የምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት ‼️
ዛሬ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ የብረት ኢንዱስትሪ መንደር የሚገኘውን ስቲሊ አር. ኤም. አይ ኃላ/የተ/የግ/ ማህበር (STEELY RMI P.L.C) የብረታብረት ማምረቻ ፋብሪካን ጎብኝተናል።
ፋብሪካው ዘመናዊ የዲጂታል አሠራርን እና የታዳሽ ኃይልን በመጠቀም ከዚህ ቀደም ይጣሉ የነበሩ የብረት ቁርጥራጮችን መልሶ ጥቅም ላይ እያዋለ ይገኛል፡፡ በዚህም ለተለያዩ የግንባታ ግብዓት የሚውሉ የብረታብረት ምርቶችን እያመረተ መሆኑ የሚደነቅ ነው።
የብረታብረት ፋብሪካው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ አበረታች ውጤቶች እያመጣ እንዳለም ተመልክተናል፡፡
መንግሥት የብድር፣ የመሠረተ ልማትና የአሠራር ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የግሉ ዘርፍ ለኢኮኖሚ ዕድገቱ ዋና አንቀሳቃሽ (ሞተር) እንዲሆን የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል።
ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም
ዛሬ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ የብረት ኢንዱስትሪ መንደር የሚገኘውን ስቲሊ አር. ኤም. አይ ኃላ/የተ/የግ/ ማህበር (STEELY RMI P.L.C) የብረታብረት ማምረቻ ፋብሪካን ጎብኝተናል።
ፋብሪካው ዘመናዊ የዲጂታል አሠራርን እና የታዳሽ ኃይልን በመጠቀም ከዚህ ቀደም ይጣሉ የነበሩ የብረት ቁርጥራጮችን መልሶ ጥቅም ላይ እያዋለ ይገኛል፡፡ በዚህም ለተለያዩ የግንባታ ግብዓት የሚውሉ የብረታብረት ምርቶችን እያመረተ መሆኑ የሚደነቅ ነው።
የብረታብረት ፋብሪካው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት ረገድ አበረታች ውጤቶች እያመጣ እንዳለም ተመልክተናል፡፡
መንግሥት የብድር፣ የመሠረተ ልማትና የአሠራር ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር የግሉ ዘርፍ ለኢኮኖሚ ዕድገቱ ዋና አንቀሳቃሽ (ሞተር) እንዲሆን የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ይቀጥላል።
ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም
👍11❤7👎4
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍3
በኦሮሚያ ክልል ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት ተሰበሰበ
**********************
(ኢ ፕ ድ )
በ2017 የምርት ዘመን ሰባት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ እስካሁን ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት መሰብሰቡን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ። በክልሉ 165 ሺህ 321 አርሶ አደሮች በአቮካዶ ልማት መሠማራታቸው ተጠቁሟል፡፡
በቢሮው የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ተገኝ ኢራና ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በክልሉ የአቮካዶ ማሳ ሽፋን 55 ሺህ 112 ሄክታር መሬት የደረሰ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 30 ሺህ 145 ሄክታር የሚሆነው መሬት ላይ የተተከለው የአቮካዶ ዛፍ ምርት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ባለፈው ዓመት ስድስት ነጥብ አምስት ኩንታል የአቮካዶ ምርት ማግኘት መቻሉን አውስተው፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን ሰባት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁንም ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በ21 ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 185 ወረዳዎች በአንድ ሺህ 751 ክላስተር በማደራጀት አቮካዶ መተከሉን የገለጹት አቶ ተገኝ፤ 165 ሺህ 321 ወንድና ሴት አርሶ አደሮች በአቮካዶ ማልማት ሥራ ተሠማርተው….
https://press.et/?p=143334
**********************
(ኢ ፕ ድ )
በ2017 የምርት ዘመን ሰባት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዶ እስካሁን ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት መሰብሰቡን የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ። በክልሉ 165 ሺህ 321 አርሶ አደሮች በአቮካዶ ልማት መሠማራታቸው ተጠቁሟል፡፡
በቢሮው የፍራፍሬ ልማት ዳይሬክተር አቶ ተገኝ ኢራና ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በክልሉ የአቮካዶ ማሳ ሽፋን 55 ሺህ 112 ሄክታር መሬት የደረሰ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ 30 ሺህ 145 ሄክታር የሚሆነው መሬት ላይ የተተከለው የአቮካዶ ዛፍ ምርት እየሰጠ ይገኛል፡፡
ባለፈው ዓመት ስድስት ነጥብ አምስት ኩንታል የአቮካዶ ምርት ማግኘት መቻሉን አውስተው፤ በዘንድሮው የምርት ዘመን ሰባት ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እስካሁንም ሁለት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን ኩንታል የአቮካዶ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡
በክልሉ በ21 ዞኖች ውስጥ በሚገኙ 185 ወረዳዎች በአንድ ሺህ 751 ክላስተር በማደራጀት አቮካዶ መተከሉን የገለጹት አቶ ተገኝ፤ 165 ሺህ 321 ወንድና ሴት አርሶ አደሮች በአቮካዶ ማልማት ሥራ ተሠማርተው….
