የህክምና ማዕከሉ የኮሮና ታማሚዎችን ያልተገባ ድርጊት አወገዘ
**************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት የኮሮና ህክምና ማእከል በኮሮና ቫይረስ ተይዘው ከገቡ ታማሚዎች አንዳንዶች በህክምና ክትትል ወቅት የሚያደርጓቸው ያልተፈቀዱ ድርጊቶች ተገቢ ባለመሆናቸው መታረም እንዳለባቸው ማዕከሉ አሳሰበ፡፡
የማእከሉ “ኬዝ ማናጀር“ ዶክተር ወርቅነህ ነጮ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ አስቀድሞ ለለይቶ ማቆያ የተዘጋጀ ሲሆን ወደ ለይቶ ማከሚያ ከተቀየረ ደግሞ አንድ ወር አልፎታል፡፡ የህክምና ማዕከል ከሆነ ጊዜ ጀምሮም ከ200 በላይ የኮሮና ተጠቂዎችንም አስተናግዷል፡፡
የህክምና ክትትል ሲያደርጉ ከነበሩት ታማሚዎች አንዳንዶቹ በማዕከሉ ውስጥ በድብቅ ጫት መቃም፣ ሲጋራ ማጨስና መሰል ድርጊቶችን ሲፈጽሙ እንደነበር ተደርሶበታል ያሉት ማናጀሩ፣ እነዚህንና መሰል ድርጊቶችን በህክምና ማዕከላት ውስጥ መፈጸም ያልተገባና የሚኮነን ተግባር በመሆኑ ለወደፊቱ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች እንደሚያሳዩት ባህሪ የሚገቡበት የህክምና ማእከላት ይለያያሉ ያሉት ዶክተሩ፣ በየካ ወረዳ ሰባት የሚስተናገዱት ምንም አይነት ምልክት ያልታየባቸውና ቀላል ምልክት ያሳዩ ታማሚዎች እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ቫይረሱን አቅልሎ በማየትና ለህክምና ተቋሙ ተገዢ ባለመሆን አንዳንዶች እንደ ጫት ሲጋራና መሰል ያልተፈቀዱ ነገሮችን በማስገባት በድብቅ ይጠቀሙ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ድርጊቱ የተፈጸመው ታማሚዎች ከቤተሰብ እቃ ሲላክላቸው በድብቅ በማስገባታቸው ሲሆን፤ ይህ አይነት ድርጊት ይኖራል ተብሎ ባለመታሰቡ የሚገቡት እቃዎች ላይ በወቅቱ ጠበቅ ያለ ፍተሻ አልነበረም ብለዋል፡፡
ድርጊቱ መፈጸሙን የህክምና ባለሙያዎች የህክምና ክትትል ለማድረግ በየክፍሎቹ ሲዞሩ ማረጋገጣቸውንም ዶክተር ወርቅነህ ገልጸው ሆኖም ደርጊቱ መፈጸሙ ከተረጋገጠ ወዲህ ጥብቅ ክትትልና ፍተሻ በማድረግ ማስቀረት መቻሉንም አስታውቀዋል፡፡
ዶክተር ወርቅነህ እንዲህ አይነት ተግባራትን በተለይ በህክምና ሥፍራዎች ውስጥ መፈጸም ህገ ወጥ መሆኑን ጠቅሰው፤ በማዕከሉ የሚገቡት ታካሚዎች ምንም እንኳን ጤነኛ መስለው ቢታዩም በውስጣቸው ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ተረጋግጦ ስለገቡ በሽታው ይበልጥ እንዳይበረታባቸው፤ እንዲሁም በህክምና ማእከላት ያሉትን መመሪያዎችና ባለሙያዎችን በማክበር ጭምር ራሳቸውን ከመሰል ድርጊት መቆጠብ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በማዕከሉ ለ15 ቀናት ክትትል አድርጎ የወጡት አቶ ጎሳዬ ልመነህ በበኩላቸው ፤ የጤና ባለሙያዎች ሰዎች በቫይረሱ እንዳይያዙ ቀድመው መጠንቀቅ ይገባቸዋል ሲሉ የሚመክሩት ተግባራዊ አለማድረግ አንድ ጥፋት ሆኖ ሳለ በቫይረሱ ተይዘው ወደ ማገገሚያ ማዕከላት የሚገቡ ሰዎች መሰል አስጸያፊ ተግባራትን ማድረጋቸው ተገቢ አይደለም ሲሉ ድርጊቱን ተገቢ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡
አቶ ጎሳዬ በየካ ወረዳ ሰባት የኮሮና ህክምና ማእከል በተለይ ወጣቶች ወደ ማዕከሉ ከገቡ በኋላ ተደብቀው ጫት ሲቅሙ፣ ሲጋራ ሲያጨሱ፣ አልኮል መጠጦችን ከሀይላንድ ጋር በመቀላቀል ወደ ማዕከሉ በድብቅ ሲያስገቡና መሰል ያልተገቡ ድርጊቶችን ሲያከናውኑ መታዘባቸውን በመናገር፤ ተደጋጋሚ ድርጊት እንዳይፈጸም የማዕከሉ ሠራተኞች በዕቃዎች ላይ ጥብቅ ክትትል ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
አዲስ ዘመን ነሐሴ 22/2012
**************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሰባት የኮሮና ህክምና ማእከል በኮሮና ቫይረስ ተይዘው ከገቡ ታማሚዎች አንዳንዶች በህክምና ክትትል ወቅት የሚያደርጓቸው ያልተፈቀዱ ድርጊቶች ተገቢ ባለመሆናቸው መታረም እንዳለባቸው ማዕከሉ አሳሰበ፡፡
የማእከሉ “ኬዝ ማናጀር“ ዶክተር ወርቅነህ ነጮ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ ማዕከሉ አስቀድሞ ለለይቶ ማቆያ የተዘጋጀ ሲሆን ወደ ለይቶ ማከሚያ ከተቀየረ ደግሞ አንድ ወር አልፎታል፡፡ የህክምና ማዕከል ከሆነ ጊዜ ጀምሮም ከ200 በላይ የኮሮና ተጠቂዎችንም አስተናግዷል፡፡
የህክምና ክትትል ሲያደርጉ ከነበሩት ታማሚዎች አንዳንዶቹ በማዕከሉ ውስጥ በድብቅ ጫት መቃም፣ ሲጋራ ማጨስና መሰል ድርጊቶችን ሲፈጽሙ እንደነበር ተደርሶበታል ያሉት ማናጀሩ፣ እነዚህንና መሰል ድርጊቶችን በህክምና ማዕከላት ውስጥ መፈጸም ያልተገባና የሚኮነን ተግባር በመሆኑ ለወደፊቱ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች እንደሚያሳዩት ባህሪ የሚገቡበት የህክምና ማእከላት ይለያያሉ ያሉት ዶክተሩ፣ በየካ ወረዳ ሰባት የሚስተናገዱት ምንም አይነት ምልክት ያልታየባቸውና ቀላል ምልክት ያሳዩ ታማሚዎች እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ ሆኖም ቫይረሱን አቅልሎ በማየትና ለህክምና ተቋሙ ተገዢ ባለመሆን አንዳንዶች እንደ ጫት ሲጋራና መሰል ያልተፈቀዱ ነገሮችን በማስገባት በድብቅ ይጠቀሙ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ድርጊቱ የተፈጸመው ታማሚዎች ከቤተሰብ እቃ ሲላክላቸው በድብቅ በማስገባታቸው ሲሆን፤ ይህ አይነት ድርጊት ይኖራል ተብሎ ባለመታሰቡ የሚገቡት እቃዎች ላይ በወቅቱ ጠበቅ ያለ ፍተሻ አልነበረም ብለዋል፡፡
ድርጊቱ መፈጸሙን የህክምና ባለሙያዎች የህክምና ክትትል ለማድረግ በየክፍሎቹ ሲዞሩ ማረጋገጣቸውንም ዶክተር ወርቅነህ ገልጸው ሆኖም ደርጊቱ መፈጸሙ ከተረጋገጠ ወዲህ ጥብቅ ክትትልና ፍተሻ በማድረግ ማስቀረት መቻሉንም አስታውቀዋል፡፡
ዶክተር ወርቅነህ እንዲህ አይነት ተግባራትን በተለይ በህክምና ሥፍራዎች ውስጥ መፈጸም ህገ ወጥ መሆኑን ጠቅሰው፤ በማዕከሉ የሚገቡት ታካሚዎች ምንም እንኳን ጤነኛ መስለው ቢታዩም በውስጣቸው ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ተረጋግጦ ስለገቡ በሽታው ይበልጥ እንዳይበረታባቸው፤ እንዲሁም በህክምና ማእከላት ያሉትን መመሪያዎችና ባለሙያዎችን በማክበር ጭምር ራሳቸውን ከመሰል ድርጊት መቆጠብ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
በማዕከሉ ለ15 ቀናት ክትትል አድርጎ የወጡት አቶ ጎሳዬ ልመነህ በበኩላቸው ፤ የጤና ባለሙያዎች ሰዎች በቫይረሱ እንዳይያዙ ቀድመው መጠንቀቅ ይገባቸዋል ሲሉ የሚመክሩት ተግባራዊ አለማድረግ አንድ ጥፋት ሆኖ ሳለ በቫይረሱ ተይዘው ወደ ማገገሚያ ማዕከላት የሚገቡ ሰዎች መሰል አስጸያፊ ተግባራትን ማድረጋቸው ተገቢ አይደለም ሲሉ ድርጊቱን ተገቢ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡
አቶ ጎሳዬ በየካ ወረዳ ሰባት የኮሮና ህክምና ማእከል በተለይ ወጣቶች ወደ ማዕከሉ ከገቡ በኋላ ተደብቀው ጫት ሲቅሙ፣ ሲጋራ ሲያጨሱ፣ አልኮል መጠጦችን ከሀይላንድ ጋር በመቀላቀል ወደ ማዕከሉ በድብቅ ሲያስገቡና መሰል ያልተገቡ ድርጊቶችን ሲያከናውኑ መታዘባቸውን በመናገር፤ ተደጋጋሚ ድርጊት እንዳይፈጸም የማዕከሉ ሠራተኞች በዕቃዎች ላይ ጥብቅ ክትትል ማድረግ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡
አዲስ ዘመን ነሐሴ 22/2012
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 1 ሺህ 733 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 18 ሺህ 766 የላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 733 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በትናንትናው ዕለት 586 ሠዋች ያገገሙ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በአገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 17 ሺህ 415 ሆኗል።
ካለፉት 24 ሰዓታት ምርመራ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ በኮሮናቫይረስ የተነሣ የሟቾች ቁጥር 758 ደርሷል።
በአሁኑ ወቅት 358 ሰዎች በጽኑ ሕክምና ላይ ሲገኙ፣ 29 ሺህ 965 ደግሞ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች መሆናቸው ተገልጿል።
በአጠቃላይ በአገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 48 ሺህ 140 ደርሷል።
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 18 ሺህ 766 የላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 733 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በትናንትናው ዕለት 586 ሠዋች ያገገሙ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በአገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 17 ሺህ 415 ሆኗል።
ካለፉት 24 ሰዓታት ምርመራ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ በኮሮናቫይረስ የተነሣ የሟቾች ቁጥር 758 ደርሷል።
በአሁኑ ወቅት 358 ሰዎች በጽኑ ሕክምና ላይ ሲገኙ፣ 29 ሺህ 965 ደግሞ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች መሆናቸው ተገልጿል።
በአጠቃላይ በአገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 48 ሺህ 140 ደርሷል።
"የፌዴራል መንግሥት ህውሓት እየሠራ ያለውን ግፍና በደል ሊቀለብስ የሚችል ሥራ እየሠራ አይደለም" - ዶክተር ሲሳይ መንግስቴ የፌዴራሊዝም መምህር
****************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ህውሓት እየሠራ ያለው ግፍና በደል በጣም ሰፊ ቢሆንም የፌዴራል መንግሥት ይህንን ሊቀለብስ የሚችል ሥራ እየሠራ አይደለም ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌዴራሊዝም ትምህርት ክፍል መምህር ዶክተር ሲሳይ መንግስቴ አስታወቁ።
«የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄና የማዕከላዊ መንግሥታዊ ምላሽ ከአፄ ዮሐንስ እስከ ኢህአደግ» እና «በሴራ የተፈተነች ህይወት›› መፃሐፍ ደራሲና የፌዴራሊዝም መምህሩ ዶክተር ሲሳይ መንግስቴ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ህውሓት እየሠራ ያለው ግፍና በደል በጣም ሰፊ ቢሆንም የፌዴራል መንግሥት ይህንን ሊቀለብስ የሚችል ሥራ እየሠራ አይደለም ሲሉ አመልተዋል።
‹‹በጉዳዩ የፌዴራል መንግሥት ብዙ ጊዜ ጥያቄና ወቀሳ ቀርቦበታል። ዝምታው ግን ለምን እንደሆነ አይገባኝም።በተለይም የትግራይ ክልል የተደራጀ ኃይል ያለው እንደመሆኑ ያንን መመከት የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ አይደለም›› ብለዋል።
ዝምታው ህዝቡ እንዳይጎዳ ከማሰብ የተነሳ ቀስ በቀስ አመራሩን ማዳከም የፈለገ እንደሚመስል በመጠቆምም፤ ሂደቱ በአንድ በኩል ትክክል ነው። ነገር ግን አንድ ቦታ ላይ ከሚወሰደው ዕርምጃ አኳያ አድሎ ሊመስል እንደሚችል አመልክተዋል።
የቀድሞ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አብዲ መሀመድ ኡመር በሱማሌ ክልል ችግር በፈጠረበት ጊዜ ወዲያውኑ ዕርምጃ መወሰዱን በምሳሌነት አስታውሰው፤ ትግራይ ላይ እንዲህ ዓይነት ችግር ሲፈጠር ለምንድን ነው ዝም የሚባለው? ሲሉም ጠይቀዋል።
ህወሓት በራያና በወልቃይት ህዝብን እያፈነ ይገኛል፣ እየተፈፀመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፤ ጉልበት ያለው እንዳሻው እያፈነ ሊቀጥል፤ ብዙም ጉልበት የለውም ተብሎ የሚታሰበውን ዕርምጃ የሚወሰድበት ሁኔታ መኖር የለበትም ብለዋል።
የህውሓት አክራሪ አመራር ላይ ጠበቅ ያለ ህጋዊ፣ አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ዕርምጃ መወሰድ አለበት። በሂደት ደግሞ እያዳከመ ሄዶ ህዝብንና ድርጅቱን ለይቶ ጠንከር ያለ ዕርምጃ የሚወሰድበትን ሁኔታ ማሰብ በጣም አስፈላጊ እንደሆነም አመልክተዋል።
