ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዘርባጃን ሪፐብሊክ የነበራቸውን ጉብኝት በማጠናቀቅ ዛሬ ከሰአት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።
Following a successful Official Visit to the Republic of Azerbaijan, Prime Minister Abiy Ahmed has returned to Ethiopia this afternoon.
#PMOEthiopia
Following a successful Official Visit to the Republic of Azerbaijan, Prime Minister Abiy Ahmed has returned to Ethiopia this afternoon.
#PMOEthiopia
❤14
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለ130ኛው የዐድዋ ድል በዓል ያስተላለፉት መልዕክት
++++++++++++
የዐድዋ ድል የኢትዮጵያውያንን የማይቀየር ዐቋምና ዐቅም ያሳየ ድል ነው። ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ብሔራዊ ጥቅም፣ ነጻነትና ሉዓላዊነት ላይ የማይቀየር ዐቋም አላቸው። ይሄንን ዐቋማቸውን በጽኑ መሠረት ላይ ለመትከል ደግሞ ሁሉንም አቅማቸውን ይጠቀማሉ።
ሥርዓታትና መሪዎች ሊቀየሩ ይችላሉ፤ በአንዳንድ ጉዳዮች ልዩነቶች ይኖሯቸው ይሆናል፤ ስለ ሀገራቸው ያላቸው ዐቋምና ለሀገራቸው የሚያወጡት አቆም ግን አይቀየርም።
ወደ ዐድዋ የዘመቱ ጀግኖቻችን ሁሉ በሁሉም ነገር የተስማሙ አይደሉም። አንድ ዓላማ ነበራቸው እንጂ አንድ ዓይነት አልነበሩም። አንድ ሀገር ነበራቸው እንጂ አንድ ባህልና እምነት አልነበራቸውም።
በዚያ ጊዜ ሀገራቸውን ከድተው ከጠላት ጋር ያበሩ ባንዳዎች ነበሩ። ለጊዜያዊ ጥቅም ሲሉ ዘላቂ የሀገራቸውን ጥቅም የሸጡ ምንደኞችም ነበሩ። ከባዳ ጋር ወግነው ወገናቸውን ያስማሙ ደላሎችም ነበሩ።
ጀግኖች እናቶቻችን እና አባቶቻችን የተዋጉት ከወራሪው የጣሊያን ጦር ጋር ብቻ አልነበረም። ከምንደኞች፣ ከባንዳዎች እና ከሀገር ደላሎች ጭምር እንጂ። ዐርበኝነት ማለት ባዳና ባንዳን ማሸነፍ ማለት ነው። ዐርበኝነት ማለት ለሀገር ጥቅም ሲባል የግል ጥቅምን ማሸነፍ ማለት ነው። ዐርበኝነት ማለት ለሀገር ክብር ሲባል የራስን ክብር መሠዋት ነው።
የዐድዋ ድል በዓል እነዚህን ሁሉ የምናስታውስበት ነው። የዐድዋ ድል በዓል የኢትዮጵያውያንን ዐቅምና አቋም እንደገለጠው ሁሉ ዛሬም በጸና አቋም፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዐቅም የምንገልጥበት ጊዜ ነው። በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በማዕድን እና በዲጂታል ሀገራችን ያላትን ዐቅም መግለጥ አለብን። የዐድዋን ድል በሁሉም ዘርፍ ለመድገም፣ የኢትዮጵያ ዐቅም ጽኑ መሠረት ሊኖረው ይገባል።
ሀገርን ዐቅም ያሳድጋታል፤ ዐቅም ይገነባታል። ሀገርን ዐቅም ይሠራታል። ዐቋም ያጸናታል። ሀገርን ዐቅም ያራምዳታል፤ ዐቋም ያሻግራታል።
የዐድዋ ድል በዓላችን የኢትዮጵያን ዐቅም ይበልጥ የምንገነባበትና የኢትዮጵያውያንን ዐቋም ይበልጥ የምናጸናበት እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
++++++++++++
የዐድዋ ድል የኢትዮጵያውያንን የማይቀየር ዐቋምና ዐቅም ያሳየ ድል ነው። ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ብሔራዊ ጥቅም፣ ነጻነትና ሉዓላዊነት ላይ የማይቀየር ዐቋም አላቸው። ይሄንን ዐቋማቸውን በጽኑ መሠረት ላይ ለመትከል ደግሞ ሁሉንም አቅማቸውን ይጠቀማሉ።
