የቦሌ አራብሳ ዘመናዊ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ተመረቀ
************
(ኢፕድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቀን 30 ሚሊዮን ሊትር ፍሳሽ የማጣራት አቅም ያለውን የቦሌ አራብሳ ዘመናዊ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ መርቀው ከፈቱ፡፡
ከንቲባ አዳነች እንደገለጹት፤ የዚህ ፕሮጀክት መመረቅ የከተማችንን የፍሳሽ ማጣራት አቅም ከአምስት ዓመት በፊት ከነበረበት በቀን 48 ሺሕ ሜትር ኪዮብ ወደ በቀን 233 ሺሕ ሜትር ኪዮብ ከፍ ማድረግ አስችሎናል::
ማጣሪያ ጣቢያው ከ240 ሺህ በላይ የሚሆኑ የአካባቢውን ነዋሪዎች የዘመናዊ ፍሳሽ ማጣሪያ ስርዓት ተጠቃሚ የሚያደርግ ነዉ ያሉት ከንቲባ አዳነች፤ ፕሮጀክቱ ከለዉጡ ወዲህ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ጀምሮ የመጨረስ አንዱ ማሳያ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ለአንድ ከተማ ወሳኝ ከሆኑ መሰረተ ልማቶች መካከል የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓትን ማዘመን ትልቅ ስራ ነው ያሉት ክቲባ አዳነች፣ ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብ ከመፍጠር አኳያ ያለው ሚና እጅግ ከፍተኛ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም ይህ የፍሳሽ ማጣሪያ ስራ የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓታችንን የሚያዘምን፣ የከተማችን ነዋሪዎችን እና በአጎራባች አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎት የረዥም ጊዜ ቅሬታን ምላሽ የሚሰጥ ፣ከተማችንን ከብክለት የጸዳች፣ ውብ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የጀመርነውን ስራ እዉን የሚያደርግ ነዉ ብለዋል።
ከንቲባ አዳነች፤ ፕሮጀክቱ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽዖ ላደረጉት የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ኮንትራክተርና አማካሪ ድርጅት፣ ለክፍለከተማውና ከምንም በላይ በፈቃደኝነት ለልማት ከቦታው ለተነሱ አርሶ አደሮች በነዋሪው እና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመስግነዋል፡፡
************
(ኢፕድ)
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በቀን 30 ሚሊዮን ሊትር ፍሳሽ የማጣራት አቅም ያለውን የቦሌ አራብሳ ዘመናዊ የፍሳሽ ማጣሪያ ጣቢያ ፕሮጀክቱ መርቀው ከፈቱ፡፡
ከንቲባ አዳነች እንደገለጹት፤ የዚህ ፕሮጀክት መመረቅ የከተማችንን የፍሳሽ ማጣራት አቅም ከአምስት ዓመት በፊት ከነበረበት በቀን 48 ሺሕ ሜትር ኪዮብ ወደ በቀን 233 ሺሕ ሜትር ኪዮብ ከፍ ማድረግ አስችሎናል::
ማጣሪያ ጣቢያው ከ240 ሺህ በላይ የሚሆኑ የአካባቢውን ነዋሪዎች የዘመናዊ ፍሳሽ ማጣሪያ ስርዓት ተጠቃሚ የሚያደርግ ነዉ ያሉት ከንቲባ አዳነች፤ ፕሮጀክቱ ከለዉጡ ወዲህ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ጀምሮ የመጨረስ አንዱ ማሳያ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
ለአንድ ከተማ ወሳኝ ከሆኑ መሰረተ ልማቶች መካከል የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓትን ማዘመን ትልቅ ስራ ነው ያሉት ክቲባ አዳነች፣ ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብ ከመፍጠር አኳያ ያለው ሚና እጅግ ከፍተኛ እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
በመሆኑም ይህ የፍሳሽ ማጣሪያ ስራ የፍሳሽ አወጋገድ ስርዓታችንን የሚያዘምን፣ የከተማችን ነዋሪዎችን እና በአጎራባች አካባቢዎች የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎት የረዥም ጊዜ ቅሬታን ምላሽ የሚሰጥ ፣ከተማችንን ከብክለት የጸዳች፣ ውብ እና ለነዋሪዎቿ ምቹ ለማድረግ የጀመርነውን ስራ እዉን የሚያደርግ ነዉ ብለዋል።
ከንቲባ አዳነች፤ ፕሮጀክቱ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽዖ ላደረጉት የውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ኮንትራክተርና አማካሪ ድርጅት፣ ለክፍለከተማውና ከምንም በላይ በፈቃደኝነት ለልማት ከቦታው ለተነሱ አርሶ አደሮች በነዋሪው እና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመስግነዋል፡፡
👍7👎1
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍5❤1
ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሎስ አንጀለስ ሰደድ እሳት ሳቢያ በደረሰው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገለጸ
***********************
(ኢፕድ)
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአሜሪካ የካሊፎርኒያ ግዛት በሎስ አንጀለስ አካባቢ በደረሰው ከባድ ሰደድ እሳት ሳቢያ በደረሰው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል፡፡
ሚኒስቴሩ ባወጣው የሀዘን መግለጫ፤ በአሜሪካ የካሊፎርኒያ ግዛት በሎስ አንጀለስ አካባቢ በደረሰው ከባድ ሰደድ እሳት የሰው ህይወት በመጥፋቱ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቀያቸው በመፈናቀላቸው እና ንብረት በመውደሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዚህ አስቸጋሪና ፈታኝ ወቅት በሎስ አንጀለስ አካባቢ ለሚኖሩ የአሜሪካ ህዝብና መንግስት እንዲሁም ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
***********************
(ኢፕድ)
የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአሜሪካ የካሊፎርኒያ ግዛት በሎስ አንጀለስ አካባቢ በደረሰው ከባድ ሰደድ እሳት ሳቢያ በደረሰው ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል፡፡