https://press.et/?p=143334
👍5👏2
የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባት ለሀገር ውስጥ ባንኮች ዕድል ወይስ ስጋት?
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከተጀመረ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ እድሜ አለው።
በእነዚህ ጊዜያትም ያጋጠሙትን መልካም እድሎች እና ፈተናዎች ተሻግሮ ዛሬ ላይ ደርሷል።
የዛሬ ቁመናውም ቢሆን የእድሜውን ያህል እንዳልሆነ በዘርፉ የተሠማሩ ምሁራን ይናገራሉ።
ይህንን እውነታ ለመለወጥ መንግሥት የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረግ የሚያስችል አዋጅ አርቅቆ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ እንዲጸድቅ አድርጓል።
የሕጉ መጽደቅ በብዙ የሚጠበቅ ቢሆንም፤ አሁንም ዜጎችም ሆነ በመስኩ የሚገኙ ምሁራን የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ ነው።
የውጭ ባለሀብቶች በባንክ ዘርፍ እንዲሠማሩ የሚፈቅደው አዋጅ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ምን ይዞ ይመጣል፤ ተስፋ ወይስ ስጋት? በሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት የሚኖረው ጠቀሜታስ ምን ይመስላል በሚለው ሃሳብ ላይ የዘርፉ ባለሙያዎች ምላሽ ሰጥተውናል፡፡
አቶ ክቡር ገና ይባላሉ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ናቸው። አዋጁ መጽደቁ የውጭ ባንኮች ሀገር ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ የሚጋብዝ መሆኑን፤ ባንኮቹ ሊሠሩ የሚችሉትንና የማይችሉትን በዝርዝር ማስቀመጡን ይናገራሉ፡፡
የአዋጁ አቀራረብ ባንኮቹ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ የሚችል ነው ወይስ አይደለም የሚለው ወደፊት ተግባራዊ ሲሆን የሚታይ ነው፡፡ የለውጡ ሂደት…
https://press.et/?p=143333
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከተጀመረ ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ እድሜ አለው።
በእነዚህ ጊዜያትም ያጋጠሙትን መልካም እድሎች እና ፈተናዎች ተሻግሮ ዛሬ ላይ ደርሷል።
የዛሬ ቁመናውም ቢሆን የእድሜውን ያህል እንዳልሆነ በዘርፉ የተሠማሩ ምሁራን ይናገራሉ።
ይህንን እውነታ ለመለወጥ መንግሥት የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ማድረግ የሚያስችል አዋጅ አርቅቆ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ እንዲጸድቅ አድርጓል።
የሕጉ መጽደቅ በብዙ የሚጠበቅ ቢሆንም፤ አሁንም ዜጎችም ሆነ በመስኩ የሚገኙ ምሁራን የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ ነው።
የውጭ ባለሀብቶች በባንክ ዘርፍ እንዲሠማሩ የሚፈቅደው አዋጅ ለሀገር ውስጥ ባንኮች ምን ይዞ ይመጣል፤ ተስፋ ወይስ ስጋት? በሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት የሚኖረው ጠቀሜታስ ምን ይመስላል በሚለው ሃሳብ ላይ የዘርፉ ባለሙያዎች ምላሽ ሰጥተውናል፡፡
አቶ ክቡር ገና ይባላሉ ከፍተኛ የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ናቸው። አዋጁ መጽደቁ የውጭ ባንኮች ሀገር ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ የሚጋብዝ መሆኑን፤ ባንኮቹ ሊሠሩ የሚችሉትንና የማይችሉትን በዝርዝር ማስቀመጡን ይናገራሉ፡፡
የአዋጁ አቀራረብ ባንኮቹ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ሊያደርግ የሚችል ነው ወይስ አይደለም የሚለው ወደፊት ተግባራዊ ሲሆን የሚታይ ነው፡፡ የለውጡ ሂደት…
https://press.et/?p=143333
👍4
በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት ከ160 ሺህ በላይ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት አድርገዋል
