Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
343 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍3
በኦሮሚያ ክልል ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት ተሰበሰበ
**********************
(ኢ ፕ ድ )
በ2017 የምርት ዘመን ሰባት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ እስካሁን ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት መሰብሰቡን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ። በክልሉ 165 ሺህ 321 አርሶ አደሮች በአቮካዶ ልማት መሠማራታቸው ተጠቁሟል፡፡

በቢሮው የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ተገኝ ኢራና ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በክልሉ የአቮካዶ ማሳ ሽፋን 55 ሺህ 112 ሄክታር መሬት የደረሰ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 30 ሺህ 145 ሄክታር የሚሆነው መሬት ላይ የተተከለው የአቮካዶ ዛፍ ምርት እየሰጠ ይገኛል፡፡

ባለፈው ዓመት ስድስት ነጥብ አምስት ኩንታል የአቮካዶ ምርት ማግኘት መቻሉን አውስተው፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን ሰባት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁንም ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ በ21 ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 185 ወረዳዎች በአንድ ሺህ 751 ክላስተር በማደራጀት አቮካዶ መተከሉን የገለጹት አቶ ተገኝ፤ 165 ሺህ 321 ወንድና ሴት አርሶ አደሮች በአቮካዶ ማልማት ሥራ ተሠማርተው….

https://press.et/?p=143334
👍5👏2
የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባት ለሀገር ውስጥ ባንኮች ዕድል ወይስ ስጋት?
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከተጀመረ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ እድሜ አለው።
በእነዚህ ጊዜያትም ያጋጠሙትን መልካም እድሎች እና ፈተናዎች ተሻግሮ ዛሬ ላይ ደርሷል።

የዛሬ ቁመናውም ቢሆን የእድሜውን ያህል እንዳልሆነ በዘርፉ የተሠማሩ ምሁራን ይናገራሉ።

ይህንን እውነታ ለመለወጥ መንግሥት የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረግ የሚያስችል አዋጅ አርቅቆ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ እንዲጸድቅ አድርጓል።

የሕጉ መጽደቅ በብዙ የሚጠበቅ ቢሆንም፤ አሁንም ዜጎችም ሆነ በመስኩ የሚገኙ ምሁራን የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ ነው።

የውጭ ባለሀብቶች በባንክ ዘርፍ እንዲሠማሩ የሚፈቅደው አዋጅ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ምን ይዞ ይመጣል፤ ተስፋ ወይስ ስጋት? በሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት የሚኖረው ጠቀሜታስ ምን ይመስላል በሚለው ሃሳብ ላይ የዘርፉ ባለሙያዎች ምላሽ ሰጥተውናል፡፡

አቶ ክቡር ገና ይባላሉ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ናቸው። አዋጁ መጽደቁ የውጭ ባንኮች ሀገር ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ የሚጋብዝ መሆኑን፤ ባንኮቹ ሊሠሩ የሚችሉትንና የማይችሉትን በዝርዝር ማስቀመጡን ይናገራሉ፡፡

የአዋጁ አቀራረብ ባንኮቹ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ የሚችል ነው ወይስ አይደለም የሚለው ወደፊት ተግባራዊ ሲሆን የሚታይ ነው፡፡ የለውጡ ሂደት…

https://press.et/?p=143333
👍4
#ውብአዲስ
አዲስ እንደ ስሟ‼️
👍3👎3
በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት ከ160 ሺህ በላይ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት አድርገዋል
*******************
(ኢ ፕ ድ )
በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት ከ160 ሺህ በላይ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ማድረጋቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎች ክብራቸው፣ መብታቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ አገራት ለስራ የሚሄዱበትን ስርዓት መዘርጋቱ ይታወቃል።

የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎችን የሙያ ክህሎት በማስታጠቅ በውጭ አገራት የስራ ስምሪት ተወዳዳሪና ተቀባይነት እንዲኖራቸው የጀመራቸው ስራዎች ውጤታማ በመሆን ላይ ይገኛሉ፡፡

የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንዳሉት ሚኒስቴሩ ክህሎት መር የስራ እድልን ለመፍጠር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።

እንዲሁም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት በማድረግ ዜጎች በውጭ አገራት መብታቸው፣ ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ለማስቻል እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም የውጭ አገር የስራ ገበያ በማፈላለግ፣ መዳረሻ አገራትን በመለየትና የሁለትዮሽ ስምምነት በመፈጸም ዜጎች ህጋዊ የስራ ዕድል እንዲያገኙ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በአገራቱ ያለውን የስራ ፍላጎት በመለየት ተወዳዳሪና ብቁ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።

