የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባዔ (UNFSS+4) በአዲስ አበባ ይካሄዳል
****
(ኢ ፕ ድ)
በጣልያን የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ ከዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) የዘላቂ ልማት ግቦች ቢሮ ዳይሬክተር ስቴፋኖስ ፎቲዩ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው ከሐምሌ 21 እስከ 23 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባዔ መደረግ ስላለበት የቅድመ ዝግጅት ስራ፤ ለጉባዔው ዝግጅት የጋራ ኮሚቴ ለማቋቋም ተስማምተዋል።
የዘንድሮው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባዔ የረጅም ጊዜ ፈተናዎች ምላሽ መስጠት የሚያስችል ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል።
ፋኦ ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ጉባዔውን እንደሚያዘጋጅ በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
በጣልያን የኢትዮጵያ አምባሳደር ደሚቱ ሀምቢሳ ከዓለም ምግብ እና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) የዘላቂ ልማት ግቦች ቢሮ ዳይሬክተር ስቴፋኖስ ፎቲዩ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይታቸው ከሐምሌ 21 እስከ 23 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባዔ መደረግ ስላለበት የቅድመ ዝግጅት ስራ፤ ለጉባዔው ዝግጅት የጋራ ኮሚቴ ለማቋቋም ተስማምተዋል።
የዘንድሮው የተባበሩት መንግስታት የምግብ ስርዓት ጉባዔ የረጅም ጊዜ ፈተናዎች ምላሽ መስጠት የሚያስችል ጠንካራ የምግብ ስርዓት መገንባት ላይ ያተኮረ መሆኑ ተገልጿል።
ፋኦ ከኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ጉባዔውን እንደሚያዘጋጅ በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
👍6👎1
በምዕራብ ጎንደር ዞን 23 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ጥጥ እየተሰበሰበ መሆኑ ተገለፀ
****
(ኢ ፕ ድ)
በምዕራብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት 23 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ጥጥ በጥራት እየተሰበሰበ መሆኑ ተገለጸ።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የሰብል ልማትና ጥበቃ ባለሙያ አቶ ደግሰው አየለ ፤ እየተሰበሰበ ያለው የጥጥ ምርት በጥራት ተሰናድቶ ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት እንደሚቀርብ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በመኸሩ ወቅት በጥጥ ከለማው አጠቃላይ መሬት ውስጥ 12 ሺህ 300 ሄክታር የሚጠጋው በባለሃብቶች፤ ቀሪው ደግሞ በአርሶ አደሮች የለማ መሆኑን አስረድተዋል።
የምርት አሰባሰቡ ሂደት እስከ ተያዘው ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ታቅዶ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አመልክተው፤ አጠቃላይ ከለማው መሬት ከ422 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች ከተገነቡ የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካዎች እና የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር በመፍጠር ጥጡ የሚቀርብ መሆኑን ገልጸዋል።
በመኽር ወቅቱ 4 ሄክታር መሬት ላይ ጥጥ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ የተናገሩት ደግሞ በመተማ ወረዳ ኮኪት ቀበሌ አርሶ አደር ቢሰጥ አየናቸው ናቸው።
ባለፉት ዓመታት በጥጥ ምርት ላይ የገበያ ችግር እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን ጥጥን በግብዓትነት የሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋታቸው ተፈላጊነቱ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።
በዚሁ ወረዳው የደለሎ ፋና ቀበሌ አርሶ አደር ደሴ አሻግሬ፤ በመኽር ወቅት በጥጥ ከሸፈኑት 3 ሄክታር መሬት ውስጥ 1 ሄክታር የሚሆነውን መሰብሰባቸውን ገልጸዋል።
ካለሙት መሬት ከ50 ኩንታል በላይ የጥጥ ምርት እንደሚጠብቁ ጠቅሰው፤ከምርት ሽያጭም የተሻለ ጥቅም አገኛለሁ ብለዋል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
በምዕራብ ጎንደር ዞን በመኸር ወቅት 23 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የለማ ጥጥ በጥራት እየተሰበሰበ መሆኑ ተገለጸ።