ሥርዓታትና መሪዎች ሊቀየሩ ይችላሉ፤ በአንዳንድ ጉዳዮች ልዩነቶች ይኖሯቸው ይሆናል፤ ስለ ሀገራቸው ያላቸው ዐቋምና ለሀገራቸው የሚያወጡት አቆም ግን አይቀየርም።
ወደ ዐድዋ የዘመቱ ጀግኖቻችን ሁሉ በሁሉም ነገር የተስማሙ አይደሉም። አንድ ዓላማ ነበራቸው እንጂ አንድ ዓይነት አልነበሩም። አንድ ሀገር ነበራቸው እንጂ አንድ ባህልና እምነት አልነበራቸውም።
በዚያ ጊዜ ሀገራቸውን ከድተው ከጠላት ጋር ያበሩ ባንዳዎች ነበሩ። ለጊዜያዊ ጥቅም ሲሉ ዘላቂ የሀገራቸውን ጥቅም የሸጡ ምንደኞችም ነበሩ። ከባዳ ጋር ወግነው ወገናቸውን ያስማሙ ደላሎችም ነበሩ።
ጀግኖች እናቶቻችን እና አባቶቻችን የተዋጉት ከወራሪው የጣሊያን ጦር ጋር ብቻ አልነበረም። ከምንደኞች፣ ከባንዳዎች እና ከሀገር ደላሎች ጭምር እንጂ። ዐርበኝነት ማለት ባዳና ባንዳን ማሸነፍ ማለት ነው። ዐርበኝነት ማለት ለሀገር ጥቅም ሲባል የግል ጥቅምን ማሸነፍ ማለት ነው። ዐርበኝነት ማለት ለሀገር ክብር ሲባል የራስን ክብር መሠዋት ነው።
የዐድዋ ድል በዓል እነዚህን ሁሉ የምናስታውስበት ነው። የዐድዋ ድል በዓል የኢትዮጵያውያንን ዐቅምና አቋም እንደገለጠው ሁሉ ዛሬም በጸና አቋም፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዐቅም የምንገልጥበት ጊዜ ነው። በግብርና፣ በኢንዱስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በማዕድን እና በዲጂታል ሀገራችን ያላትን ዐቅም መግለጥ አለብን። የዐድዋን ድል በሁሉም ዘርፍ ለመድገም፣ የኢትዮጵያ ዐቅም ጽኑ መሠረት ሊኖረው ይገባል።
ሀገርን ዐቅም ያሳድጋታል፤ ዐቅም ይገነባታል። ሀገርን ዐቅም ይሠራታል። ዐቋም ያጸናታል። ሀገርን ዐቅም ያራምዳታል፤ ዐቋም ያሻግራታል።
የዐድዋ ድል በዓላችን የኢትዮጵያን ዐቅም ይበልጥ የምንገነባበትና የኢትዮጵያውያንን ዐቋም ይበልጥ የምናጸናበት እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
የካቲት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
❤6
“የዓድዋ ድል ለጥቁር ህዝቦች የጥንካሬ ምንጭ ሆኗል”
- አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ዓድዋ ለአፍሪካውያንና ለመላው የጥቁር ህዝብ የጥንካሬ ምንጭ ተደርጎ የሚወሰድ ድል ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ገለጹ፡፡
ቃል አቀባዩ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ከጋዜጣ ፕላስ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በፋሺስት ኢጣሊያ የተቃጣባትን የቅኝ ግዛት ወረራ በዓድዋ በመቀልበስ እና ድል በማድረግ ነጻነቷን አረጋግጣለች፡፡
የዓድዋ ድል በጥቁር ህዝቦች ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ታሪክ ነው ያሉት አምባሳደር ነቢያት፤ ድሉ ለአፍሪካውያን የጥንካሬ ምንጭ ተደርጎ የሚወሰድ ድል ብለዋል።
የዓድዋ ድል በጥቁር ህዝቦች ዘንድ ወራሪ ኃይልን መስበር ይቻላል የሚል እምነት የፈጠረ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ዓድዋ በጸረ ቅኝ ግዛት ትግሉን በሚመሩ ልሂቃን መካከል የሚታወቅ ታሪክ እንደሆነ በመግለጽ፤ ድሉ ትልቅ የመንፈስ ስንቅና ጥንካሬ ሆኖ ለሌሎች ጸረ ቅኝ ግዛት ትግሎች እርሾ ነበር ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የነጻነት ተጋድሎና ውጤቱ በኢትዮጵያ ተጀምሮ በኢትዮጵያ የሚያልቅ እንዳልሆነ የገለጹት አምባሳደር ነቢያት፤ ድሉ ለመላው አፍሪካውያንና ጥቁር ህዝቦች የነጻነት አርማና ማህተም ሆኖ ይኖራል ብለዋል።
