የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️
በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳትና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው። በሥራው ለተሳተፉ ሁሉ በተለይ በክብር ለተሞሉት እንግዳ ተቀባይ የጎንደር ነዋሪዎች በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን ለመግለጽ እወዳለሁ።
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳትና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው። በሥራው ለተሳተፉ ሁሉ በተለይ በክብር ለተሞሉት እንግዳ ተቀባይ የጎንደር ነዋሪዎች በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን ለመግለጽ እወዳለሁ።
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
👍12🤣3❤1👏1
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት 16 ቢሊዮን ብር ገቢ ሰብስቧ
*******
(ኢ ፕ ድ)
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ከ16 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ።
በሀሰተኛ የጉዞ ሰነድ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ከ13 ሺህ በላይ ዜጎች ላይ አሰተዳደራዊ ርምጃ ተወስዷል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ፣ ተቋሙ ባለፋት ስድስት ወራት 10 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ከ16 ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰብስቧል።
በሐሰተኛና በተጭበረበሩ የጉዞ ሰነዶች አገልግሎት ለማግኘት ሲቀሳቀሱ የነበሩት 13 ሺህ 322 ዜጎች ላይ አስተዳድራዊ ርምጃዎችን ተወስዷል ሲሉ ገልጸዋል።
ከ721 ሺህ 623 በላይ ፓስፖርቶችን የማተም ስራ ተሰርቷል። ከታተመው 98 በመቶው ለተገልጋዮች ተሰጥቷል።
ለ14 ሺህ 367 ለሚሆኑ የውጭ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የመኖሪያ ፍቃድ የመስጠት ስራ ተከናውኗል። በዚህም ለ20 ግለሰቦች ዜግነት ተሰጧቸዋል ሲሉ አብራርተዋል።
ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሠው ሀይሉን የማጠናከር፤ አሰራሩን በቴክኖሎጂ የማገዝ ስራ ይሰራል።
በታደሠ ብናልፈው
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
*******
(ኢ ፕ ድ)
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት ከ16 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታወቀ።
በሀሰተኛ የጉዞ ሰነድ ሲንቀሳቀሱ በነበሩ ከ13 ሺህ በላይ ዜጎች ላይ አሰተዳደራዊ ርምጃ ተወስዷል።
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በሰጡት መግለጫ፣ ተቋሙ ባለፋት ስድስት ወራት 10 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ ከ16 ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ሰብስቧል።
በሐሰተኛና በተጭበረበሩ የጉዞ ሰነዶች አገልግሎት ለማግኘት ሲቀሳቀሱ የነበሩት 13 ሺህ 322 ዜጎች ላይ አስተዳድራዊ ርምጃዎችን ተወስዷል ሲሉ ገልጸዋል።
ከ721 ሺህ 623 በላይ ፓስፖርቶችን የማተም ስራ ተሰርቷል። ከታተመው 98 በመቶው ለተገልጋዮች ተሰጥቷል።
ለ14 ሺህ 367 ለሚሆኑ የውጭ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የመኖሪያ ፍቃድ የመስጠት ስራ ተከናውኗል። በዚህም ለ20 ግለሰቦች ዜግነት ተሰጧቸዋል ሲሉ አብራርተዋል።
ለዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሠው ሀይሉን የማጠናከር፤ አሰራሩን በቴክኖሎጂ የማገዝ ስራ ይሰራል።
በታደሠ ብናልፈው
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
👍9😁5❤2👎1
የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት
ዛሬ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር የጎንደር የኮሪደር ልማትና የፋሲለደስ ግንብ እድሳት የደረሰበትን ደረጃ ጎብኝተናል።
የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራና የፋሲለደስ እድሳት እጅግ ውብ፣ የከተማዋን ታሪካዊነት ይበልጥ በሚያጎላና የቱሪስት መዳረሻነቷን በሚያሳድግ ሁኔታ በመሰራት ላይ ነዉ።
በዚህ የለውጥ ዘመን የኢትዮጵያ ከተሞች የተሰጣቸው ትኩረት እጅግ ትልቅ ሲሆን፣ በተለይም ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ውብ እንዲሁም ለቱሪስት መስህብ መሆናቸውን እጅግ የሚጨምር ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
ዛሬ ከክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር የጎንደር የኮሪደር ልማትና የፋሲለደስ ግንብ እድሳት የደረሰበትን ደረጃ ጎብኝተናል።
የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራና የፋሲለደስ እድሳት እጅግ ውብ፣ የከተማዋን ታሪካዊነት ይበልጥ በሚያጎላና የቱሪስት መዳረሻነቷን በሚያሳድግ ሁኔታ በመሰራት ላይ ነዉ።
በዚህ የለውጥ ዘመን የኢትዮጵያ ከተሞች የተሰጣቸው ትኩረት እጅግ ትልቅ ሲሆን፣ በተለይም ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ውብ እንዲሁም ለቱሪስት መስህብ መሆናቸውን እጅግ የሚጨምር ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
👏6👍5❤3😁1
በጎንደር የጥምቀት በዓል የሚከበርበት ስፍራ የእድሳት ስራ መጠናቀቁን የከተማው ባሕልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ
****
(ኢ ፕ ድ)
በጎንደር ከተማ የጥምቀት በዓል የሚከበርበት የፋሲለደስ መጠመቂያ ስፍራ የእድሳት ስራ ተጠናቆ ለበዓሉ ዝግጁ መደረጉን የከተማው ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ተወካይ ኃላፊ አቶ ልዕልና አበበ እንደገለጹት፤ የጥምቀተ ባሕሩን የውኃ ስርገት ለመከላከል የሚያስችል የጥገና ስራ መከናወኑንና አሁን ላይም ከ10 ሺህ ሜትር ኪዩብ በላይ ውኃ የመሙላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በጥምቀተ ባሕሩ መንበረ ታቦታቱ የሚያርፉባቸው ስፍራዎችን የማጽዳትና ለምዕመናኑ ምቹ የማድረግ ስራዎች በአብዛኛው መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡
በበዓሉ የሚታደሙ የሀገር ውስጥና የውጪ ጎብኚዎችን ጨምሮ ለታላላቅ እንግዶች የሚውሉ የማረፊያ ስፍራዎች ደህንነታቸው በተጠበቀ መንገድ ዝግጁ መደረጋቸውን ጠቁመዋል፡፡
እስከ 400 እንግዶችን ማስተናገድ የሚያስችሉ የብረት አግዳሚ ወንበሮች ጥራታቸውን በጠበቀ መንገድ ተሰርተው ለአገልግሎት መዘጋጀታቸውንም አመልክተዋል፡፡
ክብረ በዓሉን በቀጥታ ስርጭት ለሀገር ውስጥና ለመላው ዓለም ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ጊዜያዊ የቴሌቪዠን ማሰራጫ ስቱዲዮዎች የሚተከሉባቸው ስፍራዎች መደራጀታቸውንም ጠቁመዋል፡፡
ጊዜያዊ መፀዳጃ ቤቶችን ጨምሮ የኤሌክትሪክ፣የውኃና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን የማሟላት ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው፤ የመጀመሪያ ደረጃ ሕክምና መስጫ ቦታዎችም ተዘጋጅተዋል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ዘንድሮ በከተማው በሚከበረው የጥምቀት በዓል ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶችን ጨምሮ በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይታደማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
በጎንደር ከተማ የጥምቀት በዓል የሚከበርበት የፋሲለደስ መጠመቂያ ስፍራ የእድሳት ስራ ተጠናቆ ለበዓሉ ዝግጁ መደረጉን የከተማው ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ተወካይ ኃላፊ አቶ ልዕልና አበበ እንደገለጹት፤ የጥምቀተ ባሕሩን የውኃ ስርገት ለመከላከል የሚያስችል የጥገና ስራ መከናወኑንና አሁን ላይም ከ10 ሺህ ሜትር ኪዩብ በላይ ውኃ የመሙላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በጥምቀተ ባሕሩ መንበረ ታቦታቱ የሚያርፉባቸው ስፍራዎችን የማጽዳትና ለምዕመናኑ ምቹ የማድረግ ስራዎች በአብዛኛው መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል፡፡
በበዓሉ የሚታደሙ የሀገር ውስጥና የውጪ ጎብኚዎችን ጨምሮ ለታላላቅ እንግዶች የሚውሉ የማረፊያ ስፍራዎች ደህንነታቸው በተጠበቀ መንገድ ዝግጁ መደረጋቸውን ጠቁመዋል፡፡
እስከ 400 እንግዶችን ማስተናገድ የሚያስችሉ የብረት አግዳሚ ወንበሮች ጥራታቸውን በጠበቀ መንገድ ተሰርተው ለአገልግሎት መዘጋጀታቸውንም አመልክተዋል፡፡
ክብረ በዓሉን በቀጥታ ስርጭት ለሀገር ውስጥና ለመላው ዓለም ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችሉ ጊዜያዊ የቴሌቪዠን ማሰራጫ ስቱዲዮዎች የሚተከሉባቸው ስፍራዎች መደራጀታቸውንም ጠቁመዋል፡፡
ጊዜያዊ መፀዳጃ ቤቶችን ጨምሮ የኤሌክትሪክ፣የውኃና የኢንተርኔት አገልግሎቶችን የማሟላት ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀው፤ የመጀመሪያ ደረጃ ሕክምና መስጫ ቦታዎችም ተዘጋጅተዋል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ዘንድሮ በከተማው በሚከበረው የጥምቀት በዓል ላይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶችን ጨምሮ በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይታደማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
👍4👏1
#ጎንደር_የፋሲል ቤተመንግስት ዕድሳት‼️
የፋሲለደስ ዕድሳት እጅግ ውብ፣ የከተማዋን ታሪካዊነት በሚያጎላና የቱሪስት መዳረሻነቷን በሚያሳድግ ሁኔታ በመሰራት ላይ ይገኛል። የፋሲለደስ የዕድሳት ስራ አሁናዊ ገፅታ‼️
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
የፋሲለደስ ዕድሳት እጅግ ውብ፣ የከተማዋን ታሪካዊነት በሚያጎላና የቱሪስት መዳረሻነቷን በሚያሳድግ ሁኔታ በመሰራት ላይ ይገኛል። የፋሲለደስ የዕድሳት ስራ አሁናዊ ገፅታ‼️
ጥር 7 ቀን 2017 ዓም
👏4👍3