዳከም እየተረባረቡ መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጠቁመዋል።

"እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን" ያሉት ኢታማዦር ሹሙ፤ ታዝሎ የሚመጣውን የውጭ ጠላትና አዝሎ የሚመጣውን የሀገር ውስጥ ባንዳ በእኩል ደረጃ ተዋግቶ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።

በክብረአብ በላቸው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ዓድዋ #ሉዓላዊነት #ጀግንነት #ብርሃኑ_ጁላ #አርበኝነት #130ኛው_ዓድዋ
👍31
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በ130ኛው የዓድዋ ድል በዓል ላይ ከተናገሩት የተወሰደ
👍1
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት

ዛሬ፤ በመላው አፍሪካ እና ጥቁር ህዝብ ላይ ጨልሞ በነበረ ሰማይ ጸሀይ የፈነጠቀበት ቀን ነው! ኢትዮጵያ ድንበሯን ገፍቶ ሉዐላዊነቷንና የህዝቧን ነጻነት የደፈረውን የወራሪውን ጦር በአድዋ ተራሮች ድል የነሳችበትና ለሶስት ሺህ አመታት ያልተደፈረውን ስልጣኔዋን ያጸናችበት ቀኗ ነው፡፡ ተከብረን የምንኖርባትን ኢትዮጵያን ከድንቅ ስልጣኔ እና ታሪክ ጋር ከነታላቅ ክብሯ በደም መስዋእትነት ላስረከቡን አባቶቻችን ክብር ይገባቸዋል፡፡

ዛሬ የምንኖር ኢትዮጵያውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን ሞተው ያቆሙልንን ሀገር በአንድነትና በፍቅር በመኖር ልናስቀጥል ይገባል፡፡

ከእነሱ ተምረን ድህነትን፣ መከፋፍልንና ኋላ ቀር አስተሳሰብን አሻፈረኝ በማለት ኢትዮጵያን ወደ ብልጽግና ልናሻግር ይገባል፡፡ ኢትዮጵያ ከሆነችው በላይ ታላቅ የምትሆንበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም!
3
ዛሬ ምሽት እንደተለመደው በረመዳን መንፈስ ከቡሩንዲ፣ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ከሶማሊያ፣ ከኢራቅ፣ ከሶሪያ፣ ከፍልስጤም፣ ከአፍጋኒስታን፣ ከኤርትራ፣ ከየመንና ሱዳን ከመጡ ስደተኞች ጋር አፍጥር ታድመናል።

-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢዜአ ጋር በትግርኛ ያደረጉት ቆይታ- ነገ ምሽት 2:30 ይጠብቁን!

ቀዳማይ ሚኒስትር ዐቢይ ኣሕመድ(ዶ/ር) ምስ ኢዜኣ ብቋንቋ ትግርኛ ዝገበርዎ ፃንሒት- ፅባሕ ምሸት ሰዓት 2፡30 ይፀበዩና!

#PMOEthiopia
5🔥5
🔥 ተመሳሳይ ያረጁ ዜናዎችን ማንበብ ይብቃዎ! አልጎሪዝምዎን ይቀይሩ።

🇪🇹 🌍 ከኢትዮጵያ፣ ከአፍሪካ እና ከአለም አቀፍ ዙሪያ የተሰሙ አዳዲስ ክስተቶችን በተለየ ምልከታ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ይከታተሉ እንዲሁም ያልተጋሩ ፎቶዎችንና ቪዲዮዎችን በየእለቱ በስፑትኒክ ኢትዮጵያ ብቻ ያገኛሉ።

ከሌሎች መገናኛ ብዙኃን የማያገኟቸውን ትኩስ ትኩስ መረጃዎችን ስፑትኒክ ኢትዮጵያ ለእርስኦ ያቀርብልዎታል።

📌አዳዲስ መረጃዎችን በየእለቱ ለመከታተል አሁኑኑ ቻናላችንን በመቀላቀል ያልተሰሙ መረጃዎችን ይከታተሉ::
👇🏾👇🏾👇🏾
https://t.me/+eM_pls45dPAyZjZi
5👍1
“ኢትዮጵያ የባሕር በር አያስፈልጋትም የሚል የፖለቲካ ፓርቲ ካለ መሰረዝ ነው ያለበት”

- አቶ ግርማ ሰይፉ
+++++++++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ የባሕር በር አያስፈልጋትም የሚል የፖለቲካ ፓርቲ ካለ ከፓርቲነት ተሰርዞ ከፖለቲካው ምዕራፍ መውጣት እንዳለበት የኢዜማ አመራርና የአዲስ አበባ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ ግርማ ሰይፉ ተናገሩ።

አቶ ግርማ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ የሀገሪቱን የባሕር በር የማረጋገጥ ጉዳይ በቀጣይ ሕገ-መንግሥቱ በሚሻሻልበት ወቅት ትኩረት ተሰጥቶት የመንግሥት ግዴታ ተደርጎ ሊደነገግ ይገባል።

ለዚህም እንደ ምሳሌ ያነሱት የግብፅ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 19 የናይልን ውኃ ደኅንነት ማስጠበቅ የመንግሥት ግዴታ መሆኑን እንደሚደነግግ ጠቅሰው፣ በኢትዮጵያም የባሕር በርን ማስጠበቅ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታ ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።
ብሔራዊ ጥቅምን የማስከበር ኃላፊነት በመንግሥት ላይ መጣል እንዳለበት የገለጹት አቶ ግርማ፤ ከዚህ ብሔራዊ ጥቅም በተቃራኒ የሚቆሙ አካላትን መቆጣጠር የመንግሥት ግዴታ ሊሆን እንደሚገባም አመልክተዋል።