ዓድዋ በየጊዜው ሲዘከር ብዙ ታሪክ የሚመዘዝለት እንደሆነና በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የሚታወቅ ታሪካዊ ክስተት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
+++++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት
@ጋዜጣ-ፕላስ
#ዓድዋ #ጥቁር_ሕዝቦች #አፍሪካ #ኢትዮጵያ #AdwaVictory #PanAfricanism
- አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው
+++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ዓድዋ ለአፍሪካውያንና ለመላው የጥቁር ህዝብ የጥንካሬ ምንጭ ተደርጎ የሚወሰድ ድል ነው ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ገለጹ፡፡
ቃል አቀባዩ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው ከጋዜጣ ፕላስ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በፋሺስት ኢጣሊያ የተቃጣባትን የቅኝ ግዛት ወረራ በዓድዋ በመቀልበስ እና ድል በማድረግ ነጻነቷን አረጋግጣለች፡፡
የዓድዋ ድል በጥቁር ህዝቦች ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ታሪክ ነው ያሉት አምባሳደር ነቢያት፤ ድሉ ለአፍሪካውያን የጥንካሬ ምንጭ ተደርጎ የሚወሰድ ድል ብለዋል።
የዓድዋ ድል በጥቁር ህዝቦች ዘንድ ወራሪ ኃይልን መስበር ይቻላል የሚል እምነት የፈጠረ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ዓድዋ በጸረ ቅኝ ግዛት ትግሉን በሚመሩ ልሂቃን መካከል የሚታወቅ ታሪክ እንደሆነ በመግለጽ፤ ድሉ ትልቅ የመንፈስ ስንቅና ጥንካሬ ሆኖ ለሌሎች ጸረ ቅኝ ግዛት ትግሎች እርሾ ነበር ሲሉ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ የነጻነት ተጋድሎና ውጤቱ በኢትዮጵያ ተጀምሮ በኢትዮጵያ የሚያልቅ እንዳልሆነ የገለጹት አምባሳደር ነቢያት፤ ድሉ ለመላው አፍሪካውያንና ጥቁር ህዝቦች የነጻነት አርማና ማህተም ሆኖ ይኖራል ብለዋል።
ዓድዋ በየጊዜው ሲዘከር ብዙ ታሪክ የሚመዘዝለት እንደሆነና በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የሚታወቅ ታሪካዊ ክስተት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በማርቆስ በላይ
+++++++++++++++++
@የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት
@ጋዜጣ-ፕላስ
#ዓድዋ #ጥቁር_ሕዝቦች #አፍሪካ #ኢትዮጵያ #AdwaVictory #PanAfricanism
❤3
ዓመታዊ ባህል
የቅዱሱን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው የማኅበረሰባችን ክፍሎች የኢፍጣር መርሃ-ግብር አካሂደናል። የዛሬው ኢፍጣር በመተዛዘን፣ በፍቅር፣ በአንድነት እና ማኅበራዊ ዋጋን ከፍ በማድረግ ተከናውኗል።
-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
የቅዱሱን የረመዳን ወር ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላላቸው የማኅበረሰባችን ክፍሎች የኢፍጣር መርሃ-ግብር አካሂደናል። የዛሬው ኢፍጣር በመተዛዘን፣ በፍቅር፣ በአንድነት እና ማኅበራዊ ዋጋን ከፍ በማድረግ ተከናውኗል።
-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
👍8❤2
ከዐድዋ ተራሮች እስከ ጉባ፤ ዐድዋ በልኩ ሲዘከር!
