Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
344 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ መልዕክት‼️

በልምላሜ ከተሞሸረችው፣ ከውበት ሰገነቷ ስፍራ፣ ከተፈጥሮ የቅኔ መዳረሻ፣ ከሰው አክባሪዎቹና ከሸማ ፈታዮቹ ምድርና ከአርባ ምንጮቹ መገኛ፣ አርባ ምንጭ ከተማ ገብተናል፡፡

አርባ ምንጭ አውሮፕላን ማረፊያ ስንደርስ ደማቅ አቀባበል ላደረጉልን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ለአርባ ምንጭ ከተማ ህዝብ ላቅ ያለ ምስጋና አቀርባለሁ።

ህዳር 28 ቀን 2017 ዓም
👍3
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአርባምንጭ ከተማ‼️
4
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት‼️

ከአምስት ወራት በፊት ከነበረኝ ጉብኝት በመቀጠል ዛሬ የአርባምንጭ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የደረሰበትን የእድገት ደረጃ ገምግመናል። ይኽ ሥራ የሀገራችንን የቱሪዝም አቅም የሚያጠናክር የአካባቢውን አስደናቂ የተፈጥሮ መልክዓ ምድርና የተትረፈረፈ ሀብት ቆጥሮ የሚጠቀም ሁሉን ያካተተ ነው።

ቱሪዝምን ከማሳደግ ባሻገር ለአካባቢው ማኅበረሰብ ፕሮጀክቱ ትርጉም ባለው ደራጃ የሥራ ዕድል ይፈጥራል። እነዚህን መሰል ሥራዎች በስኬት ሥራ ሲጀምሩ ለዘላቂ ልማትና ብልፅግና መንገድ የሚጠርጉ ይሆናሉ።

ህዳር 28 ቀን 2017 ዓም
6👍4
#አርባምንጭከተማ

19ኛው የብሔሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን "ሀገራዊ መግባባት ለኅብረብሔራዊ አንድነት"

19ኛው የብሄር ብሄረሰብ በዓል በአርባምንጭ ከተማ በአርባምንጭ ከተማ በደማቅ ሁኔታ እየተከበረ ይገኛል።

ህዳር 29 ቀን 2017 ዓም
👍31