ሀገራዊ ኃይል የማመንጨት አቅም ከስድስት ሺህ ጊጋ ዋት በላይ ደርሷል
******
(ኢ ፕ ድ)
ሀገራዊ ኃይል የማመንጨት አቅም ከስድስት ሺህ ጊጋ ዋት በላይ መድረሱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በሚኒስቴሩ የኤሌክትሪፊኬሽንና የኢነርጂ መረጃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ዳቢ እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር በሁሉም ዘርፍ በቂ የታዳሽ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር እየተሠራ ነው፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮት ኃይል የማመንጨት አቅም ከስድስት ሺህ ጊጋ ዋት በላይ ማድረስ ተችሏል፡፡ በሁለትና ሦስት ዓመታት ጊዜ ውስጥም ይህን ቁጥር በእጥፍ ለማሳግ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡
በሁሉም ዘርፍ ነዳጅ ላይ ያለውን ጥገኝት በመቀነስ ታዳሽ ኃይል ላይ መሠረት ያደረገ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ በቂ የማመንጨት አቅም፣ ኃይል የማስተላለፍና መሠረተ ልማት መገንባት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት አቶ መስፍን፤ ከ20ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ተከናውኗል፡ ፡ የማሰራጫ መሠረተ ልማቶችም ከ150 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ ደርሰዋል፡፡
ከዚህ በፊት የትራንስፖርት ዘርፉ ሙሉ በሙሉ የነዳጅ ምርቶች ላይ ጥገኛ ነበር ያሉት መሪ ሥራ አስፈጻሚው፤ ታዳሽ ኃይል ላይ መሠረት ያደረገ የትራንስፖርት አቅርቦት እንዲኖር በቂ የኃይል አቅርቦት......https://press.et/?p=141902
******
(ኢ ፕ ድ)
ሀገራዊ ኃይል የማመንጨት አቅም ከስድስት ሺህ ጊጋ ዋት በላይ መድረሱን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
በሚኒስቴሩ የኤሌክትሪፊኬሽንና የኢነርጂ መረጃ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ዳቢ እንደገለጹት፤ እንደ ሀገር በሁሉም ዘርፍ በቂ የታዳሽ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር እየተሠራ ነው፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮት ኃይል የማመንጨት አቅም ከስድስት ሺህ ጊጋ ዋት በላይ ማድረስ ተችሏል፡፡ በሁለትና ሦስት ዓመታት ጊዜ ውስጥም ይህን ቁጥር በእጥፍ ለማሳግ እየተሠራ ነው ብለዋል፡፡
በሁሉም ዘርፍ ነዳጅ ላይ ያለውን ጥገኝት በመቀነስ ታዳሽ ኃይል ላይ መሠረት ያደረገ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ በቂ የማመንጨት አቅም፣ ኃይል የማስተላለፍና መሠረተ ልማት መገንባት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት አቶ መስፍን፤ ከ20ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ተከናውኗል፡ ፡ የማሰራጫ መሠረተ ልማቶችም ከ150 ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ ደርሰዋል፡፡
ከዚህ በፊት የትራንስፖርት ዘርፉ ሙሉ በሙሉ የነዳጅ ምርቶች ላይ ጥገኛ ነበር ያሉት መሪ ሥራ አስፈጻሚው፤ ታዳሽ ኃይል ላይ መሠረት ያደረገ የትራንስፖርት አቅርቦት እንዲኖር በቂ የኃይል አቅርቦት......https://press.et/?p=141902
👍5😁2❤1
🔥2
"ብልፅግና ፓርቲ ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ ፓርቲ ነው"
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንትና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
******
(ኢ ፕ ድ)
ብልፅግና ፓርቲ በአምስት ዓመታት ጉዞው በሁሉም ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ የአፍሪካ ግዙፉ ፓርቲ ነው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንትና የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት ምስረታ በዓል ሀገራዊ ማጠቃለያ መርሐግብር ዓድዋ መታሳቢያ ሙዚየም ተካሄዷል፡፡
በወቅቱ የብልፅግና ፕሬዚዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ብልፅግና ኢትዮጵያ ከድህነትና ከችግር እንድትወጣ ሌት ተቀን የሚሰራ ፓርቲ ነው። ፓርቲው አባላቱና መላውን ህዝብ በማስተባበርና በማሳተፍ ሁለተናዊ ስኬቶችን አስመዝግቧል።
ብልጽግና ራዕያችን እንድናሳካ፤ ህልማችንንና ችግሮቻችን ፈትተን እንድንስራ የሚያደርገን ጉልበታችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ መላ ኢትዮጵያዊያን የወል እውነታችን ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ብልጽግና መለያው እውነት፣ እውቀትና ጥበብ መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያን የላቀ ከፍታ ላይ ለማድረስ ሙሉ ዕይታ ያለውና በሁሉም ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ ፓርቲ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዲፕሎማሲ፣ በኢኮኖሚ፣ በኮሪደር ልማት፣ በግብርና፣ በቱሪዝም፣በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች የሚጨበጡና የሚታዩ ስኬቶችን ባለፉት አምስት ዓመታት ማስመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡
በጌትነት ምህረቴ
ህዳር 21 ቀን 2017 ዓም
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
- የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንትና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
******
(ኢ ፕ ድ)
ብልፅግና ፓርቲ በአምስት ዓመታት ጉዞው በሁሉም ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ የአፍሪካ ግዙፉ ፓርቲ ነው ሲሉ የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንትና የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት ምስረታ በዓል ሀገራዊ ማጠቃለያ መርሐግብር ዓድዋ መታሳቢያ ሙዚየም ተካሄዷል፡፡
በወቅቱ የብልፅግና ፕሬዚዳንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ብልፅግና ኢትዮጵያ ከድህነትና ከችግር እንድትወጣ ሌት ተቀን የሚሰራ ፓርቲ ነው። ፓርቲው አባላቱና መላውን ህዝብ በማስተባበርና በማሳተፍ ሁለተናዊ ስኬቶችን አስመዝግቧል።
ብልጽግና ራዕያችን እንድናሳካ፤ ህልማችንንና ችግሮቻችን ፈትተን እንድንስራ የሚያደርገን ጉልበታችን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)፤ መላ ኢትዮጵያዊያን የወል እውነታችን ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡
ብልጽግና መለያው እውነት፣ እውቀትና ጥበብ መሆኑን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያን የላቀ ከፍታ ላይ ለማድረስ ሙሉ ዕይታ ያለውና በሁሉም ዘርፎች በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ ፓርቲ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በዲፕሎማሲ፣ በኢኮኖሚ፣ በኮሪደር ልማት፣ በግብርና፣ በቱሪዝም፣በቴክኖሎጂና በሌሎች ዘርፎች የሚጨበጡና የሚታዩ ስኬቶችን ባለፉት አምስት ዓመታት ማስመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡
በጌትነት ምህረቴ
ህዳር 21 ቀን 2017 ዓም
ቲክቶክ https://www.tiktok.com/@ethiopianpressagency...