የዐድዋ ድል የጦር ሜዳ ድል ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል በራሷ እንደምትወስን ለዓለም የታወጀበት አዋጅ ነበር።
መስዋዕትነታቸውን የምንዘክረው በትላንትናው ግርማ በመኖር ብቻ ሳይሆን፣ የዛሬውን አሻራችንን በመገንባት ነው። በዐድዋ መንፈስ እየተመራን የሀገራችንን የወደፊት እጣ ፈንታ መቅረጻችንን እንቀጥላለን።
ከዐባይ ወንዝ የተነሳው 'ሁለተኛው ዐድዋችን' ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ ያለፈውን ዘመን የምንዘክረው የአሁኑን ጊዜ በአሸናፊነት በመምራት መሆኑን ሕያው ምስክር ነው።
መደመርን ባነጸው በዐድዋ መንፈስ ስንመራ ሀገራችን የማታሳካው አንዳች ነገር አይኖርም። በአንድ ዓላማ በመሰለፍ በመደመር ስንጓዝ የኢትዮጵያ አቅም ከቶ ሊገታ አይችልም። ታላቅ የነበርን፤ ይበልጥም ታላቅ እንሆናለን!
#PMOEthiopia
የዐድዋ ድል የጦር ሜዳ ድል ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል በራሷ እንደምትወስን ለዓለም የታወጀበት አዋጅ ነበር።
መስዋዕትነታቸውን የምንዘክረው በትላንትናው ግርማ በመኖር ብቻ ሳይሆን፣ የዛሬውን አሻራችንን በመገንባት ነው። በዐድዋ መንፈስ እየተመራን የሀገራችንን የወደፊት እጣ ፈንታ መቅረጻችንን እንቀጥላለን።
ከዐባይ ወንዝ የተነሳው 'ሁለተኛው ዐድዋችን' ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ ያለፈውን ዘመን የምንዘክረው የአሁኑን ጊዜ በአሸናፊነት በመምራት መሆኑን ሕያው ምስክር ነው።
መደመርን ባነጸው በዐድዋ መንፈስ ስንመራ ሀገራችን የማታሳካው አንዳች ነገር አይኖርም። በአንድ ዓላማ በመሰለፍ በመደመር ስንጓዝ የኢትዮጵያ አቅም ከቶ ሊገታ አይችልም። ታላቅ የነበርን፤ ይበልጥም ታላቅ እንሆናለን!
