በሀገሪቱ የተከሰቱ ሁከቶችና ግጭቶች ከሙስና ወንጀል ጋር እንደሚያያዙ ኮሚሽኑ ገለጸ
*************************
(ኢፕድ)
አዳማ:- ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተለያዩ ቦታዎች እየደረሱ ያሉት ሁከቶች እና ግጭቶች ኢንዲሁም ከዚህ የመነጨው የዜጎች መፈናቀል ከሙስና ወንጀል ጋር የተያያዘ መሆኑን የጸረ ሙስና ኮሚሽን ገለጸ።
በኮሚሽኑ የ10 ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ፣ የ2013 ዓ.ም ዓመታዊ እቅድና የስነ ምግባር መከታተያ መመሪያ ዙሪያ ሲሰጥ በቆየውና ዛሬ በሚጠናቀቀው ስልጠና ላይ የሥራ መመሪያ የሰጡት በኮሚሽኑ የክልል ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ መለስ ተገኝ፤ ሙስና አሁን በዓለም ደረጃ እጅግ አሳሳቢ የሆነ፣ የአደጉ አገራትንም የፈተነ፣ በተለይም የአረብ አገራትን እስከማፈራረስ የደረሰ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የአረብ አገር ህዝቦች በአገራቸው መኖር ያልቻሉበትና ወደ ኢትዮጵያ ለመሰደድ የተገደዱት ከዚሁ ችግር በመነጨ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ ኢትዮጵያ በማደግ ላይ ያለች እንደመሆኗ አደጋው ቢከሰትባት እጅግ በጣም አስከፊ እንደሚሆን አመልክተዋል።
‹‹በሙስና የተዘፈቁ ሰዎች በዛች አገር ሆነው የዘረፉትን ገንዘብ እየበሉ መኖር የሚችሉት አገር ሲበጠበጥና ሰላም ሲጠፋ ነው›› ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ሰላም ከሰፈነ፣ አንድነት ከተፈጠረ እንደሚጠየቁ ያውቃሉ ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በአገሪቱ አልፎ አልፎ የሚስተዋሉት ሁከትና ግጭቶች በሙስና የተዘፈቁ ሰዎች አጀንዳ መሆኑን ማሰብ ብልህነት ይሆናል ብለዋል፡፡
እንቅስቃሴው እውነት ለዘራቸው፣ ለብሄራቸው ወይም ለሃይማኖታቸው ተቆርቁረው አይደለም ያሉት አቶ መለስ፤ በሙስና የተዘፈቁ ዜጎችን ጠያቂ ህብረተሰብ እንዳይፈጠር አጀንዳ ለመቀየር እየተደረገ ያለ ጥረት አካል እንደሆነ አመልክተዋል።
በዚህም ምክንያት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች እየደረሰ ያለው ግጭትና ሁከት ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። ውስብስብ የሆነ፣ እጅግ በጣም በረቀቀ እና በቡድን የተሳሰረ መልኩ የሚከናወንን ሙስና ተበታትኖ መታገል እንደማይቻል ጠቁመዋል፡፡
ቀደም ሲል የተደረጉ ጥረቶች መልካም እንደነበሩ፣ ካለው የችግሩ ግዝፈት አንጻር በተሻለና ወጥነት ባለው አገራዊ መልክ በያዘ የእቅድ ማእቀፍ ተዘጋጅቶ በመደጋገፍ ለመስራት ዕቅዱ ጸድቆ ወደ ትግበራ መሸጋገሩንም ጠቁመዋል፡፡
ዕቅዱ ቀድሞ ከተከናወነው የላቀ በመተግበር፣ ያለውን የገዘፈ ችግር ያገናዘበና ወጥ የሆነ ትግል ማድረግ የሚያስችል መሆኑን ያመለከቱት አቶ መለስ፤ ትግሉን የሚያንቀሳቅሱ በሁሉም የእርከን ደረጃ ያሉ ባለሙያዎች እርስ በርስ በመናበብ፣ የተቀናጀና የተናበበ ተግባር በማከናወን ስኬታማ ተግባር ለማከናወን እንደሚያስችል አመልክተዋል።
በኮሚሽኑ የስልጠናና ጥናት ምርምር ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሻሜቦ በበኩላቸው፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የጸረ ሙስና ትግሉ በተለያዩ ተቋማት የሚካሄድ በመሆኑ የሙስና ወንጀሎችን ለመታገል አዳጋች መሆኑን ገልጸዋል። የሙስና ተጋላጭነትም እየጨመረ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በተቋማት ለሙስናና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነት መበራከትም ለመልካም አስተዳደር እንቅፋት መሆኑንም ያመለከቱት አቶ ተስፋዬ፣ የጸረ ሙስና ትግሉ በቴክኖሎጂ አለመደገፉ እና በተቋማት ውስጥ በሚፈጸሙ ኢ-ስነ ምግባራዊ ድርጊቶች ምክንያት በሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ሮሮዎችና ቅሬታዎች መበራከታቸውን ጠቁመዋል። ለተማሪዎች የስነ ምግባር ብልሽት መንስኤ የሚሆኑ በአቋራጭ የመበልጸግ ፍላጎት መጨመርንም እንደተግዳሮት አንስተዋል።
እቅዱ ሙስናና ብልሹ አሰራርን የመከላከል አቅምን የሚያሳድግ መሆኑን አመልክተው፤ የአገሪቱን የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን የመከላከል ደረጃ እንደሚያሳድግ፣ በሙስና መከላከል ላይ የኮሚሽኑና የአገሪቱ ገጽታ ለመገንባት አስተዋጽኦ የጎላ እንደሚሆንም ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
ኮሚሽኑ ጠንካራና ኃላፊነቱን በብቃት መፈጸም የሚችል ተቋም መገንባት፣ የተቋማትን የስነ ምግባር መከታተያ ክፍሎችን የመፈጸም አቅም ማሳደግ፣ በሀገሪቱ ሙስናና በብልሹ አሰራሮችን የመከላከል አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ፣ ተማሪዎች በመልካም ሽነ ምግባር ታንጸው ሙስና እንዲጠየፉ ማድረግ እንዲሁም በኢትዮጵያ የተቋማት የሙስና ተጋላጭነት እንዲቀንስ በማድረግ በአፍሪካ ሙስናን በመከላከል ግንባር ቀደም ሆኖ መገኘት ከእቅዱ የሚጠበቁ ውጤቶች መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
አገራዊ የስነ ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስትራቴጂያዊ እቅዱ ከ2013 ዓ.ም እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ ለ10 ዓመታት የሚተገበር ነው።
አዲስ ዘመን መስከረም 13/201
*************************
(ኢፕድ)
አዳማ:- ከተወሰኑ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የተለያዩ ቦታዎች እየደረሱ ያሉት ሁከቶች እና ግጭቶች ኢንዲሁም ከዚህ የመነጨው የዜጎች መፈናቀል ከሙስና ወንጀል ጋር የተያያዘ መሆኑን የጸረ ሙስና ኮሚሽን ገለጸ።
በኮሚሽኑ የ10 ዓመታት ስትራቴጂክ እቅድ፣ የ2013 ዓ.ም ዓመታዊ እቅድና የስነ ምግባር መከታተያ መመሪያ ዙሪያ ሲሰጥ በቆየውና ዛሬ በሚጠናቀቀው ስልጠና ላይ የሥራ መመሪያ የሰጡት በኮሚሽኑ የክልል ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ መለስ ተገኝ፤ ሙስና አሁን በዓለም ደረጃ እጅግ አሳሳቢ የሆነ፣ የአደጉ አገራትንም የፈተነ፣ በተለይም የአረብ አገራትን እስከማፈራረስ የደረሰ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የአረብ አገር ህዝቦች በአገራቸው መኖር ያልቻሉበትና ወደ ኢትዮጵያ ለመሰደድ የተገደዱት ከዚሁ ችግር በመነጨ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ ኢትዮጵያ በማደግ ላይ ያለች እንደመሆኗ አደጋው ቢከሰትባት እጅግ በጣም አስከፊ እንደሚሆን አመልክተዋል።
‹‹በሙስና የተዘፈቁ ሰዎች በዛች አገር ሆነው የዘረፉትን ገንዘብ እየበሉ መኖር የሚችሉት አገር ሲበጠበጥና ሰላም ሲጠፋ ነው›› ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ሰላም ከሰፈነ፣ አንድነት ከተፈጠረ እንደሚጠየቁ ያውቃሉ ብለዋል።
ዳይሬክተሩ በአገሪቱ አልፎ አልፎ የሚስተዋሉት ሁከትና ግጭቶች በሙስና የተዘፈቁ ሰዎች አጀንዳ መሆኑን ማሰብ ብልህነት ይሆናል ብለዋል፡፡
እንቅስቃሴው እውነት ለዘራቸው፣ ለብሄራቸው ወይም ለሃይማኖታቸው ተቆርቁረው አይደለም ያሉት አቶ መለስ፤ በሙስና የተዘፈቁ ዜጎችን ጠያቂ ህብረተሰብ እንዳይፈጠር አጀንዳ ለመቀየር እየተደረገ ያለ ጥረት አካል እንደሆነ አመልክተዋል።
በዚህም ምክንያት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች እየደረሰ ያለው ግጭትና ሁከት ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል። ውስብስብ የሆነ፣ እጅግ በጣም በረቀቀ እና በቡድን የተሳሰረ መልኩ የሚከናወንን ሙስና ተበታትኖ መታገል እንደማይቻል ጠቁመዋል፡፡
ቀደም ሲል የተደረጉ ጥረቶች መልካም እንደነበሩ፣ ካለው የችግሩ ግዝፈት አንጻር በተሻለና ወጥነት ባለው አገራዊ መልክ በያዘ የእቅድ ማእቀፍ ተዘጋጅቶ በመደጋገፍ ለመስራት ዕቅዱ ጸድቆ ወደ ትግበራ መሸጋገሩንም ጠቁመዋል፡፡
ዕቅዱ ቀድሞ ከተከናወነው የላቀ በመተግበር፣ ያለውን የገዘፈ ችግር ያገናዘበና ወጥ የሆነ ትግል ማድረግ የሚያስችል መሆኑን ያመለከቱት አቶ መለስ፤ ትግሉን የሚያንቀሳቅሱ በሁሉም የእርከን ደረጃ ያሉ ባለሙያዎች እርስ በርስ በመናበብ፣ የተቀናጀና የተናበበ ተግባር በማከናወን ስኬታማ ተግባር ለማከናወን እንደሚያስችል አመልክተዋል።
በኮሚሽኑ የስልጠናና ጥናት ምርምር ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ሻሜቦ በበኩላቸው፤ በአገር አቀፍ ደረጃ የጸረ ሙስና ትግሉ በተለያዩ ተቋማት የሚካሄድ በመሆኑ የሙስና ወንጀሎችን ለመታገል አዳጋች መሆኑን ገልጸዋል። የሙስና ተጋላጭነትም እየጨመረ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
በተቋማት ለሙስናና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነት መበራከትም ለመልካም አስተዳደር እንቅፋት መሆኑንም ያመለከቱት አቶ ተስፋዬ፣ የጸረ ሙስና ትግሉ በቴክኖሎጂ አለመደገፉ እና በተቋማት ውስጥ በሚፈጸሙ ኢ-ስነ ምግባራዊ ድርጊቶች ምክንያት በሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ሮሮዎችና ቅሬታዎች መበራከታቸውን ጠቁመዋል። ለተማሪዎች የስነ ምግባር ብልሽት መንስኤ የሚሆኑ በአቋራጭ የመበልጸግ ፍላጎት መጨመርንም እንደተግዳሮት አንስተዋል።
እቅዱ ሙስናና ብልሹ አሰራርን የመከላከል አቅምን የሚያሳድግ መሆኑን አመልክተው፤ የአገሪቱን የሙስናና ብልሹ አሰራሮችን የመከላከል ደረጃ እንደሚያሳድግ፣ በሙስና መከላከል ላይ የኮሚሽኑና የአገሪቱ ገጽታ ለመገንባት አስተዋጽኦ የጎላ እንደሚሆንም ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል።
ኮሚሽኑ ጠንካራና ኃላፊነቱን በብቃት መፈጸም የሚችል ተቋም መገንባት፣ የተቋማትን የስነ ምግባር መከታተያ ክፍሎችን የመፈጸም አቅም ማሳደግ፣ በሀገሪቱ ሙስናና በብልሹ አሰራሮችን የመከላከል አቅም ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ፣ ተማሪዎች በመልካም ሽነ ምግባር ታንጸው ሙስና እንዲጠየፉ ማድረግ እንዲሁም በኢትዮጵያ የተቋማት የሙስና ተጋላጭነት እንዲቀንስ በማድረግ በአፍሪካ ሙስናን በመከላከል ግንባር ቀደም ሆኖ መገኘት ከእቅዱ የሚጠበቁ ውጤቶች መሆናቸውንም አስታውቀዋል።
አገራዊ የስነ ምግባር ግንባታና ሙስና መከላከል ስትራቴጂያዊ እቅዱ ከ2013 ዓ.ም እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ ለ10 ዓመታት የሚተገበር ነው።
አዲስ ዘመን መስከረም 13/201
በ130 ሺህ የስልክ መስመሮች ላይ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል መፈጸሙ ተገለጸ
********************
(ኢ ፕ ድ)
በ2012 በጀመት ዓመት በ130 ሺህ የስልክ መስመሮች ላይ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል መፈጨሙን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ።
የኢትዮ- ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ፍሬሕይወት ለዝግጅት ክፍላችን በላኩት መግለጫ ላይ እንደገለጹት፤ ኩባንያው በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥርና ክትትል ሥርዓትን በመዘርጋት ቀደም ሲል የነበሩትን የቴሌኮም መሰረተ ልማት ስርቆቶችንና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎችን መቀነስ ችሏል፡፡
እንደ ዋና ስራ አሰፈጻሚዋ ገለጻ፤ አሁንም ቢሆን ህገ ወጦች በደንበኞች በኩል የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ተጠቅመው የሚፈጸሙት የወንጀል ደርጊቶችና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎች ከጊዜው ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል፡፡ በተጠናቀቀው የበጀት አመትም በ130 ሺህ የኩባንያው ደንበኞች የመስመር ስልክ ላይ የማጭበርበር ወንጀል ተፈጽሞባቸዋል።
ደንበኞቹ በተለያዩ አጋጣሚ የሞባይል ስልካቸው በሚጠፍበት ወቅት ወዲያወኑ ባለማዘጋታቸው፣ በማወቅም ይሁን ባለማወቅም የስልክ መስመራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፈው በመስጠት የተነሳ ወንጀለኞች የስልክ መስመሩን ለተለያዩ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎች እየተጠቀሙበት መሆኑን ወ/ሪት ፍሬህይወት አስታውቀዋል።