ህወሓቶች ምርጫ እናደርጋለን ብለው እያደረጉት ያለው የማዋከብ ሥራ በህዝቡ ላይ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው ሁሉ ሌላ ተጨማሪ የጎን ውጋት ሆኖበታል። በምርጫ ያልተመዘገበ ሰው በክልሉ መኖር እንደማይችል ተነግሮታል። በተለይም ፍቃደኛ ያልሆነ ወጣት በቤተሰቡ በኩል በግድ እንዲመዘገብ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።
እንደ ዶክተር ሲሳይ ማብራሪያ፤ የምርጫ ባህሪ ማንም ሰው በፍላጎት የሚመርጥበትን መብት ይሰጣል። ይሁን እንጂ ህወሓት ይህንን መብት በመጋፋት ከፍተኛ ተፅእኖ እያደረሰ ይገኛል። ተጽዕኖው በተለይ ራያና ወልቃይት ላይ በጣም በከፋ መልኩ የሚታይበት ሁኔታ አለ።
‹‹ምርጫውን ልክ የትግራይ ህዝብ የነፃነት መገለጫ አድርገው ነው እየቆጠሩት ያሉት። ህወሓት የአገሪቱን ህገመንግሥት ብቻ ሳይሆን የራሳቸውን ህገመንግሥት ጭምር የሚጥስ ሥራ እየሠራ ነው›› ሲሉም ነው የተናገሩት።
የክልሉን ልዩ ኃይል ቁጥር በመጨመር የማሳፈንና የማሰር ሁኔታ ተስፋፍቷል ያሉት ዶክተር ሲሳይ፤ በተለይ ሰሞኑን ‹‹ምርጫውን ይቃወማሉ፣ ያደናቅፋሉ ብለው የሚያስቧቸውን በርካታ ቁጥር ያላቸውን ወጣቶችን እያሰሩና እያስፈራሩ ናቸው። ማሳደዱና እንግልቱ በጣም በሚያስፈራ ሁኔታ የበለጠ ጨምሯል ብለዋል።
ወደትግራይ ክልል ለመሄድ በየአምስት ኪሎ ሜትሩ ባሉ ኬላዎች ላይ አስፈሪ ፍተሻ ይደረጋል፤ በገዛ አካባቢሽ ላይ ደርግ ያደርገው እንደነበረው ገበያ ቦታ ሳይቀር መታወቂያ ይጠየቃል። ከአንዱ ቀበሌ ወደ ሌላኛው ቀበሌ ለመንቀሳቀስ መታወቂያ ካልያዝሽ ከፍተኛ እንግልት ይደርሳል ሲሉም ተናግረዋል።
ራያ ቆቦና ራያ አላማጣ የተዋሃደ ቤተሰብ ቢሆንም በሁለት ክልሎች የሚተዳደሩ ናቸው። በመሆኑም የራያ ቆቦ አካባቢ ነዋሪ የአማራ ክልል መታወቂያ ይዞ ከተገኘ ተጨማሪ እንግልት ይገጥመዋል። እንዲህ ዓይነት ግፍና በደል በጣም ጎልቶ ወጥቷል። በመሆኑም ምርጫው ህገወጥ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ህዝቡን እያንገላቱበትና እያሰቃዩበት ያለ በመሆኑ በእጅጉ የሚወገዝና በእዚህ መልክ መቀጠል የማይገባው ነው ሲሉም አመልክተዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
****************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ህውሓት እየሠራ ያለው ግፍና በደል በጣም ሰፊ ቢሆንም የፌዴራል መንግሥት ይህንን ሊቀለብስ የሚችል ሥራ እየሠራ አይደለም ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፌዴራሊዝም ትምህርት ክፍል መምህር ዶክተር ሲሳይ መንግስቴ አስታወቁ።
«የራያ ህዝብ የማንነት ጥያቄና የማዕከላዊ መንግሥታዊ ምላሽ ከአፄ ዮሐንስ እስከ ኢህአደግ» እና «በሴራ የተፈተነች ህይወት›› መፃሐፍ ደራሲና የፌዴራሊዝም መምህሩ ዶክተር ሲሳይ መንግስቴ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ህውሓት እየሠራ ያለው ግፍና በደል በጣም ሰፊ ቢሆንም የፌዴራል መንግሥት ይህንን ሊቀለብስ የሚችል ሥራ እየሠራ አይደለም ሲሉ አመልተዋል።
‹‹በጉዳዩ የፌዴራል መንግሥት ብዙ ጊዜ ጥያቄና ወቀሳ ቀርቦበታል። ዝምታው ግን ለምን እንደሆነ አይገባኝም።በተለይም የትግራይ ክልል የተደራጀ ኃይል ያለው እንደመሆኑ ያንን መመከት የሚያስችል እንቅስቃሴ እየተደረገ አይደለም›› ብለዋል።
ዝምታው ህዝቡ እንዳይጎዳ ከማሰብ የተነሳ ቀስ በቀስ አመራሩን ማዳከም የፈለገ እንደሚመስል በመጠቆምም፤ ሂደቱ በአንድ በኩል ትክክል ነው። ነገር ግን አንድ ቦታ ላይ ከሚወሰደው ዕርምጃ አኳያ አድሎ ሊመስል እንደሚችል አመልክተዋል።
የቀድሞ የሱማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አብዲ መሀመድ ኡመር በሱማሌ ክልል ችግር በፈጠረበት ጊዜ ወዲያውኑ ዕርምጃ መወሰዱን በምሳሌነት አስታውሰው፤ ትግራይ ላይ እንዲህ ዓይነት ችግር ሲፈጠር ለምንድን ነው ዝም የሚባለው? ሲሉም ጠይቀዋል።
ህወሓት በራያና በወልቃይት ህዝብን እያፈነ ይገኛል፣ እየተፈፀመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው፤ ጉልበት ያለው እንዳሻው እያፈነ ሊቀጥል፤ ብዙም ጉልበት የለውም ተብሎ የሚታሰበውን ዕርምጃ የሚወሰድበት ሁኔታ መኖር የለበትም ብለዋል።
የህውሓት አክራሪ አመራር ላይ ጠበቅ ያለ ህጋዊ፣ አስተዳደራዊና ፖለቲካዊ ዕርምጃ መወሰድ አለበት። በሂደት ደግሞ እያዳከመ ሄዶ ህዝብንና ድርጅቱን ለይቶ ጠንከር ያለ ዕርምጃ የሚወሰድበትን ሁኔታ ማሰብ በጣም አስፈላጊ እንደሆነም አመልክተዋል።
ህወሓቶች ምርጫ እናደርጋለን ብለው እያደረጉት ያለው የማዋከብ ሥራ በህዝቡ ላይ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው ሁሉ ሌላ ተጨማሪ የጎን ውጋት ሆኖበታል። በምርጫ ያልተመዘገበ ሰው በክልሉ መኖር እንደማይችል ተነግሮታል። በተለይም ፍቃደኛ ያልሆነ ወጣት በቤተሰቡ በኩል በግድ እንዲመዘገብ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።
እንደ ዶክተር ሲሳይ ማብራሪያ፤ የምርጫ ባህሪ ማንም ሰው በፍላጎት የሚመርጥበትን መብት ይሰጣል። ይሁን እንጂ ህወሓት ይህንን መብት በመጋፋት ከፍተኛ ተፅእኖ እያደረሰ ይገኛል። ተጽዕኖው በተለይ ራያና ወልቃይት ላይ በጣም በከፋ መልኩ የሚታይበት ሁኔታ አለ።
‹‹ምርጫውን ልክ የትግራይ ህዝብ የነፃነት መገለጫ አድርገው ነው እየቆጠሩት ያሉት። ህወሓት የአገሪቱን ህገመንግሥት ብቻ ሳይሆን የራሳቸውን ህገመንግሥት ጭምር የሚጥስ ሥራ እየሠራ ነው›› ሲሉም ነው የተናገሩት።
የክልሉን ልዩ ኃይል ቁጥር በመጨመር የማሳፈንና የማሰር ሁኔታ ተስፋፍቷል ያሉት ዶክተር ሲሳይ፤ በተለይ ሰሞኑን ‹‹ምርጫውን ይቃወማሉ፣ ያደናቅፋሉ ብለው የሚያስቧቸውን በርካታ ቁጥር ያላቸውን ወጣቶችን እያሰሩና እያስፈራሩ ናቸው። ማሳደዱና እንግልቱ በጣም በሚያስፈራ ሁኔታ የበለጠ ጨምሯል ብለዋል።
ወደትግራይ ክልል ለመሄድ በየአምስት ኪሎ ሜትሩ ባሉ ኬላዎች ላይ አስፈሪ ፍተሻ ይደረጋል፤ በገዛ አካባቢሽ ላይ ደርግ ያደርገው እንደነበረው ገበያ ቦታ ሳይቀር መታወቂያ ይጠየቃል። ከአንዱ ቀበሌ ወደ ሌላኛው ቀበሌ ለመንቀሳቀስ መታወቂያ ካልያዝሽ ከፍተኛ እንግልት ይደርሳል ሲሉም ተናግረዋል።
ራያ ቆቦና ራያ አላማጣ የተዋሃደ ቤተሰብ ቢሆንም በሁለት ክልሎች የሚተዳደሩ ናቸው። በመሆኑም የራያ ቆቦ አካባቢ ነዋሪ የአማራ ክልል መታወቂያ ይዞ ከተገኘ ተጨማሪ እንግልት ይገጥመዋል። እንዲህ ዓይነት ግፍና በደል በጣም ጎልቶ ወጥቷል። በመሆኑም ምርጫው ህገወጥ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ህዝቡን እያንገላቱበትና እያሰቃዩበት ያለ በመሆኑ በእጅጉ የሚወገዝና በእዚህ መልክ መቀጠል የማይገባው ነው ሲሉም አመልክተዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
ዳያስፖራው ከ800 ሺ ዶላር በላይ ለህዳሴው ግድብ ድጋፍ አደረገ
*****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የዳያስፖራው ማህበረሰብ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ከ800 ሺ ዶላር በላይ የቦንድ ግዢ ማከናወኑንና በስጦታ ማበርከቱን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት ዳያስፖራው ማህበረሰብ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ሲጀመር ጀምሮ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ቦንድ በመግዛት ስጦታ በማበርከትና በሙያው ድጋፉን ሲያደርግ ቆይቷል። በእነዚህም ዓመታት ከ42 ሚሊየን ዶላር በላይ ማስገባት የተቻለ ሲሆን፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ ሙሌቱ እስከተጀመረበት ቀን ደረስ ከ800 ሺ ዶላር በላይ የቦንድ ግዢና ስጦታ አከናውኗል።
ሀብት የማሰባሰቡ ሥራ በዘመቻ መልክ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በመጠቆምም በቀጣይ ዓመትም ከ200 ሚሊየን ብር በላይ ለማሰባሰብ አቅድ የተያዘ ሲሆን፤ ዘንድሮ ሙሌቱ ከተጀመረ በኋላ ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለውን የድርድር ሂደትም በመላው ዓለም በእንግሊዝኛ፤ በፈረንሳይኛና በአረብኛ ቋንቋዎች የተለያዩ ሚድያዎችን በመጠቀም ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በስፋት ድጋፍ እየሰጡበት መሆኑን ገልጸዋል።
የኮሮና ቫይረስ መከሰትንም ተከትሎ ዳያስፖራው የተቻለውን ሲያደርግ ቆይቷል ያሉት ወይዘሮ ሰላማዊት እስከአሁን ከ300 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን፤ ይህም በሽታው እስከሚጠፋ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ሃሳብን በነፃነት መግለጽም ሆነ መንግሥትን መቃወም መብት ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ኤንባሲዎች አካባቢ እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት ግን ከኢትዮጵያዊነት ስነ ምግባር ያፈነገጡ ብቻ ሳይሆን በህግ የሚያስጠይቁም ናቸው ብለዋል። በመሆኑም ማንኛውም ሰው ያለውን ጥያቄም ሆነ ተቃውሞ ስርዓት በጠበቀና የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት በማይነካ መልኩ ማቅረብ እንዳለበት አሳስበዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
*****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የዳያስፖራው ማህበረሰብ ለታላቁ የህዳሴ ግድብ ከ800 ሺ ዶላር በላይ የቦንድ ግዢ ማከናወኑንና በስጦታ ማበርከቱን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ሰላማዊት ዳዊት በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት ዳያስፖራው ማህበረሰብ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ሲጀመር ጀምሮ ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት ቦንድ በመግዛት ስጦታ በማበርከትና በሙያው ድጋፉን ሲያደርግ ቆይቷል። በእነዚህም ዓመታት ከ42 ሚሊየን ዶላር በላይ ማስገባት የተቻለ ሲሆን፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ብቻ ሙሌቱ እስከተጀመረበት ቀን ደረስ ከ800 ሺ ዶላር በላይ የቦንድ ግዢና ስጦታ አከናውኗል።
ሀብት የማሰባሰቡ ሥራ በዘመቻ መልክ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በመጠቆምም በቀጣይ ዓመትም ከ200 ሚሊየን ብር በላይ ለማሰባሰብ አቅድ የተያዘ ሲሆን፤ ዘንድሮ ሙሌቱ ከተጀመረ በኋላ ኢትዮጵያ እያደረገችው ያለውን የድርድር ሂደትም በመላው ዓለም በእንግሊዝኛ፤ በፈረንሳይኛና በአረብኛ ቋንቋዎች የተለያዩ ሚድያዎችን በመጠቀም ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በስፋት ድጋፍ እየሰጡበት መሆኑን ገልጸዋል።
የኮሮና ቫይረስ መከሰትንም ተከትሎ ዳያስፖራው የተቻለውን ሲያደርግ ቆይቷል ያሉት ወይዘሮ ሰላማዊት እስከአሁን ከ300 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን፤ ይህም በሽታው እስከሚጠፋ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል ሃሳብን በነፃነት መግለጽም ሆነ መንግሥትን መቃወም መብት ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአንዳንድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ኤንባሲዎች አካባቢ እየተከናወኑ ያሉት ተግባራት ግን ከኢትዮጵያዊነት ስነ ምግባር ያፈነገጡ ብቻ ሳይሆን በህግ የሚያስጠይቁም ናቸው ብለዋል። በመሆኑም ማንኛውም ሰው ያለውን ጥያቄም ሆነ ተቃውሞ ስርዓት በጠበቀና የሀገርን ክብርና ሉአላዊነት በማይነካ መልኩ ማቅረብ እንዳለበት አሳስበዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
“የእንጦጦና ሸራተን አካባቢ ፓርኮች ለሌሎች ፕሮጀክቶች የልምድ ማሳያ መሆን ይችላሉ" አምባሳደር ደግፌ ቡላ