#PMOEthiopia
🥰2❤1
53ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው መደመር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአዋጅ ቁጥር 1294/2015 መሠረት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የሚቋቋም ሲሆን በዘርፉ ወጣቶችን ለማሰልጠንና ለሀገር ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ምሁራንን ለማፍራት የሚሰራ ነው፡፡ ደንቡ የዩኒቨርሲቲውን ተግባርና ሃላፊነት በመደንገግ ተቋሙ ለሀገር ዕድገት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው ለባለሃብቶች ካሳ ለመክፈል ግዴታ የሚገባበትን ሁኔታ ለመወሰን በቀረበ ደንብ ላይ ነው፡፡ ባለሀብቶች የሀገራችንን የኢኮኖሚ እድገት ሊያፋጥኑ በሚችሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው በሶስት የፋይናንስ ድጋፍ ሰምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪው ለብሄራዊ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል ከኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ የስልሳ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሃያ ሶስት ሺ /60,223,000/ የአሜሪካን ዶላር ብድር ሲሆን ከወለድ ነጻ፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች 0.1% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበት እና የ15 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡
ሁለተኛው ለታዳሽ፣ የተቀናጀ፣ ዘላቂ ኃይል እና ዲጂታላይዜሽን ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከፈረንሳይ የልማት ኤጄንሲ የሰማንያ ሚሊዮን /80,000,000/ ዩሮ ብድር ሲሆን አነስተኛ ወለድ 1.2% የሚከፈልበት፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች 0.5% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበት እና የ7 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ20 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡
ሶስተኛው ለከተማ ልማታዊ ሴፍትኔትና ሥራ ፈጠራ የሚውል ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር የአንድ መቶ ሰማንያ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ /184,100,000/ ኤስ ዲ አር ብድር ሲሆን ከወለድ ነጻ፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች እንዲሁም ጥቅም ላይ ላልዋለው ገንዘብ 1.25% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበትና የ6 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ30 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ሶስቱም የብድር ስምምነቶች ከአገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ ረቂቅ አዋጆቹ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርአት ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በሀገራችን የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዐትን ተግባራዊ ለማድረግ አዋጅ ቁጥር 372/1996 ወጥቶ በስራ ላይ የቆየ ቢሆንም ለአዋጁ ማስፈጸሚያ ደንብ ባለመውጣቱ በአፈጻጸም ሂደት ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶችን ለማረም፣ ለአዋጁ አፈጻጸም አስቻይ የሆኑ ዝርዝር ጉዳዮችን ለመደንገግና አስፈላጊውን የቁጥጥር ሥርዐትና መዋቅራዊ አደረጃጀት ለመፍጠር እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
5. በተጨማሪም የወርቅ ማዕድን እና የብረት ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ከማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ከመፍጠር፣ ለኢኮኖሚያችን አዎንታዊ ሚና ከመወጣት አንጻር ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡
6. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የቱሪዝም ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ የነበረው የቱሪዝም ልማት ፖሊሲ በዘርፉ የተከሰቱ ለውጦችን ከማስተናገድ፣ መልካም አጋጣሚዎችና የመልማት አቅሞችን ከመጠቀም እና ለአገራዊ ዕድገት ሚናውን ከመወጣት አንጻር ክፍተቶች የነበሩበት ነው፡፡ ዘርፉን በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከተቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ ጋር አጣጥሞ በመምራት እና በማልማት ለአገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ማስቻል አስፈላጊ በመሆኑ ረቀቂ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