*******************
(ኢ ፕ ድ )
በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት ከ160 ሺህ በላይ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ማድረጋቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎች ክብራቸው፣ መብታቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ አገራት ለስራ የሚሄዱበትን ስርዓት መዘርጋቱ ይታወቃል።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎችን የሙያ ክህሎት በማስታጠቅ በውጭ አገራት የስራ ስምሪት ተወዳዳሪና ተቀባይነት እንዲኖራቸው የጀመራቸው ስራዎች ውጤታማ በመሆን ላይ ይገኛሉ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንዳሉት ሚኒስቴሩ ክህሎት መር የስራ እድልን ለመፍጠር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።
እንዲሁም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት በማድረግ ዜጎች በውጭ አገራት መብታቸው፣ ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ለማስቻል እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም የውጭ አገር የስራ ገበያ በማፈላለግ፣ መዳረሻ አገራትን በመለየትና የሁለትዮሽ ስምምነት በመፈጸም ዜጎች ህጋዊ የስራ ዕድል እንዲያገኙ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በአገራቱ ያለውን የስራ ፍላጎት በመለየት ተወዳዳሪና ብቁ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።
ዜጎች በቅድሚያ የቁጠባ የሂሳብ ደብተር እንዲከፍቱ በማድረግ ወደ አገራቸው ሲመለሱ በቆጠቡት ገንዘብ ሀብት አፍርተው ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩንም ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ዜጎች የስራ መታወቂያ እንዲኖራቸውና በቂ ስልጠና እንዲያገኙ በማድረግ የግልጸኝነት ስርዓት እንዲዘረጋ ማስቻሉን ተናግረዋል።
እስካሁን ባለው ከስድስት አገራትና ከተለያዩ ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት በመፈፀም የውጭ አገር የስራ ስምሪት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት የውጭ አገራት የስራ ስምሪት ያደረጉ ዜጎች ቁጥር ከ160ሺህ ማለፉን ተናግረዋል።
ዜጎች መብትና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ህጋዊ የውጭ አገር ስራ ስምሪት ስርአትን ተከትለው ሊሄዱ እንደሚገባም ተናግረዋል።
በደላሎች ተታለው በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገራት ማቅናት ከእንግልት እስከ ህይወት ማጣት የሚያስከትል በመሆኑ ዜጎች ራሳቸውን ከመሰል አደጋ መጠበቅ እንዳለባቸውም ገልፀዋል።
ሚኒስቴሩ የማህበረሰብ አቀፍ ራዲዮ ባለሙያዎች በህገ ወጥ ስደት ላይ እንዲያተኩሩ ስልጠና መስጠቱን በዚሁ ወቅት አንስተዋል፡፡
ታህሳስ 11ቀን 2017 ዓ.ም
*******************
(ኢ ፕ ድ )
በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት ከ160 ሺህ በላይ ዜጎች በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ የውጭ ሀገራት የስራ ስምሪት ማድረጋቸውን የስራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መንግስት ዜጎች ክብራቸው፣ መብታቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ በህጋዊ መንገድ ወደተለያዩ አገራት ለስራ የሚሄዱበትን ስርዓት መዘርጋቱ ይታወቃል።
የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎችን የሙያ ክህሎት በማስታጠቅ በውጭ አገራት የስራ ስምሪት ተወዳዳሪና ተቀባይነት እንዲኖራቸው የጀመራቸው ስራዎች ውጤታማ በመሆን ላይ ይገኛሉ፡፡