*****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- ሸገርን የማስዋብ አካል የሆኑት የአንጦጦ የሸራተን አካባቢ ፓርክ ግንባታዎች በመላ ኢትዮጵያ ተግባራዊ ለሚደረጉ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ የልምድ ማሳያ መሆን እንደሚችሉ አምባሳደር ደግፌ ቡላ ተናገሩ።
የፌዴራል የፍትህ፤ የህግ ጥናትና ምርምር ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ አንድነት እና እንጦጦ ፓርኮችን ከጎበኙ በኋላ እንደገለጹት፤ በሸገር ማስዋብ ፕሮጀክት ስር ያሉት የሸራተን አካባቢ አረንጓዴ ፓርክን እና እንጦጦ ፓርክ በአጭር ጊዜያት ተጠናቀው ጎብኚዎችን ማስተናገድ በመቻላቸው በተለያየ መንገድ በቀጣይ ሊገነቡ ለታሰቡ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች የልምድ ማሳያ በመሆን ማገልገል ይችላሉ።
ፓርኮቹ በአጭር ጊዜ በመጠናቀቃቸው በአንድ በኩል በግንባታ ፍጥነት ረገድ ተሞክሮ ለማካፈል እንደሚረዱ የገለጹት አምባሳደር ደግፌ፤ በሌላ መልኩ ደግሞ ተፈጥሮን እና ሰው ሠራሽ መዝናኛዎችን በአንድ መያዝ በመቻላቸው በቱሪዝም ዘርፉ ያሉ አማራጮችን በሌሎች ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ለማድረግ በር ከፋች መሆናቸውን ተናግረዋል።
እንጦጦ ከዚህ ቀደም በባህር ዛፍ የተሸፈነ በመሆኑ በአካባቢው ያሉ እናቶቻችን እንጨት እና ቅጠል የሚለቅሙበት ቦታ መሆኑን አስታውሰው፤ ማንም ሰው እስከአሁን ዞር ብሎ ያላየው ልዩ ሀብት ያለበት ቦታ እንደነበረ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለውጥ ከመጣ በኋላ ግን ዶክተር አብይ አህመድ በወሰዱት ዕርምጃ ለትውልድ የሚተላለፍ መዝናኛ ማልዕከል መገንባቱ በዘርፉ ትልቅ ልምድ ያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል።
በተመሳሳይ የሸራተን አካባቢ እና የአንድነት ፓርኮች ከአዲስ አበባ ውጪ ሊገነቡ ለታሰቡ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች በሥራ ጥራት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ ትልቅ ተሞክሮ ማካፈያ መሆን እንደሚችሉ ገልጸዋል።
እንደ አምባሳደር ደግፌ ከሆነ፤ ገበታ ለሀገር በሚል ምዕራፍ ሊገነቡ ለታቀዱ በኦሮሚያ ክልል ለሚገኘውን የወንጪ ሐይቅ ፤ በአማራ ክልል የሚገኘውን ጎርጎራን እና በደቡብ ኢትዮጵያ ለሚገኘውን የኮንታ ኮይሻ ፕሮጀክቶች ውጥን መሳካት ከሸገር ማስዋብ ፕሮጀክት ተግባራዊ ልምድ መውሰድ ይቻላል።
በተመሳሳይ በመላ ኢትዮጵያ መልማት የሚችሉ አካባቢዎች ላይ ፕሮጀክቶችን በማዘጋጀት ለነዋሪው ንጹህ አየርን ማስገኘት ብቻ ሳይሆን ሀብት መሰብሰብ እንደሚቻል የሸገር ፕሮጀክቶች በአይን የሚታይ ትምህርት ሰጪ ናቸው ብለዋል።
ከዚህ ቀደም ባለው ልምድ የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች በተለይም የአፍሪካ መሪዎች አዲስ አበባ ሲመጡ በቅርበ የሚያገኙትን ሉሲን ብቻ ጎብኝተው እንደሚመለሱ ያስታወሱት አምባሳደር ደግፌ፤ ከዚህ በኋላ ግን በመዲናዋ ሊጎበኙ የሚችሉ በርካታ አማራጮች በመስፋፋታቸው የዲፕሎማቶችም ሆነ የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ተጨማሪ ገቢ ለሀገር ማስገባት የሚያስችል ዕድል እንደተፈጠረ ገልጸዋል።
በመሃል ከተማ የተገነቡትን ፓርኮች እና እንጦጦ ፓርክን መመልከት ቢቻል በአጭር ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ምን ያክል ለቱሪዝም ምቹ የሆነች ሀገር እንድትሆን እየተሠራ እንዳለ መገንዘብ እንደሚቻል ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ፓርኮቹን እንደእራስ ሀብት በመንከባከብ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፉበትን መንገድ ማሰብ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
የእንጦጦ እና ሸገር ፓርኮች ጥሞናን ለሚፈልጉ የህግና ጥናትና ምርምሮች ወሳኝ ቦታዎች መሆናቸውን የተናገሩት አምባሳደር ደግፌ፤ በዚህ ረገድ የሀገር ውስጥ ምሁራንም ሆነ በኢንስቲትዩቱ በኩል ከውጭ ሀገራት ለጥናት የሚመጡ ምሁራንን ወደፓርኮቹ በመጋበዝ አዳዲስ ሃሳቦችን እንዲያፈልቁ ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል።
መጥፎ ሃሳብ ለሰው ልጅ ውድቀት ምክንያት እንደሚሆን ሁሉ ፓርኮቹን ለመገንባት የቻሉ ሃሳቦች ደግሞ ልማትን በመፍጠራቸው ሊደነቁ ይገባቸዋል። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ለዚህ ሥራ የጣሩ የሥራ ባልደረቦች በሙሉ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
ጌትነት ተስፋማርያም
*****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- ሸገርን የማስዋብ አካል የሆኑት የአንጦጦ የሸራተን አካባቢ ፓርክ ግንባታዎች በመላ ኢትዮጵያ ተግባራዊ ለሚደረጉ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ተግባራዊ የልምድ ማሳያ መሆን እንደሚችሉ አምባሳደር ደግፌ ቡላ ተናገሩ።
የፌዴራል የፍትህ፤ የህግ ጥናትና ምርምር ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አምባሳደር ደግፌ ቡላ አንድነት እና እንጦጦ ፓርኮችን ከጎበኙ በኋላ እንደገለጹት፤ በሸገር ማስዋብ ፕሮጀክት ስር ያሉት የሸራተን አካባቢ አረንጓዴ ፓርክን እና እንጦጦ ፓርክ በአጭር ጊዜያት ተጠናቀው ጎብኚዎችን ማስተናገድ በመቻላቸው በተለያየ መንገድ በቀጣይ ሊገነቡ ለታሰቡ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች የልምድ ማሳያ በመሆን ማገልገል ይችላሉ።
ፓርኮቹ በአጭር ጊዜ በመጠናቀቃቸው በአንድ በኩል በግንባታ ፍጥነት ረገድ ተሞክሮ ለማካፈል እንደሚረዱ የገለጹት አምባሳደር ደግፌ፤ በሌላ መልኩ ደግሞ ተፈጥሮን እና ሰው ሠራሽ መዝናኛዎችን በአንድ መያዝ በመቻላቸው በቱሪዝም ዘርፉ ያሉ አማራጮችን በሌሎች ፕሮጀክቶች ተግባራዊ ለማድረግ በር ከፋች መሆናቸውን ተናግረዋል።
እንጦጦ ከዚህ ቀደም በባህር ዛፍ የተሸፈነ በመሆኑ በአካባቢው ያሉ እናቶቻችን እንጨት እና ቅጠል የሚለቅሙበት ቦታ መሆኑን አስታውሰው፤ ማንም ሰው እስከአሁን ዞር ብሎ ያላየው ልዩ ሀብት ያለበት ቦታ እንደነበረ ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ለውጥ ከመጣ በኋላ ግን ዶክተር አብይ አህመድ በወሰዱት ዕርምጃ ለትውልድ የሚተላለፍ መዝናኛ ማልዕከል መገንባቱ በዘርፉ ትልቅ ልምድ ያስገኘ መሆኑን አስረድተዋል።
በተመሳሳይ የሸራተን አካባቢ እና የአንድነት ፓርኮች ከአዲስ አበባ ውጪ ሊገነቡ ለታሰቡ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች በሥራ ጥራት እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ረገድ ትልቅ ተሞክሮ ማካፈያ መሆን እንደሚችሉ ገልጸዋል።
እንደ አምባሳደር ደግፌ ከሆነ፤ ገበታ ለሀገር በሚል ምዕራፍ ሊገነቡ ለታቀዱ በኦሮሚያ ክልል ለሚገኘውን የወንጪ ሐይቅ ፤ በአማራ ክልል የሚገኘውን ጎርጎራን እና በደቡብ ኢትዮጵያ ለሚገኘውን የኮንታ ኮይሻ ፕሮጀክቶች ውጥን መሳካት ከሸገር ማስዋብ ፕሮጀክት ተግባራዊ ልምድ መውሰድ ይቻላል።
በተመሳሳይ በመላ ኢትዮጵያ መልማት የሚችሉ አካባቢዎች ላይ ፕሮጀክቶችን በማዘጋጀት ለነዋሪው ንጹህ አየርን ማስገኘት ብቻ ሳይሆን ሀብት መሰብሰብ እንደሚቻል የሸገር ፕሮጀክቶች በአይን የሚታይ ትምህርት ሰጪ ናቸው ብለዋል።
ከዚህ ቀደም ባለው ልምድ የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች በተለይም የአፍሪካ መሪዎች አዲስ አበባ ሲመጡ በቅርበ የሚያገኙትን ሉሲን ብቻ ጎብኝተው እንደሚመለሱ ያስታወሱት አምባሳደር ደግፌ፤ ከዚህ በኋላ ግን በመዲናዋ ሊጎበኙ የሚችሉ በርካታ አማራጮች በመስፋፋታቸው የዲፕሎማቶችም ሆነ የጎብኚዎችን የቆይታ ጊዜ በማራዘም ተጨማሪ ገቢ ለሀገር ማስገባት የሚያስችል ዕድል እንደተፈጠረ ገልጸዋል።
በመሃል ከተማ የተገነቡትን ፓርኮች እና እንጦጦ ፓርክን መመልከት ቢቻል በአጭር ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ምን ያክል ለቱሪዝም ምቹ የሆነች ሀገር እንድትሆን እየተሠራ እንዳለ መገንዘብ እንደሚቻል ተናግረዋል። በዚህ ረገድ ፓርኮቹን እንደእራስ ሀብት በመንከባከብ ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፉበትን መንገድ ማሰብ እንደሚያስፈልግ አመልክተዋል።
የእንጦጦ እና ሸገር ፓርኮች ጥሞናን ለሚፈልጉ የህግና ጥናትና ምርምሮች ወሳኝ ቦታዎች መሆናቸውን የተናገሩት አምባሳደር ደግፌ፤ በዚህ ረገድ የሀገር ውስጥ ምሁራንም ሆነ በኢንስቲትዩቱ በኩል ከውጭ ሀገራት ለጥናት የሚመጡ ምሁራንን ወደፓርኮቹ በመጋበዝ አዳዲስ ሃሳቦችን እንዲያፈልቁ ጥረት እንደሚደረግ ገልጸዋል።
መጥፎ ሃሳብ ለሰው ልጅ ውድቀት ምክንያት እንደሚሆን ሁሉ ፓርኮቹን ለመገንባት የቻሉ ሃሳቦች ደግሞ ልማትን በመፍጠራቸው ሊደነቁ ይገባቸዋል። በዚህ ረገድ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና ለዚህ ሥራ የጣሩ የሥራ ባልደረቦች በሙሉ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
ጌትነት ተስፋማርያም
ብሔራዊ ሙዚየም በኮሮና ምክንያት 150 ሺ ጎብኚዎችን አጥቷል
***************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- ኮሮና ወረርሽኝ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ የጉብኝት አገልግሎቱ በመቋረጡ በአምስት ወራት ውስጥ 150 ሺ ጎብኚዎችን ማጣቱን ብሔራዊ ሙዚየም አስታወቀ።
በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን የብሔራዊ ሙዚየም ዳይሬክተር አቶ ኤፍሬም አማረ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ የኮሮና በሽታ ወደኢትዮጵያ ከገባ ከመጋቢት 15 ቀን 2012 ጀምሮ የብሔራዊ ሙዚያም ለጥንቃቄ ሲባል ለጎብኚዎች ዝግ ሆኖ ቆይቷል። በዚህም ምክንያት ባለፉት አምስት ወራት ሙዚየሙን ሊጎበኙ ለሚችሉ 150ሺህ ሰዎች አገልግሎት መስጠት አልተቻለም።
ቀደም ባለው ጊዜ ባለው ልምድ መሰረት ብሔራዊ ሙዚየምን በየቀኑ የሚጎበኙ ሰዎች ቁጥር በአማካይ አንድ ሺ ይደርሳል። በተለይ በክረምት ወቅት ከትምህርት ቤቶች እና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙዚየሙን ለመጎብኘት የሚመጡ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምር አመልክተው፣ የውጭ ሃገራት ጎብኚዎችም በብዛት ወደኢትዮጵያ እንደሚመጡ የሚጠበቅበት ወቅት እንደነበር አስታውቀዋል።
ሙዚየሙ በኮሮና በሽታ ምክንያት ሲዘጋ አገልግሎቱን ማግኘት ካልቻሉ 150 ሺህ ሰዎች መካከል 45ሺህ የሚሆኑት ከውጭ ሀገራት የሚመጡ ጎብኝዎች እንደሚሆኑ ይገመታል ያሉት አቶ ኤፍሬም፤ ጎብኚዎቹ በመቅረታቸው የባህል እቃዎች እና አልባሳት አቅራቢዎችን
ገቢ ክፉኛ እንደጎዳው ተናግረዋል።
በተለይ ከዚህ ቀደም በነበረው ልምድ መሰረት አብዛኛዎቹ ሙዚየሙን የጎበኙ የውጭ ዜጐች በመቀጠል የሃገር ባህል አልባሳትን ለመግዛት ወደሽሮ ሜዳ እና አካባቢው ያቀኑ እነደነበር አስታውሰዋል። አሁን ላይ ግን ጎብኚዎቹም ባለመኖራቸው የሽሮሜዳ ነጋዴዎችም ገቢ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳሳደረ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅተ በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ሙዚየሞች የኮሮናን በሽታ ባገናዘበ ሁኔታ ጥንቃቄ እያደረጉ በከፊል አገልግሎት ወደመስጠት መሸጋገራቸውን የተናገሩት አቶ ኤፍሬም ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየምም በቀጣይ በቁጥር የተወሰኑ ጎብኚዎችን እያስተናገደ እንዲሠራ ለሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ መቅረቡን አስታውቀዋል።
በጉዳዩ ላይ ውይይት እየተደረገ በመሆኑ በ2013 ዓ.ም መስከረም ወር አጋማሽ ጀምሮ ሙዚየሙ በከፊል አገልግሎት ሊጀምር እንደሚችል ቅድመ ግምት መቀመጡን ገልጸዋል። ሙዚየሙ እስኪከፈት ድረስ ግን ለዝግጅት የሚረዱ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።