ዜጎች በቅድሚያ የቁጠባ የሂሳብ ደብተር እንዲከፍቱ በማድረግ ወደ አገራቸው ሲመለሱ በቆጠቡት ገንዘብ ሀብት አፍርተው ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩንም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ዜጎች የስራ መታወቂያ እንዲኖራቸውና በቂ ስልጠና እንዲያገኙ በማድረግ የግልጸኝነት ስርዓት እንዲዘረጋ ማስቻሉን ተናግረዋል።

እስካሁን ባለው ከስድስት አገራትና ከተለያዩ ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት በመፈፀም የውጭ አገር የስራ ስምሪት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት የውጭ አገራት የስራ ስምሪት ያደረጉ ዜጎች ቁጥር ከ160ሺህ ማለፉን ተናግረዋል።

ዜጎች መብትና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ህጋዊ የውጭ አገር ስራ ስምሪት ስርአትን ተከትለው ሊሄዱ እንደሚገባም ተናግረዋል።

በደላሎች ተታለው በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገራት ማቅናት ከእንግልት እስከ ህይወት ማጣት የሚያስከትል በመሆኑ ዜጎች ራሳቸውን ከመሰል አደጋ መጠበቅ እንዳለባቸውም ገልፀዋል።

ሚኒስቴሩ የማህበረሰብ አቀፍ ራዲዮ ባለሙያዎች በህገ ወጥ ስደት ላይ እንዲያተኩሩ ስልጠና መስጠቱን በዚሁ ወቅት አንስተዋል፡፡

ታህሳስ 11ቀን 2017 ዓ.ም
👍8😁21
የምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት‼️

የሰባት ሐይቆች መገኛዋ ቢሾፍቱ በተቀናጀ የኮሪደር ልማት ላይ ትገኛለች።

በከተማዋ የተጀመሩ የተፈጥሮ ጸጋን ወደ ጥቅም የሚቀይሩ የልማትና የስማርት ሲቲ ተግባራት የሚበረታቱ እንዲሁም የቢሾፍቱን የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስት መናገሻነት በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሳድጉ ናቸው።

የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራዎቹ የከተማዋን ገፅታ፣ ዘመናዊነትና የነዋሪዎቿን ኑሮ የሚያሻሽሉ ናቸው፡፡

እነዚህ የልማት ስራዎች በከተማዋ አመራርና በፕሮጀክት ሠራተኞች የሌት ተቀን ትጋት በአጭር ጊዜ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ ሙሉ እምነት አለን።

መንግስት ከተሞች በአረንጓዴ ውበት እና በዘመናዊ የክትመት ስርዓት ተመራጭ የአገልግሎትና ምቹ የመኖሪያ ማዕከላት እንዲሆኑ የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

ታህሳስ 11ቀን 2017ዓ.ም
9👍6👎2
እንደምን አደሩ‼️
#አዲስ_ዘመን_ዛሬ‼️
የታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ ዘመን ጋዜጣ
https://press.et/?p=143413
መልካም ቀን!
👏21👎1
“ግብጽን የሚያዋጣት ሕግ የሆነውን የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነት ፈርሞ መቀበል ነው”
- ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ (ዶ/ር) የታሪክ ምሁር
****
(ኢ ፕ ድ)

በአሁኑ ወቅት ግብጽን የሚያዋጣት ከወራት በፊት ተፈርሞ ሕግ የሆነውን የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነትን ፈርሞ መቀበል እንደሆነ የታሪክ ምሁር ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ (ዶ/ር) አስታወቁ።

ኢትዮጵያ 130 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ይዛ ያለ ባሕር በር መኖር የማይታሰብ ነገር እንደሆነም አመልክተዋል።

ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ አብላጫዎቹ የተፋሰሱ ሀገራት የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነትን መቀበላቸውን በፊርማቸው ከማረጋገጥም ባሻገር የሀገራቸው ሕግ አድርገው አጽድቀውታል።

የትብብር ማሕቀፍ ስምምነት በስድስት የተፋሰሱ ሀገሮች በመጽደቁም ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ ሕግ መሆኑን ያስታወሱት የታሪክ ምሁሩ ፤ ለግብጽም መልካም የሚሆነው ማሕቀፉን ተቀብላ ከኢትዮጵያ ጋር ተባብራ ብትሠራ እንደሆነ አመልክተዋል። ተባብራ መሥራቷም የበለጠ ተጠቃሚ ያደርጋታል ብለዋል ።

እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ በኢትዮጵያ በኩል ዋናው ቁም ነገር በአቋም መጽናት ነው። የትብብር ማሕቀፉ ሥራ ላይ እንዲውል በማድረጉ በኩል አሁን የመጣችበት መንገድ መልካም የሚባል ነው፤ ይህንኑ አጠናክሮ መቀጠል ተገቢ ነው።

በኢትዮጵያ ጉዳይ አርፋ መቀመጥን የማትወደዋ ግብጽ፣ እንዲሁ ከመድከም ባለፈ ምንም ማድረግ አልቻለችም ያሉት ተባባሪ ፕሮፌሰሩ ፣ የትብብር ማሕቀፉን ፈርማ በማጽደቅ ተጠቃሚ........https://press.et/?p=143416
👍12
የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ወደ ኢትዮጵያ መምጣት የሀገራቱን ግንኙነት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል
*****
(ኢ ፕ ድ )
የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ኢትዮጵያ መምጣታቸው የሀገራቱን ግንኙነት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል ሲሉ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ቋሚ ኮሚቴ አባል አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ፡፡

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ኢትዮጵያና ፈረንሳይ በዲፕሎማሲ፣ በትምህርት፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ፣ በባህልና በሌሎች ዘርፎች 126 ዓመታትን ያስቆጠረ ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው ለኢፕድ ገልጸዋል፡፡

የፈረንሳይ መንግስት በተለያዩ ምክንያቶች የተዘረፉ የአፍሪካ ቅርሶችን በመመለስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ለላሊበላ ውቅር አብያተክርስቲያናት ጥገና ድጋፍ እያደረገ ሲሆን፤ ይህም ለሌሎች ሀገራት ትምህርት የሚሆን ነው ብለዋል፡፡

ሁለቱ ሀገራት ግንኙነታቸውን አጠናክረው ለማስቀጠል የተለያዩ ስራዎችን መስራት እንደሚጠበቅባቸው አመላክተዋል፡፡

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ወደ ኢትዮጵያ መምጣት የሀገራቱን ግንኙነት ለማሳደግ ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያልም ብለዋል፡፡

በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ደረጃ ያሉ መሪዎች ኢትዮጵያ መምጣታቸው የሀገሪቱ ተሰሚነት ማደጉን የሚያሳይ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

የሀገሪቱን ገጽታ ለመግባት እንዲሁም ሁለቱ ሀገራት በተለያየ ዘርፍ ያለቸውን ግንኙነት ለማጠናከር እገዛ እንዳለው አስታውቀዋል፡፡

ፈረንሳይ የፕሪቶሪያውን ስምምነት ከሚደግፉ ሀገራት አንዷ መሆኗንም አንስተዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን እአአ 2019 በመጋቢት ወር በኢትዮጵያ ያደረጉት ጉብኝት የሀገራቱን ሁለትዮሽ ግንኙነት አጠናክሯል።

በሄለን ወንድምነው

ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓም
👍162👎1
ዲፕሎማሲያዊ ጉብኝት‼️
3👍1
የኢትዮጵያና የፈረንሳይ ዘርፈብዙ ግንኙነቶች‼️

✍️ ፈረንሳይ ለኢትዮጵያ አምስተኛዋ የወጪ ንግድ መዳረሻ ሀገር ናት፣

✍️ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ ጋር በሁለተኛ ደረጃ የንግድ ልውውጥ ታደርጋለች፣

✍️ እአአ በ2019 በሐምሌ ወር ከማርሴ - አዲስ አበባ አዲስ የጉዞ መስመር ተጀምሯል፣

✍️ ፈረንሳይ ለላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ዕድሳት ድጋፍ አድርጋለች፣

✍️ ሊሴ ገብረማርያም ትምህርት ቤት በፈረንሳይ ይደገፋል፣

✍️ በወታደራዊ ዘርፍ ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ ጋር የሁለትዮሽ ትብብር አላት፤ የመከላከያ ትብብር ስምምነት ተፈርሟል፣

✍️ ፈረንሳይ የኢትዮጵያን የባህር ኃይል መልሶ ለመገንባት ድጋፍ ታደርጋለች፣

ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓም
20👍7👎2😁2
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️

ወንድሜና የኢትዮጵያ የልብ ወዳጅ የፈረንሳይ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ባለፉት ስድስት አመታት ለሁለተኛ ጊዜ ለጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ እንኳን በደህና መጡ እላለሁ።

በሁለቱ ሀገሮቻችን መካከል ያለው ግንኙነት የበለጠ በመጠናከር ላይ ይገኛል። ክቡር ፕሬዚዳንት በሚኖራቸው ቆይታ ፍሬያማ ውይይት እንደሚኖረን እምነቴ ፅኑ ነው።

ታህሳስ 12 ቀን 2017 ዓም
👍21👏5