በተጠቀሰው የማጭበርበር ወንጀል የተነሳ ደንበኞች ለአንግልትና ለወንጀል ድርጊት ተጠያቂነት እየተዳረጉ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ ኩባንያውም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ኪሳራ እንደደረሰበት አስታውቀዋል።
የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል መከላከል እንዲቻል ደንበኞች በተለያየ አጋጣሚ የሞባይል ስልካቸው በሚጠፋበት ወቅት በአቅሪያባቸው በሚገኙ የሽያጭ ማዕከላት በመቅረብ ማሳወቅ ይጠበቅባቸው ያሉት ዋና ስራ አሰፈጻሚዋ፤ የስልክ መስመራቸውን በማዘጋትም ምትክ ሲም ካርድ መውስድ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ደንበኞች የስልክ መስመራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ ባለመስጠትና ለወንጀለኞች ተባባሪ ባለመሆን በስልክ መስመራቸው አማካኝነት ከሚፈጸም ወንጀል እንዲጠነቀቁም አሳስበዋል፡፡
በወንድማገኝ አሸብር
********************
(ኢ ፕ ድ)
በ2012 በጀመት ዓመት በ130 ሺህ የስልክ መስመሮች ላይ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል መፈጨሙን ኢትዮ ቴሌኮም አስታወቀ።
የኢትዮ- ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ፍሬሕይወት ለዝግጅት ክፍላችን በላኩት መግለጫ ላይ እንደገለጹት፤ ኩባንያው በቴክኖሎጂ የታገዘ የቁጥጥርና ክትትል ሥርዓትን በመዘርጋት ቀደም ሲል የነበሩትን የቴሌኮም መሰረተ ልማት ስርቆቶችንና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎችን መቀነስ ችሏል፡፡
እንደ ዋና ስራ አሰፈጻሚዋ ገለጻ፤ አሁንም ቢሆን ህገ ወጦች በደንበኞች በኩል የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ተጠቅመው የሚፈጸሙት የወንጀል ደርጊቶችና የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎች ከጊዜው ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል፡፡ በተጠናቀቀው የበጀት አመትም በ130 ሺህ የኩባንያው ደንበኞች የመስመር ስልክ ላይ የማጭበርበር ወንጀል ተፈጽሞባቸዋል።
ደንበኞቹ በተለያዩ አጋጣሚ የሞባይል ስልካቸው በሚጠፍበት ወቅት ወዲያወኑ ባለማዘጋታቸው፣ በማወቅም ይሁን ባለማወቅም የስልክ መስመራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፈው በመስጠት የተነሳ ወንጀለኞች የስልክ መስመሩን ለተለያዩ የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀሎች እየተጠቀሙበት መሆኑን ወ/ሪት ፍሬህይወት አስታውቀዋል።
በተጠቀሰው የማጭበርበር ወንጀል የተነሳ ደንበኞች ለአንግልትና ለወንጀል ድርጊት ተጠያቂነት እየተዳረጉ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ፤ ኩባንያውም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ኪሳራ እንደደረሰበት አስታውቀዋል።
የቴሌኮም ማጭበርበር ወንጀል መከላከል እንዲቻል ደንበኞች በተለያየ አጋጣሚ የሞባይል ስልካቸው በሚጠፋበት ወቅት በአቅሪያባቸው በሚገኙ የሽያጭ ማዕከላት በመቅረብ ማሳወቅ ይጠበቅባቸው ያሉት ዋና ስራ አሰፈጻሚዋ፤ የስልክ መስመራቸውን በማዘጋትም ምትክ ሲም ካርድ መውስድ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ደንበኞች የስልክ መስመራቸውን ለሶስተኛ ወገን አሳልፎ ባለመስጠትና ለወንጀለኞች ተባባሪ ባለመሆን በስልክ መስመራቸው አማካኝነት ከሚፈጸም ወንጀል እንዲጠነቀቁም አሳስበዋል፡፡
በወንድማገኝ አሸብር
የትምህርት ቤቶች ትምህርት ማስጀመር ሂደት በሶስት ዙር እንደሚከናወን ተገለጸ
************************
(ኢ.ፕ.ድ)
የትምህርት ቤቶች ትምህርት ማስጀመር ሂደት በሶስት ዙር እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡
በመጀመሪያው ዙር ማለትም ጥቅምት 9 ቀን 2013 ዓ.ም በገጠር ወረዳና ቀበሌ ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ የውሳኔ ምክረ ሃሳብ ቀርቧል።
በ2ኛ ዙር ጥቅምት 16 ቀን 2013 ደግሞ በሁሉም የዞንና የክልል ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ ነው ምክረ ሃሳብ የቀረበው።
በአዲስ አበባና በፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የሚገኙ ትምህርት ቤቶችም ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ትምህርት እንዲጀምሩ የውሳኔ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።
ትምህርት ቤቶችን ዳግም መክፈት በሚቻልበት የውሳኔ ሃሳብ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በተገኙበት ውይይት እየተካሄደ ነው።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እየተካሄደ ባለው ውይይት የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ሚኒስትሮችም ተገኝተዋል።
በቀረበው ምክረ ሃሳብ ላይ የሚደረገው ውይይት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
************************
(ኢ.ፕ.ድ)
የትምህርት ቤቶች ትምህርት ማስጀመር ሂደት በሶስት ዙር እንደሚከናወን ተገልጿል፡፡
በመጀመሪያው ዙር ማለትም ጥቅምት 9 ቀን 2013 ዓ.ም በገጠር ወረዳና ቀበሌ ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ የውሳኔ ምክረ ሃሳብ ቀርቧል።
በ2ኛ ዙር ጥቅምት 16 ቀን 2013 ደግሞ በሁሉም የዞንና የክልል ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ ነው ምክረ ሃሳብ የቀረበው።
በአዲስ አበባና በፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የሚገኙ ትምህርት ቤቶችም ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ትምህርት እንዲጀምሩ የውሳኔ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።
ትምህርት ቤቶችን ዳግም መክፈት በሚቻልበት የውሳኔ ሃሳብ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን በተገኙበት ውይይት እየተካሄደ ነው።
በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እየተካሄደ ባለው ውይይት የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ሌሎች ሚኒስትሮችም ተገኝተዋል።
በቀረበው ምክረ ሃሳብ ላይ የሚደረገው ውይይት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
የ8ኛ እና 12ኛ ክፍሎች ብሔራዊ ፈተና መውሰጃ ቀናት ይፋ ሆነ
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ትምህርት ቤቶችን ዳግም ለመክፈት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እየተደረገ ባለው ውይይት ላይ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ገለፃ አድርገዋል።
በዚህም መሰረት የ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሕዳር 22 እና 23 ቀን 2013 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ፈተና ላይ መቀመጥ የሚችሉት 7ኛ ክፍልን ተምረው ያጠናቀቁና የ8ኛ ክፍልን የአንደኛ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው ተብሏል።
በተመሳሳይ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መውሰድ የሚችሉት የ11ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀቁና የ12ኛ ክፍልን የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው ተብሏል።
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሕዳር 28 እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚሰጥም በምክረ ሀሳቡ ላይ ተጠቅሷል።
የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን በተመለከተ ለመንግስት ትምህርት ቤቶች የሚወጣው መመዘኛ በግል ትምህርት ቤቶችም ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል።
የግል ትምህርት ቤቶች የምዝገባ ክፍያ በ2012 ዓ.ም በነበረው መጠንና የክፍያ ስርዓት መሆን እንዳለበትም ተገልጿል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ የትምህርት ቤቶች የክፍያ ስርዓት በባንክ በኩል ብቻ መፈጸም እንዳለበትም ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ትምህርት ቤቶችን ዳግም ለመክፈት በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እየተደረገ ባለው ውይይት ላይ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ገለፃ አድርገዋል።
በዚህም መሰረት የ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሕዳር 22 እና 23 ቀን 2013 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ፈተና ላይ መቀመጥ የሚችሉት 7ኛ ክፍልን ተምረው ያጠናቀቁና የ8ኛ ክፍልን የአንደኛ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው ተብሏል።
በተመሳሳይ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መውሰድ የሚችሉት የ11ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀቁና የ12ኛ ክፍልን የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው ተብሏል።
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሕዳር 28 እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚሰጥም በምክረ ሀሳቡ ላይ ተጠቅሷል።
የትምህርት አሰጣጥ ሂደቱን በተመለከተ ለመንግስት ትምህርት ቤቶች የሚወጣው መመዘኛ በግል ትምህርት ቤቶችም ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል።
የግል ትምህርት ቤቶች የምዝገባ ክፍያ በ2012 ዓ.ም በነበረው መጠንና የክፍያ ስርዓት መሆን እንዳለበትም ተገልጿል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ የትምህርት ቤቶች የክፍያ ስርዓት በባንክ በኩል ብቻ መፈጸም እንዳለበትም ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።
እነ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 18 ተከሳሾች ወደ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ታዘዘ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ፍርድ ቤቱ እነ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 18 ተከሳሾች ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ አዘዘ።
በጥበቃ በኩል ስጋት ካለ እንደሚከታተልም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የሕገ መንግስት እና የፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት አስታውቋል።
ፍርድ ቤቱ በችሎት ያልቀረቡ ተከሳሾች እንዲቀርቡ ትዛዝ ሰቷል።
በችሎት ያልቀረቡት ተከሳሾች ባሉበት ክስ ለማንበብ መስከረም 21 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ፍርድ ቤቱ እነ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ 18 ተከሳሾች ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ አዘዘ።