#PMOEthiopia
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 53ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡
1. በቅድሚያ ምክር ቤቱ የተወያየው መደመር የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው በአዋጅ ቁጥር 1294/2015 መሠረት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ሆኖ የሚቋቋም ሲሆን በዘርፉ ወጣቶችን ለማሰልጠንና ለሀገር ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ምሁራንን ለማፍራት የሚሰራ ነው፡፡ ደንቡ የዩኒቨርሲቲውን ተግባርና ሃላፊነት በመደንገግ ተቋሙ ለሀገር ዕድገት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ የህግ ማዕቀፍ ሆኖ እንዲያገለግል ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በረቂቅ ደንቡ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
2. በመቀጠል ምክር ቤቱ የተወያየው ለባለሃብቶች ካሳ ለመክፈል ግዴታ የሚገባበትን ሁኔታ ለመወሰን በቀረበ ደንብ ላይ ነው፡፡ ባለሀብቶች የሀገራችንን የኢኮኖሚ እድገት ሊያፋጥኑ በሚችሉ ትላልቅ ፕሮጀክቶች እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
3. ከዚያም ምክር ቤቱ የተወያየው በሶስት የፋይናንስ ድጋፍ ሰምምነቶች ላይ ነው፡፡ የመጀመሪው ለብሄራዊ ኤሌክትሪክ ኃይል ማስፋፊያ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የሚውል ከኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ የስልሳ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሃያ ሶስት ሺ /60,223,000/ የአሜሪካን ዶላር ብድር ሲሆን ከወለድ ነጻ፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች 0.1% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበት እና የ15 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ40 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡
ሁለተኛው ለታዳሽ፣ የተቀናጀ፣ ዘላቂ ኃይል እና ዲጂታላይዜሽን ፕሮጀክት ማስፈፀሚያ የሚውል ከፈረንሳይ የልማት ኤጄንሲ የሰማንያ ሚሊዮን /80,000,000/ ዩሮ ብድር ሲሆን አነስተኛ ወለድ 1.2% የሚከፈልበት፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች 0.5% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበት እና የ7 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ20 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡
ሶስተኛው ለከተማ ልማታዊ ሴፍትኔትና ሥራ ፈጠራ የሚውል ከዓለም ዓቀፍ የልማት ማህበር የአንድ መቶ ሰማንያ አራት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ /184,100,000/ ኤስ ዲ አር ብድር ሲሆን ከወለድ ነጻ፣ ብድሩን በማስተዳደር ረገድ ለሚወጡ ወጪዎች እንዲሁም ጥቅም ላይ ላልዋለው ገንዘብ 1.25% የአገልግሎት ክፍያ የሚከፈልበትና የ6 ዓመት የችሮታ ጊዜን ጨምሮ በ30 ዓመት ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ነው፡፡ ምክር ቤቱ ሶስቱም የብድር ስምምነቶች ከአገራችን የብድር አስተዳደር ፖሊሲ ጋር የሚጣጣሙ መሆናቸውን በማረጋገጥ ረቂቅ አዋጆቹ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
4. ሌላው ምክር ቤቱ የተወያየው የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርአት ረቂቅ ደንብ ላይ ነው፡፡ በሀገራችን የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዐትን ተግባራዊ ለማድረግ አዋጅ ቁጥር 372/1996 ወጥቶ በስራ ላይ የቆየ ቢሆንም ለአዋጁ ማስፈጸሚያ ደንብ ባለመውጣቱ በአፈጻጸም ሂደት ይስተዋሉ የነበሩ ክፍተቶችን ለማረም፣ ለአዋጁ አፈጻጸም አስቻይ የሆኑ ዝርዝር ጉዳዮችን ለመደንገግና አስፈላጊውን የቁጥጥር ሥርዐትና መዋቅራዊ አደረጃጀት ለመፍጠር እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