የባሕር በር ጥያቄ ከፖለቲካ ወገንተኝነት ባለፈ የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑንና ማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት ለዚህ ግብ መሳካት ቅድሚያ መስጠት እንዳለበትም በአጽንኦት ገልጸዋል።

በማህሌት አብዱል
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #የባሕር_በር #ብሔራዊ_ጥቅም #ፖለቲካ_ፓርቲ #ግርማ_ሰይፉ #ሕገ_መንግሥት
8👍1
የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ማድረግ የዘመናችን ዓድዋ ነው
+++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ምላሽ እንዲያገኝ ማድረግና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የዘመናችን የዓድዋ ድል ተደርጎ የሚቆጠር መሆኑን የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር ሰለሞን ተፈራ ገለጹ።

ምሁሩ ሰለሞን ተፈራ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ የዓድዋ ድል የሀገሪቱን የግዛት ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ የተደረገ ታላቅ ተጋድሎ እንደነበረ ሁሉ፣ እውነተኛ ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው ደግሞ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ነፃነት ማረጋገጥ ሲቻል ነው።

የባሕር በር ማጣት ኢትዮጵያን የጂኦግራፊ እስረኛ በማድረግ የኢኮኖሚ ነፃነቷን እንደሚገድብ የጠቀሱት ምሁሩ፣ ይህንን ጥያቄ መፍታት የዘመናችን የዓድዋ ድል ተደርጎ እንደሚወሰድ አስረድተዋል።

እንደ ሰለሞን ማብራሪያ፤ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በዓድዋ መንፈስና በአንድነት በመቆማችን የተመዘገበ ሁለተኛው የዓድዋ ድል ነው።

በተመሳሳይ የባሕር በር ጉዳይም መላው ኢትዮጵያውያን በአንድነት ቆመው ሊያሳኩት የሚገባ ብሔራዊ አጀንዳ መሆኑን ጠቁመዋል።

አየር መንገድ ያስጀመረው አዲስ አየር ማረፊያ እና የኒውክሌር ኃይል ግንባታ ጥረቶችም የአባቶቻችንን የፖለቲካ ድል በኢኮኖሚ በማጀብ የሀገርን ክብር የሚያጸኑ ግዙፍ ፕሮጀክቶች መሆናቸውን አመልክተዋል።

በፋንታነሽ ክንዴ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ዓድዋ_ድል #ኢትዮጵያ #የባሕር_በር #ሉዓላዊነት #ኢኮኖሚ #ሰለሞን_ተፈራ
4👍3
“አፍሪካውያን ጂኦ-ፖለቲካዊ ጥቅማቸውን ለማስከበር ከዓድዋ ሊማሩ ይገባል”

- ፓን አፍሪካኒስቶች
+++++++++++++++++++++++

#ጋዜጣ_ፕላስ | አፍሪካውያን ጂኦ-ፖለቲካዊ ጥቅማቸውንና ሉዓላዊነታቸውን ለማስከበር የዓድዋን የአንድነትና የእኩልነት እሳቤ ሊቀስሙ እንደሚገባ የፓን አፍሪካኒስት ባለሙያዎች ገለጹ።

ባለሙያዎቹ ይህንን የገለጹት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ሲሆን፤ የአፍሪካ ሕዝቦች የፓን አፍሪካኒዝም እሳቤን ማጎልበት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ፓን አፍሪካኒስት ሕይወት አዳነ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ዓድዋ ያለ አንድነትና ትብብር ድል እንደሌለ በተግባር ያሳየና የውጭ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ሥነ-ልቦናዊ ጫናዎችን ለመቋቋም ያስቻለ ታላቅ ድል ነው።

በአሁኑ ወቅት የምዕራቡ ዓለም ርዕዮተ ዓለምና የኃያላን ፉክክር በአፍሪካ ላይ ጫና እያስከተለ መሆኑን ጠቁመዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካና ኤዥያ ጥናት ተመራማሪ ዳዊት መዝገበጸጋዬ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በምዕራባውያን ተቋማትና መንግሥታት የሚደርሰውን ጫና ለመቀነስና የቀጠናውን ጥቅም ለማስከበር ዓድዋ ዋነኛው መንገድ መሆኑን ገልጸዋል።

የአፍሪካ መሪዎችና አህጉራዊ ተቋማት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የወታደራዊ ጥንካሬን ለመገንባት በአንድነት ሊሠሩ እንደሚገባ መክረዋል።

ዓለም አቀፋዊ ጫናዎችን ለመቋቋም አፍሪካውያን በዓድዋ የአንድነት መንፈስ በመመራት የጋራ ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ በጋራ መቆም እንዳለባቸውም ባለሙያዎቹ በአጽንኦት አሳስበዋል።

በልጅዓለም ፍቅሬ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ዓድዋ #ፓን_አፍሪካኒዝም #አፍሪካ #ጂኦ_ፖለቲካ #ሉዓላዊነት #ሕይወት_አዳነ #ዳዊት_መዝገበጸጋዬ
1👍1