በጥበቃ በኩል ስጋት ካለ እንደሚከታተልም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የሕገ መንግስት እና የፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት አስታውቋል።
ፍርድ ቤቱ በችሎት ያልቀረቡ ተከሳሾች እንዲቀርቡ ትዛዝ ሰቷል።
በችሎት ያልቀረቡት ተከሳሾች ባሉበት ክስ ለማንበብ መስከረም 21 2013 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ኤፍቢሲ ዘግቧል።
በቀጣይ 10 ዓመታት የመገናኛ ብዙሃን ቋንቋ 82 ለማድረስ ታቅዷል
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
በቀጣይ 10 ዓመታት የመገናኛ ብዙሃን ቋንቋ ተደራሽነትን 82 ለማድረስ መታቀዱን የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የ10 ዓመት መሪ እቅድ እንዲሁም በሰላም ግንባታ የሚዲያ ሚና ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የተቋሙን የ10 ዓመት መሪ እቅድ ያቀረቡት የተቋሙ አማካሪ አቶ ግዛው ተስፋዬ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት 60 የሀገሪቱ ቋንቋዎች የመገናኛ ብዙሃን ቋንቋ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይ 10 ዓመታት ሁሉም የሀገሪቱ ቋንቋዎች የመገናኛ ብዙሃን ቋንቋ እንዲሆን ይሰራል።
በውይይት መድረኩ በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ የሚስተዋሉ ጥንካሬዎች፣ ዕጥረቶች፣ መልካም አጋጣሚዎችና፣ ስጋቶችና አስቻይ ሁኔታዎች ተዳሰዋል።
በውይይት መድረኩ የመገናኛ ብዙሃን ሃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ቦርድ አመራሮች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት እንዲሁም የፌዴራል የዲሞክራሲ ተቋማት የበላይ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
በመላኩ ኤሮሴ
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
በቀጣይ 10 ዓመታት የመገናኛ ብዙሃን ቋንቋ ተደራሽነትን 82 ለማድረስ መታቀዱን የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የ10 ዓመት መሪ እቅድ እንዲሁም በሰላም ግንባታ የሚዲያ ሚና ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እያካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የተቋሙን የ10 ዓመት መሪ እቅድ ያቀረቡት የተቋሙ አማካሪ አቶ ግዛው ተስፋዬ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት 60 የሀገሪቱ ቋንቋዎች የመገናኛ ብዙሃን ቋንቋ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በቀጣይ 10 ዓመታት ሁሉም የሀገሪቱ ቋንቋዎች የመገናኛ ብዙሃን ቋንቋ እንዲሆን ይሰራል።
በውይይት መድረኩ በመገናኛ ብዙሃን ዘርፍ የሚስተዋሉ ጥንካሬዎች፣ ዕጥረቶች፣ መልካም አጋጣሚዎችና፣ ስጋቶችና አስቻይ ሁኔታዎች ተዳሰዋል።
በውይይት መድረኩ የመገናኛ ብዙሃን ሃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ቦርድ አመራሮች፣ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባላት እንዲሁም የፌዴራል የዲሞክራሲ ተቋማት የበላይ አመራሮች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
በመላኩ ኤሮሴ
ለመስቀል ደመራ በዓል ዝግ የሚደረጉ መንገዶችን ፖሊስ ይፋ አደረገ፡፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መሰከረም 16 ቀን 2013 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የሚከበረው የደመራ በዓል ተጀምሮ አስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግየሚደረጉ መንገዶችን ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሰረት፦
.ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ
.ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ
.ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት
.ከቸርችል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አገር አስተዳደር መብራት ወይም ኢሚግሬሽን መ/ቤት አካባቢ
.ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ
.ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ
.ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ
.ከሳሪስ በጎተራ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ
.ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ
.ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ፣ ሜክሲኮ ፣ ለገሀር መብራት የሚወስደውመንገድ ለገሃር መብራት አካባቢ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ ሲሆን፣ ደመራው የሚደመርበት መስቀል አደባባይ እና ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ስታዲዬም እንዲሁም ከሃራምቤ ሆቴል ወደ ሴንጅ ዮሰፍ የሚያቋርጠው መስቀለኛ መንገድ ለበዓሉ በሚደረገው ዝግጅት ምክንያት ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡
በመሆኑም ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን አስተላልፏል፡
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን መሰከረም 16 ቀን 2013 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ የሚከበረው የደመራ በዓል ተጀምሮ አስከሚጠናቀቅ ድረስ ለተሽከርካሪዎች ዝግየሚደረጉ መንገዶችን ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሰረት፦
.ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒየም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አከባቢ
.ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያ አካባቢ
.ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ባሻወልዴ ችሎት ወይም ፓርላማ መብራት
.ከቸርችል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አገር አስተዳደር መብራት ወይም ኢሚግሬሽን መ/ቤት አካባቢ
.ከተክለ ሀይማኖት በሜትሮሎጂ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሜትሮሎጂ መስሪያ ቤት አካባቢ
.ከተክለ ሀይማኖት ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ጥቁር አንበሳ የኋላ በር አካባቢ
.ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያትር የሚወስደው መንገድ ጎማ ቁጠባ
.ከሳሪስ በጎተራ የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ
.ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ሜክሲኮ አደባባይ
.ከጦር ኃይሎች ፣ ልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ፣ ሜክሲኮ ፣ ለገሀር መብራት የሚወስደውመንገድ ለገሃር መብራት አካባቢ ይለፍ ለሌላቸው ተሽከርካሪዎች ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ዝግጅቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ዝግ ሲሆን፣ ደመራው የሚደመርበት መስቀል አደባባይ እና ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ወደ ስታዲዬም እንዲሁም ከሃራምቤ ሆቴል ወደ ሴንጅ ዮሰፍ የሚያቋርጠው መስቀለኛ መንገድ ለበዓሉ በሚደረገው ዝግጅት ምክንያት ከጠዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡
በመሆኑም ህብረተሰቡ ከፖሊስ የተሰጠውን መረጃ ተገንዝቦ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን አስተላልፏል፡
12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እና ምዝገባ በኦንላይን እንደሚካሄድ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
************************
(ኢ ፕ ድ)
ከኮቪድ ወረርሽን ጋር በተያያዘ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እና ምዝገባ በኦንላይን እንደሚካሄድ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቋል።
ተማሪዎች ለፈተና ከመቀመጣቸው በፊትም የ45 ቀን የማካካሻ እና የቴክኖሎጂ መለማመጃ ጊዜም እንደሚሰጣቸው በትምህርት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሐረጓ ማሞ ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቶች የሚከፈቱት እና ፈተናም የሚሰጠው ትምህርት ቤቶች የኮቪድ ወረርሽኝን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ማሟላት ሲችሉ ብቻ መሆኑን ዳይሬክተሯ ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶች እንዲከፈቱ ያስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ሳይሸራረፉ እንዲተገበሩ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥሪ መቅረቡን አስታውቋል።
************************
(ኢ ፕ ድ)
ከኮቪድ ወረርሽን ጋር በተያያዘ የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እና ምዝገባ በኦንላይን እንደሚካሄድ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቋል።
ተማሪዎች ለፈተና ከመቀመጣቸው በፊትም የ45 ቀን የማካካሻ እና የቴክኖሎጂ መለማመጃ ጊዜም እንደሚሰጣቸው በትምህርት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሐረጓ ማሞ ተናግረዋል።
ትምህርት ቤቶች የሚከፈቱት እና ፈተናም የሚሰጠው ትምህርት ቤቶች የኮቪድ ወረርሽኝን ለመከላከል አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ማሟላት ሲችሉ ብቻ መሆኑን ዳይሬክተሯ ገልጸዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶች እንዲከፈቱ ያስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ሳይሸራረፉ እንዲተገበሩ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥሪ መቅረቡን አስታውቋል።
አርቲስት አልማዝ ኃይሌ (ማሚ) ከዚህ አለም በሞት ተለየች።
********************
(ኢ ፕ ድ)
በበርካታ የትያትርና ፊልም ስራዎች የምትታወቀው አርቲስት አልማዝ ኃይሌ (ማሚ) ከዚህ አለም በሞት ተለየች።
ለሳምንታት በህመም ላይ የነበረችው አርቲስቷ ዛሬ ማለዳ ነው ማረፏ የተሰማው።
የአርቲስቷ ስርዓተ ቀብር ነገ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈፀማል።
እንደ ኢቢሲ ዘገባ አርቲስቷ ከ40 ዓመት በላይ በኪነ ጥበቡ ዓለም በመቆየት በርካታ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎችን አበርክታለች።
********************
(ኢ ፕ ድ)
በበርካታ የትያትርና ፊልም ስራዎች የምትታወቀው አርቲስት አልማዝ ኃይሌ (ማሚ) ከዚህ አለም በሞት ተለየች።
ለሳምንታት በህመም ላይ የነበረችው አርቲስቷ ዛሬ ማለዳ ነው ማረፏ የተሰማው።
የአርቲስቷ ስርዓተ ቀብር ነገ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈፀማል።
እንደ ኢቢሲ ዘገባ አርቲስቷ ከ40 ዓመት በላይ በኪነ ጥበቡ ዓለም በመቆየት በርካታ ዘመን ተሻጋሪ ስራዎችን አበርክታለች።
በለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 7,227 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 486 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 72,173 ደርሷል።
