Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
343 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መልዕክት‼️

ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ እየተገነቡ ካሉ ሜጋ ፕሮጀክቶች በተጓዳኝ በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ ወገኖችን የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽሉ በርካታ ስራዎች ተከናውነዋል። በዛሬው እለትም የኢትዮጵያ ወዳጅ የሆኑት የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ፕሬዝዳንት ሸኽ መሀመድ ቢን ዛይድ አልናህያን ድጋፍ የተገነባውን የኦሮሚያ አብዲ ቦሩ የህጻናት ማሳደጊያ ማዕከልን መርቀን ከፍተናል። ማዕከሉ ወላጅ የሌላቸውንና በችግር ውስጥ ያሉ ህጻናትን ከማሳደግ ባሻገር የሁለቱ ወዳጅ ሀገራት ትብብር ማሳያ ነው።

ታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓም
👍13👎2
#ዓድዋን በዜማ፣ #ዓባይን በቅኔ........‼️

✍️ ሙዚቀኛ፣የግጥምና የዜማ ደራሲ፣ ዓድዋን በዜማ፣ ዓባይን በቅኔ የገለጠች፣

✍️ እኤአ በኖቬምበር 22 2024 በተለቀቀው ግላዲያተር ሁለት ማጀቢያ ሙዚቃ ላይ ተሳትፋለች፣

✍️ “ኢትዮጵያ”፣ “ዓባይ”፣ “ካህኔ”፣ “ናፈቀኝ” ሥራዎቿ በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ጥልቅ ስፍራን ይዘው ይገኛሉ፣

✍️ “ዓድዋ” የተሰኘው ሙዚቃዋ ኢትዮጵያውያን ለነጻነት የከፈሉትን መሥዋዕትነት አሳይታበታለች፣
🥰1611👍6🎉2
ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የሚያስተላልፈው መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት ጀመረ
*******
(ኢ ፕ ድ)
የምስራቅ አፍሪካ ኤሌክትሪክ ሀይዌይ ፕሮጀክት አካል የሆነው ኃይል ከኬንያ ወደ ታንዛንያ የሚያስተላልፈው መስመር የሙከራ የኃይል አቅርቦት መጀመሩን ውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ገለፀ።

የምስራቅ አፍሪካ ኤሌክትሪክ ሀይዌይ ፕሮጀክት የመጀመሪያው የኃይል ትስስር ከኢትዮጵያ ወደ ኬንያ በተዘረጋው የኃይል አቅርቦት መሰረተልማት በኩል የኃይል ትስስሩ እውን ሆኗል፡፡

የፕሮጀክቱ ሁለተኛና ከኢትዮጵያ - ኬንያ ፕሮጀክት በመቀጠል በኬኒያና በታንዛንያ መካካል የተዘረጋው የኃይል አቅርቦት ትስስር መስመር ነው፤ ይህ የኤሌክትሪክ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተጠናቆ የሙከራ ኃይል አቅርቦት ጀምሯል፡፡

ይህ ቀጠናዊ የኃይል ትስስር በተመጣጣኝ ዋጋ አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በማረጋገጥ በሀገራት መካካል ትብብርን ያመጣል፤ ብለጽግናን ያሰፍናል፡፡

የኃይል ትስስሩ ኢትዮጵያን ያላትን የታዳሽ ኃይል አቅርቦት በማስፋፋት የአረንጓዴ የኤሌክትሪክ ኃይል ግብይትን በቀጠናው እንዲስፋፋ ሚና እንድትጫወት በማስቻል በመጀመሪያዎቹ የግብይት ዘመናት በዓመት ከ200 ሚሊዮን ዶላር ያላነሰ ገቢ እንድታገኝም ያደርጋታል።

ለፕሮጀክቱ የአልም ባንክ ፣ የአፍሪካ ልማት ባንክና የፈረንሳይ የልማት ፋይናንስ ተቋም ድጋፍ አድርገዋል።

ታህሳስ 6 ቀን 2017 ዓም
👍83🥰1
የኮሪደር ልማት የከተማዋን ኢኮኖሚያዊ እድገት መሸከም የሚችሉና መጪውን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ ናቸው
*****
(ኢ ፕ ድ)

