“እኛ ለዜጎቻችን የምናስበውን ያህል ለግብጾችም ለሱዳኖችም እናስባለን”
– ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር
******
(ኢ ፕ ድ)
“እኛ ለዜጎቻችን የምናስበውን ያህል ለግብጾችም ለሱዳኖችም እናስባለን፤ ለሁሉም የሚሻለው ባልተገባ መንገድ ወዲህና ወዲያ ማለት ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር ነው” ሲሉ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) አስታወቁ። ከዓባይ ግድብ በኋላ ብዙ የዓባይ ግድቦችን መገንባት እንደሚጠበቅም አመለከቱ።
ኢንጂነር ሀብታሙ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ሁሌም የምትከተለው የፍትሃዊ ተጠቃሚነትን መርህ ነው። በምትከተለው መርህ መሠረት ለራሷ ዜጎች እንደምታስበው ሁሉ ለግብጾችም፣ ለሱዳኖችም ታስባለች፡፡
ለግብጻውያን የሚሻለው ባልተገባ መንገድ ወዲህና ወዲያ ማለት ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ጥሩውና አዋጩ መንገድ የትብብር ማዕቀፉ ነው ብለዋል፡፡ ይህ ሕግ ሆኖ የጸደቀው ማሕቀፍ፤ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገሮች ማስጠለል የሚችል ትልቅ ጥላ ነው ሲሉም አስረድተዋል።
ግብጾች የዓባይ ግድብ ግንባታ እንዳይሳካ ያላደረጉትና ያልሞከሩት ጥረት አልነበረም፡፡ ዛሬ ሲታይ ግን እነርሱ ያሉት ሳይሆን እኛ ያልነው ትክክል ሆኖ ተገኝቷል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግድቡ ሙሉ በሙሉ እነርሱን የሚጎዳ አድርገው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሲናገሩ የነበረ ቢሆንም፤ መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን......https://press.et/?p=142231
– ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር
******
(ኢ ፕ ድ)
“እኛ ለዜጎቻችን የምናስበውን ያህል ለግብጾችም ለሱዳኖችም እናስባለን፤ ለሁሉም የሚሻለው ባልተገባ መንገድ ወዲህና ወዲያ ማለት ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር ነው” ሲሉ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) አስታወቁ። ከዓባይ ግድብ በኋላ ብዙ የዓባይ ግድቦችን መገንባት እንደሚጠበቅም አመለከቱ።
ኢንጂነር ሀብታሙ (ዶ/ር) ለኢፕድ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያ ሁሌም የምትከተለው የፍትሃዊ ተጠቃሚነትን መርህ ነው። በምትከተለው መርህ መሠረት ለራሷ ዜጎች እንደምታስበው ሁሉ ለግብጾችም፣ ለሱዳኖችም ታስባለች፡፡
ለግብጻውያን የሚሻለው ባልተገባ መንገድ ወዲህና ወዲያ ማለት ሳይሆን በጠረጴዛ ዙሪያ መነጋገር ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ጥሩውና አዋጩ መንገድ የትብብር ማዕቀፉ ነው ብለዋል፡፡ ይህ ሕግ ሆኖ የጸደቀው ማሕቀፍ፤ ሁሉንም የተፋሰሱ ሀገሮች ማስጠለል የሚችል ትልቅ ጥላ ነው ሲሉም አስረድተዋል።
ግብጾች የዓባይ ግድብ ግንባታ እንዳይሳካ ያላደረጉትና ያልሞከሩት ጥረት አልነበረም፡፡ ዛሬ ሲታይ ግን እነርሱ ያሉት ሳይሆን እኛ ያልነው ትክክል ሆኖ ተገኝቷል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግድቡ ሙሉ በሙሉ እነርሱን የሚጎዳ አድርገው ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሲናገሩ የነበረ ቢሆንም፤ መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን......https://press.et/?p=142231
👍4👎4👏1😁1
ኮሎምቢያ ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ ለመክፈት እንቅስቃሴ መጀመሯን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሰታወቀ
👉ባለፉት ሳምንታት ከ20 በላይ ኩንያዎች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል፣
👉በአዲስ አበባ የሚገኙ የውጪ አገራት ኤምባሲዎች ቁጥር ወደ 137 ከፍ ብሏል
*
(ኢ ፕ ድ)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፣በአዲስ አበባ የሚገኙ የውጪ አገራት ኤምባሲዎች ቁጥር ወደ 137 ከፍ ብሏል።
በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ኮሚቴ ተቋቁሞ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ የሚገኙ የውጪ አገራት ኤምባሲዎች ቁጥር 137 ከፍ ማለቱን በመግለጽ በቅርቡ 24 የውጪ አገራት አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤቸውን ለፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ስላሴ አቅርበዋል ብለዋል።
አምባሳደሮቹ አገሮቻቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ተናግረዋል።
ኮሎምቢያ አዲስ ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ ለመክፈት እንቅስቃሴ መጀመሯንም ጠቁመዋል።
ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው አዲስ መነቃቃትን ፈጥሯል። ባለፉት ሳምንታት ከ20 በላይ ኩንያዎች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል ብለዋል።
በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ከማይናማር በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በሊባኖስ ለደህንነታቸው አስጊ የሆኑ 2 ሺህ ዜጎችን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
ህዳር 26 ቀን 2017 ዓም
👉ባለፉት ሳምንታት ከ20 በላይ ኩንያዎች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል፣
👉በአዲስ አበባ የሚገኙ የውጪ አገራት ኤምባሲዎች ቁጥር ወደ 137 ከፍ ብሏል
*
(ኢ ፕ ድ)
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፣በአዲስ አበባ የሚገኙ የውጪ አገራት ኤምባሲዎች ቁጥር ወደ 137 ከፍ ብሏል።
በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ኮሚቴ ተቋቁሞ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ የሚገኙ የውጪ አገራት ኤምባሲዎች ቁጥር 137 ከፍ ማለቱን በመግለጽ በቅርቡ 24 የውጪ አገራት አዳዲስ አምባሳደሮች የሹመት ደብዳቤቸውን ለፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ስላሴ አቅርበዋል ብለዋል።
አምባሳደሮቹ አገሮቻቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር እንደሚሰሩ መግለጻቸውን ተናግረዋል።
ኮሎምቢያ አዲስ ኤምባሲዋን በአዲስ አበባ ለመክፈት እንቅስቃሴ መጀመሯንም ጠቁመዋል።
ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው አዲስ መነቃቃትን ፈጥሯል። ባለፉት ሳምንታት ከ20 በላይ ኩንያዎች በኢትዮጵያ ጉብኝት አድርገዋል ብለዋል።
በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ከማይናማር በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው በሊባኖስ ለደህንነታቸው አስጊ የሆኑ 2 ሺህ ዜጎችን ለመመለስ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በማርቆስ በላይ
ህዳር 26 ቀን 2017 ዓም
👍6❤2
በ2016 ዓመተ ምህረት የምርት ዘመን የስንዴ ምርት በምን ያህል ከፍተኛ ደረጃ ማደጉን ያውቁ ይሆን?
አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎች 3.6 ሚሊዮን ሄክታር አርሰው 123 ሚሊዮን ኩንታል ሲያመርቱ በመስኖ ከታረሰው 2.9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ደግሞ 107.7 ሚሊዮን ኩንታል ማምረት ተችሏል። የ2016 የኢትዮጵያ የስንዴ ምርት በድምሩ 230 ሚሊዮን ኩንታል ደርሷል።
ከ2012 የምርት ዘመን ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎቹ 54 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ብቻ ነበር ያመረቱት። ዛሬ ይህ ቁጥር ትርጉም ባለው መጠን ከፍ ብሏል። ይህ እመርታ በፅኑ አመራር፣ በአስቻይ ፖሊሲዎች ብሎም ምርትን ለማሳደግ በተተገበረ ያላሰለሰ ጥረት የተገኘ ነው።
#PMOEthiopia
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ቴሌግራም https://t.me/ethpress
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎች 3.6 ሚሊዮን ሄክታር አርሰው 123 ሚሊዮን ኩንታል ሲያመርቱ በመስኖ ከታረሰው 2.9 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ደግሞ 107.7 ሚሊዮን ኩንታል ማምረት ተችሏል። የ2016 የኢትዮጵያ የስንዴ ምርት በድምሩ 230 ሚሊዮን ኩንታል ደርሷል።
ከ2012 የምርት ዘመን ጋር ሲነፃፀር አነስተኛ ማሳ ተጠቃሚ ገበሬዎቹ 54 ሚሊዮን ኩንታል ስንዴ ብቻ ነበር ያመረቱት። ዛሬ ይህ ቁጥር ትርጉም ባለው መጠን ከፍ ብሏል። ይህ እመርታ በፅኑ አመራር፣ በአስቻይ ፖሊሲዎች ብሎም ምርትን ለማሳደግ በተተገበረ ያላሰለሰ ጥረት የተገኘ ነው።
#PMOEthiopia
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
ቴሌግራም https://t.me/ethpress
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
❤3😁1
ሥራ ፈላጊ ነዎት❓
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
መልካም ዕድል‼️
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች‼️
ትዊተር https://twitter.com/PressEthio
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍3🔥1
2ኛው የምሥራቅ አፍሪካ የጥበባትና ባህል ፌስቲቫል
******
(ኢ ፕ ድ)
2ኛው የምሥራቅ አፍሪካ የጥበብና ባህል ፌስቲቫል "ጥበብና ባህል ለቀጠናዊ ትብብር" በሚል መሪ ቃል ከጥር 15 እስከ 18 በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
ከቀጠናው ሀገራት አምባሳደሮች ጋር ለመወያየት በተዘጋጀው መድረክ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማህዲን እንደገለፁት፤ ፌስቲቫሉ የምሥራቅ አፍሪካ አገራትን ትስስርን ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል።
ፌስቲቫሉን ኢትዮጵያ ማስተናገዷ የአገሪቱን ባህል አጉልቶ ለማሳየት እንደሚያስችል ጠቁመው፤ ፌስቲቫሉ የምሥራቅ አፍሪካ አገራት የሚሰባሰቡበት አጋጣሚን ይፈጥራል።
የመጀመሪያው የምሥራቅ አፍሪካ የጥበባትና ባህል ፌስቲቫል በ2014 ዓ.ም በወዳጅነት ፓርክ ተካሄዷል።
ህዳር 27 ቀን 2017 ዓም
******
(ኢ ፕ ድ)