በዞኑ ግብርና መምሪያ የሰብል ልማትና ጥበቃ ባለሙያ አቶ ደግሰው አየለ ፤ እየተሰበሰበ ያለው የጥጥ ምርት በጥራት ተሰናድቶ ለኢንዱስትሪዎች ግብዓት እንደሚቀርብ ለኢዜአ ተናግረዋል።
በመኸሩ ወቅት በጥጥ ከለማው አጠቃላይ መሬት ውስጥ 12 ሺህ 300 ሄክታር የሚጠጋው በባለሃብቶች፤ ቀሪው ደግሞ በአርሶ አደሮች የለማ መሆኑን አስረድተዋል።
የምርት አሰባሰቡ ሂደት እስከ ተያዘው ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ ታቅዶ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አመልክተው፤ አጠቃላይ ከለማው መሬት ከ422 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ አስታውቀዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች ከተገነቡ የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካዎች እና የጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር በመፍጠር ጥጡ የሚቀርብ መሆኑን ገልጸዋል።
በመኽር ወቅቱ 4 ሄክታር መሬት ላይ ጥጥ የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ የተናገሩት ደግሞ በመተማ ወረዳ ኮኪት ቀበሌ አርሶ አደር ቢሰጥ አየናቸው ናቸው።
ባለፉት ዓመታት በጥጥ ምርት ላይ የገበያ ችግር እንደነበር አስታውሰው፤ አሁን ግን ጥጥን በግብዓትነት የሚጠቀሙ ኢንዱስትሪዎች መስፋፋታቸው ተፈላጊነቱ እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።
በዚሁ ወረዳው የደለሎ ፋና ቀበሌ አርሶ አደር ደሴ አሻግሬ፤ በመኽር ወቅት በጥጥ ከሸፈኑት 3 ሄክታር መሬት ውስጥ 1 ሄክታር የሚሆነውን መሰብሰባቸውን ገልጸዋል።
ካለሙት መሬት ከ50 ኩንታል በላይ የጥጥ ምርት እንደሚጠብቁ ጠቅሰው፤ከምርት ሽያጭም የተሻለ ጥቅም አገኛለሁ ብለዋል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
👍8
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
❤2
በፈታኝ ሁኔታዎች አመርቂ የዲኘሎማሲ ስኬቶች ተመዝግበዋል - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
👉 በተለያዩ ሃገራት በችግር ውስጥ የነበሩ 33ሺህ ዜጎች ወደሀገራቸው ተመልሰዋል፣
👉 ለ968 የአጎራባች ሀገራት ተማሪዎች ነፃ የከፍተኛ የትምህርት ዕድል ተሰጥቷል፣
*****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት የተሰሩት የውጭ ግንኙነት ስራዎች በፈታኝ ሁኔታዎች አመርቂ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሰታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ባለፉት ስድስት ወራት በውጭ ግንኙነት የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎችን እና ወቅታዊ የዲኘሎማሲ እንቅስቃሴዎችን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማራመድ ተጨባጭ ውጤቶችን ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው በቀጣናው ሰላም ማስከበር ያላት ሚና እውቅና እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል።
ከሃገራት ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ያስቻሉ ከ128 በላይ የከፍተኛ ባለስልጣናት ጉብኝቶች መደረጋቸው ተገልጿል። የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅሞችና ወቅታዊ አቋሞች ለማስረፅ ያስቻሉ እንደሆኑም አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በመንግስታቱ ድርጅት ሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ሆና መመረጧ ባለፉት ስድሰት ወራት ከነበሩ ስኬቶች አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አምባሳደር ነብያት፤ ይህም በባለብዙ ወገን ዲኘሎማሲ መስክ የኢትዮጵያን ሚና ከፍ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።
ከተለያዩ ሃገራት ጋር የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ለማጠናከር በርካታ ስራዎች መሰራታቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ለ968 የአጎራባች ሀገራት ተማሪዎች ነፃ የከፍተኛ የትምህርት ዕድል መስጠቷንም አብራርተዋል።
በሌላ በኩል በተለያዩ ሃገራት በችግር ውስጥ የነበሩ 28 ሺህ ዜጎችን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ታቅዶ 33ሺህ ዜጎችን መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
👉 በተለያዩ ሃገራት በችግር ውስጥ የነበሩ 33ሺህ ዜጎች ወደሀገራቸው ተመልሰዋል፣