ሚኒስቴሩ ባወጣው የሀዘን መግለጫ፤ በአሜሪካ የካሊፎርኒያ ግዛት በሎስ አንጀለስ አካባቢ በደረሰው ከባድ ሰደድ እሳት የሰው ህይወት በመጥፋቱ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ከቀያቸው በመፈናቀላቸው እና ንብረት በመውደሙ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል።
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በዚህ አስቸጋሪና ፈታኝ ወቅት በሎስ አንጀለስ አካባቢ ለሚኖሩ የአሜሪካ ህዝብና መንግስት እንዲሁም ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታውቋል።
👍8🤣5
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀ ስላሴ ዩጋንዳ ገቡ
******************
(ኢፕድ)
ፕሬዝደንቱ ዩጋንዳ የገቡት በአፍሪካ አስተማማኝ የግብርናና የምግብ ስርዓት መገንባት በሚል መሪ ሃሳብ በድህረ ማላቦ አጠቃላይ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮገራም አፈጻጸም ላይ የሚመክር የአፍሪካ ህብረት ልዩ ጉባኤ ለመካፈል ነው፡፡
ፕሬዝዳንት ታዬ በኢንተቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡
******************
(ኢፕድ)
ፕሬዝደንቱ ዩጋንዳ የገቡት በአፍሪካ አስተማማኝ የግብርናና የምግብ ስርዓት መገንባት በሚል መሪ ሃሳብ በድህረ ማላቦ አጠቃላይ የአፍሪካ ግብርና ልማት ፕሮገራም አፈጻጸም ላይ የሚመክር የአፍሪካ ህብረት ልዩ ጉባኤ ለመካፈል ነው፡፡
ፕሬዝዳንት ታዬ በኢንተቤ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡
👍8
አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቱሪስቶች ክልሉን ጎብኝተዋል
*****************************
(ኢፕድ)
በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች የአማራ ክልል መጎብኘታቸውን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
በዚህም ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ሁለት ነጥብ አራት ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ቢሮው ጨምሮ ገልጿል፡፡
የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ ለጋዜጣ ፕላስ እንዳስታወቁት፤ ባለፉት ስድስት ወራት አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቱሪስቶች የክልሉን የተለያዩ ቦታዎች ጉብኝተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች አራት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ በክልሉ የቱሪስት የቆይታ ጊዜ የሚያራዝሙና የታቀደውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችሉ በርካታ ምቹ ሁኔታዎች አሉ ብለዋል፡፡
የልደት በዓልን ጨምሮ በቀጣይ በክልሉ በጥር ወር የሚከበሩ ሐይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት የክልሉን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ይበልጥ እንደሚያሳድግ አብራርተዋል፡፡
ልጅዓለም ፍቅሬ
*****************************
(ኢፕድ)
በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች የአማራ ክልል መጎብኘታቸውን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
በዚህም ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ሁለት ነጥብ አራት ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ቢሮው ጨምሮ ገልጿል፡፡
የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ ለጋዜጣ ፕላስ እንዳስታወቁት፤ ባለፉት ስድስት ወራት አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቱሪስቶች የክልሉን የተለያዩ ቦታዎች ጉብኝተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች አራት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ በክልሉ የቱሪስት የቆይታ ጊዜ የሚያራዝሙና የታቀደውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችሉ በርካታ ምቹ ሁኔታዎች አሉ ብለዋል፡፡
የልደት በዓልን ጨምሮ በቀጣይ በክልሉ በጥር ወር የሚከበሩ ሐይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት የክልሉን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ይበልጥ እንደሚያሳድግ አብራርተዋል፡፡
ልጅዓለም ፍቅሬ
👍18🤣6❤5😱3
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍5❤2🥰1
የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ለአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ድጋፍ አደረገ
******************
(ኢፕድ)
ጽህፈት ቤቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ፤ በጤናው ዘርፍ የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ መሆኑን ጠቅሷል።
በዛሬው ዕለትም ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ ከተባለ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ለአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የተለያዩ መድሀኒቶችን ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል፡፡
******************
(ኢፕድ)
ጽህፈት ቤቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ፤ በጤናው ዘርፍ የተለያዩ ስራዎችን በመስራት ላይ መሆኑን ጠቅሷል።
በዛሬው ዕለትም ጉድ ኔበርስ ኢትዮጵያ ከተባለ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በጋራ በመሆን ለአዲስ አበባ ጤና ቢሮ የተለያዩ መድሀኒቶችን ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል፡፡
👍9❤1👎1