ብሔራዊ ሙዚየም ዝግ በሆነባቸው ጊዜያት መጠነኛ ጥገና እንደተረገለት የገለጹት አቶ ኤፍሬም፤ ፍሳሽ ያስገባ የነበረው ጣሪያው ሙሉ እድሳት እንደተደረገለት ተናግረዋል። ለእድሳቱም ከ300ሺ ብር በላይ ወጪ መሆኑንም ገልጸዋል።
በተጨማሪ ሙዚየሙ በሳምንት አንድ ጊዜ እየተከፈተ አስፈላጊው የፅዳት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፤ በሙዚየሙ ብቻ የሚገኙ ከሁለት ሺ በላይ ቅርሶችም ያለምንም ጉዳት በመልካም ይዞታ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
እንደ አቶ ኤፍሬም ከሆነ፤ የሉሲ ቅሪተ አካል እና ሌሎችም ቅሪት አካላት ጉዳት ቢደርስባቸው ምንም መተኪያ ስለሌላቸው በሳይንሳዊ ዘዴ የተሠራላቸው አምሳያ /ሳይንቲፊክ ሪፕሊካ/ በሙዚየሙ ውስጥ ተቀምጧል። ትክክለኛዎቹ ቅሪት አካላት ግን ለጥንቃቄ ሲባል በቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ሕንፃ ውስጥ ተቀምጠው ለወሳኝ ጥናትና ምርምር ሥራ ሲፈለጉ ብቻ ክፍት ይደረጋሉ ብለዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
ጌትነት ተስፋማርያም
***************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- ኮሮና ወረርሽኝ ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ጀምሮ የጉብኝት አገልግሎቱ በመቋረጡ በአምስት ወራት ውስጥ 150 ሺ ጎብኚዎችን ማጣቱን ብሔራዊ ሙዚየም አስታወቀ።
በቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን የብሔራዊ ሙዚየም ዳይሬክተር አቶ ኤፍሬም አማረ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ የኮሮና በሽታ ወደኢትዮጵያ ከገባ ከመጋቢት 15 ቀን 2012 ጀምሮ የብሔራዊ ሙዚያም ለጥንቃቄ ሲባል ለጎብኚዎች ዝግ ሆኖ ቆይቷል። በዚህም ምክንያት ባለፉት አምስት ወራት ሙዚየሙን ሊጎበኙ ለሚችሉ 150ሺህ ሰዎች አገልግሎት መስጠት አልተቻለም።
ቀደም ባለው ጊዜ ባለው ልምድ መሰረት ብሔራዊ ሙዚየምን በየቀኑ የሚጎበኙ ሰዎች ቁጥር በአማካይ አንድ ሺ ይደርሳል። በተለይ በክረምት ወቅት ከትምህርት ቤቶች እና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙዚየሙን ለመጎብኘት የሚመጡ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጨምር አመልክተው፣ የውጭ ሃገራት ጎብኚዎችም በብዛት ወደኢትዮጵያ እንደሚመጡ የሚጠበቅበት ወቅት እንደነበር አስታውቀዋል።
ሙዚየሙ በኮሮና በሽታ ምክንያት ሲዘጋ አገልግሎቱን ማግኘት ካልቻሉ 150 ሺህ ሰዎች መካከል 45ሺህ የሚሆኑት ከውጭ ሀገራት የሚመጡ ጎብኝዎች እንደሚሆኑ ይገመታል ያሉት አቶ ኤፍሬም፤ ጎብኚዎቹ በመቅረታቸው የባህል እቃዎች እና አልባሳት አቅራቢዎችን
ገቢ ክፉኛ እንደጎዳው ተናግረዋል።
በተለይ ከዚህ ቀደም በነበረው ልምድ መሰረት አብዛኛዎቹ ሙዚየሙን የጎበኙ የውጭ ዜጐች በመቀጠል የሃገር ባህል አልባሳትን ለመግዛት ወደሽሮ ሜዳ እና አካባቢው ያቀኑ እነደነበር አስታውሰዋል። አሁን ላይ ግን ጎብኚዎቹም ባለመኖራቸው የሽሮሜዳ ነጋዴዎችም ገቢ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳሳደረ ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅተ በተለያዩ ዓለማት የሚገኙ ሙዚየሞች የኮሮናን በሽታ ባገናዘበ ሁኔታ ጥንቃቄ እያደረጉ በከፊል አገልግሎት ወደመስጠት መሸጋገራቸውን የተናገሩት አቶ ኤፍሬም ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየምም በቀጣይ በቁጥር የተወሰኑ ጎብኚዎችን እያስተናገደ እንዲሠራ ለሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ መቅረቡን አስታውቀዋል።
በጉዳዩ ላይ ውይይት እየተደረገ በመሆኑ በ2013 ዓ.ም መስከረም ወር አጋማሽ ጀምሮ ሙዚየሙ በከፊል አገልግሎት ሊጀምር እንደሚችል ቅድመ ግምት መቀመጡን ገልጸዋል። ሙዚየሙ እስኪከፈት ድረስ ግን ለዝግጅት የሚረዱ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመዋል።
ብሔራዊ ሙዚየም ዝግ በሆነባቸው ጊዜያት መጠነኛ ጥገና እንደተረገለት የገለጹት አቶ ኤፍሬም፤ ፍሳሽ ያስገባ የነበረው ጣሪያው ሙሉ እድሳት እንደተደረገለት ተናግረዋል። ለእድሳቱም ከ300ሺ ብር በላይ ወጪ መሆኑንም ገልጸዋል።
በተጨማሪ ሙዚየሙ በሳምንት አንድ ጊዜ እየተከፈተ አስፈላጊው የፅዳት አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው፤ በሙዚየሙ ብቻ የሚገኙ ከሁለት ሺ በላይ ቅርሶችም ያለምንም ጉዳት በመልካም ይዞታ ላይ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
እንደ አቶ ኤፍሬም ከሆነ፤ የሉሲ ቅሪተ አካል እና ሌሎችም ቅሪት አካላት ጉዳት ቢደርስባቸው ምንም መተኪያ ስለሌላቸው በሳይንሳዊ ዘዴ የተሠራላቸው አምሳያ /ሳይንቲፊክ ሪፕሊካ/ በሙዚየሙ ውስጥ ተቀምጧል። ትክክለኛዎቹ ቅሪት አካላት ግን ለጥንቃቄ ሲባል በቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ሕንፃ ውስጥ ተቀምጠው ለወሳኝ ጥናትና ምርምር ሥራ ሲፈለጉ ብቻ ክፍት ይደረጋሉ ብለዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
ጌትነት ተስፋማርያም
ከጣና የሚገኘው የዓሣ ምርት በ1 ሺ 700ቶን ቀንሷል
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በእንቦጭ አረም እና ተያያዥ ችግሮች የተነሳ ከጣና ሐይቅ በዓመት ይገኝ የነበረው የዓሣ ምርት በ1 ሺ 700ቶን መቀነሱ ተገለጸ። እንቦጭ አረም በዓሣ ሀብትና አጥማጆች ሕይወት ላይም በከፍተኛ ደረጃ እያዛባ መሆኑም ተገልጿል። ከ9,000 ወደ 7,000 ቶን መቀነሱ የባህርዳር የዓሣና ሌሎች የውሃ ውስጥ ህይወት ምርምር ማዕከል ተመራማሪና የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ተዋበ በተለይም ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ በጣና ሐይቅ ላይ የዓሣ አስጋሪዎች ቁጥርና የምርቱ ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ ቢሆንም ከሐይቁ የሚገኘው ምርት በከፍተኛ ደረጃ እየነቀሰ ነው።
ተመራማሪ ጥናቶችን ዋቢ አድርገውእንዳስታወቁት፤ በቅርቡ በተካሄደው ጥናት 5 ሺ 4,000 ዓሣ አስጋሪዎች በዓመት 7 ሺ 300 ቶን ዓሣ አምርተዋል። እ.ኤ.አ በ2013 በፈረንጆች አቆጣጠር 3 ሺ 114 አስጋሪዎች በነበሩበት ወቅት ግን 9,000 ቶን አምርተው ነበር። ይህ የሚያሳያው የዓሣ አጥማጆች ቁጥር እና የምርቱ ተጠቃሚዎች ፍላጎት እየጨመረ ሲሄድ ዓሣ ሀብቱ እየቀነሰ ነው።
ለምርቱ መቀነስ አንዱ ምክንት የእንቦጭ አረም መስፋፋት እንደሆነ ተመራማሪው አመልክተው፤ እንቦጭ በባህሪው በፍጥነት እና በስፋት የሚራባና የሚባዛ መሆኑን አስታውቀዋል።
"አረሙ በቅድሚያ የዓሣ መራቢያ ቦታ ይይዛል፣ የዓሣ ዕንቁላልም ለመራባት ምቹ ሁኔታ አያገኝም። በተጨማሪም የፀሐይ ብርሃን ወደ ውሃ ውስጥ እንዳይገባ ያደርጋል። እንቦጩ ሲወገድና ሲሞት በሐይቁ ውስጥ ሌላ ኬሚካል የሚለቅ በመሆኑ በውሃ ውስጥ ያለውን የአየር ዝውውር ያዛባል" ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት በጣና ሐይቅ ላይ የተከሰተው እንቦጭ አረም የዓሣ ዋንኛው የመራቢያ ስፍራ የሆነውን ቦታ መያዙን ያመለከቱት ተመራማሪው፣ ይህም በቀጥታ በዓሣ መራባትና ሀብት ዕድገት ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
ከሐይቁ ምሥራቃዊ ክፍል በእንቦጭ ክፉኛ መጠቃቱን ያመለከቱት ተመራማሪው፤ አካባቢው በታንኳ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ እየሆነ በመምጣቱ የዓሣ ማስገር ሥራውን አስቸጋሪ አድርጎታል ብለዋል። ዓሣ ማስገሪያ መረቦች ዓሣ ከመያዝ ይልቅ በእምቦጭ እየተሞሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።
እንቦጭ ዓሣን ጨምሮ ሌሎች ሃይቅ ውስጥ የሚኖሩ እንስሳት የሚመገቧቸውን ዕጽዋት በማጥፋትቀዳሚ እንደሆነ ያመለከቱት ተመራማሪው፣ ችግሩ የዓሣ ዝርያ እና መጠንን በመቀነስ አደጋ መፈጠሩን ገልጸዋል።
በበጋ ወቅት ጣና ውሃ ሲቀንስ አርሶ አደሩ ጣና ዙሪያ (ባህረ ሸሽ) እርሻ የሚያካሂድ ሲሆን፤ ቀደም ሲል አንድ አርሶ አደር ብቻውን 0 ነጥብ 25 ሄክታር መሬት ለማረስ ይችል ነበር ብለዋል። የእቦጭ አረም ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ ግን 0 ነጥብ 25 ሄክታር መሬት ለማረስ 9 ሰው ማስፈለጉን አመልክተዋል። ይህም እንቦጭ እያስከተለ ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግር ተጨማሪ አንድ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመዋል።
የባህርዳር የዓሣና ሌሎች የውሃ ውስጥ ህይወት ምርምር ማዕከል በ1992 ዓ.ም የተመሰረተ ማዕከል ሲሆን፤ ዘርፈ ብዙ የምርምር ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
ክፍለዮሐንስ አንበርብር
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በእንቦጭ አረም እና ተያያዥ ችግሮች የተነሳ ከጣና ሐይቅ በዓመት ይገኝ የነበረው የዓሣ ምርት በ1 ሺ 700ቶን መቀነሱ ተገለጸ። እንቦጭ አረም በዓሣ ሀብትና አጥማጆች ሕይወት ላይም በከፍተኛ ደረጃ እያዛባ መሆኑም ተገልጿል። ከ9,000 ወደ 7,000 ቶን መቀነሱ የባህርዳር የዓሣና ሌሎች የውሃ ውስጥ ህይወት ምርምር ማዕከል ተመራማሪና የማዕከሉ ዳይሬክተር አቶ ደረጀ ተዋበ በተለይም ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ በጣና ሐይቅ ላይ የዓሣ አስጋሪዎች ቁጥርና የምርቱ ተጠቃሚዎች ቁጥር እየጨመረ ቢሆንም ከሐይቁ የሚገኘው ምርት በከፍተኛ ደረጃ እየነቀሰ ነው።
ተመራማሪ ጥናቶችን ዋቢ አድርገውእንዳስታወቁት፤ በቅርቡ በተካሄደው ጥናት 5 ሺ 4,000 ዓሣ አስጋሪዎች በዓመት 7 ሺ 300 ቶን ዓሣ አምርተዋል። እ.ኤ.አ በ2013 በፈረንጆች አቆጣጠር 3 ሺ 114 አስጋሪዎች በነበሩበት ወቅት ግን 9,000 ቶን አምርተው ነበር። ይህ የሚያሳያው የዓሣ አጥማጆች ቁጥር እና የምርቱ ተጠቃሚዎች ፍላጎት እየጨመረ ሲሄድ ዓሣ ሀብቱ እየቀነሰ ነው።
ለምርቱ መቀነስ አንዱ ምክንት የእንቦጭ አረም መስፋፋት እንደሆነ ተመራማሪው አመልክተው፤ እንቦጭ በባህሪው በፍጥነት እና በስፋት የሚራባና የሚባዛ መሆኑን አስታውቀዋል።
"አረሙ በቅድሚያ የዓሣ መራቢያ ቦታ ይይዛል፣ የዓሣ ዕንቁላልም ለመራባት ምቹ ሁኔታ አያገኝም። በተጨማሪም የፀሐይ ብርሃን ወደ ውሃ ውስጥ እንዳይገባ ያደርጋል። እንቦጩ ሲወገድና ሲሞት በሐይቁ ውስጥ ሌላ ኬሚካል የሚለቅ በመሆኑ በውሃ ውስጥ ያለውን የአየር ዝውውር ያዛባል" ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት በጣና ሐይቅ ላይ የተከሰተው እንቦጭ አረም የዓሣ ዋንኛው የመራቢያ ስፍራ የሆነውን ቦታ መያዙን ያመለከቱት ተመራማሪው፣ ይህም በቀጥታ በዓሣ መራባትና ሀብት ዕድገት ላይ ተፅዕኖ እየፈጠረ እንደሚገኝ አመልክተዋል።
ከሐይቁ ምሥራቃዊ ክፍል በእንቦጭ ክፉኛ መጠቃቱን ያመለከቱት ተመራማሪው፤ አካባቢው በታንኳ ለመንቀሳቀስ አስቸጋሪ እየሆነ በመምጣቱ የዓሣ ማስገር ሥራውን አስቸጋሪ አድርጎታል ብለዋል። ዓሣ ማስገሪያ መረቦች ዓሣ ከመያዝ ይልቅ በእምቦጭ እየተሞሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።
እንቦጭ ዓሣን ጨምሮ ሌሎች ሃይቅ ውስጥ የሚኖሩ እንስሳት የሚመገቧቸውን ዕጽዋት በማጥፋትቀዳሚ እንደሆነ ያመለከቱት ተመራማሪው፣ ችግሩ የዓሣ ዝርያ እና መጠንን በመቀነስ አደጋ መፈጠሩን ገልጸዋል።
በበጋ ወቅት ጣና ውሃ ሲቀንስ አርሶ አደሩ ጣና ዙሪያ (ባህረ ሸሽ) እርሻ የሚያካሂድ ሲሆን፤ ቀደም ሲል አንድ አርሶ አደር ብቻውን 0 ነጥብ 25 ሄክታር መሬት ለማረስ ይችል ነበር ብለዋል። የእቦጭ አረም ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ ግን 0 ነጥብ 25 ሄክታር መሬት ለማረስ 9 ሰው ማስፈለጉን አመልክተዋል። ይህም እንቦጭ እያስከተለ ያለውን ዘርፈ ብዙ ችግር ተጨማሪ አንድ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመዋል።