2ኛው የምሥራቅ አፍሪካ የጥበብና ባህል ፌስቲቫል "ጥበብና ባህል ለቀጠናዊ ትብብር" በሚል መሪ ቃል ከጥር 15 እስከ 18 በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
ከቀጠናው ሀገራት አምባሳደሮች ጋር ለመወያየት በተዘጋጀው መድረክ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማህዲን እንደገለፁት፤ ፌስቲቫሉ የምሥራቅ አፍሪካ አገራትን ትስስርን ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል።
ፌስቲቫሉን ኢትዮጵያ ማስተናገዷ የአገሪቱን ባህል አጉልቶ ለማሳየት እንደሚያስችል ጠቁመው፤ ፌስቲቫሉ የምሥራቅ አፍሪካ አገራት የሚሰባሰቡበት አጋጣሚን ይፈጥራል።
የመጀመሪያው የምሥራቅ አፍሪካ የጥበባትና ባህል ፌስቲቫል በ2014 ዓ.ም በወዳጅነት ፓርክ ተካሄዷል።
ህዳር 27 ቀን 2017 ዓም
👍6👏1
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር 10 ሚሊየን ደረሰ
*****
(ኢ ፕ ድ)
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር 10 ሚሊየን መድረሱን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል፡፡
የፕሮግራሙ የኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አቤኔዘር ፈለቀ እንደገለጹት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሁሉን አቀፍ፣ አካታችና አስተማማኝ አገልግሎት መስጠት ያስችላል፡፡
የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አሰራር ሥርዓት በማዘመንና ዲጂታል በማድረግ ብልሹ አሠራርን ለመቀነስ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
ዲጂታል መታወቂያ በተለያዩ ተቋማት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው÷በቀጣይ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መታወቂያውን እንደ ቅድመ ሁኔታ እንደሚጠይቁ አንስተዋል፡፡
በቅርቡም በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የባንክ አካውንት ለመክፈት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንደቅድመ ሁኔታ መጠየቅ እንደሚጀመር ጠቁመዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም በመዲናዋ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማግኘት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን መያዝ አስገዳጅ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
እስካሁን ድረስም 10 ሚሊየን በላይ ዜጎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንደወሰዱ ነው አቶ አቤኔዘር ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የገለጹት፡፡
ስለሆነም ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ የተለያዩ ማዕከላት ተመዝግበው ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
ህዳር 27 ቀን 2017 ዓም
*****
(ኢ ፕ ድ)
ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር 10 ሚሊየን መድረሱን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታውቋል፡፡
የፕሮግራሙ የኮሙኒኬሽንና ሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አቤኔዘር ፈለቀ እንደገለጹት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሁሉን አቀፍ፣ አካታችና አስተማማኝ አገልግሎት መስጠት ያስችላል፡፡
የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን አሰራር ሥርዓት በማዘመንና ዲጂታል በማድረግ ብልሹ አሠራርን ለመቀነስ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
ዲጂታል መታወቂያ በተለያዩ ተቋማት ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸው÷በቀጣይ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት መታወቂያውን እንደ ቅድመ ሁኔታ እንደሚጠይቁ አንስተዋል፡፡
በቅርቡም በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የባንክ አካውንት ለመክፈት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንደቅድመ ሁኔታ መጠየቅ እንደሚጀመር ጠቁመዋል፡፡
ከዚህ ባለፈም በመዲናዋ የሚሰጡ አገልግሎቶችን ለማግኘት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን መያዝ አስገዳጅ እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
እስካሁን ድረስም 10 ሚሊየን በላይ ዜጎች ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንደወሰዱ ነው አቶ አቤኔዘር ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የገለጹት፡፡
ስለሆነም ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ የተለያዩ ማዕከላት ተመዝግበው ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንዲያገኙ ጥሪ አቅርበዋል ሲል ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
ህዳር 27 ቀን 2017 ዓም
👍9