በሌላ በኩል 402 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ስሆን በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ 29,863 ሰዎች ከበሽታው ማገገም ችለዋል።
በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 72,173 ደርሷል።
በሌላ በኩል 402 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ስሆን በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ 29,863 ሰዎች ከበሽታው ማገገም ችለዋል።
“በህገወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ መጓዝ ከመቼውም ጊዜ በላይ አደገኛ ነው“ ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚ በመጎዳቱ ምክንያት በህገወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ መጓዝ ከመቼውም ጊዜ በላይ አደገኛ መሆኑን በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳሰበ።
በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ደቡብ አፍሪካ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ክፉኛ ኢኮኖሚዋ ተጎድቷል።
በርካታ ሰዎች በቫይረሱ በመያዛቸውም የስራ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች ተዳክመዋል። ሀገሪቷ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለች ደግሞ ኢትዮጵያውያን በህገወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ ቢያስቡ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የከፋ ችግር ያጋጥማቸዋልና ባይሞክሩት ይበጃል።
እንደ አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው ከሆነ፤ በደቡብ አፍሪካ ያለው የኢኮኖሚ እየተቀዛቀዘ ሲሄድ የውጭ ሀገራት ዜጎች የነዋሪውን ስራ እየተሻሙ ነው የሚል ቅሬታ በየጊዜው መቅረብ ጀምሯል።
በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች ላይ ጥቃት ሲደርስ ቆይቷል። መጤ ጠል አስተሳሰብ እየተስፋፋ በመሆኑ በህገወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት የሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን አደጋ ላይ ከመጣል ሊጠነቁቁ ይገባል።
በ2012 ዓም ሁለት ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ደቡብ አፍሪካን ለቀው ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱ ሲሆን፤ ቀድሞ ጥቂት ኢትዮጵያውያን ብቻ እያሉ የነበረው የስራ አማራጭ አሁን ላይ እምብዛም በመሆኑ በህገወጥ መንገድ ወደሀገሪቷ መግባት ከሌሎች ጊዜያት በበለጠ የከፋ አደጋን ያስከትላል።
የመንግሥት ለመንግሥት የሚደረጉ ስምምነቶች እስኪከናወኑ ወደ ደቡብ አፍሪካ በሀገወጥ መንገድ መሄድ አደጋው የበዛ እንደሚሆን የገለጹት ዶክተር ሸፈራው፤ በህገወጥ መንገድ በእግር እና በተሽከርካሪ ሀገራትን እያቋረጡ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ማሰብ ግን ህይወትን መጥላት እና ቤተሰብንም ለሰቀቀን የሚዳርግ በመሆኑ በተለይ ወጣቶች ሊጠነቀቁ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በታንዛኒያ እና ሞዛምቢክ በኩል አቋርጠው ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሉ በቅረቡ ህይወታቸውን ያጡ በርካታ ዜጎች መኖራቸውን ዶክተር ሽፈራው አስታውሰው፤ በህገወጥ መንገድ የሚጓዙ ዜጎችም አብዛኛዎቹ ተይዘው በእስር ቤት እንደሚያሳልፉ እና ወደኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ገልጸዋል። በቅርቡ እንኳን ከታንዛኒያ እስር ቤት የነበሩ ከሁለት ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ከብዙ መከራ በኋላ ወደሀገራቸው መመለሳቸውን አስረድተዋል።
በየመንገዱ ያሉ ህገወጥ ደላሎች የሚያደርሱትን መከራ አልፈው በህይወት እና በሞት መካከል ሆነው ደቡብ አፍሪካ የሚደርሱ ጥቂት ኢትዮጵያውያንም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ስራ ለማግኘት ከባድ ፈተና እየገጠማቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በደቡብ አፍሪካ እና በኢትዮጵያ በኩል በጣምራ ሀገወጥ የሰዎችን ዝውውር ሊቀንስ የሚችል የአሰሪና ሰራተኛ ስምምነት ለማድረግ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው፤ ስምምነቱ ሲከናወን ኢትዮጵያውያን በህጋዊ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው የሚሰሩበት መንገድ በቀጣይ እንደሚመቻች አስረድተዋል። ማንኛውም ሰርቶ መለወጥ የሚችል ሰው ህገወጥ ስደት ከመምረጡ በፊት ሀገሩ ላይ በሚመረጠው ዘርፍ ለመስራት ማሰብ እንደሚገባው መልዕክት አስተላልፈዋል።
በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ በአካባቢው የሚገኙ ስድስት ሀገራት ማለትም ናሚቢያ ፣ ቦትስዋና፣ ሞዛምቢክ፣ ማዳጋስካር፣ ስዋቲኒ እና ሌሴቶ ላይ ስራውን እያከናወነ ይገኛል። በደቡብ አፍሪካ ብቻ ሁለት መቶ ሺህ ኢትዮጵያወያን እንደሚኖሩ ይገመታል።
አዲስ ዘመን መስከረም 16/2013
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የደቡብ አፍሪካ ኢኮኖሚ በመጎዳቱ ምክንያት በህገወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ መጓዝ ከመቼውም ጊዜ በላይ አደገኛ መሆኑን በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳሰበ።
በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ደቡብ አፍሪካ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ክፉኛ ኢኮኖሚዋ ተጎድቷል።
በርካታ ሰዎች በቫይረሱ በመያዛቸውም የስራ እና የንግድ እንቅስቃሴዎች ተዳክመዋል። ሀገሪቷ በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለች ደግሞ ኢትዮጵያውያን በህገወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመሄድ ቢያስቡ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የከፋ ችግር ያጋጥማቸዋልና ባይሞክሩት ይበጃል።
እንደ አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው ከሆነ፤ በደቡብ አፍሪካ ያለው የኢኮኖሚ እየተቀዛቀዘ ሲሄድ የውጭ ሀገራት ዜጎች የነዋሪውን ስራ እየተሻሙ ነው የሚል ቅሬታ በየጊዜው መቅረብ ጀምሯል።
በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ የውጭ ዜጎች ላይ ጥቃት ሲደርስ ቆይቷል። መጤ ጠል አስተሳሰብ እየተስፋፋ በመሆኑ በህገወጥ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለማቅናት የሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን አደጋ ላይ ከመጣል ሊጠነቁቁ ይገባል።
በ2012 ዓም ሁለት ሺህ የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ደቡብ አፍሪካን ለቀው ወደ ኢትዮጵያ የተመለሱ ሲሆን፤ ቀድሞ ጥቂት ኢትዮጵያውያን ብቻ እያሉ የነበረው የስራ አማራጭ አሁን ላይ እምብዛም በመሆኑ በህገወጥ መንገድ ወደሀገሪቷ መግባት ከሌሎች ጊዜያት በበለጠ የከፋ አደጋን ያስከትላል።
የመንግሥት ለመንግሥት የሚደረጉ ስምምነቶች እስኪከናወኑ ወደ ደቡብ አፍሪካ በሀገወጥ መንገድ መሄድ አደጋው የበዛ እንደሚሆን የገለጹት ዶክተር ሸፈራው፤ በህገወጥ መንገድ በእግር እና በተሽከርካሪ ሀገራትን እያቋረጡ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ማሰብ ግን ህይወትን መጥላት እና ቤተሰብንም ለሰቀቀን የሚዳርግ በመሆኑ በተለይ ወጣቶች ሊጠነቀቁ እንደሚገባ ተናግረዋል።
በታንዛኒያ እና ሞዛምቢክ በኩል አቋርጠው ደቡብ አፍሪካ ለመግባት ሲሉ በቅረቡ ህይወታቸውን ያጡ በርካታ ዜጎች መኖራቸውን ዶክተር ሽፈራው አስታውሰው፤ በህገወጥ መንገድ የሚጓዙ ዜጎችም አብዛኛዎቹ ተይዘው በእስር ቤት እንደሚያሳልፉ እና ወደኢትዮጵያ እንደሚመለሱ ገልጸዋል። በቅርቡ እንኳን ከታንዛኒያ እስር ቤት የነበሩ ከሁለት ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ከብዙ መከራ በኋላ ወደሀገራቸው መመለሳቸውን አስረድተዋል።
በየመንገዱ ያሉ ህገወጥ ደላሎች የሚያደርሱትን መከራ አልፈው በህይወት እና በሞት መካከል ሆነው ደቡብ አፍሪካ የሚደርሱ ጥቂት ኢትዮጵያውያንም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ስራ ለማግኘት ከባድ ፈተና እየገጠማቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በደቡብ አፍሪካ እና በኢትዮጵያ በኩል በጣምራ ሀገወጥ የሰዎችን ዝውውር ሊቀንስ የሚችል የአሰሪና ሰራተኛ ስምምነት ለማድረግ ዝግጅቶች እየተከናወኑ መሆኑን የገለጹት አምባሳደር ዶክተር ሽፈራው፤ ስምምነቱ ሲከናወን ኢትዮጵያውያን በህጋዊ መንገድ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዘው የሚሰሩበት መንገድ በቀጣይ እንደሚመቻች አስረድተዋል። ማንኛውም ሰርቶ መለወጥ የሚችል ሰው ህገወጥ ስደት ከመምረጡ በፊት ሀገሩ ላይ በሚመረጠው ዘርፍ ለመስራት ማሰብ እንደሚገባው መልዕክት አስተላልፈዋል።
በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲ በአካባቢው የሚገኙ ስድስት ሀገራት ማለትም ናሚቢያ ፣ ቦትስዋና፣ ሞዛምቢክ፣ ማዳጋስካር፣ ስዋቲኒ እና ሌሴቶ ላይ ስራውን እያከናወነ ይገኛል። በደቡብ አፍሪካ ብቻ ሁለት መቶ ሺህ ኢትዮጵያወያን እንደሚኖሩ ይገመታል።
አዲስ ዘመን መስከረም 16/2013
ከመስከረም 25 በኋላ “ህጋዊ መንግስት የለም” በሚል ትርምስ ለመፍጠር የሚጥሩ ሃይሎችን እንደማይታገስ ፖሊስ አስጠነቀቀ
*************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ ፦ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከመስከረም 25 በኋላ “ህጋዊ መንግስት የለም” በሚል አገራዊ ትርምስ ለመፍጠር በሚሰሩ አካላት ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ። ኮሚሽኑ የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወኑ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉንም ገለጸ።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል እንደሻው ጣሰው የመስቀል እና የኢሬቻ በዓል ቅድመ ዝግጅትን እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ከመስከረም 25 በኋላ “መንግስት የለም” በሚል አገራዊ ትርምስ ለመፍጠር በሚሰሩ አካላት ላይ ፖሊስ ጠንካራ እርምጃ ይወስዳል።
‹‹ከመስከረም 25 በኋላ ኢትዮጵያ ትፈርሳለች›› የሚሉ ጥሪዎች በማህበራዊ ገጾች እየተላለፉ መሆኑን አመልክተው ፣ የህብረተሰቡን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል በአመጽ ጥሪው በሚሳተፉ አካላት ላይ ፖሊስና የፀጥታ አካሉ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አሳስበዋል፡፡
ህዝቡን ለአመፅ እንዲነሳሳ የሚያደርጉ መልዕክቶችን በስፋት የሚያሰራጩ አካላት እንዳሉ የገለጹት ኮሚሽነር ጀነራሉ ፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል፡፡
ማንኛውም ጥያቄ ያለው አካል ህገ መንግስቱን ተከትሎ በሰላማዊ መንገድ ጥያቄውን ማቅረብእንደሚኖርበት የጠቆሙት ኮሚሽነር ጀነራሉ ፣ ከሰላማዊ እንቅስቃሴ ውጪ ያሉ ተግባራትን ለማምከን ፖሊስ በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡
አያይዘውም ፖሊስ የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላት በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ያስታወቁት ኮሚሽነር ጀነራል እንደሻው ፣ የበዓሉን እንቅስቃሴ ለማደፍረስ ዕቅድ ያላቸው ሃይሎች እንዳሉ ፖሊስ በምርመራ የደረሰበት መሆኑን ጠቁመዋል። የበዓሉ አከባበር ወግና ሥርዓት ከሚፈቅደው ውጭ በዓሉን ለመረበሽ የሚፈልጉ ኃይሎች መለየታቸውንም አስታውቀዋል፡፡
በዓላቱ ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ እንዴት መከበር እንዳለበት አስቀድሞ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያት ከስምምነት መደረሱን ገልፀው፣ በበዓሉ ለመታደም የሚመጡ ምዕምናንና እንግዶች የይለፍ ባጅ ማድርጋቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው አመልክተዋል።
ይህን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ ፖሊስ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳሰቡት ኮሚሽነር ጀነራሉ፣ ተመሳሳይ የይለፍ ባጅ አሰርተው ለመግባት የሚሞክሩ አካላት መለየት የሚያስችል አሰራር መኖሩን አስታውቀዋል። ተመሳሳይ ባጅ ይዞ የሚገኝ አካል በአገሪቱ የወንጀል መቅጫ ህጎች መሰረት ለህግ እንደሚቀርብ ጠቁመዋል፡፡
በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ወደ አዲስ አበባ መግቢያ በሮች በሱሉልታ፣ ለገጣፎ፣ ቡራዩ፣ ገላንና ሰበታ ፍተሻ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚከበረው የመስቀል በዓል የፀጥታ ዝግጅት መደረጉን ያስታወቁት ኮሚሽነር ጀነራሉ፣ ከአዲስ አበባ ውጭ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለሚከበረው የመስቀል በዓል የፀጥታ ሃይሉ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
በዓላቱን ተገን አድርገው ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠርም ሆነ ሀገር ለማፍረስ የሚንቀሳቀስ ማንኛውም አካል ፖሊስ እንደማይታገስም አሳስበዋል።
የመስቀልም ሆነ የኢሬቻ በዓል ተሳታፊዎች ቁጥራቸው ውስን እንዲሆን የተደረገው ከፀጥታ ሥጋት ጋር ሳይሆን ከኮቪድ-19 መከላከል ጋር ተያይዞ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
አዲስ ዘመን መስከረም 16/2013
*************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ ፦ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ከመስከረም 25 በኋላ “ህጋዊ መንግስት የለም” በሚል አገራዊ ትርምስ ለመፍጠር በሚሰሩ አካላት ላይ ጠንካራ እርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ። ኮሚሽኑ የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላት ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወኑ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉንም ገለጸ።
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል እንደሻው ጣሰው የመስቀል እና የኢሬቻ በዓል ቅድመ ዝግጅትን እና ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ትናንት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ከመስከረም 25 በኋላ “መንግስት የለም” በሚል አገራዊ ትርምስ ለመፍጠር በሚሰሩ አካላት ላይ ፖሊስ ጠንካራ እርምጃ ይወስዳል።
‹‹ከመስከረም 25 በኋላ ኢትዮጵያ ትፈርሳለች›› የሚሉ ጥሪዎች በማህበራዊ ገጾች እየተላለፉ መሆኑን አመልክተው ፣ የህብረተሰቡን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል በአመጽ ጥሪው በሚሳተፉ አካላት ላይ ፖሊስና የፀጥታ አካሉ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ አሳስበዋል፡፡
ህዝቡን ለአመፅ እንዲነሳሳ የሚያደርጉ መልዕክቶችን በስፋት የሚያሰራጩ አካላት እንዳሉ የገለጹት ኮሚሽነር ጀነራሉ ፣ እነዚህ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል፡፡
ማንኛውም ጥያቄ ያለው አካል ህገ መንግስቱን ተከትሎ በሰላማዊ መንገድ ጥያቄውን ማቅረብእንደሚኖርበት የጠቆሙት ኮሚሽነር ጀነራሉ ፣ ከሰላማዊ እንቅስቃሴ ውጪ ያሉ ተግባራትን ለማምከን ፖሊስ በቂ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡
አያይዘውም ፖሊስ የመስቀል እና የኢሬቻ በዓላት በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት ማጠናቀቁን ያስታወቁት ኮሚሽነር ጀነራል እንደሻው ፣ የበዓሉን እንቅስቃሴ ለማደፍረስ ዕቅድ ያላቸው ሃይሎች እንዳሉ ፖሊስ በምርመራ የደረሰበት መሆኑን ጠቁመዋል። የበዓሉ አከባበር ወግና ሥርዓት ከሚፈቅደው ውጭ በዓሉን ለመረበሽ የሚፈልጉ ኃይሎች መለየታቸውንም አስታውቀዋል፡፡
በዓላቱ ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ እንዴት መከበር እንዳለበት አስቀድሞ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመወያት ከስምምነት መደረሱን ገልፀው፣ በበዓሉ ለመታደም የሚመጡ ምዕምናንና እንግዶች የይለፍ ባጅ ማድርጋቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው አመልክተዋል።
ይህን ተላልፎ በሚገኝ ማንኛውም አካል ላይ ፖሊስ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳሰቡት ኮሚሽነር ጀነራሉ፣ ተመሳሳይ የይለፍ ባጅ አሰርተው ለመግባት የሚሞክሩ አካላት መለየት የሚያስችል አሰራር መኖሩን አስታውቀዋል። ተመሳሳይ ባጅ ይዞ የሚገኝ አካል በአገሪቱ የወንጀል መቅጫ ህጎች መሰረት ለህግ እንደሚቀርብ ጠቁመዋል፡፡
በዓሉ በሰላም ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ወደ አዲስ አበባ መግቢያ በሮች በሱሉልታ፣ ለገጣፎ፣ ቡራዩ፣ ገላንና ሰበታ ፍተሻ እየተደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
ከአዲስ አበባ ውጭ ለሚከበረው የመስቀል በዓል የፀጥታ ዝግጅት መደረጉን ያስታወቁት ኮሚሽነር ጀነራሉ፣ ከአዲስ አበባ ውጭ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለሚከበረው የመስቀል በዓል የፀጥታ ሃይሉ ዝግጅት መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
በዓላቱን ተገን አድርገው ሁከትና ብጥብጥ ለመፍጠርም ሆነ ሀገር ለማፍረስ የሚንቀሳቀስ ማንኛውም አካል ፖሊስ እንደማይታገስም አሳስበዋል።
የመስቀልም ሆነ የኢሬቻ በዓል ተሳታፊዎች ቁጥራቸው ውስን እንዲሆን የተደረገው ከፀጥታ ሥጋት ጋር ሳይሆን ከኮቪድ-19 መከላከል ጋር ተያይዞ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
አዲስ ዘመን መስከረም 16/2013
ከብር ኖት ቅያሬ ጋር በተያያዘ በቀን በአማካይ ከ16 ሺ 700 በላይ አዳዲስ የሒሳብ ደብተሮች እየተከፈቱ ነው
*********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- ከብር ኖት ለውጡ ጋር በተያያዘ በአማካኝ በቀን ከ16 ሺ 700 በላይ ሰዎች አዲስ የሒሳብ ደብተር እንደሚከፍቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። በየእለቱ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ንግድ ባንኩ ገቢ እንደሚሆን ገለጸ።
የባንኩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት ፤ የብር ኖቱ መቀየሩ በባንኮች የሚቆጠበውንም ሆነ የሚቀመጠውን ብር ሆነ የደንበኞችን ቁጥር ያሳድጋል።
ባንኩ ከ5ሺ ብር በላይ ለቅያሬ ይዘው የሚመጡ ሰዎች የቁጠባ ደብተር እንዲከፍቱ እያደረገ መሆኑን አመልክተው ፣ የቁጠባ ሒሳብ ደብተር የሚከፍቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አስታውቀዋል።
በቀን በአማካኝ ከ16ሺህ 700 በላይ ሰዎች የቁጠባ ሒሳብ እንዲከፈቱ ጠቁመው ፣ የቁጠባ ሂሳቡ በየእለቱ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደሚሆን አስታውቀዋል። በቀጣይም የተገልጋዩ ቁጥር እንደሚጨምር ጠቁመዋል። ገንዘብን ቤት ማስቀመጥ በርካታ ችግሮችን ሊያስከትል እንደሚችል አመልክተው ፣ በባንኮች ማስቀመጥ ራስን ከመታደግ አይተናነስም ብለዋል።
ብሔራዊ ባንክ ውክልና የሰጣቸው 36 ገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎች እንዳሉም አስታውቀው፣ በነሱ በኩል ከ1600 በላይ ቅርንጫፎቹን ሊያዳርስ በሚችል መልኩ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ገንዘብ የማዳረሱ ሥራ ከፍተኛ ጥንቃቄን እንደሚጠይቅ ተናግረው፣ ቅርንጫፎቹ ባሉበት ሁሉ በመድረስ ለመስራት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የብር ኖት ለውጡ በየቀኑ የሚከናወን በመሆኑ ምን ያህል ቅያሬ እንደተደረገ ለመግለጽ ልዩነቶች ይኖሩታል ያሉት አቶ የአብስራ፣ በዚህም ከሦስት ቀን በፊት በነበረ መረጃ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ከብሔራዊ ባንክ ተቀብሎ ለለገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎቹ እንዳስረከበ አስታውቀዋል። ቅርንጫፎቹም ትናንትን ጨምሮ የማከፋፈሉን ሥራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ አቶ የአብስራ ገለጻ፤ ህብረተሰቡ አዲሱን የብር ኖት መቀየሩ ብቻ በቂ አይደለም። ለውጡን ፈጽሞ ወደነበረበት አሰራርም መመለስ የለበትም። ደንበኞች የተለያዩ የቁጠባ ሒሳቦች በመኖራቸው ገንዘባቸውን በባንኮች በማስቀመጥ አገራቸውንም ሆነ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ይገባል ብለዋል ።
በተለይም ገንዘብ በቤታቸው የሚያስቀምጡ ሰዎች ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። በተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች ብዙ ንብረቶች እየጠፉና እየወደሙ ናቸው። ከዚያ በተጨማሪም ለዘረፋ የሚዳረጉበት ሁኔታም ሰፊ ነው። ለመጭበርበርም በር ይከፍታል። እነዚህንና መሰል ችግሮች እንዳይደርስባቸው ገንዘባቸውን በባንክ ማስቀመጡን ልምድ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተዋል::
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ1 ሺ 600 በላይ ቅርንጫፎች፤ ከ100 በላይ ንዑስ ቅርንጫፎችና ከ25 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት። ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ኤትኤም ካርድ፤ ከ 4 ነጥብ 25 በላይ ደግሞ የሞባይል ባንክና ከ3ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የሲቢኢ ብር ተጠቃሚዎች እንዳሉት ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013
*********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- ከብር ኖት ለውጡ ጋር በተያያዘ በአማካኝ በቀን ከ16 ሺ 700 በላይ ሰዎች አዲስ የሒሳብ ደብተር እንደሚከፍቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። በየእለቱ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ንግድ ባንኩ ገቢ እንደሚሆን ገለጸ።
የባንኩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት ፤ የብር ኖቱ መቀየሩ በባንኮች የሚቆጠበውንም ሆነ የሚቀመጠውን ብር ሆነ የደንበኞችን ቁጥር ያሳድጋል።
ባንኩ ከ5ሺ ብር በላይ ለቅያሬ ይዘው የሚመጡ ሰዎች የቁጠባ ደብተር እንዲከፍቱ እያደረገ መሆኑን አመልክተው ፣ የቁጠባ ሒሳብ ደብተር የሚከፍቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አስታውቀዋል።
በቀን በአማካኝ ከ16ሺህ 700 በላይ ሰዎች የቁጠባ ሒሳብ እንዲከፈቱ ጠቁመው ፣ የቁጠባ ሂሳቡ በየእለቱ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደሚሆን አስታውቀዋል። በቀጣይም የተገልጋዩ ቁጥር እንደሚጨምር ጠቁመዋል። ገንዘብን ቤት ማስቀመጥ በርካታ ችግሮችን ሊያስከትል እንደሚችል አመልክተው ፣ በባንኮች ማስቀመጥ ራስን ከመታደግ አይተናነስም ብለዋል።