የባህርዳር የዓሣና ሌሎች የውሃ ውስጥ ህይወት ምርምር ማዕከል በ1992 ዓ.ም የተመሰረተ ማዕከል ሲሆን፤ ዘርፈ ብዙ የምርምር ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 23/2012
ክፍለዮሐንስ አንበርብር
መስቀል አደባባይ ዓለም አቀፍ ደረጃን በጠበቀ መልኩ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ጠ/ር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ታሪካዊውን መስቀል አደባባይ ዓለም አቀፍ ደረጃን በጠበቀ መልኩ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታውቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ“ባለፉት ጥቂት ወራት በመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ያለ መታከት ሲደክሙ በቆዩት ወገኖች እጅግ ተደንቄያለሁ” ብለዋል፡፡
በዚህኛው ዙር በአጠቃላይ 5 ሺህ ያህል ሠራተኞች የተሳተፉ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንን ታሪካዊ አደባባይ ዓለም አቀፍ ደረጃን በጠበቀ መልኩ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ታሪካዊውን መስቀል አደባባይ ዓለም አቀፍ ደረጃን በጠበቀ መልኩ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታውቀዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ“ባለፉት ጥቂት ወራት በመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ያለ መታከት ሲደክሙ በቆዩት ወገኖች እጅግ ተደንቄያለሁ” ብለዋል፡፡
በዚህኛው ዙር በአጠቃላይ 5 ሺህ ያህል ሠራተኞች የተሳተፉ መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንን ታሪካዊ አደባባይ ዓለም አቀፍ ደረጃን በጠበቀ መልኩ ለማጠናቀቅ እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል።
“ድሮን እየኖሩ ትውልዱን ወደኋላ እየመለሱ መስዋዕት የሚያደርጉ ፖለቲከኞች ጡረታ ሊወጡ ይገባል”አቶ ሙሳ አደም የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ
*********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በድሮ አስተሳሰብ እየኖሩ በአዲሱ ኃይል ጉልበት፤ ዕጣ ፋንታ፤ የወደፊት ራዕይ ላይ በመጫወት መስዋዕትነት የሚያስከፍሉት ፖለቲከኞች ጡረታ መውጣት እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሙሳ አደም ገለጹ።
የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሙሳ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ የዓለም ፖለቲካ በጣም ተለዋዋጭ ነው። ትናንት የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ዛሬ አይሠራም፤ የለምም። በእኛ አገር ፖለቲካ ትናንት የሁልጊዜ ውሎ ነው። ገና ኃይለስላሴና ምኒልክ ዘመንን ያልተሻገረ ፖለቲከኛ ይዘን ቀጥለናል። ይህ ሁኔታ አገርን ስለማያሻግር እነዚህ ፖለቲከኞች ጡረታ ሊወጡ ይገባል። በምትኩ የሚሠራ ኃይል ወንበሩን መረከብ አለበት።
እነዚህ አካላት በጊዜያቸው ወቅቱ የሚጠይቀውን መንገድ ሂደው ብዙ ሠርተዋል፤ ለአገርም ያበረከቱት ነገር አለ። ይሁንና ‹‹እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል›› አባባላቸው ዛሬም ቀጥሏል። ይህ ደግሞ ወጣቱን እንዳይሠራና አገሩን እነርሱ በሠሩት ላይ ጨምሮ እንዳያሻግር እንቅ ፋት ሆነውበታል ብለዋል። ሀገራዊ ፖለቲካውና ፖለቲከኛው እንዲሻሻል ከተፈለገ እነዚህ ዘመናቸው ያበቃ ፖለቲከኞች ለተተኪው ወንበር መለቀቅ እንደሚኖርባቸው አስታውቀዋል።
የቀድሞ ሀገራዊ የፖለቲካ አካሄድ መልካምም መጥፎም ታሪኮች እንደነበሩት የሚያነሱት አቶ ሙሳ፤ በዘመናቸው የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ይህንን እንዲያደርጉ አስገድዷቸዋልና አድርገውት አልፈዋል። አገርንም ለዛሬው ትውልድ ሠርተውለታል። ሆኖም ያንን ታሪክ አድርገን እንጂ ኑሯችን አድርገን መቀጠል የለብንም። ታሪኩ እንደ ታሪክነቱ ይነበብ፤ ይታወቅ፤ እውነታውን ሁሉም ይረዳው፤ ነገር ግን በዚያ ታሪክ እንድንኖር ሊፈረድብን አይገባም ብለዋል።
ትውልዱ ነገው እንዲበላሽ መፍቀድ የለበትም የሚሉት ሰብሳቢው፤ ዛሬ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። በዛሬው አካሄድ የዛሬው ትውልድ መሠራት አለበት። ነገን እያነሱ ትውልዱን ወደትናንት መውሰዱና ማበጣበጡ አገርን ወደኋላ ከመመለስ አይተናነስም። በተለይ ፖለቲከኛው የትናንቱን ለትናንት በመተው ዛሬ በራሱ መንገድ እንዲሻገር እና ለውጥ እንዲመጣ ለተተኪዎች ቦታውን መልቀቅ እንደሚኖርበት አመልክተዋል።
አገሪቱ በርከት ያሉ በእውቀት መምራትና መሥራት የሚችሉ ወጣት ፖለቲከኞች አሏት፤ እነዚህን ወደ ሥራ ማስገባት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ የሚገልጹት አቶ ሙሳ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ያለፉት ዓመታትን የምንኖርበት ሊሆን አይገባምና ተሠርታ ያለቀችውን ኢትዮጵያን እንዲሠሩ ለትውልዱ እንፍቀድ ብለዋል።
የቀደሙት የትናንት ፖለቲከኞች ሌላ ሰው እንዲመጣባቸው አይፈልጉም፤ ወጣት ፖለቲከኛን ማየት ያማቸዋል ያሉት አቶ ሙሳ ፤ ይህ ደግሞ በሀገሪቱ ፖለቲከኛም ሆነ ፖለቲካው እንዳይፈጠር ከማድረጉም በላይ ወጣቱን የእሳት እራት እንጂ ባለተስፋ አላደረጉትም ብለዋል። የመሥራት ባህልን እንዲያዳብር እንዳልረዱትም አመልክተዋል።
እንደ አቶ ሙሳ ገለጻ፤ የተማረና የተመራመረ፤ የተሻለውን ለአገር ለማምጣት የሚጥር፤ ጉልበት ያለው ሯጭ ፖለቲከኛ አገር ያስፈልጋታል። እንደውም ‹‹ የተማረ ይግደለኝ›› እንደሚባለው የአገር ፖለቲካ መፈጠር የሚጀምረው ፖለቲከኛውም ፖለቲካውም በእውቀትና በአዲስ አስተሳሰብ ሲቃኝ ብቻ ነው። ስለሆነም የወቅቱን የፖለቲካ ጽንሰሃሳብ ያልተረዱ ሰዎች እየመሩ ግራ ከሚያጋቡ ጡረታ መውጣቱ ለነሱም ለሀገርም እንደሚበጅ ጠቁመዋል።
ፓርቲ የሚባለውም በዘመድ ተሰባስቦ የሚመሰረት ነው። ይህ ደግሞ አገር ለመምራት ሳይሆን ቤተሰብ ለማስተዳደር ብቻ የሚያስብ የሚያደርገው ተግባር ነው። እናም መሰረታዊ የፓርቲ ቁመና ያለው በሃሳብ ልዕልና የሚያምን ፓርቲ ከሌለ ፖለቲካም ፖለቲከኛም ሊፈጠር አይችልም።
ሁለቱም ያለመኖራቸው መንስኤ ነው አሁን ለአገር ፈተናና ዋጋ ማስከፈል ያበቃው ብለዋል። ፓርቲው እንደ ፓርቲ የሚሠራው ሥራ የለም። ህዝቡም ከፓርቲው የሚጠብቀውን እያገኘ አይደለም። ስለዚህም ህዝብ ከመጠቀም ይልቅ በችግር ውስጥ ተዘፍቆ ዓመታትን ዋጋ እየከፈለ እንዲኖር መደረጉንም አመልክተዋል።
ዘመኑን ያልዋጀ፤ አገርን ከፍ ለማድረግ በማያስችል ጉዳይ ላይ መስዋዕት እየከፈልን ነው የሚሉት አቶ ሙሳ፤ ትውልዱን በማደንቆር የተካኑ ፖለቲከኞች ጡረታ ይውጡና አዳዲስ የፖለቲካ አስተሳሰብና እውቀቱ ያላቸው አካላት ወንበሩን ይረከቡ ብለዋል።
ሀገራዊ የፖለቲካ አካሂዶች በመርህ፤ በፖሊሲ ላይ የተመሰረቱና ከአገርና ከህዝብ ጥቅም አንጻር የተቃኙ መሆን መቻልም አለባቸው። በዚህ ላይም በስፋት መሥራት መጀመር አለብን ሲሉም ተናግረዋል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 24/2012
*********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- በድሮ አስተሳሰብ እየኖሩ በአዲሱ ኃይል ጉልበት፤ ዕጣ ፋንታ፤ የወደፊት ራዕይ ላይ በመጫወት መስዋዕትነት የሚያስከፍሉት ፖለቲከኞች ጡረታ መውጣት እንደሚገባቸው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሙሳ አደም ገለጹ።
የጋራ ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ሙሳ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ የዓለም ፖለቲካ በጣም ተለዋዋጭ ነው። ትናንት የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ዛሬ አይሠራም፤ የለምም። በእኛ አገር ፖለቲካ ትናንት የሁልጊዜ ውሎ ነው። ገና ኃይለስላሴና ምኒልክ ዘመንን ያልተሻገረ ፖለቲከኛ ይዘን ቀጥለናል። ይህ ሁኔታ አገርን ስለማያሻግር እነዚህ ፖለቲከኞች ጡረታ ሊወጡ ይገባል። በምትኩ የሚሠራ ኃይል ወንበሩን መረከብ አለበት።
እነዚህ አካላት በጊዜያቸው ወቅቱ የሚጠይቀውን መንገድ ሂደው ብዙ ሠርተዋል፤ ለአገርም ያበረከቱት ነገር አለ። ይሁንና ‹‹እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል›› አባባላቸው ዛሬም ቀጥሏል። ይህ ደግሞ ወጣቱን እንዳይሠራና አገሩን እነርሱ በሠሩት ላይ ጨምሮ እንዳያሻግር እንቅ ፋት ሆነውበታል ብለዋል። ሀገራዊ ፖለቲካውና ፖለቲከኛው እንዲሻሻል ከተፈለገ እነዚህ ዘመናቸው ያበቃ ፖለቲከኞች ለተተኪው ወንበር መለቀቅ እንደሚኖርባቸው አስታውቀዋል።
የቀድሞ ሀገራዊ የፖለቲካ አካሄድ መልካምም መጥፎም ታሪኮች እንደነበሩት የሚያነሱት አቶ ሙሳ፤ በዘመናቸው የነበረው የፖለቲካ አረዳድ ይህንን እንዲያደርጉ አስገድዷቸዋልና አድርገውት አልፈዋል። አገርንም ለዛሬው ትውልድ ሠርተውለታል። ሆኖም ያንን ታሪክ አድርገን እንጂ ኑሯችን አድርገን መቀጠል የለብንም። ታሪኩ እንደ ታሪክነቱ ይነበብ፤ ይታወቅ፤ እውነታውን ሁሉም ይረዳው፤ ነገር ግን በዚያ ታሪክ እንድንኖር ሊፈረድብን አይገባም ብለዋል።
ትውልዱ ነገው እንዲበላሽ መፍቀድ የለበትም የሚሉት ሰብሳቢው፤ ዛሬ ብዙ ነገሮች ተለውጠዋል። በዛሬው አካሄድ የዛሬው ትውልድ መሠራት አለበት። ነገን እያነሱ ትውልዱን ወደትናንት መውሰዱና ማበጣበጡ አገርን ወደኋላ ከመመለስ አይተናነስም። በተለይ ፖለቲከኛው የትናንቱን ለትናንት በመተው ዛሬ በራሱ መንገድ እንዲሻገር እና ለውጥ እንዲመጣ ለተተኪዎች ቦታውን መልቀቅ እንደሚኖርበት አመልክተዋል።
አገሪቱ በርከት ያሉ በእውቀት መምራትና መሥራት የሚችሉ ወጣት ፖለቲከኞች አሏት፤ እነዚህን ወደ ሥራ ማስገባት ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ የሚገልጹት አቶ ሙሳ፤ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ያለፉት ዓመታትን የምንኖርበት ሊሆን አይገባምና ተሠርታ ያለቀችውን ኢትዮጵያን እንዲሠሩ ለትውልዱ እንፍቀድ ብለዋል።
የቀደሙት የትናንት ፖለቲከኞች ሌላ ሰው እንዲመጣባቸው አይፈልጉም፤ ወጣት ፖለቲከኛን ማየት ያማቸዋል ያሉት አቶ ሙሳ ፤ ይህ ደግሞ በሀገሪቱ ፖለቲከኛም ሆነ ፖለቲካው እንዳይፈጠር ከማድረጉም በላይ ወጣቱን የእሳት እራት እንጂ ባለተስፋ አላደረጉትም ብለዋል። የመሥራት ባህልን እንዲያዳብር እንዳልረዱትም አመልክተዋል።
እንደ አቶ ሙሳ ገለጻ፤ የተማረና የተመራመረ፤ የተሻለውን ለአገር ለማምጣት የሚጥር፤ ጉልበት ያለው ሯጭ ፖለቲከኛ አገር ያስፈልጋታል። እንደውም ‹‹ የተማረ ይግደለኝ›› እንደሚባለው የአገር ፖለቲካ መፈጠር የሚጀምረው ፖለቲከኛውም ፖለቲካውም በእውቀትና በአዲስ አስተሳሰብ ሲቃኝ ብቻ ነው። ስለሆነም የወቅቱን የፖለቲካ ጽንሰሃሳብ ያልተረዱ ሰዎች እየመሩ ግራ ከሚያጋቡ ጡረታ መውጣቱ ለነሱም ለሀገርም እንደሚበጅ ጠቁመዋል።
ፓርቲ የሚባለውም በዘመድ ተሰባስቦ የሚመሰረት ነው። ይህ ደግሞ አገር ለመምራት ሳይሆን ቤተሰብ ለማስተዳደር ብቻ የሚያስብ የሚያደርገው ተግባር ነው። እናም መሰረታዊ የፓርቲ ቁመና ያለው በሃሳብ ልዕልና የሚያምን ፓርቲ ከሌለ ፖለቲካም ፖለቲከኛም ሊፈጠር አይችልም።
ሁለቱም ያለመኖራቸው መንስኤ ነው አሁን ለአገር ፈተናና ዋጋ ማስከፈል ያበቃው ብለዋል። ፓርቲው እንደ ፓርቲ የሚሠራው ሥራ የለም። ህዝቡም ከፓርቲው የሚጠብቀውን እያገኘ አይደለም። ስለዚህም ህዝብ ከመጠቀም ይልቅ በችግር ውስጥ ተዘፍቆ ዓመታትን ዋጋ እየከፈለ እንዲኖር መደረጉንም አመልክተዋል።
ዘመኑን ያልዋጀ፤ አገርን ከፍ ለማድረግ በማያስችል ጉዳይ ላይ መስዋዕት እየከፈልን ነው የሚሉት አቶ ሙሳ፤ ትውልዱን በማደንቆር የተካኑ ፖለቲከኞች ጡረታ ይውጡና አዳዲስ የፖለቲካ አስተሳሰብና እውቀቱ ያላቸው አካላት ወንበሩን ይረከቡ ብለዋል።
ሀገራዊ የፖለቲካ አካሂዶች በመርህ፤ በፖሊሲ ላይ የተመሰረቱና ከአገርና ከህዝብ ጥቅም አንጻር የተቃኙ መሆን መቻልም አለባቸው። በዚህ ላይም በስፋት መሥራት መጀመር አለብን ሲሉም ተናግረዋል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 24/2012