👉 ለ968 የአጎራባች ሀገራት ተማሪዎች ነፃ የከፍተኛ የትምህርት ዕድል ተሰጥቷል፣
*****
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት የተሰሩት የውጭ ግንኙነት ስራዎች በፈታኝ ሁኔታዎች አመርቂ ስኬቶች መመዝገባቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሰታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ባለፉት ስድስት ወራት በውጭ ግንኙነት የተሰሩ ዋና ዋና ስራዎችን እና ወቅታዊ የዲኘሎማሲ እንቅስቃሴዎችን አስመልክተው መግለጫ ሰጥተዋል።
ባለፉት ስድስት ወራት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማራመድ ተጨባጭ ውጤቶችን ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር የሚያጠናክሩ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው በቀጣናው ሰላም ማስከበር ያላት ሚና እውቅና እንዲያገኝ ማድረግ መቻሉንም ገልፀዋል።
ከሃገራት ጋር የሁለትዮሽ ግንኙነትን ለማጠናከር ያስቻሉ ከ128 በላይ የከፍተኛ ባለስልጣናት ጉብኝቶች መደረጋቸው ተገልጿል። የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅሞችና ወቅታዊ አቋሞች ለማስረፅ ያስቻሉ እንደሆኑም አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በመንግስታቱ ድርጅት ሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ሆና መመረጧ ባለፉት ስድሰት ወራት ከነበሩ ስኬቶች አንዱ መሆኑን የጠቀሱት አምባሳደር ነብያት፤ ይህም በባለብዙ ወገን ዲኘሎማሲ መስክ የኢትዮጵያን ሚና ከፍ እንደሚያደርገው ተናግረዋል።
ከተለያዩ ሃገራት ጋር የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ለማጠናከር በርካታ ስራዎች መሰራታቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ለ968 የአጎራባች ሀገራት ተማሪዎች ነፃ የከፍተኛ የትምህርት ዕድል መስጠቷንም አብራርተዋል።
በሌላ በኩል በተለያዩ ሃገራት በችግር ውስጥ የነበሩ 28 ሺህ ዜጎችን ወደ ሃገር ቤት ለመመለስ ታቅዶ 33ሺህ ዜጎችን መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
❤2👍2👎1
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
የምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት‼️
የርዕደ መሬት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዝግጁነታችንና የምላሽ ሁኔታችን ባለን ቴክኖሎጂ፣ ሳይንሳዊ ምርምር፣ ትንተናና የትንበያ አቅም የሚወሰን ነው፡፡
ዛሬ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ የስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት ባደረግነው ጉብኝት በርዕደ መሬት ነክ ሳይንሳዊ ምርምር አበረታች ስራዎችን አይተናል።
ባለፈው ሳምንት ባካሄድነው የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በርዕደ መሬት ክስተት ዙሪያ ባስቀመጥነው አቅጣጫ መሰረት ወደ ተጠናከረ ተግባር ተገብቷል፡፡
አደጋው በተከሰተባቸው አካባቢዎች የመሠረተ-ልማት፣ የጊዜያዊ መጠለያ፣ የሰብአዊ ድጋፍ፣ የሳይንሳዊ ትንተና እና ትንበያ ቡድኖችን በማደራጀት በዕቅድ ላይ የተመሰረተ ሥራ እየተከናወነ ነው።
መንግሥት የአጭርና የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ዝግጁነትን ለማጎልበት የጥናትና ምርምር ተቋማት ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ኃይል ጠንካራ ቁመና እንዲፈጥሩ ድጋፍ ያደርጋል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
የርዕደ መሬት ቅድመ ማስጠንቀቂያ ዝግጁነታችንና የምላሽ ሁኔታችን ባለን ቴክኖሎጂ፣ ሳይንሳዊ ምርምር፣ ትንተናና የትንበያ አቅም የሚወሰን ነው፡፡
ዛሬ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስ፣ የስፔስ ሳይንስ እና አስትሮኖሚ ኢንስቲትዩት ባደረግነው ጉብኝት በርዕደ መሬት ነክ ሳይንሳዊ ምርምር አበረታች ስራዎችን አይተናል።
ባለፈው ሳምንት ባካሄድነው የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ በርዕደ መሬት ክስተት ዙሪያ ባስቀመጥነው አቅጣጫ መሰረት ወደ ተጠናከረ ተግባር ተገብቷል፡፡
አደጋው በተከሰተባቸው አካባቢዎች የመሠረተ-ልማት፣ የጊዜያዊ መጠለያ፣ የሰብአዊ ድጋፍ፣ የሳይንሳዊ ትንተና እና ትንበያ ቡድኖችን በማደራጀት በዕቅድ ላይ የተመሰረተ ሥራ እየተከናወነ ነው።
መንግሥት የአጭርና የረጅም ጊዜ ሀገራዊ ዝግጁነትን ለማጎልበት የጥናትና ምርምር ተቋማት ዘመኑን በዋጀ ቴክኖሎጂና ብቁ የሰው ኃይል ጠንካራ ቁመና እንዲፈጥሩ ድጋፍ ያደርጋል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