ብሔራዊ ባንክ ውክልና የሰጣቸው 36 ገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎች እንዳሉም አስታውቀው፣ በነሱ በኩል ከ1600 በላይ ቅርንጫፎቹን ሊያዳርስ በሚችል መልኩ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ገንዘብ የማዳረሱ ሥራ ከፍተኛ ጥንቃቄን እንደሚጠይቅ ተናግረው፣ ቅርንጫፎቹ ባሉበት ሁሉ በመድረስ ለመስራት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የብር ኖት ለውጡ በየቀኑ የሚከናወን በመሆኑ ምን ያህል ቅያሬ እንደተደረገ ለመግለጽ ልዩነቶች ይኖሩታል ያሉት አቶ የአብስራ፣ በዚህም ከሦስት ቀን በፊት በነበረ መረጃ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ከብሔራዊ ባንክ ተቀብሎ ለለገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎቹ እንዳስረከበ አስታውቀዋል። ቅርንጫፎቹም ትናንትን ጨምሮ የማከፋፈሉን ሥራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ አቶ የአብስራ ገለጻ፤ ህብረተሰቡ አዲሱን የብር ኖት መቀየሩ ብቻ በቂ አይደለም። ለውጡን ፈጽሞ ወደነበረበት አሰራርም መመለስ የለበትም። ደንበኞች የተለያዩ የቁጠባ ሒሳቦች በመኖራቸው ገንዘባቸውን በባንኮች በማስቀመጥ አገራቸውንም ሆነ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ይገባል ብለዋል ።
በተለይም ገንዘብ በቤታቸው የሚያስቀምጡ ሰዎች ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። በተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች ብዙ ንብረቶች እየጠፉና እየወደሙ ናቸው። ከዚያ በተጨማሪም ለዘረፋ የሚዳረጉበት ሁኔታም ሰፊ ነው። ለመጭበርበርም በር ይከፍታል። እነዚህንና መሰል ችግሮች እንዳይደርስባቸው ገንዘባቸውን በባንክ ማስቀመጡን ልምድ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተዋል::
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ1 ሺ 600 በላይ ቅርንጫፎች፤ ከ100 በላይ ንዑስ ቅርንጫፎችና ከ25 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት። ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ኤትኤም ካርድ፤ ከ 4 ነጥብ 25 በላይ ደግሞ የሞባይል ባንክና ከ3ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የሲቢኢ ብር ተጠቃሚዎች እንዳሉት ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ አስር ዩኒቨርሲቲዎች ተርታ መመደቡ ተገለጸ
*****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ ፡- የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ አስር ዩኒቨርሲቲዎች ተርታ መመደቡን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ገለጹ፡፡ በህትመት ስኬታማነት በአፍሪካ ካሉ ሶስት ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ መሆኑም ተጠቆመ፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባደረጋቸው ችግር ፈቺ የምርምር ተግባራት በዓለም አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ መዳቢ አካላት በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ አስር ዩኒቨርሲቲዎች ተርታ መመደቡን ገልጸዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ለዚህ የበቃው በምርምር ውጤቶችና በዩኒቨርሲቲው የሚታተሙ ህትመቶች ለሌሎች ተመራማሪዎች እና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ባላቸው የችግር ፈቺነት አቅም መሆኑን አመልክተዋል።
የካይሮ ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚያሳትመው ህትመት ብዛት እንደሚበልጥ ያመለከቱት ፕሬዝደንቱ ፤ በህትመቶች ተጠቃሽነት ግን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደሚበልጥ አስታውቀዋል።
ይህ የሆነው በዩኒቨርሲቲው የሚደረጉ ጥናቶች እና ምርምሮች ከካይሮ ዩኒቨርሲቲ በበለጠ ለህብረተሰባችን ፣ ለአፍሪካ ብሎም ለዓለም ሊጠቅሙ የሚችሉ ጥናቶች እንደሆኑ በደረጃ መዳቢ አካላት እውቅና በማግኘቱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ሌሎች የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች እዚህ ውድድር ውስጥ ገብተው እንደነበር የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ ፤ ነገር ግን በሀገራችን ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች የአዲስ አበባ እና የጎንደር የኒቨርሲቲ ብቻ ከ1 ሺ 500 ምርጥ የዓለማችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መካተታቸውን ገልጸዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከአፍሪካ 49ኛ ደረጃ ላይ መሆኑንም አመልክተዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው በ26 ወሳኝ የምርምር ጉዳዮች ላይ ቅድሚያ በመስጠት በሀገሪቱ ፣ በአህጉሪቱ እና በዓለም ችግር ላይ ሁነኛ መፍትሔ ለመፈለግ እየተጋ ያለ ዩኒቨርሲቲ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ፤ በአሁኑ ሰዓት በአፍሪካ ካሉ አስር ምርጥ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ከመሆን ባለፈም በህትመት ስኬታማነት ደግሞ በአፍሪካ ካሉ ሶስት ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ነው ብለዋል።
እንደ ፕሬዚደንቱ ገለጻ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር ፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ላይ በመሳተፍ ለአለፉት ሰባ ዓመታት በርካታ ስራዎችን ሲከናውን ቆይቷል።
ዩኒቨርሲቲው በ1950 ዓ.ም 33 ተማሪዎች እና 7 አስተማሪዎች ትምህርት እና ምርምር በማካሄድ የጀመረው መሆኑን ጠቁመው፤ በአሁኑ ሰዓት ከ3 ሺ በላይ መምህራን ፣ 5 ሺ የሚሆኑ የአስተዳደር ሰራተኞች ፣ 1 ሺ 200 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች ፣ ከ46 ሺ በላይ ተማሪዎች ፣ 12 ኮሌጆች እና 10 የምርምር ተቋማትን ይዞ የሀገሪቱን የልማት አቅጣጫ ተከትሎ እየሰራ ያለ ትልቅ ተቋም መሆኑን አመልክተዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ካሉት ዩኒቨርሲቲዎች ልዩ የሚያደርገው በእድሜ ትንሹ እና ብቸኛው በቅኝ ገዥዎች ያልተቋቋመ ዩኒቨርሲቲ ነው ያሉት ፕሬዚደንቱ ፤ ይሁን እንጂ እድሜ ሳይገድበው እድሜ ጠገብ ከሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ቀድሞ መቆም የቻለ መሆኑን አስታውቀዋል።
ዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ በሁለንተናዊ መልኩ ከአምስት ዓመት ወዲህ እያሳየ ያለው መሻሻል ወደ ፊት በአፍሪካ ብሎም በዓለም ከሚገኙ ዩኒቨርሰቲዎች ተርታ ቀዳሚ ሊያደርገው እንደሚችልም እምነታቸው እንደሆነ ጠቁመዋል።
አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013
*****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ ፡- የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ አስር ዩኒቨርሲቲዎች ተርታ መመደቡን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ገለጹ፡፡ በህትመት ስኬታማነት በአፍሪካ ካሉ ሶስት ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ መሆኑም ተጠቆመ፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባደረጋቸው ችግር ፈቺ የምርምር ተግባራት በዓለም አቀፍ የዩኒቨርሲቲዎች ደረጃ መዳቢ አካላት በአፍሪካ ከሚገኙ ምርጥ አስር ዩኒቨርሲቲዎች ተርታ መመደቡን ገልጸዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ለዚህ የበቃው በምርምር ውጤቶችና በዩኒቨርሲቲው የሚታተሙ ህትመቶች ለሌሎች ተመራማሪዎች እና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ባላቸው የችግር ፈቺነት አቅም መሆኑን አመልክተዋል።
የካይሮ ዩኒቨርሲቲ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚያሳትመው ህትመት ብዛት እንደሚበልጥ ያመለከቱት ፕሬዝደንቱ ፤ በህትመቶች ተጠቃሽነት ግን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደሚበልጥ አስታውቀዋል።
ይህ የሆነው በዩኒቨርሲቲው የሚደረጉ ጥናቶች እና ምርምሮች ከካይሮ ዩኒቨርሲቲ በበለጠ ለህብረተሰባችን ፣ ለአፍሪካ ብሎም ለዓለም ሊጠቅሙ የሚችሉ ጥናቶች እንደሆኑ በደረጃ መዳቢ አካላት እውቅና በማግኘቱ እንደሆነ ጠቁመዋል።
ሌሎች የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች እዚህ ውድድር ውስጥ ገብተው እንደነበር የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ ፤ ነገር ግን በሀገራችን ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች የአዲስ አበባ እና የጎንደር የኒቨርሲቲ ብቻ ከ1 ሺ 500 ምርጥ የዓለማችን ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ መካተታቸውን ገልጸዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከአፍሪካ 49ኛ ደረጃ ላይ መሆኑንም አመልክተዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲው በ26 ወሳኝ የምርምር ጉዳዮች ላይ ቅድሚያ በመስጠት በሀገሪቱ ፣ በአህጉሪቱ እና በዓለም ችግር ላይ ሁነኛ መፍትሔ ለመፈለግ እየተጋ ያለ ዩኒቨርሲቲ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ፤ በአሁኑ ሰዓት በአፍሪካ ካሉ አስር ምርጥ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ከመሆን ባለፈም በህትመት ስኬታማነት ደግሞ በአፍሪካ ካሉ ሶስት ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ ነው ብለዋል።
እንደ ፕሬዚደንቱ ገለጻ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመማር ማስተማር ፣ በምርምር እና በማህበረሰብ አገልግሎት ላይ በመሳተፍ ለአለፉት ሰባ ዓመታት በርካታ ስራዎችን ሲከናውን ቆይቷል።
ዩኒቨርሲቲው በ1950 ዓ.ም 33 ተማሪዎች እና 7 አስተማሪዎች ትምህርት እና ምርምር በማካሄድ የጀመረው መሆኑን ጠቁመው፤ በአሁኑ ሰዓት ከ3 ሺ በላይ መምህራን ፣ 5 ሺ የሚሆኑ የአስተዳደር ሰራተኞች ፣ 1 ሺ 200 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች ፣ ከ46 ሺ በላይ ተማሪዎች ፣ 12 ኮሌጆች እና 10 የምርምር ተቋማትን ይዞ የሀገሪቱን የልማት አቅጣጫ ተከትሎ እየሰራ ያለ ትልቅ ተቋም መሆኑን አመልክተዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ካሉት ዩኒቨርሲቲዎች ልዩ የሚያደርገው በእድሜ ትንሹ እና ብቸኛው በቅኝ ገዥዎች ያልተቋቋመ ዩኒቨርሲቲ ነው ያሉት ፕሬዚደንቱ ፤ ይሁን እንጂ እድሜ ሳይገድበው እድሜ ጠገብ ከሆኑ ዩኒቨርሲቲዎች ቀድሞ መቆም የቻለ መሆኑን አስታውቀዋል።
ዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ በሁለንተናዊ መልኩ ከአምስት ዓመት ወዲህ እያሳየ ያለው መሻሻል ወደ ፊት በአፍሪካ ብሎም በዓለም ከሚገኙ ዩኒቨርሰቲዎች ተርታ ቀዳሚ ሊያደርገው እንደሚችልም እምነታቸው እንደሆነ ጠቁመዋል።
አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013
በጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ዘርፍ በሁለት ወራት ብቻ ከወጪ ንግድ 31 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር መገኘቱ ተገለጸ