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰለሞን ሶካ ለኢዜአ እንዳሉት ሚኒስቴሩ ክህሎት መር የስራ እድልን ለመፍጠር በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።
እንዲሁም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከሀገራት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት በማድረግ ዜጎች በውጭ አገራት መብታቸው፣ ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ለማስቻል እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም የውጭ አገር የስራ ገበያ በማፈላለግ፣ መዳረሻ አገራትን በመለየትና የሁለትዮሽ ስምምነት በመፈጸም ዜጎች ህጋዊ የስራ ዕድል እንዲያገኙ እየሰራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በአገራቱ ያለውን የስራ ፍላጎት በመለየት ተወዳዳሪና ብቁ ዜጎችን ለማፍራት የሚያስችል ስልጠና እየተሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል።
ዜጎች በቅድሚያ የቁጠባ የሂሳብ ደብተር እንዲከፍቱ በማድረግ ወደ አገራቸው ሲመለሱ በቆጠቡት ገንዘብ ሀብት አፍርተው ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎችም የስራ እድል እንዲፈጥሩ የሚያስችል ሁኔታ መፈጠሩንም ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ የስራ ገበያ መረጃ ስርዓት ዜጎች የስራ መታወቂያ እንዲኖራቸውና በቂ ስልጠና እንዲያገኙ በማድረግ የግልጸኝነት ስርዓት እንዲዘረጋ ማስቻሉን ተናግረዋል።
እስካሁን ባለው ከስድስት አገራትና ከተለያዩ ተቋማት ጋር የሁለትዮሽ ስምምነት በመፈፀም የውጭ አገር የስራ ስምሪት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው በተያዘው በጀት አመት ባለፉት ወራት የውጭ አገራት የስራ ስምሪት ያደረጉ ዜጎች ቁጥር ከ160ሺህ ማለፉን ተናግረዋል።
ዜጎች መብትና ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ህጋዊ የውጭ አገር ስራ ስምሪት ስርአትን ተከትለው ሊሄዱ እንደሚገባም ተናግረዋል።
በደላሎች ተታለው በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገራት ማቅናት ከእንግልት እስከ ህይወት ማጣት የሚያስከትል በመሆኑ ዜጎች ራሳቸውን ከመሰል አደጋ መጠበቅ እንዳለባቸውም ገልፀዋል።
ሚኒስቴሩ የማህበረሰብ አቀፍ ራዲዮ ባለሙያዎች በህገ ወጥ ስደት ላይ እንዲያተኩሩ ስልጠና መስጠቱን በዚሁ ወቅት አንስተዋል፡፡
ታህሳስ 11ቀን 2017 ዓ.ም
👍8😁2❤1
የምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት‼️
የሰባት ሐይቆች መገኛዋ ቢሾፍቱ በተቀናጀ የኮሪደር ልማት ላይ ትገኛለች።
በከተማዋ የተጀመሩ የተፈጥሮ ጸጋን ወደ ጥቅም የሚቀይሩ የልማትና የስማርት ሲቲ ተግባራት የሚበረታቱ እንዲሁም የቢሾፍቱን የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስት መናገሻነት በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሳድጉ ናቸው።
የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራዎቹ የከተማዋን ገፅታ፣ ዘመናዊነትና የነዋሪዎቿን ኑሮ የሚያሻሽሉ ናቸው፡፡
እነዚህ የልማት ስራዎች በከተማዋ አመራርና በፕሮጀክት ሠራተኞች የሌት ተቀን ትጋት በአጭር ጊዜ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ ሙሉ እምነት አለን።
መንግስት ከተሞች በአረንጓዴ ውበት እና በዘመናዊ የክትመት ስርዓት ተመራጭ የአገልግሎትና ምቹ የመኖሪያ ማዕከላት እንዲሆኑ የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ታህሳስ 11ቀን 2017ዓ.ም
የሰባት ሐይቆች መገኛዋ ቢሾፍቱ በተቀናጀ የኮሪደር ልማት ላይ ትገኛለች።
በከተማዋ የተጀመሩ የተፈጥሮ ጸጋን ወደ ጥቅም የሚቀይሩ የልማትና የስማርት ሲቲ ተግባራት የሚበረታቱ እንዲሁም የቢሾፍቱን የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስት መናገሻነት በከፍተኛ ሁኔታ የሚያሳድጉ ናቸው።
የተቀናጀ የኮሪደር ልማት ሥራዎቹ የከተማዋን ገፅታ፣ ዘመናዊነትና የነዋሪዎቿን ኑሮ የሚያሻሽሉ ናቸው፡፡