ፍርድ ቤቱ በአቶ ልደቱ ላይ ክስ እስከሚመሰርት መርማሪ ፖሊስ እንዲሰጠው የጠየቀውን ተጨማሪ ጊዜ ውድቅ አደረገ
*********************
(ኢፕድ)
አቶ ልደቱ አያሌው ላይ ፖሊስ ሲያካሂድ የቆየውን ምርመራ ማጠናቀቁን ገልፆ አቃቤ ህግ ክስ እስከሚመሰርት ድረስ 14 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ ሲል ፍርድ ቤቱን የጠየቀ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የፖሊስ ጥያቄ የህግ አግባብነት የለውም ሲል ውድቅ አደረገ።
ፍርድ ቤቱ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ መዘጋቱን ገልፆ አቶ ልደቱ አያሌው በሌላ መዝገብ የዋስትና ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ አዟል።
ለአራተኛ ጊዜ በቢሾፍቱ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት የቀረቡት አቶ ልደቱ አያሌው ”ፍርድ ቤቱ የጤናዬን ሁኔታ ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት፣ ከዚህ በፊት ያቀረብኩት የህክምና ማስረጃ የልብ ህመምተኛ መሆኔን ተከትሎ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተጋላጭ እንደሚያደርገኝ ተጠቅሶ የተፃፈ ቢሆንም፥ በፖሊስ ጣቢያ የኮቪድ-19 ምርመራ አልተደረገም፣ ጤናዬን ከግምት ውስጥ ያስገባ ርቀትን የጠበቀ አያያዝ አልተደረገልኝም፣ በተጓዳኝ ደግሞ በአንድ መፀዳጃ ቤት 50 እስረኞች እንደሚጠቀሙና ይህም ለጤናዬ አደጋ ነው‘ ብለዋል።
”ፖሊስ እስከ ዛሬ ሲያከናውን የነበረው ምርመራ አዲስ ውጤት ያልታከለበት፣ አስተባብረሃቸዋል የተባሉ ተባባሪዎች ያልተያዙበት እና ምስክሮቼ ያልቀረቡበት ነው‘ ሲሉ መቃወሚያ አሰምተዋል።
ፖሊስም እስካሁን ሲያከናውን የነበረው ምርመራ በእጃቸው ላይ የነበሩ የስልክ መልዕክቶችን እንዲሁም በእጃቸው ላይ የተገኘ የሽግግር መንግስት መመስረቻ ሰነዶች ውጤትን በመዝገቡ ማካተቱን ገልፆ፥ ይሁንና ”ምርመራዬን አጠናቅቂያለሁ፣ ይህም መዝገቡንም አቃቤ ህግ መርምሮ ክስ እስከሚመሰርት ድረስ ተጨማሪ 14 ቀን ይሰጠኝ‘ ሲል ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱም ”በዚህ መዝገብ ላይ ምርመራ መጠናቀቁን በመግለፅ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ህግ አንቀፅ 59 1 እና 2 መሰረት ያቀረብከው ጥያቄ አግባብነት የሌለውና ያጠናቀከው መዝገብ ተጨማሪ ጊዜ የማያሰጥ ነው፣ ጥያቄህም የህግ አግባብነት የለውም‘ ሲል ውድቅ አድርጎበታል።
ይሁንና በዛሬው ዕለት በሁለት ጠበቃ ተወክለው የቀረቡት አቶ ልደቱ አያሌው የጠየቁት የዋስትና ጥያቄ በዚህ የተዘጋ መዝገብ ሳይሆን በሌላ መዝገብ ማቅረብ ይችላሉ ሲል የመርማሪ ፖሊስ መዝገቡን ዘግቷል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል።
*********************
(ኢፕድ)
አቶ ልደቱ አያሌው ላይ ፖሊስ ሲያካሂድ የቆየውን ምርመራ ማጠናቀቁን ገልፆ አቃቤ ህግ ክስ እስከሚመሰርት ድረስ 14 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ ሲል ፍርድ ቤቱን የጠየቀ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ የፖሊስ ጥያቄ የህግ አግባብነት የለውም ሲል ውድቅ አደረገ።
ፍርድ ቤቱ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ መዘጋቱን ገልፆ አቶ ልደቱ አያሌው በሌላ መዝገብ የዋስትና ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ አዟል።
ለአራተኛ ጊዜ በቢሾፍቱ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት የቀረቡት አቶ ልደቱ አያሌው ”ፍርድ ቤቱ የጤናዬን ሁኔታ ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት፣ ከዚህ በፊት ያቀረብኩት የህክምና ማስረጃ የልብ ህመምተኛ መሆኔን ተከትሎ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተጋላጭ እንደሚያደርገኝ ተጠቅሶ የተፃፈ ቢሆንም፥ በፖሊስ ጣቢያ የኮቪድ-19 ምርመራ አልተደረገም፣ ጤናዬን ከግምት ውስጥ ያስገባ ርቀትን የጠበቀ አያያዝ አልተደረገልኝም፣ በተጓዳኝ ደግሞ በአንድ መፀዳጃ ቤት 50 እስረኞች እንደሚጠቀሙና ይህም ለጤናዬ አደጋ ነው‘ ብለዋል።
”ፖሊስ እስከ ዛሬ ሲያከናውን የነበረው ምርመራ አዲስ ውጤት ያልታከለበት፣ አስተባብረሃቸዋል የተባሉ ተባባሪዎች ያልተያዙበት እና ምስክሮቼ ያልቀረቡበት ነው‘ ሲሉ መቃወሚያ አሰምተዋል።
ፖሊስም እስካሁን ሲያከናውን የነበረው ምርመራ በእጃቸው ላይ የነበሩ የስልክ መልዕክቶችን እንዲሁም በእጃቸው ላይ የተገኘ የሽግግር መንግስት መመስረቻ ሰነዶች ውጤትን በመዝገቡ ማካተቱን ገልፆ፥ ይሁንና ”ምርመራዬን አጠናቅቂያለሁ፣ ይህም መዝገቡንም አቃቤ ህግ መርምሮ ክስ እስከሚመሰርት ድረስ ተጨማሪ 14 ቀን ይሰጠኝ‘ ሲል ጠይቋል።
ፍርድ ቤቱም ”በዚህ መዝገብ ላይ ምርመራ መጠናቀቁን በመግለፅ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስርዓት ህግ አንቀፅ 59 1 እና 2 መሰረት ያቀረብከው ጥያቄ አግባብነት የሌለውና ያጠናቀከው መዝገብ ተጨማሪ ጊዜ የማያሰጥ ነው፣ ጥያቄህም የህግ አግባብነት የለውም‘ ሲል ውድቅ አድርጎበታል።
ይሁንና በዛሬው ዕለት በሁለት ጠበቃ ተወክለው የቀረቡት አቶ ልደቱ አያሌው የጠየቁት የዋስትና ጥያቄ በዚህ የተዘጋ መዝገብ ሳይሆን በሌላ መዝገብ ማቅረብ ይችላሉ ሲል የመርማሪ ፖሊስ መዝገቡን ዘግቷል ሲል ኤፍቢሲ ዘግቧል።
ከሊባኖስ 165 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው ተመለሱ
*********************************
(ኢፕድ)
በሊባኖስ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 165 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ኢትዮጵያውያኑ ወደ አገራቸው የተመለሱት በግለሰቦች፣ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችና ቡድኖች በተደረገላቸው የትራንስፖርት ወጪ ነው፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተመላሾቹ የአውሮፕላን ቲኬት ቅናሽ በማድረጉም ተገልጿል፡፡
በቀጣይም በራሳቸው ሙሉ ወጪ 243 ኢትዮጵውያን ወደ አገራቸው ይመለሳሉ ተብሏል፡፡
ወደ አገራቸው ለመመለስ ከ650 በላይ ዜጎች መመዝገባቸውም ተመልክቷል ፡፡
መንግሥትም በሊባኖስ የሚስተዋሉትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ተከትሎ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተነግሯል፡፡
ተመላሾቹ ቦሌ አለም አቀፍ አየር መንገድ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
መንግሥት ከጥቅምት 2012 ዓ.ም ጀምሮ 2ሺህ 300 ዜጎችን ከሊባኖስ ወደ አገራቸው መልሷል፡፡
ሊባኖስ በገጠማት የኢኮኖሚ ቀውስ፣የኮቪድ 19 ወረርሽኝና በቅርቡ ቤይሩት ወደብ ላይ የደረሰው ፍንዳታ ተዳምሮ ችግር ውስጥ መሆኗ ይታወቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡
*********************************
(ኢፕድ)
በሊባኖስ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 165 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ኢትዮጵያውያኑ ወደ አገራቸው የተመለሱት በግለሰቦች፣ ግብረ ሰናይ ድርጅቶችና ቡድኖች በተደረገላቸው የትራንስፖርት ወጪ ነው፡፡
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለተመላሾቹ የአውሮፕላን ቲኬት ቅናሽ በማድረጉም ተገልጿል፡፡
በቀጣይም በራሳቸው ሙሉ ወጪ 243 ኢትዮጵውያን ወደ አገራቸው ይመለሳሉ ተብሏል፡፡
ወደ አገራቸው ለመመለስ ከ650 በላይ ዜጎች መመዝገባቸውም ተመልክቷል ፡፡
መንግሥትም በሊባኖስ የሚስተዋሉትን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ተከትሎ ዜጎችን ወደ አገራቸው ለመመለስ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተነግሯል፡፡
ተመላሾቹ ቦሌ አለም አቀፍ አየር መንገድ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
መንግሥት ከጥቅምት 2012 ዓ.ም ጀምሮ 2ሺህ 300 ዜጎችን ከሊባኖስ ወደ አገራቸው መልሷል፡፡
ሊባኖስ በገጠማት የኢኮኖሚ ቀውስ፣የኮቪድ 19 ወረርሽኝና በቅርቡ ቤይሩት ወደብ ላይ የደረሰው ፍንዳታ ተዳምሮ ችግር ውስጥ መሆኗ ይታወቃል ሲል ኢዜአ ዘግቧል፡፡
“ህወሓት ኢትዮጵያዊ ያልሆነ፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የቆመ እጅግ መሰሪ የፖለቲካ ኃይል ነው” - አቶ አገዘው ህዳሩ፣የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር፤
************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- ህወሓት እጅግ መሰሪ የሆነና ኢትዮጵያዊ ያልሆነ፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የቆመ የፖለቲካ ኃይል መሆኑን የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አገዘው ህዳሩ አስታወቁ። በወንጀል ሊጠየቅ፤ ከፖለቲካ ፓርቲነት ሊሰረዝ፤ በአሸባሪነት ሊፈረጅ እንደሚገባም አሳሰቡ፡አቶ አገዘው ህዳሩ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፣ ህወሓትን እየዘወሩ ያሉ ሐይሎች ከአስተሳሰባቸው ጀምሮ ኢትዮጵያውያን አይደሉም። በኢትዮጵያ ስም መጠቀም እስከቻሉ ድረስ በኢትዮጵያዊነት አብረው መቆየት የሚፈልጉ ናቸው፤ እነሱ መጠቀም እና በስልጣን መቆየት ካልቻሉ ኢትዮጵያን ለእነሱ ስጋት በማትሆን መንገድ መስራትና አፈራርሶ መሄድ ይፈልጋሉ።
ለዚህም የራሳቸውን ኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ የሚሊተሪና የፀጥታ አቅም አዳብረው መጠቀም እስከቻሉ ድረስ አብረው ለመቆየት ችግር የለባቸውም ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ራሳቸው መጠቀምና ሌላውን በሚፈልጉት መንገድ ማሽከርከር ካልቻሉ ኢትዮጵያን አፍርሰው መልሰው ለእነሱ ስጋት እንዳትሆን አድርገው መሄድ ፍላጎታቸው መሆኑን ጠቁመዋል።
“ህወሓት ለህዝቡም አይጠቅምም፤ እጅግ መሰሪ የሆነና ኢትዮጵያዊ ያልሆነ፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የቆመ የፖለቲካ ኃይል ነው። ስለዚህ ከዚህ ጋር የሚተባበር ኢትዮጵያዊ መኖር የለበትም ብዬ አምናለሁ። ይሄን የምለውም እኛ ከስር መሰረታቸው ስለምናውቃቸው ነው። ምናልባት ሌላው ህዝብ ግፍና በደሉን ብቻ ነው የሚያየው፤ እኛ ግን አስተሳሰባቸውንም ጭምር እናውቃለን “ብለዋል ።
የትግራይን ህዝብ ጨምሮ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ላይ ሆኖ የነዚህን ሰዎች ህልውናቸውን ማሳጠር እንዳለበት ያመለከቱት አቶ አገዘው፣ ለመላው ህዝባችን የሚጠቅመው አንድነቱ፣ ኢትዮጵያዊነቱ እና የጋራ ተጠቃሚነቱ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ከእኩልነትና ከኢትዮጵያ አንድነት የሚገኘው ትርፍ እጅጉን የገዘፈ እንደሆነ በአጽዕኖት የተናገሩት ሊቀመንበሩ፣ ከህወሓት የገንጣይና ነጣይ ባህሪ አንጻር /ምን አይነት ስነልቡና እንደሆነ ባላውቅም/ ኢትዮጵያዊ ሆኖ ከህወሓት የፖለቲካ ጥቅም አገኛለሁ ብሎ የሚዶልት፤ የሚያሴር የፖለቲካ ሃይል ተግባር በጣም አስገራሚ እንደሆነ አመልክተዋል።
“እነዚህ ሰዎች ባልጠበቁት ሁኔታ ያውም በማይታመን መልኩ በፈጣሪ እርዳታ ከመሃል የኢትዮጵያ ክፍል ተገልለው ወደ አንድ ዳር እንዲሰበሰቡ ሆኗል። እነዚህ ሰዎች ደግሞ መልሰው ስልጣን መያዝ አይችሉም። ከዚህ አንጻር ፍላጎታቸውን ለመፈጸም ብዙ ሞክረዋል። ዙሪያውን ሄደው ኢትዮጵያን ለማመስ ያላደረጉት ጥረት የለም።
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፤በጋምቤላ፣ በሶማሌ ሁሉ ሞክረዋል፤ በደቡብ አሁንም እየሞከሩ ነው፤ በኦሮሚያም ሙከራ አለ። ››ሲሉ አብራርተዋል።