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በ2013 በጀት ዓመት በሐምሌና በነሐሴ ወር ብቻ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት ዘርፍ ከወጪ ንግድ 31 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት መቻሉን ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
የኢንስቲትዩቱ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ባንቲሁን ገሰስ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በ2013 በጀት ዓመት ከውጭ ንግድ ለማግኘት ከታቀደው 210 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በሁለቱ ወራት ብቻ 31 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል፡፡ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘ ገቢ ጋር ሲነጻጻር የተሻለ ገቢ መገኘቱን እንደሚያመላክት አስታውቀዋል።
ኮቪድ 19 ቫይረስ በጨርቃጨርቅና አልባሳት ዘርፍ የውጭ ሀገራት የንግድ ግንኙነት ላይ ተጽዕኖ ያሳደረ መሆኑን የተናገሩት አቶ ባንቲሁን፤ እንደዛም ሆኖ ግን ከዘርፉ ከውጭ ገበያ ለማግኘት ከታቀደው ገቢያ አኳያ ሲታይ ከተላኩ ምርቶች የተሻለ ገቢ ተገኝቷል፡፡
ምንም እንኳን ቫይረሱ ከፍተኛ ተጽዕኖ የፈጠረ ቢሆንም ፤ መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረትና በፋብሪካዎች ጥረት ቫይረሱን በመቋቋም የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፤ ካምፓኒዎችም ገበያውን ሳያቋርጡ ምርቶቹን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተሻለ የውጭ ገቢያ እንዲገኝ ማድረግ የቻሉ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የገበያ መዳረሻዎቹ ጀርመን፣ ጣሊያን ፣ አሜሪካ ፣ ቻይና እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሲሆኑ፤ የገበያ መዳረሻዎቹን ለማስፋት ከተለያዩ የውጭ አገራት ገበያ ጋር ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ገቢ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ኃላፊው አስረድተው፤ ለውጭ ንግድ ገበያ የተላኩት ምርቶች ክር፣ ጨርቅ ፤ አልባሳትና ባህላዊ አልባሳት መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡
ከሀገሪቱ ከ200 በላይ የሚሆኑ መካከለኛና ከፍተኛ የጨርቃጨርቅና የአልባሳትና ኢንዱስትሪዎች ያሉ ሲሆን፤ 60 ያህል ፋብሪካዎች በውጭ ንግድ ገበያው ተሳታፊ መሆናቸውን ጠቅሰው ፤ አብዛኛዎቹ የሀገር ውስጥ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ፋብሪካዎች የሀገር ውስጥ ገበያ ላይ በመሰማራታቸው ወደ ዓለም ገበያ ከመግባት አኳያ ክፍተቶች ያሉ መሆኑን አመልክተዋል አክለውም በቅርቡ ወደ ገበያ እየገቡ ያሉ እንደ ደስታ ጋርመንት አይነት አዳዲስ ፋብሪካዎች መኖራቸውን አስረድተዋል፡፡
ፋብሪካዎች የኤክስፖርት ገበያ ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያገኙ የመወዳደር አቅማቸውን በማሳደግ ፣ ዓለም አቀፍ ጥራት የጠበቀ ምርት በማምረት በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚሠሩ ሥራዎች አሉ ያሉት ኃላፊው፤ የቀጣይ 5 ና 10 ዓመታት የስትራቴጂ በማዘጋጀት ፋብሪካዎችን በማሳተፍ ባለድርሻ አካላትም የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ለማድረግ እየተሠራ መሆን አስረድተዋል፡፡
እንደ ኃላፊው ገለጻ፤ በግብዓት አቅርቦት ረገድ ችግር እንዳይገጥም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡ ለጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ዘርፉ የጥጥ ግብዓት አቅርቦት ትልቁን ድርሻ እንዳለው የሚጠቅሱት ኃላፊው፤ በአፋር አካባቢ የአዋሽ ወንዝ ባስከተለው ጎርፉ በ 7 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የነበረ የ26 ባለሀብቶች የጥጥ እርሻ ወድሟል። በውድመቱም 500 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ያጋጠመ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በቅርቡ በአዋሽ ወንዝ ሙላት ምክንያት የጥጥ እርሻቸው ለወደመባቸው ባለሀብቶች መንግሥት ተከታታይነት ያለው ድጋፍ ይሰጣል ያሉት ኃላፊው፤ በቅርቡም የደረሰውን ጉዳት አጥንቶ ለመንግሥት ሪፖርት የሚያቀርብ ቡድን ወደ ስፍራው የሚሰማራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ባለሀብቱን በማቋቋም ረገድ የተለያዩ ድጋፎች በመስጠት ታቅዶ እንቅስቃሴ የተጀመረበት ሁኔታ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ጎርፉ ባደረሰው ኪሳራ የጥጥ ግብዓት ከውጭ በማስገባት በመጠቀም ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እንደሚደረግ የጠቆሙት ኃላፊው፤ በቀጣይ የግብዓት አቅርቦት እጥረት ሊያስከትል የሚችል መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ለዚህም የጨርቃ ጨርቅ ዘርፉ ግብዓት ከሚያቀርቡ አቅራቢ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በ2013 በጀት ዓመት በሐምሌና በነሐሴ ወር ብቻ ከጨርቃጨርቅና አልባሳት ዘርፍ ከወጪ ንግድ 31 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት መቻሉን ጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
የኢንስቲትዩቱ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ባንቲሁን ገሰስ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በ2013 በጀት ዓመት ከውጭ ንግድ ለማግኘት ከታቀደው 210 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በሁለቱ ወራት ብቻ 31 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ማግኘት ተችሏል፡፡ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተገኘ ገቢ ጋር ሲነጻጻር የተሻለ ገቢ መገኘቱን እንደሚያመላክት አስታውቀዋል።
ኮቪድ 19 ቫይረስ በጨርቃጨርቅና አልባሳት ዘርፍ የውጭ ሀገራት የንግድ ግንኙነት ላይ ተጽዕኖ ያሳደረ መሆኑን የተናገሩት አቶ ባንቲሁን፤ እንደዛም ሆኖ ግን ከዘርፉ ከውጭ ገበያ ለማግኘት ከታቀደው ገቢያ አኳያ ሲታይ ከተላኩ ምርቶች የተሻለ ገቢ ተገኝቷል፡፡
ምንም እንኳን ቫይረሱ ከፍተኛ ተጽዕኖ የፈጠረ ቢሆንም ፤ መንግሥት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረትና በፋብሪካዎች ጥረት ቫይረሱን በመቋቋም የተሻለ ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፤ ካምፓኒዎችም ገበያውን ሳያቋርጡ ምርቶቹን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የተሻለ የውጭ ገቢያ እንዲገኝ ማድረግ የቻሉ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የገበያ መዳረሻዎቹ ጀርመን፣ ጣሊያን ፣ አሜሪካ ፣ ቻይና እና የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ሲሆኑ፤ የገበያ መዳረሻዎቹን ለማስፋት ከተለያዩ የውጭ አገራት ገበያ ጋር ግንኙነት በመፍጠር የተሻለ ገቢ ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ኃላፊው አስረድተው፤ ለውጭ ንግድ ገበያ የተላኩት ምርቶች ክር፣ ጨርቅ ፤ አልባሳትና ባህላዊ አልባሳት መሆናቸውን አመልክተዋል፡፡
ከሀገሪቱ ከ200 በላይ የሚሆኑ መካከለኛና ከፍተኛ የጨርቃጨርቅና የአልባሳትና ኢንዱስትሪዎች ያሉ ሲሆን፤ 60 ያህል ፋብሪካዎች በውጭ ንግድ ገበያው ተሳታፊ መሆናቸውን ጠቅሰው ፤ አብዛኛዎቹ የሀገር ውስጥ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ፋብሪካዎች የሀገር ውስጥ ገበያ ላይ በመሰማራታቸው ወደ ዓለም ገበያ ከመግባት አኳያ ክፍተቶች ያሉ መሆኑን አመልክተዋል አክለውም በቅርቡ ወደ ገበያ እየገቡ ያሉ እንደ ደስታ ጋርመንት አይነት አዳዲስ ፋብሪካዎች መኖራቸውን አስረድተዋል፡፡
ፋብሪካዎች የኤክስፖርት ገበያ ላይ የተሻለ ውጤት እንዲያገኙ የመወዳደር አቅማቸውን በማሳደግ ፣ ዓለም አቀፍ ጥራት የጠበቀ ምርት በማምረት በዓለም ገበያ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚሠሩ ሥራዎች አሉ ያሉት ኃላፊው፤ የቀጣይ 5 ና 10 ዓመታት የስትራቴጂ በማዘጋጀት ፋብሪካዎችን በማሳተፍ ባለድርሻ አካላትም የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ለማድረግ እየተሠራ መሆን አስረድተዋል፡፡
እንደ ኃላፊው ገለጻ፤ በግብዓት አቅርቦት ረገድ ችግር እንዳይገጥም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው፡፡ ለጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ዘርፉ የጥጥ ግብዓት አቅርቦት ትልቁን ድርሻ እንዳለው የሚጠቅሱት ኃላፊው፤ በአፋር አካባቢ የአዋሽ ወንዝ ባስከተለው ጎርፉ በ 7 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ የነበረ የ26 ባለሀብቶች የጥጥ እርሻ ወድሟል። በውድመቱም 500 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ያጋጠመ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
በቅርቡ በአዋሽ ወንዝ ሙላት ምክንያት የጥጥ እርሻቸው ለወደመባቸው ባለሀብቶች መንግሥት ተከታታይነት ያለው ድጋፍ ይሰጣል ያሉት ኃላፊው፤ በቅርቡም የደረሰውን ጉዳት አጥንቶ ለመንግሥት ሪፖርት የሚያቀርብ ቡድን ወደ ስፍራው የሚሰማራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ባለሀብቱን በማቋቋም ረገድ የተለያዩ ድጋፎች በመስጠት ታቅዶ እንቅስቃሴ የተጀመረበት ሁኔታ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ጎርፉ ባደረሰው ኪሳራ የጥጥ ግብዓት ከውጭ በማስገባት በመጠቀም ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እንደሚደረግ የጠቆሙት ኃላፊው፤ በቀጣይ የግብዓት አቅርቦት እጥረት ሊያስከትል የሚችል መሆኑን አመልክተዋል፡፡ ለዚህም የጨርቃ ጨርቅ ዘርፉ ግብዓት ከሚያቀርቡ አቅራቢ ድርጅቶች ጋር በቅንጅት የሚሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የበረሃ አንበጣን ለመቆጣጠር እየሰሩ ላሉ የፌደራል ተቋማት ምስጋና አቀረቡ
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በአንዳንድ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ጉዳት እያደረሰ ያለውን የበረሃ አንበጣ ለመቆጣጠር ከክልሎች ጋር በትብብር እየሰሩ ላሉ የፌደራል ተቋማት ምስጋና አቀረቡ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፦
"በሀገር ደረጃ ዓለም አቀፉን የጤና ቀውስ እንዲሁም በርካታ የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመቋቋም እየተረባረብን ነው፤ በዚህ ወቅት፣ ከክልል አቻዎቻቸው ጋር ተባብረው የበረሃ አንበጣን ለመከላከል በከፍተኛ ጥረት ላይ ለሚገኙት የፌደራል ተቋማት ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ" ብለዋል
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በአንዳንድ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ጉዳት እያደረሰ ያለውን የበረሃ አንበጣ ለመቆጣጠር ከክልሎች ጋር በትብብር እየሰሩ ላሉ የፌደራል ተቋማት ምስጋና አቀረቡ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት፦
"በሀገር ደረጃ ዓለም አቀፉን የጤና ቀውስ እንዲሁም በርካታ የተፈጥሮ አደጋዎችን ለመቋቋም እየተረባረብን ነው፤ በዚህ ወቅት፣ ከክልል አቻዎቻቸው ጋር ተባብረው የበረሃ አንበጣን ለመከላከል በከፍተኛ ጥረት ላይ ለሚገኙት የፌደራል ተቋማት ምስጋናዬን ለማቅረብ እወዳለሁ" ብለዋል