እነዚህ የልማት ስራዎች በከተማዋ አመራርና በፕሮጀክት ሠራተኞች የሌት ተቀን ትጋት በአጭር ጊዜ ተጠናቅቀው ለአገልግሎት እንደሚበቁ ሙሉ እምነት አለን።
መንግስት ከተሞች በአረንጓዴ ውበት እና በዘመናዊ የክትመት ስርዓት ተመራጭ የአገልግሎትና ምቹ የመኖሪያ ማዕከላት እንዲሆኑ የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ታህሳስ 11ቀን 2017ዓ.ም
❤9👍6👎2
“ግብጽን የሚያዋጣት ሕግ የሆነውን የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነት ፈርሞ መቀበል ነው”
- ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ (ዶ/ር) የታሪክ ምሁር
****
(ኢ ፕ ድ)
በአሁኑ ወቅት ግብጽን የሚያዋጣት ከወራት በፊት ተፈርሞ ሕግ የሆነውን የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነትን ፈርሞ መቀበል እንደሆነ የታሪክ ምሁር ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ኢትዮጵያ 130 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ይዛ ያለ ባሕር በር መኖር የማይታሰብ ነገር እንደሆነም አመልክተዋል።
ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ አብላጫዎቹ የተፋሰሱ ሀገራት የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነትን መቀበላቸውን በፊርማቸው ከማረጋገጥም ባሻገር የሀገራቸው ሕግ አድርገው አጽድቀውታል።
የትብብር ማሕቀፍ ስምምነት በስድስት የተፋሰሱ ሀገሮች በመጽደቁም ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ ሕግ መሆኑን ያስታወሱት የታሪክ ምሁሩ ፤ ለግብጽም መልካም የሚሆነው ማሕቀፉን ተቀብላ ከኢትዮጵያ ጋር ተባብራ ብትሠራ እንደሆነ አመልክተዋል። ተባብራ መሥራቷም የበለጠ ተጠቃሚ ያደርጋታል ብለዋል ።
እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ በኢትዮጵያ በኩል ዋናው ቁም ነገር በአቋም መጽናት ነው። የትብብር ማሕቀፉ ሥራ ላይ እንዲውል በማድረጉ በኩል አሁን የመጣችበት መንገድ መልካም የሚባል ነው፤ ይህንኑ አጠናክሮ መቀጠል ተገቢ ነው።
በኢትዮጵያ ጉዳይ አርፋ መቀመጥን የማትወደዋ ግብጽ፣ እንዲሁ ከመድከም ባለፈ ምንም ማድረግ አልቻለችም ያሉት ተባባሪ ፕሮፌሰሩ ፣ የትብብር ማሕቀፉን ፈርማ በማጽደቅ ተጠቃሚ........https://press.et/?p=143416
- ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ (ዶ/ር) የታሪክ ምሁር
****
(ኢ ፕ ድ)
በአሁኑ ወቅት ግብጽን የሚያዋጣት ከወራት በፊት ተፈርሞ ሕግ የሆነውን የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነትን ፈርሞ መቀበል እንደሆነ የታሪክ ምሁር ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ (ዶ/ር) አስታወቁ።
ኢትዮጵያ 130 ሚሊዮን የሚገመት ሕዝብ ይዛ ያለ ባሕር በር መኖር የማይታሰብ ነገር እንደሆነም አመልክተዋል።
ተባባሪ ፕሮፌሰር አየለ በክሪ ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ አብላጫዎቹ የተፋሰሱ ሀገራት የናይል ትብብር ማሕቀፍ ስምምነትን መቀበላቸውን በፊርማቸው ከማረጋገጥም ባሻገር የሀገራቸው ሕግ አድርገው አጽድቀውታል።
የትብብር ማሕቀፍ ስምምነት በስድስት የተፋሰሱ ሀገሮች በመጽደቁም ካለፈው ጥቅምት ወር ጀምሮ ሕግ መሆኑን ያስታወሱት የታሪክ ምሁሩ ፤ ለግብጽም መልካም የሚሆነው ማሕቀፉን ተቀብላ ከኢትዮጵያ ጋር ተባብራ ብትሠራ እንደሆነ አመልክተዋል። ተባብራ መሥራቷም የበለጠ ተጠቃሚ ያደርጋታል ብለዋል ።
እንደ እርሳቸው ገለጻ፤ በኢትዮጵያ በኩል ዋናው ቁም ነገር በአቋም መጽናት ነው። የትብብር ማሕቀፉ ሥራ ላይ እንዲውል በማድረጉ በኩል አሁን የመጣችበት መንገድ መልካም የሚባል ነው፤ ይህንኑ አጠናክሮ መቀጠል ተገቢ ነው።
በኢትዮጵያ ጉዳይ አርፋ መቀመጥን የማትወደዋ ግብጽ፣ እንዲሁ ከመድከም ባለፈ ምንም ማድረግ አልቻለችም ያሉት ተባባሪ ፕሮፌሰሩ ፣ የትብብር ማሕቀፉን ፈርማ በማጽደቅ ተጠቃሚ........https://press.et/?p=143416
👍12