እነዚህ ሰዎች ተፈጥሮ ፍትህን፣ እኩልነትን፣ ነጻነትን፣ ኢትዮጵያዊነትን እና በኢትዮጵያ ማዕቀፍ የፈለገው የፖለቲካም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ችግር ቢኖር፤ በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ፍትሃዊ ያልሆነውን አሰራር እየታገልክ ኢትዮጵያዊነትን እንደ አንድ ምሰሶ ይዘህ ኢትዮጵያን ማቆየት የሚል ህልም እንደሌላቸውም አስታውቀዋል።
ለውጡና የለውጡ ሀይል የሚያቀነቅነው ከእነሱ አስተሳሰብ በተቃራኒው ነው ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ኢትዮጵያዊነትን እንደ አንድ ምሰሶ የያዘ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሀይል የፈለገው አይነት የፖለቲካ ችግር ቢኖር በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ መፈታት አለበት የሚል አቋም እንዳለው ጠቅሰው፣ እነሱ ግን በልዩነት ላይ የተመሰረተ፣ በብሄር ብሄረሰቦች መካከል ተቃርኖ እንዲኖር ማድረግ ነው። ሌላው ቀርቶ የእነሱ ህልውና የሚረጋገጥ የሚመስላቸው ራሳቸውን የበላይና ሁሉን ነገር አድራጊና ፈጣሪ አድርገው በመመልከት፣ በመሳልና በዛው ልክ በመግለጽ ነው ብለዋል። ይህንንም በአብነት ሲጠቅሱ ጎንደርና ጎጃም እንዲሁም ወሎና ጎንደር የጋራ ነገር የለውም ብለው እንደሚስቡም አመልክተዋል።
“ይልቁንም እኛ ነን አንድ ያደረግነው ብለው ነው የሚያስቡት። ኦሮሞን አንድ ያደረግነው እኛ ነን ብለው ነው የሚያስቡት። ከዚህ በመነሳትም ነው አሁን ላይ እነዚህን አካባቢዎች ለማፈራረስና እንደፈለገን ለመበታተን ምክንያቶች አሉን ብለው በማመን ይሄን ለማድረግ እንቅስቃሴ ጀምረዋል ብለዋል።
በዚህ ደረጃ ኦሮሞን አንድ አድርጋችሁ፤ አማራን አንድ አድርጋችሁ ነው ለስጋት የዳረጋችሁን ብለው የሚወቅሷቸው ኃይሎች እንዳሉም ሊቀመንበሩ ተናግረዋል። ስለዚህ ቀድሞ አስተሳሰባቸው የተመሰረተው በማህበረሰቦች መካከል ተቃርኖ በመፍጠር በሚፈጠር የፖለቲካ ልዩነት የእነርሱን እድሜ ማራዘም እንደሆነም አስታውቀዋል።
“ የትግራይ ህዝብ ገና ለውጡ ከመምጣቱ በፊት በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ እነዚህ ሰዎች ሲሰሩት በነበረው ግፍና በደል ምክንያት ከእነሱ ጋራ በአቻ መንገድ እየታየን በየትኛውም ቦታ የመንቀሳቀስና ሄደን የመስራት ስጋት እየተፈጠረብን ነው የሚል ምሬት ነበረው።
ልጆቻችንንና አገራችንን አጥብበውብናል የሚል አስተሳሰብ በትላልቆቹ ሰዎች ዘንድ ነበረ። ››ያሉት ሊቀመንበሩ፣ አሁንም ቢሆን ህወሓት ለትግራይ ህዝብ እንደማይጠቅም አስታውቀዋል። ይልቁንም የህወሓት ህልውና እየጨመረ በሄደ ቁጥር የትግራይ ህዝብ በህወሓት ዓይን እየታየ የበለጠ ተጎጂ እየሆነ ነው የሚሄደው”ብለዋል።
የትግራይ ህዝብም ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር አንድነቱን አጥብቆ እነሱን መታገል አለበት፤ በእውነተኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኩልም እያየን ያለነው ውጣ ውረድ ሊወገድ፤ አንዳንዶቹም ወደ ህወሓት በመጠጋት ህልውናቸውን ለማቆየት እየሂዱበት ያለው መንገድ ሊታረሙ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ከዚህ ባለፈ ህወሓት የተወሰኑ ወራት በቆየ ቁጥር የኢትዮጵያ ፖለቲካ በሽታ እያመረቀዘ እንዲሄድ ማድረግ ነው ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ህወሓት በምንም ሃይል በኢትዮጵያውያን አንድነት መጥፋት ያለበት ነቀርሳ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
“ይሄ ብቻም ሳይሆን በወንጀልም ሊጠየቅ፤ ከፖለቲካ ፓርቲነትም መሰረዝ፤ በአሸባሪነትም መፈረጅ ያለበት የፖለቲካ ፓርቲ ነው። ለዚህ አስፈላጊ ከሆነ የመረጃ ማሰባሰብ ስራ ቢሰራ የፈጸሙት ተግባር ከእነዚህ ሰዎች ጋር እንኳን ዜግነት ሰውነት መጋራት ሁሉ እስኪቀፍህ ድረስ ህውሃት እጅግ በጣም የክፉዎች ስብስብ ነው። ››ሲሉም ተናግረዋል። የዚህ ስብስብ መጥፋት ለኢትዮጵያ ህዳሴ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያውያን አንድነትና አብሮነት አንድ ትልቅ ነቀርሳ እንደመንቀል ነው ብለዋል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 26/2012
ወንድወሰን ሽመልስ
************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- ህወሓት እጅግ መሰሪ የሆነና ኢትዮጵያዊ ያልሆነ፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የቆመ የፖለቲካ ኃይል መሆኑን የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር አቶ አገዘው ህዳሩ አስታወቁ። በወንጀል ሊጠየቅ፤ ከፖለቲካ ፓርቲነት ሊሰረዝ፤ በአሸባሪነት ሊፈረጅ እንደሚገባም አሳሰቡ፡አቶ አገዘው ህዳሩ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት፣ ህወሓትን እየዘወሩ ያሉ ሐይሎች ከአስተሳሰባቸው ጀምሮ ኢትዮጵያውያን አይደሉም። በኢትዮጵያ ስም መጠቀም እስከቻሉ ድረስ በኢትዮጵያዊነት አብረው መቆየት የሚፈልጉ ናቸው፤ እነሱ መጠቀም እና በስልጣን መቆየት ካልቻሉ ኢትዮጵያን ለእነሱ ስጋት በማትሆን መንገድ መስራትና አፈራርሶ መሄድ ይፈልጋሉ።
ለዚህም የራሳቸውን ኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ የሚሊተሪና የፀጥታ አቅም አዳብረው መጠቀም እስከቻሉ ድረስ አብረው ለመቆየት ችግር የለባቸውም ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ራሳቸው መጠቀምና ሌላውን በሚፈልጉት መንገድ ማሽከርከር ካልቻሉ ኢትዮጵያን አፍርሰው መልሰው ለእነሱ ስጋት እንዳትሆን አድርገው መሄድ ፍላጎታቸው መሆኑን ጠቁመዋል።
“ህወሓት ለህዝቡም አይጠቅምም፤ እጅግ መሰሪ የሆነና ኢትዮጵያዊ ያልሆነ፤ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የቆመ የፖለቲካ ኃይል ነው። ስለዚህ ከዚህ ጋር የሚተባበር ኢትዮጵያዊ መኖር የለበትም ብዬ አምናለሁ። ይሄን የምለውም እኛ ከስር መሰረታቸው ስለምናውቃቸው ነው። ምናልባት ሌላው ህዝብ ግፍና በደሉን ብቻ ነው የሚያየው፤ እኛ ግን አስተሳሰባቸውንም ጭምር እናውቃለን “ብለዋል ።
የትግራይን ህዝብ ጨምሮ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ ላይ ሆኖ የነዚህን ሰዎች ህልውናቸውን ማሳጠር እንዳለበት ያመለከቱት አቶ አገዘው፣ ለመላው ህዝባችን የሚጠቅመው አንድነቱ፣ ኢትዮጵያዊነቱ እና የጋራ ተጠቃሚነቱ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ከእኩልነትና ከኢትዮጵያ አንድነት የሚገኘው ትርፍ እጅጉን የገዘፈ እንደሆነ በአጽዕኖት የተናገሩት ሊቀመንበሩ፣ ከህወሓት የገንጣይና ነጣይ ባህሪ አንጻር /ምን አይነት ስነልቡና እንደሆነ ባላውቅም/ ኢትዮጵያዊ ሆኖ ከህወሓት የፖለቲካ ጥቅም አገኛለሁ ብሎ የሚዶልት፤ የሚያሴር የፖለቲካ ሃይል ተግባር በጣም አስገራሚ እንደሆነ አመልክተዋል።
“እነዚህ ሰዎች ባልጠበቁት ሁኔታ ያውም በማይታመን መልኩ በፈጣሪ እርዳታ ከመሃል የኢትዮጵያ ክፍል ተገልለው ወደ አንድ ዳር እንዲሰበሰቡ ሆኗል። እነዚህ ሰዎች ደግሞ መልሰው ስልጣን መያዝ አይችሉም። ከዚህ አንጻር ፍላጎታቸውን ለመፈጸም ብዙ ሞክረዋል። ዙሪያውን ሄደው ኢትዮጵያን ለማመስ ያላደረጉት ጥረት የለም።
ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፤በጋምቤላ፣ በሶማሌ ሁሉ ሞክረዋል፤ በደቡብ አሁንም እየሞከሩ ነው፤ በኦሮሚያም ሙከራ አለ። ››ሲሉ አብራርተዋል።
እነዚህ ሰዎች ተፈጥሮ ፍትህን፣ እኩልነትን፣ ነጻነትን፣ ኢትዮጵያዊነትን እና በኢትዮጵያ ማዕቀፍ የፈለገው የፖለቲካም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ችግር ቢኖር፤ በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ፍትሃዊ ያልሆነውን አሰራር እየታገልክ ኢትዮጵያዊነትን እንደ አንድ ምሰሶ ይዘህ ኢትዮጵያን ማቆየት የሚል ህልም እንደሌላቸውም አስታውቀዋል።
ለውጡና የለውጡ ሀይል የሚያቀነቅነው ከእነሱ አስተሳሰብ በተቃራኒው ነው ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ኢትዮጵያዊነትን እንደ አንድ ምሰሶ የያዘ መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሀይል የፈለገው አይነት የፖለቲካ ችግር ቢኖር በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ መፈታት አለበት የሚል አቋም እንዳለው ጠቅሰው፣ እነሱ ግን በልዩነት ላይ የተመሰረተ፣ በብሄር ብሄረሰቦች መካከል ተቃርኖ እንዲኖር ማድረግ ነው። ሌላው ቀርቶ የእነሱ ህልውና የሚረጋገጥ የሚመስላቸው ራሳቸውን የበላይና ሁሉን ነገር አድራጊና ፈጣሪ አድርገው በመመልከት፣ በመሳልና በዛው ልክ በመግለጽ ነው ብለዋል። ይህንንም በአብነት ሲጠቅሱ ጎንደርና ጎጃም እንዲሁም ወሎና ጎንደር የጋራ ነገር የለውም ብለው እንደሚስቡም አመልክተዋል።
“ይልቁንም እኛ ነን አንድ ያደረግነው ብለው ነው የሚያስቡት። ኦሮሞን አንድ ያደረግነው እኛ ነን ብለው ነው የሚያስቡት። ከዚህ በመነሳትም ነው አሁን ላይ እነዚህን አካባቢዎች ለማፈራረስና እንደፈለገን ለመበታተን ምክንያቶች አሉን ብለው በማመን ይሄን ለማድረግ እንቅስቃሴ ጀምረዋል ብለዋል።
በዚህ ደረጃ ኦሮሞን አንድ አድርጋችሁ፤ አማራን አንድ አድርጋችሁ ነው ለስጋት የዳረጋችሁን ብለው የሚወቅሷቸው ኃይሎች እንዳሉም ሊቀመንበሩ ተናግረዋል። ስለዚህ ቀድሞ አስተሳሰባቸው የተመሰረተው በማህበረሰቦች መካከል ተቃርኖ በመፍጠር በሚፈጠር የፖለቲካ ልዩነት የእነርሱን እድሜ ማራዘም እንደሆነም አስታውቀዋል።
“ የትግራይ ህዝብ ገና ለውጡ ከመምጣቱ በፊት በየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ እነዚህ ሰዎች ሲሰሩት በነበረው ግፍና በደል ምክንያት ከእነሱ ጋራ በአቻ መንገድ እየታየን በየትኛውም ቦታ የመንቀሳቀስና ሄደን የመስራት ስጋት እየተፈጠረብን ነው የሚል ምሬት ነበረው።
ልጆቻችንንና አገራችንን አጥብበውብናል የሚል አስተሳሰብ በትላልቆቹ ሰዎች ዘንድ ነበረ። ››ያሉት ሊቀመንበሩ፣ አሁንም ቢሆን ህወሓት ለትግራይ ህዝብ እንደማይጠቅም አስታውቀዋል። ይልቁንም የህወሓት ህልውና እየጨመረ በሄደ ቁጥር የትግራይ ህዝብ በህወሓት ዓይን እየታየ የበለጠ ተጎጂ እየሆነ ነው የሚሄደው”ብለዋል።
የትግራይ ህዝብም ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር አንድነቱን አጥብቆ እነሱን መታገል አለበት፤ በእውነተኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኩልም እያየን ያለነው ውጣ ውረድ ሊወገድ፤ አንዳንዶቹም ወደ ህወሓት በመጠጋት ህልውናቸውን ለማቆየት እየሂዱበት ያለው መንገድ ሊታረሙ እንደሚገባም አስገንዝበዋል። ከዚህ ባለፈ ህወሓት የተወሰኑ ወራት በቆየ ቁጥር የኢትዮጵያ ፖለቲካ በሽታ እያመረቀዘ እንዲሄድ ማድረግ ነው ያሉት ሊቀመንበሩ፣ ህወሓት በምንም ሃይል በኢትዮጵያውያን አንድነት መጥፋት ያለበት ነቀርሳ መሆኑንም አስገንዝበዋል።
“ይሄ ብቻም ሳይሆን በወንጀልም ሊጠየቅ፤ ከፖለቲካ ፓርቲነትም መሰረዝ፤ በአሸባሪነትም መፈረጅ ያለበት የፖለቲካ ፓርቲ ነው። ለዚህ አስፈላጊ ከሆነ የመረጃ ማሰባሰብ ስራ ቢሰራ የፈጸሙት ተግባር ከእነዚህ ሰዎች ጋር እንኳን ዜግነት ሰውነት መጋራት ሁሉ እስኪቀፍህ ድረስ ህውሃት እጅግ በጣም የክፉዎች ስብስብ ነው። ››ሲሉም ተናግረዋል። የዚህ ስብስብ መጥፋት ለኢትዮጵያ ህዳሴ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያውያን አንድነትና አብሮነት አንድ ትልቅ ነቀርሳ እንደመንቀል ነው ብለዋል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 26/2012
ወንድወሰን ሽመልስ
“በሰለጠነ አገር ሆነው ያልሰለጠነ መልዕክትና ፀያፍ ነገሮችን ከማስተላለፍ ይልቅ ወደ ህሊናቸው ተመልሰው ሁኔታዎችን ዳግም ማየት አለባቸው” - አቶ ፍቃዱ ተሰማ፣የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ኃላፊ፤