አሜሪካ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ አደረገች
******************
(ኢ ፕ ድ)
የአሜሪካ መከላከያ ሰራዊት ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያላቸው የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገች፡፡
ይህ ድጋፍ ሰራዊቱ በቀጠናው የሚስተዋለውን ሽብርተኛነትንና የአልሸ ባብን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር እያደረገው ላለው ጥረት የሚያግዝ መሆኑን በአዲስ አበባ የአሜሪካን ኤንባሲ አስታውቋል፡፡
ድጋፍ የተደረጉት ቁሳቁሶችም አምቡላንስ፣ የጭነትና የነዳጅ ማጓጓዣ ተሸከርካሪዎች፣ ለኦፕሬሽን ማዕክል የሚያገለግሉ ዘመናዊ ኮምፒተሮች፣ የሰራዊቱ መንቀሳቀሻ መኪናና ሌሎች ናቸው ተብሏል፡፡
ይህ ድጋፍ የአሜሪካ ሰራዊት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጋር ሽብርተኝነትን ለመከላከል በጋራ እየሰሩ እንዳሉ የሚያሳይ መሆኑንም ኤንባሲው አስታውቋል።
******************
(ኢ ፕ ድ)
የአሜሪካ መከላከያ ሰራዊት ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት 2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዶላር ግምት ያላቸው የተለያዩ ቁሳቁሶችን ድጋፍ አደረገች፡፡
ይህ ድጋፍ ሰራዊቱ በቀጠናው የሚስተዋለውን ሽብርተኛነትንና የአልሸ ባብን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር እያደረገው ላለው ጥረት የሚያግዝ መሆኑን በአዲስ አበባ የአሜሪካን ኤንባሲ አስታውቋል፡፡
ድጋፍ የተደረጉት ቁሳቁሶችም አምቡላንስ፣ የጭነትና የነዳጅ ማጓጓዣ ተሸከርካሪዎች፣ ለኦፕሬሽን ማዕክል የሚያገለግሉ ዘመናዊ ኮምፒተሮች፣ የሰራዊቱ መንቀሳቀሻ መኪናና ሌሎች ናቸው ተብሏል፡፡
ይህ ድጋፍ የአሜሪካ ሰራዊት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጋር ሽብርተኝነትን ለመከላከል በጋራ እየሰሩ እንዳሉ የሚያሳይ መሆኑንም ኤንባሲው አስታውቋል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚፈጸሙ ጥቃቶች በክልሉ የመንግስት መዋቅር ክፍተት መሆኑ ተገለጸ
************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚፈጸሙ ጥቃቶች በክልሉ የመንግስት መዋቅር ክፍተት እና በአንዳንድ አመራሮች ችግር ምክንያት መሆኑን የአማራ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት በበኩሉ ችግሮችን ለይቶ እርምጃ መውሰዱን ገልጿል።
የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ትናንት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግስት መዋቅር ክፍተት አለ ፤ ይህንን ክፍተት የክልሉ መንግስት በአቋም ደረጃ ወስዶ አልሰራበትም። በዚህም ምክንያት በአማራና በአገው ብሄረሰቦች ላይ ጥቃት ሊደርስ ችሏል።
ለችግሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ዘላቂ መፍትሄ እየተሰጠ አይደለም፤ እሳት የማጥፋት ስራ ነው እየተሰራ ያሉት አቶ ግዛቸው፤ ከዘላቂ መፍትሄ አንጻር ከክልሉ አመራሮች ጋር በመድረክ ስምምነት የተደረሰበት አማራው፣ አገው እና ሁሉም ዜጋ በአፈጻጸሙና በብቃቱ ተመርጦ በየአካባቢው መደራጀትና የአካባቢውን ጸጥታ መጠበቅ እንዳለበት አመልክተዋል።
“የክልሉ መንግስት አመራሮች በመድረክ ደረጃ የሌላውን ብሄር አደረጃጀት በመዋቅር ውስጥ ለማስገባት ፈቃደኛ ናቸው፤ ምክንያቱም ችግሩ የጋራ ነውና፤ ግድያው አማራን እና አገውን አነጣጥሮ ቢፈጸምም አልተባበር ያለውን ጉሙዝን እና ሺናሻንም ያካተተ ነው ጥቃት አድራሹ ጽንፈኛ ቡድን የክልሉን መንግስትም አዳክሞ ወደ ስልጣን የመምጣት ፍላጎት ያለው እንደሆነም አመልክተዋል።
“የቤኒሻንጉል ጉሙዝ መንግስት ይሄንን ያውቃል። ስለዚህ ይሄን አልቀበልም አይልም፤ ችግሩ ያለው ቁርጠኛ ሆኖ መፈጸም ላይ ነው፤ ይሄ ደግሞ የሆነው መሃላቸው ላይ የዚህ ጽንፈኛ አመለካከት ተጋሪዎች ስላሉ ነው። ይሄንን ማረም አለባቸው” ብለዋል።
አማራ እና አገውን ከሚሊሻ፣ ከቀበሌና ከወረዳ አደረጃጀት ውስጥ ያገለለ ነው ያሉት አቶ ግዛቸው፤ በዚህም ምክንያት የጥቃቱ ሰለባ የሚሆኑ ወገኖች ራሳቸውን የመከላከል አቅም እንዳጡ አመልክተዋል።
በአማራና በአገው ብሄር ተወላጆች ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት መድረሱን ያስታወሱት አቶ ግዛቸው በሰሞኑ ጥቃት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የአማራ ክልላዊ መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ከአጭር ጊዜ መፍትሄ አንጻር በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ የማድረግና የማረጋጋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ በዚህም አስፈላጊው የእለት ደራሽ ሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበላቸው መሆኑን አስታውቀዋል።
በጉዳይ ዙሪያ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መለሰ በየነ በበኩላቸው፤ “የተፈጠረው ችግር ሁላችንንም አሳስቦናል፤ በእኛ መዋቅር ድክመት የተፈጠረ ችግር ነው፤ ያንን ችግር እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በአብሮነት በጋራ መፍታት እና በጀመርነው ልክ መሄድ አንድ መፍትሄ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
ቀደም ብሎ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የክልሉን መዋቅር መልሶ የማየትና የማስተካከል ስራ መከናወኑን የገለጹት አቶ መለሰ፤ በሁሉም ወረዳዎችና ዞኖች ላይ የአመራር ሁኔታ ተፈትሾ ፤ በሂስና በግለ ሂስ ውጤት መሰረት ከሃላፊነት የሚነሱት በሙሉ ተነስተዋል፤ በህግ የሚጠየቁም አመራሮች ተለይተዋል ብለዋል።
“ጥቃቱን እያደረሱት ያሉት የትኛውንም ማህበረሰብ የማይወክሉ ሽፍታዎች ናቸው፤ እነዚህን ሽፍታዎች ደግሞ በጋራ በመሆን የመደምሰስ ስራ ይሰራል፤ አሁንም በተጨባጭ እየተካሄደ ያለው ይሄው ነው” ያሉት አቶ መለሰ፤ የችግሩ ዘላቂ መፍትሄ የጋራ ልማት ማከናወን መሆኑን በማንሳት፤ ከዚህ አንጻር ሁለቱ ክልሎች የጋራ የልማት ትብብር እንዳላቸው አመልክተዋል።
የሁለቱ ክልሎች የ3 ዓመት የጋራ የልማት ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል፤ ይሄንን በይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ጽ/ቤትና መዋቅር ለማቋቋም ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።
ከአደረጃጀት አንጻር የእኛ ክልል ምሳሌ መሆን የሚችል ነው፤ የአማራ ብሄረሰብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ከቀበሌ ጀምሮ የመዋቅሩ አካል የሚሆኑበት አሰራር አለ ያሉት አቶ መለሰ፣ በክልል ደረጃም ከህዝቡ ቁጥር አንጻር እየታየ በመዋቅር ውስጥ የሚሳተፉበት አሰራር ተግባራዊ እንደሆነ አመልክተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት በትናንትናው እለት በ45 የክልሉ አመራሮች ላይ እርምጃ መውሰዱ ታውቋል። ከነዚህም ውስጥ አስሩ አመራሮች በህግ እንዲጠየቁ ተወስኗል።
አዲስ ዘመን መስከረም 19/2013
************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚፈጸሙ ጥቃቶች በክልሉ የመንግስት መዋቅር ክፍተት እና በአንዳንድ አመራሮች ችግር ምክንያት መሆኑን የአማራ ክልላዊ መንግስት አስታወቀ። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት በበኩሉ ችግሮችን ለይቶ እርምጃ መውሰዱን ገልጿል።
የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ትናንት ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግስት መዋቅር ክፍተት አለ ፤ ይህንን ክፍተት የክልሉ መንግስት በአቋም ደረጃ ወስዶ አልሰራበትም። በዚህም ምክንያት በአማራና በአገው ብሄረሰቦች ላይ ጥቃት ሊደርስ ችሏል።
ለችግሩ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ዘላቂ መፍትሄ እየተሰጠ አይደለም፤ እሳት የማጥፋት ስራ ነው እየተሰራ ያሉት አቶ ግዛቸው፤ ከዘላቂ መፍትሄ አንጻር ከክልሉ አመራሮች ጋር በመድረክ ስምምነት የተደረሰበት አማራው፣ አገው እና ሁሉም ዜጋ በአፈጻጸሙና በብቃቱ ተመርጦ በየአካባቢው መደራጀትና የአካባቢውን ጸጥታ መጠበቅ እንዳለበት አመልክተዋል።
“የክልሉ መንግስት አመራሮች በመድረክ ደረጃ የሌላውን ብሄር አደረጃጀት በመዋቅር ውስጥ ለማስገባት ፈቃደኛ ናቸው፤ ምክንያቱም ችግሩ የጋራ ነውና፤ ግድያው አማራን እና አገውን አነጣጥሮ ቢፈጸምም አልተባበር ያለውን ጉሙዝን እና ሺናሻንም ያካተተ ነው ጥቃት አድራሹ ጽንፈኛ ቡድን የክልሉን መንግስትም አዳክሞ ወደ ስልጣን የመምጣት ፍላጎት ያለው እንደሆነም አመልክተዋል።
“የቤኒሻንጉል ጉሙዝ መንግስት ይሄንን ያውቃል። ስለዚህ ይሄን አልቀበልም አይልም፤ ችግሩ ያለው ቁርጠኛ ሆኖ መፈጸም ላይ ነው፤ ይሄ ደግሞ የሆነው መሃላቸው ላይ የዚህ ጽንፈኛ አመለካከት ተጋሪዎች ስላሉ ነው። ይሄንን ማረም አለባቸው” ብለዋል።
አማራ እና አገውን ከሚሊሻ፣ ከቀበሌና ከወረዳ አደረጃጀት ውስጥ ያገለለ ነው ያሉት አቶ ግዛቸው፤ በዚህም ምክንያት የጥቃቱ ሰለባ የሚሆኑ ወገኖች ራሳቸውን የመከላከል አቅም እንዳጡ አመልክተዋል።
በአማራና በአገው ብሄር ተወላጆች ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት መድረሱን ያስታወሱት አቶ ግዛቸው በሰሞኑ ጥቃት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የአማራ ክልላዊ መንግስት የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ከአጭር ጊዜ መፍትሄ አንጻር በጥቃቱ ጉዳት ለደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ የማድረግና የማረጋጋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ በዚህም አስፈላጊው የእለት ደራሽ ሰብአዊ ድጋፍ እየቀረበላቸው መሆኑን አስታውቀዋል።
በጉዳይ ዙሪያ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ መለሰ በየነ በበኩላቸው፤ “የተፈጠረው ችግር ሁላችንንም አሳስቦናል፤ በእኛ መዋቅር ድክመት የተፈጠረ ችግር ነው፤ ያንን ችግር እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ በአብሮነት በጋራ መፍታት እና በጀመርነው ልክ መሄድ አንድ መፍትሄ ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
ቀደም ብሎ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የክልሉን መዋቅር መልሶ የማየትና የማስተካከል ስራ መከናወኑን የገለጹት አቶ መለሰ፤ በሁሉም ወረዳዎችና ዞኖች ላይ የአመራር ሁኔታ ተፈትሾ ፤ በሂስና በግለ ሂስ ውጤት መሰረት ከሃላፊነት የሚነሱት በሙሉ ተነስተዋል፤ በህግ የሚጠየቁም አመራሮች ተለይተዋል ብለዋል።
“ጥቃቱን እያደረሱት ያሉት የትኛውንም ማህበረሰብ የማይወክሉ ሽፍታዎች ናቸው፤ እነዚህን ሽፍታዎች ደግሞ በጋራ በመሆን የመደምሰስ ስራ ይሰራል፤ አሁንም በተጨባጭ እየተካሄደ ያለው ይሄው ነው” ያሉት አቶ መለሰ፤ የችግሩ ዘላቂ መፍትሄ የጋራ ልማት ማከናወን መሆኑን በማንሳት፤ ከዚህ አንጻር ሁለቱ ክልሎች የጋራ የልማት ትብብር እንዳላቸው አመልክተዋል።
የሁለቱ ክልሎች የ3 ዓመት የጋራ የልማት ፕሮጀክት ይፋ ሆኗል፤ ይሄንን በይበልጥ ለማጠናከር የጋራ ጽ/ቤትና መዋቅር ለማቋቋም ስምምነት ላይ ተደርሷል ብለዋል።
ከአደረጃጀት አንጻር የእኛ ክልል ምሳሌ መሆን የሚችል ነው፤ የአማራ ብሄረሰብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ከቀበሌ ጀምሮ የመዋቅሩ አካል የሚሆኑበት አሰራር አለ ያሉት አቶ መለሰ፣ በክልል ደረጃም ከህዝቡ ቁጥር አንጻር እየታየ በመዋቅር ውስጥ የሚሳተፉበት አሰራር ተግባራዊ እንደሆነ አመልክተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት በትናንትናው እለት በ45 የክልሉ አመራሮች ላይ እርምጃ መውሰዱ ታውቋል። ከነዚህም ውስጥ አስሩ አመራሮች በህግ እንዲጠየቁ ተወስኗል።
አዲስ ዘመን መስከረም 19/2013