👍4😁1
ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተሰጠ ማሳሰቢያ
በካናዳ የሥራና ትምህርት ዕድል ለማመቻቸት ህጋዊ ውክልና በውጭ ጉዳይ ሚኒስት ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞትዮስ የተሰጣቸው በማስመሰል ህገ ወጥ ደብዳቤ አዘጋጅተው እያሰራጩ ያሉ አካላት መኖራቸውን ተገንዝበናል።
የሚኒስትሩ ስም ተጠቅሶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያ አውታሮች እየተዘዋወረ የሚገኘው ደብዳቤ ሀሰተኛ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
እንዲህ አይነት የወንጀል ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ጋር እየተሰራ መሆኑን በመግለፅ ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ ራሱን ከአጭበርባሪዎች እንዲጠብቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳስቧል።
በካናዳ የሥራና ትምህርት ዕድል ለማመቻቸት ህጋዊ ውክልና በውጭ ጉዳይ ሚኒስት ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞትዮስ የተሰጣቸው በማስመሰል ህገ ወጥ ደብዳቤ አዘጋጅተው እያሰራጩ ያሉ አካላት መኖራቸውን ተገንዝበናል።
የሚኒስትሩ ስም ተጠቅሶ በተለያዩ ማህበራዊ ሚድያ አውታሮች እየተዘዋወረ የሚገኘው ደብዳቤ ሀሰተኛ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
እንዲህ አይነት የወንጀል ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ጋር እየተሰራ መሆኑን በመግለፅ ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ ራሱን ከአጭበርባሪዎች እንዲጠብቅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳስቧል።
👍11❤4
ዳያስፖራው ለሀገሩ ልማትና እድገት የበኩሉን ሚና ለመወጣት ዝግጁ ነው - ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ
*
(ኢ ፕ ድ)
ዳያስፖራው በኢትዮጵያ እየተመዘገበ ላለው እድገትና ልማት የበኩሉን ሚና ለማበርከት ዝግጁ መሆን እንዳለበት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ ገለፁ።
ፕሬዝዳንቱ በኒውዮርክ እና አካባቢው ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያውያኑ በታደሰው ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ባደረጉት ጉብኝት እያንዳንዱ የቤተ መንግሥቱ የሕንጻ ክፍል የኢትዮጵያን አስደናቂ ታሪክ በጥልቀትና በስፋት እንደሚመሰክር በኤክስ ገጻቸው ገልጸዋል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
*
(ኢ ፕ ድ)
ዳያስፖራው በኢትዮጵያ እየተመዘገበ ላለው እድገትና ልማት የበኩሉን ሚና ለማበርከት ዝግጁ መሆን እንዳለበት የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታየ አጽቀሥላሴ ገለፁ።
ፕሬዝዳንቱ በኒውዮርክ እና አካባቢው ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እንኳን ደህና መጣችሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያውያኑ በታደሰው ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ባደረጉት ጉብኝት እያንዳንዱ የቤተ መንግሥቱ የሕንጻ ክፍል የኢትዮጵያን አስደናቂ ታሪክ በጥልቀትና በስፋት እንደሚመሰክር በኤክስ ገጻቸው ገልጸዋል።
ጥር 8 ቀን 2017 ዓም
👍2
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️
ማምሻውን የጥምቀት በዓልን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች ጋር ተወያይተናል።
የጥምቀት በዓል የተለመደውን ሃይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ለማድረግ ከሃይማኖቱ አባቶች ጋር የተወያየን ሲሆን ሁላችንም በዓሉ ሃይማኖታዊ እሴቱንና የቱሪስት መስህብነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ተባብረን በጋራ እንስራ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ማምሻውን የጥምቀት በዓልን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች ጋር ተወያይተናል።
የጥምቀት በዓል የተለመደውን ሃይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ለማድረግ ከሃይማኖቱ አባቶች ጋር የተወያየን ሲሆን ሁላችንም በዓሉ ሃይማኖታዊ እሴቱንና የቱሪስት መስህብነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ተባብረን በጋራ እንስራ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
👍14😱1