ድረ ገጽ https://www.press.et
👍10🖕3👎2😁1
የእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኘ
****
(ኢ ፕ ድ)
በእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዚዳንት ጂን ሊኩን የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኘ።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ጋርም ውይይት አድርገዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን አጠቃላይ የስራ እስቅስቃሴና በአፍሪካ አህጉር በመሪነት የሚጠቀስባቸውንና በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪነቱን ያስጠበቀባቸውን የስራ ክፍሎችና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችን መመልክታቸውን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ህዳር 21 ቀን 2017 ዓም
****
(ኢ ፕ ድ)
በእስያ መሰረተ ልማት ኢንቨስትመንት ባንክ ፕሬዚዳንት ጂን ሊኩን የተመራ ልዑክ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ጎበኘ።
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ጋርም ውይይት አድርገዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን አጠቃላይ የስራ እስቅስቃሴና በአፍሪካ አህጉር በመሪነት የሚጠቀስባቸውንና በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪነቱን ያስጠበቀባቸውን የስራ ክፍሎችና የአቪዬሽን ቴክኖሎጂዎችን መመልክታቸውን ከአየር መንገዱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ህዳር 21 ቀን 2017 ዓም
👍4
በገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ ስም ደረሰኝ በመጠየቅ ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ
**
(ኢ ፕ ድ)
መርካቶ በተለምዶ ድር ተራ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ በገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ ስም ደረሰኝ በመጠየቅ ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አሰታወቀ።
በህግ ቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪ ግለሰብ በመርካቶ የቢሮው ሰራተኛ ነኝ በማለት ደረሰኝ በመጠየቅ ንግድ ቤቶች በመግባት የዕቃዎች ደረሰኝ ሲጠይቅና ሲያጭበረብር የነበረ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋለው በመርካቶ በተመደቡ የቢሮው የቁጥጥር ባለሙያዎች መሆኑን የመርካቶ ቁጥር 1 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህግ ተገዥነት ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ፓርቲ ንጉሴ ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ በቢሮው የተመደቡ የቁጥጥር ባለሙያዎች በቡድን የሚንቀሳቀሱ፣ መለያ ባጅና መታወቂያ ያላቸው መሆኑን መለየት እንዳለበት ቢሮው አሳስበዋል።
መሰል ድርጊት ሲያግጥም በነፃ የስልክ መስመር 7075 እና በአቅራቢያው ለሚገኙ የህግ አስከባሪዎች መጠቆም እንዳለበት ተመላክቷል።
ህዳር 21 ቀን 2017 ዓም
**
(ኢ ፕ ድ)
መርካቶ በተለምዶ ድር ተራ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ በገቢዎች ቢሮ ሰራተኛ ስም ደረሰኝ በመጠየቅ ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ አሰታወቀ።
በህግ ቁጥጥር ስር የዋለው ተጠርጣሪ ግለሰብ በመርካቶ የቢሮው ሰራተኛ ነኝ በማለት ደረሰኝ በመጠየቅ ንግድ ቤቶች በመግባት የዕቃዎች ደረሰኝ ሲጠይቅና ሲያጭበረብር የነበረ መሆኑ ለማወቅ ተችሏል።
ተጠርጣሪው ግለሰብ በቁጥጥር ስር የዋለው በመርካቶ በተመደቡ የቢሮው የቁጥጥር ባለሙያዎች መሆኑን የመርካቶ ቁጥር 1 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የህግ ተገዥነት ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ፓርቲ ንጉሴ ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ በቢሮው የተመደቡ የቁጥጥር ባለሙያዎች በቡድን የሚንቀሳቀሱ፣ መለያ ባጅና መታወቂያ ያላቸው መሆኑን መለየት እንዳለበት ቢሮው አሳስበዋል።
መሰል ድርጊት ሲያግጥም በነፃ የስልክ መስመር 7075 እና በአቅራቢያው ለሚገኙ የህግ አስከባሪዎች መጠቆም እንዳለበት ተመላክቷል።
ህዳር 21 ቀን 2017 ዓም
👍3😁1