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ የከተማዋ ዕድገት እየጨመረ የሚሄድ በመሆኑ ልማቱ የነገውን እድገት መሸከም እንዲችል ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ነው ብለዋል።

የኮሪደር ልማት የተሰራባቸው አካባቢዎች ሲያስገቡ ከነበረው ገቢ 25 በመቶ እድገት አሳይቷል።

በአንደኛው ዙር የኮሪደር ልማት ለዋና መንገድ መጋቢ የሆኑ 10 ኪሜ ርዝመት ያላቸው 13 መንገዶች ተገንብተዋል።

የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማሳለጥና ለሰዎች አማራጭ የእግረኛ መንገድ እንዲያገኙ አስችሏል። በአንደኛው ዙር የኮሪደር ልማት ፒያሳና አካባቢውን የቀየሩ መሰረተ ልማቶች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡

የመኪና ማቆሚያዎች፣ አውቶቢስና የታክሲ ተርሚናሎች፣ ፕላዛዎችና መጋቢ መንገዶች መሰራታቸውን ጠቅሰው፣ በመሬት ውስጥ የውኃ፣ የፍሳሽ፣ የመብራት፣ የትራፊክ ማኔጂመንት፣ሲሲቲቪ ካሜራ መሰረተልማቶች ተገንብተዋል።

በልማቱ አቡነ ጴጥሮስ ፣ዳግማዊ ሚኒሊክ፣ቴዎድሮስ ሀውልት፣ሸዋ ሆቴል፣ ሜጋ አንፊ ቲያትር፣ሲኒማ ኢትዮጵያ፣አገር ፍቅር ቲያትር መታደሳቸውን ጠቅሰው፣ ነባሮችን በማደስ አዳዲሶችን ጨምሮ መስራትን ያካተተ መሆኑን.....https://press.et/?p=143007
👍5
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
2👍1
“ተጠያቂነትን ከኋላ ኪስ በማድረግ የምንሠራው ሥራ ለሀገር አደጋ ነው”
-የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነ ብርሃን (ዶ/ር)
*******
(ኢ ፕ ድ)

በፍትህ ሥርዓቱ ተጠያቂነትን ከኋላ ኪስ በማድረግ ነፃነትን ብቻ በማውለብለብ የሚሠራ ሥራ ለሀገር አደጋ መሆኑን የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ  ኤርሚያስ የማነ ብርሃን (ዶ/ር) አስታወቁ።

ከለውጡ ማግሥት ጀምሮ የሕዝቡን የፍትሕ ጥማት ለማርካት እና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመለከቱ።

ኤርሚያስ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደገለፁት በፍትህ ሥርዓቱ በተለይም ዳኞች ተጠያቂነትን በመተው ነፃነት ላይ ብቻ አትኩረው የሚሰጡት ፍትህ ለሀገር አደጋ በመሆኑ ቀጣይነት እንዳይኖረው የሪፎርም ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከለውጡ ማግስት ጀምሮ የሕዝቡን የፍትሕ ጥማት ለማርካት እና የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ የሪፎርም ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ያመለከቱት ሚኒስትሩ ፤ ሪፎርሙ ለሀገረ-መንግሥት ቀጣይነት፤ ለልማት፤ ለሕዝቦች አብሮነት ፤ መዋቅራዊ በደል እንዳይኖር ከማድረግ አንፃር የሚሠራ እንደሆነ አመልክተዋል።

ፍትህ በሌለበት ልማትን ማስቀጠል የማይቻል መሆኑን ጠቁመዋል።

አንዳንድ ቦታዎች ላይ ነፃነት በዝቶ አጉራዘለልነት የሚታይበት ሁኔታ እንደነበር ጠቁመው፤ እጅግ አማራሪ የሆኑ ዳኝነትን በገንዘብ ለመሸጥ የሚደረጉ ሙከራዎች እንደነበሩ......https://press.et/?p=143064
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍42👏1
ሥራ ፈላጊ ነዎት
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍1🔥1