5. በተጨማሪም የወርቅ ማዕድን እና የብረት ማዕድን ምርት ፈቃድ ረቂቅ ስምምነቶች ላይ ምክር ቤቱ ተወያይቷል፡፡ ለምክር ቤቱ የቀረቡት ሁለት ረቂቅ ስምምነቶች የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ከማሳደግ፣ ለዜጎች የስራ ዕድል ከመፍጠር፣ ለኢኮኖሚያችን አዎንታዊ ሚና ከመወጣት አንጻር ትልቅ ጠቀሜታ ያላቸውና ከአካባቢ ጥበቃና ከማህበረሰብ ተጠቃሚነት አንጻርም የመንግስትን የፖሊሲ አቅጣጫ የተከተሉ መሆናቸውን በማረጋገጥ የማዕድን ሚኒስቴር ስምምነቶቹን እንዲፈራረምና ወደ ስራ እንዲገቡ ምክር ቤቱ በሙሉ ድምጽ ይሁንታ ሰጥቷል፡፡
6. በመጨረሻም ምክር ቤቱ የተወያየው የቱሪዝም ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ነው፡፡ ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ላይ የነበረው የቱሪዝም ልማት ፖሊሲ በዘርፉ የተከሰቱ ለውጦችን ከማስተናገድ፣ መልካም አጋጣሚዎችና የመልማት አቅሞችን ከመጠቀም እና ለአገራዊ ዕድገት ሚናውን ከመወጣት አንጻር ክፍተቶች የነበሩበት ነው፡፡ ዘርፉን በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ከተቀመጠው የፖሊሲ አቅጣጫ ጋር አጣጥሞ በመምራት እና በማልማት ለአገራዊ ኢኮኖሚ እድገት የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ማስቻል አስፈላጊ በመሆኑ ረቀቂ ፖሊሲው ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በፖሊሲው ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል በምክር ቤቱ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
#PMOEthiopia
❤3
"አርበኛን የሚያጀግን ባንዳን የሚፀየፍ ትውልድ ልንገነባ ይገባል"
- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
+++++++++++++++++
ጋዜጣ_ፕላስ | አርበኛን የሚያጀግንና ባንዳን የሚፀየፍ ትውልድ መገንባት እንደሚገባ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ይህንን የገለጹት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ነው።
በዓድዋ ዘመን ሀገርን በመካድ ለጠላት የተሰለፉ ባንዳዎች እንደነበሩ ሁሉ፣ ዛሬም የባንዳነት ርዝራዦች ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመሰለፍ ብሔራዊ ጥቅምን ለመሸጥ እየሠሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
"ገመናን ለመሸፈን ተብሎ እውነታው ካልተገለጠ ባንዳነት በአደባባይ ወጥቶ የአርበኛ ማኅበረሰብ ግንባታን አደጋ ላይ ይጥላል" ሲሉም አሳስበዋል።
መምህራንንና የሕክምና ባለሙያዎችን የሚያግቱ፣ ተማሪዎችን የሚገድሉና የልማት ፕሮጀክቶችን ለማፍረስ የተላኩ ኃይሎች ሀገርን ለማዳከም እየተረባረቡ መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጠቁመዋል።
"እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን" ያሉት ኢታማዦር ሹሙ፤ ታዝሎ የሚመጣውን የውጭ ጠላትና አዝሎ የሚመጣውን የሀገር ውስጥ ባንዳ በእኩል ደረጃ ተዋግቶ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በክብረአብ በላቸው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ዓድዋ #ሉዓላዊነት #ጀግንነት #ብርሃኑ_ጁላ #አርበኝነት #130ኛው_ዓድዋ
- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
+++++++++++++++++
ጋዜጣ_ፕላስ | አርበኛን የሚያጀግንና ባንዳን የሚፀየፍ ትውልድ መገንባት እንደሚገባ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ።
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ይህንን የገለጹት 130ኛው የዓድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ” በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ በሚገኝበት ወቅት ነው።
በዓድዋ ዘመን ሀገርን በመካድ ለጠላት የተሰለፉ ባንዳዎች እንደነበሩ ሁሉ፣ ዛሬም የባንዳነት ርዝራዦች ከታሪካዊ ጠላቶች ጋር በመሰለፍ ብሔራዊ ጥቅምን ለመሸጥ እየሠሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
"ገመናን ለመሸፈን ተብሎ እውነታው ካልተገለጠ ባንዳነት በአደባባይ ወጥቶ የአርበኛ ማኅበረሰብ ግንባታን አደጋ ላይ ይጥላል" ሲሉም አሳስበዋል።
መምህራንንና የሕክምና ባለሙያዎችን የሚያግቱ፣ ተማሪዎችን የሚገድሉና የልማት ፕሮጀክቶችን ለማፍረስ የተላኩ ኃይሎች ሀገርን ለማዳከም እየተረባረቡ መሆኑን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ጠቁመዋል።
"እኛ የአባቶቻችን ልጆች ነን" ያሉት ኢታማዦር ሹሙ፤ ታዝሎ የሚመጣውን የውጭ ጠላትና አዝሎ የሚመጣውን የሀገር ውስጥ ባንዳ በእኩል ደረጃ ተዋግቶ የሀገርን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።
በክብረአብ በላቸው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #ዓድዋ #ሉዓላዊነት #ጀግንነት #ብርሃኑ_ጁላ #አርበኝነት #130ኛው_ዓድዋ
👍3❤1