• ለውጡ አብዮት ሳይሆን ሪፎርም ነው። ሪፎርሙ ውስጥ ደግሞ የተለያዩ አካላት አሉ። ሪፎርሙን ወደፊት ይዘው መሄድ የሚፈልጉ አሉ፤ ሪፎርሙን ወደኋላ የሚመልሱ አሉ። እነዚህ ወደኋላ መመለስ የሚፈልጉ አካላት የራሳቸውን የቡድን ፍላጎትና የግለሰብ ፍላጎት ማዕከል አድርገው ነው።
• ለውጡን ሊቀለብሱና ወደኋላ ሊመልሱ ከሚፈልጉት ውስጥ አንዱ እንደ ህወሓት አይነቱ በሴራ ፖለቲካ አካሄድ ስልጣን ላይ የነበረና ያንን ስልጣን ያጣ ነው።ከተቻለ ወደስልጣን ለመመለስ፣ ካልተቻለ ደግሞ ሀገር ለመበተን የሚደረግ ሩጫ ነው።
• ሌላው ደግሞ ከውጪ የመጣውና ለውጡን እኔ ነኝ ያመጣሁት ብሎ የሚያስበውና አክቲቪዝም በዓለም ላይ ጫፍ የረገጠበትን አጋጣሚ ተጠቅሞ በዚህ መስመር የመጣ አዲስ ተስፈኛ አካል የተፈጠረበትና ነው።
• ይህ ደግሞ ቀደም ሲል የዴሞክራሲ ምህዳር ችግር ስለነበረ በውጪ የነበሩት ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ምህዳር ወደ አገር ውስጥ የገቡ፤ የሪፎርሙ ውጤት ተደርገው የሚታሰቡ ናቸው።
• ለውጡ በአብዮት መጥቶ ቢሆን ግን ሁሉንም ጠራርጎ ነው መልክ የሚያሲዘው እንጂ ይሄን አይነት እድል አይሰጥም ነበር። ሪፎርም ግን በዚህ ሁሉ ፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ በብልሃትና በትዕግስት መስዋዕትነትም ጭምር እየከፈልክ የምትሄደው ስለሆነ፤ ያ ትዕግስትና የተከፈተው የዴሞክራሲ በር ነገሮች የመሰሉትን እንዲመስሉ አድርጓል።
• ሁሉም ወደ አገር በሚገባበት ጊዜ በሰላም እታገላለሁ ብሎ ነው የገባው። ከገባ በኋላ ግን ሁለት ቦታ የመቆም ሁኔታ ነው የታየው። በተለይ ኦነግ ሸኔ በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ በህቡዕ የሚንቀሳቀስበት ሁኔታ ነበረ።
• የተከፈተው የዴሞክራሲ በር ሰዎች እንደልባቸው እንዲፈነጩ፤ ግለሰቦች መንግስት መስለው እንዲታዩ ያደረገበት ሁኔታ ነበር፤ ይህም በየደረጃው ያለው አመራር አጣብቂኝ ውስጥ እንዲገባ አድርጓል።
• የህግ የበላይነቱን ሙሉ በሙሉ ለማስከበር የሚደረገው ጥረት በራሱ የዴሞክራሲ ምህዳሩ እንዳይጠብ የሚል ስጋት ነበር።
• የዴሞክራሲ ምህዳሩ ጠቦ ያለፉ ነገሮች ተመልሰው ዴሞክራሲው አጣብቂኝ ውስጥ እንዳይገባ በሚደረገው ጥረት ሰፊ ክፍተቶች ተፈጥረዋል። በዚህ መሀል የችግሩ ሰለባ የሆኑ ሰዎች የሉም ማለት አይቻልም። ነገር ግን በአብዛኛው አመራሩን ይገልጻል ማለት ግን አይደለም።
• በተለያየ ጊዜ የሚደረጉ የሁከትና ጥፋት ጥሪዎች የሚከሽፉበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ህብረተሰቡ ጥሪያቸውን አልሰማም ያለበት ዋናው ምክንያትም ህብረተሰቡ ውስጥ ያለው የጠነከረ አንድነት ነው፤
• የትኛውም አይነት ጽንፈኝነት በህዝብ ደረጃ ተቀባይነት የለውም። ሙስሊሙ ክርስቲያን ላይ ተነስ፤ ክርስቲያኑ ሙስሊሙ ላይ ተነስ፤ አንዱ ብሄር ሌላው ብሄር ላይ ተነስ በሚል የሚገለጽ በህብረተሰቡ ውስጥ የለም።
• ከወጣቶቹ ጋር ሰፋ ያሉ ውይይቶችን አድርገናል። ውጪ ተቀምጠው ወደዚህ የሚያስተላልፉት መልዕክት አይጠቅመንም የሚል ድምዳሜ ላይ እየደረሰ ነው።
• በየጊዜው የሚተላለፉ መልዕክቶች የሚከሽፉበት ዋናው ምክንያትም ይሄ በመሆኑ ነው። ይሄንን አጠናክሮ በመቀጠል ከውጪ የሚያዝ አካል ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሚያጣበት ሁኔታን ለመፍጠር እየተሰራ ነው።
• ህብረተሰቡ በተደራጀ አግባብ በየአካባቢው ለሰላሙ መረጋገጥ የጸጥታ ስራውን ሆነ የልማት ስራውንም እንዲሰራ፤ በዚህም የልማቱም የሰላሙም ባለቤት እንዲሆን ማስቻል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል።
• ብልጽግና የክልላችንን ህዝብ ጥያቄ ለመመለስ የመጣ ፓርቲ ነው ብዬ ነው የማየው። በስፋቱ ልክ መወከል አለብኝ የሚል ጥያቄ ነበር። ይሄ የፍትሃዊነት ጥያቄ ነው።
• የህግ የበላይነትን ከማስከበር አኳያ አጠቃላይ ህብረተሰቡን አሳትፈን ችግሩን ለዘለቄታው የመፍታት ስራ ተሰርቷል። አሁን በጥባጩ አካል የሚቆጣጠረው ዞንና ወረዳ ቀርቶ የሚቆጣጠረው ቀበሌ የለም።
• ብልጽግና አንድ ነው። በክልሎች ደረጃ ጽህፈት ቤት ነው ያለው። በአገር አቀፍ ደረጃ ዋናው ጽህፈት ቤት ነው ያለው። አንድ ወጥ ስራ አስፈጻሚ እና አንድ ወጥ ማዕከላዊ ኮሚቴም ምክር ቤትም ነው ያለው።
• እዚህ ደግሞ በክልሉ ሁለት ነገሮችን አስታርቆ ነው ብልጽግና የሚሰራው። የመጀመሪያው አገራዊ አንድነትን ፣ ሁለተኛ ደግሞ የብሄር ማንነትን ማዕከል አድርጎ ፌዴራሊዝምን ማስቀጠል ነው። ስለሆነም በጋራ ነው ተልዕኮ የምንወስደው፤ በጋራም ነው የምንፈጽመው።
• ባለፈው በክልላችን ችግሮች በሚፈጠሩበት ጊዜ ችግሩን ከመከላከል አኳያ ከአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጋር አብረን ስንሰራ ነበር።
• ጽንፈኛው ሃይል አጠቃላይ ኦሮሞ በአማራ ላይ እንደተዘመተ ተደርጎ ስለተቀሰቀሰ፤ በዛ በኩልም ይሄን ነገር ተረድቶ ይሄ ነገር እንዳልሆነና ጽንፈኛ ሃይል የቀሰቀሰው እንደሆነ፤ እና ኦሮሞ አማራ ላይ ሊነሳ እንደማይችል የማስገንዘቢያ ስራዎች ባይሰሩ እና በተቀሰቀሰው ልክ ግጭት ቢፈጠር ኖሮ ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ትልቅ ነበር የሚሆነው።
• በተመሳሳይ ከሶማሌ ብልጽግና ፓርቲ ጋር፣ ከአፋር ብልጽግና ፓርቲ ጋር፣ ባጠቃላይ ከሁሉም ክልሎች ብልጽግና ፓርቲ ጋር በየጊዜው እየተገናኘን እንገመግማለን፤ የተሞክሮ ልውውጥም እናደርጋለን። ስለዚህ አንድ ላይ ነው የምንሰራው ማለት ይቻላል።
• በአንድ ግምገማና በአንድ ኮንፍረንስ ሁሉም ችግሮች በአንድ ጊዜ ጠርተው ይጠፋሉ ማለት አይቻለም። ነገር ግን በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ከአሁን በኋላ ፈተናዎች እየቀነሱ ይሄዳሉ፤
• ህብረተሰቡ የሰላሙም የልማቱም ባለቤት እንዲሆን ካደረግነው በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ችግሮችን ማቃለል ይቻላል፤ ችግሮች ቢፈጠሩ እንኳን መቋቋም ይቻላል።
• ከቀበሌና ወረዳ ጀምሮ በትልልቅ ከተሞች ላይ ነው ማጥራት ያደረግነው። እንደገናም ወደ 11 የሚሆኑ ዞኖች ላይ የማጥራትና መልሶ የማደራጀት ስራ ሰርተናል።
• ሰፋ ያለ ቁጥር ያለው አመራር ከታች እስከላይ የማጥራትና የማስተካከል ስራ ነው የተሰራው። ይህ ደግሞ አገር መቀጠል አለበት፤ ህዝብ መቀጠል አለበት፤ ፓርቲ መቀጠል አለበት በሚል የተከናወነ ነው።
• ብልጽግና ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች በእኩልነት የሚሳተፉበት፤ በፍትሃዊነት የሚወከሉበትም ፓርቲ ነው። እንደገናም በአገራችን ፈተና እየገጠመው ዴሞክራሲ እንዲያብብ ለማድረግ ነው።
• ሀሳብ አለኝ የሚል አካል እዚህ መጥቶ ሀሳቡን ይዞ ሰላማዊ ትግል ማግረግ ይችላል ከዚህ ውጪ ከኦሮሞ ባህል፣ እሴትና ተፈጥሮ ውጪ ኦሮሞን መሳል የሚፈልጉ የኦሮሞ ጽንፈኞችን ህዝቡ በቃችሁ ሊላቸው ይገባል።
• ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ብሄር ብሄረሰቦችም ጋር አንድ ሆኖ ዋጋ የከፈለበትን ለውጥና በለውጡ የጀመረውን ጉዞ ማስቀጠል፤ አካባቢውንም ሰላም ማድረግ አለበት፤ የሚል መልዕክት አለኝ።
ምንጭ አዲስ ዘመን ነሐሴ 25/2012
• ለውጡ አብዮት ሳይሆን ሪፎርም ነው። ሪፎርሙ ውስጥ ደግሞ የተለያዩ አካላት አሉ። ሪፎርሙን ወደፊት ይዘው መሄድ የሚፈልጉ አሉ፤ ሪፎርሙን ወደኋላ የሚመልሱ አሉ። እነዚህ ወደኋላ መመለስ የሚፈልጉ አካላት የራሳቸውን የቡድን ፍላጎትና የግለሰብ ፍላጎት ማዕከል አድርገው ነው።
• ለውጡን ሊቀለብሱና ወደኋላ ሊመልሱ ከሚፈልጉት ውስጥ አንዱ እንደ ህወሓት አይነቱ በሴራ ፖለቲካ አካሄድ ስልጣን ላይ የነበረና ያንን ስልጣን ያጣ ነው።ከተቻለ ወደስልጣን ለመመለስ፣ ካልተቻለ ደግሞ ሀገር ለመበተን የሚደረግ ሩጫ ነው።
• ሌላው ደግሞ ከውጪ የመጣውና ለውጡን እኔ ነኝ ያመጣሁት ብሎ የሚያስበውና አክቲቪዝም በዓለም ላይ ጫፍ የረገጠበትን አጋጣሚ ተጠቅሞ በዚህ መስመር የመጣ አዲስ ተስፈኛ አካል የተፈጠረበትና ነው።
• ይህ ደግሞ ቀደም ሲል የዴሞክራሲ ምህዳር ችግር ስለነበረ በውጪ የነበሩት ለውጡን ተከትሎ በተፈጠረው ምህዳር ወደ አገር ውስጥ የገቡ፤ የሪፎርሙ ውጤት ተደርገው የሚታሰቡ ናቸው።
• ለውጡ በአብዮት መጥቶ ቢሆን ግን ሁሉንም ጠራርጎ ነው መልክ የሚያሲዘው እንጂ ይሄን አይነት እድል አይሰጥም ነበር። ሪፎርም ግን በዚህ ሁሉ ፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ በብልሃትና በትዕግስት መስዋዕትነትም ጭምር እየከፈልክ የምትሄደው ስለሆነ፤ ያ ትዕግስትና የተከፈተው የዴሞክራሲ በር ነገሮች የመሰሉትን እንዲመስሉ አድርጓል።
• ሁሉም ወደ አገር በሚገባበት ጊዜ በሰላም እታገላለሁ ብሎ ነው የገባው። ከገባ በኋላ ግን ሁለት ቦታ የመቆም ሁኔታ ነው የታየው። በተለይ ኦነግ ሸኔ በምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ በህቡዕ የሚንቀሳቀስበት ሁኔታ ነበረ።
• የተከፈተው የዴሞክራሲ በር ሰዎች እንደልባቸው እንዲፈነጩ፤ ግለሰቦች መንግስት መስለው እንዲታዩ ያደረገበት ሁኔታ ነበር፤ ይህም በየደረጃው ያለው አመራር አጣብቂኝ ውስጥ እንዲገባ አድርጓል።
• የህግ የበላይነቱን ሙሉ በሙሉ ለማስከበር የሚደረገው ጥረት በራሱ የዴሞክራሲ ምህዳሩ እንዳይጠብ የሚል ስጋት ነበር።
• የዴሞክራሲ ምህዳሩ ጠቦ ያለፉ ነገሮች ተመልሰው ዴሞክራሲው አጣብቂኝ ውስጥ እንዳይገባ በሚደረገው ጥረት ሰፊ ክፍተቶች ተፈጥረዋል። በዚህ መሀል የችግሩ ሰለባ የሆኑ ሰዎች የሉም ማለት አይቻልም። ነገር ግን በአብዛኛው አመራሩን ይገልጻል ማለት ግን አይደለም።
• በተለያየ ጊዜ የሚደረጉ የሁከትና ጥፋት ጥሪዎች የሚከሽፉበት ሁኔታ ተፈጥሯል። ህብረተሰቡ ጥሪያቸውን አልሰማም ያለበት ዋናው ምክንያትም ህብረተሰቡ ውስጥ ያለው የጠነከረ አንድነት ነው፤
• የትኛውም አይነት ጽንፈኝነት በህዝብ ደረጃ ተቀባይነት የለውም። ሙስሊሙ ክርስቲያን ላይ ተነስ፤ ክርስቲያኑ ሙስሊሙ ላይ ተነስ፤ አንዱ ብሄር ሌላው ብሄር ላይ ተነስ በሚል የሚገለጽ በህብረተሰቡ ውስጥ የለም።
• ከወጣቶቹ ጋር ሰፋ ያሉ ውይይቶችን አድርገናል። ውጪ ተቀምጠው ወደዚህ የሚያስተላልፉት መልዕክት አይጠቅመንም የሚል ድምዳሜ ላይ እየደረሰ ነው።
• በየጊዜው የሚተላለፉ መልዕክቶች የሚከሽፉበት ዋናው ምክንያትም ይሄ በመሆኑ ነው። ይሄንን አጠናክሮ በመቀጠል ከውጪ የሚያዝ አካል ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት የሚያጣበት ሁኔታን ለመፍጠር እየተሰራ ነው።
• ህብረተሰቡ በተደራጀ አግባብ በየአካባቢው ለሰላሙ መረጋገጥ የጸጥታ ስራውን ሆነ የልማት ስራውንም እንዲሰራ፤ በዚህም የልማቱም የሰላሙም ባለቤት እንዲሆን ማስቻል ላይ ትኩረት ተሰጥቶ ይሰራል።
• ብልጽግና የክልላችንን ህዝብ ጥያቄ ለመመለስ የመጣ ፓርቲ ነው ብዬ ነው የማየው። በስፋቱ ልክ መወከል አለብኝ የሚል ጥያቄ ነበር። ይሄ የፍትሃዊነት ጥያቄ ነው።
• የህግ የበላይነትን ከማስከበር አኳያ አጠቃላይ ህብረተሰቡን አሳትፈን ችግሩን ለዘለቄታው የመፍታት ስራ ተሰርቷል። አሁን በጥባጩ አካል የሚቆጣጠረው ዞንና ወረዳ ቀርቶ የሚቆጣጠረው ቀበሌ የለም።
• ብልጽግና አንድ ነው። በክልሎች ደረጃ ጽህፈት ቤት ነው ያለው። በአገር አቀፍ ደረጃ ዋናው ጽህፈት ቤት ነው ያለው። አንድ ወጥ ስራ አስፈጻሚ እና አንድ ወጥ ማዕከላዊ ኮሚቴም ምክር ቤትም ነው ያለው።
• እዚህ ደግሞ በክልሉ ሁለት ነገሮችን አስታርቆ ነው ብልጽግና የሚሰራው። የመጀመሪያው አገራዊ አንድነትን ፣ ሁለተኛ ደግሞ የብሄር ማንነትን ማዕከል አድርጎ ፌዴራሊዝምን ማስቀጠል ነው። ስለሆነም በጋራ ነው ተልዕኮ የምንወስደው፤ በጋራም ነው የምንፈጽመው።
• ባለፈው በክልላችን ችግሮች በሚፈጠሩበት ጊዜ ችግሩን ከመከላከል አኳያ ከአማራ ብልጽግና ፓርቲ ጋር አብረን ስንሰራ ነበር።
• ጽንፈኛው ሃይል አጠቃላይ ኦሮሞ በአማራ ላይ እንደተዘመተ ተደርጎ ስለተቀሰቀሰ፤ በዛ በኩልም ይሄን ነገር ተረድቶ ይሄ ነገር እንዳልሆነና ጽንፈኛ ሃይል የቀሰቀሰው እንደሆነ፤ እና ኦሮሞ አማራ ላይ ሊነሳ እንደማይችል የማስገንዘቢያ ስራዎች ባይሰሩ እና በተቀሰቀሰው ልክ ግጭት ቢፈጠር ኖሮ ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ትልቅ ነበር የሚሆነው።
• በተመሳሳይ ከሶማሌ ብልጽግና ፓርቲ ጋር፣ ከአፋር ብልጽግና ፓርቲ ጋር፣ ባጠቃላይ ከሁሉም ክልሎች ብልጽግና ፓርቲ ጋር በየጊዜው እየተገናኘን እንገመግማለን፤ የተሞክሮ ልውውጥም እናደርጋለን። ስለዚህ አንድ ላይ ነው የምንሰራው ማለት ይቻላል።
• በአንድ ግምገማና በአንድ ኮንፍረንስ ሁሉም ችግሮች በአንድ ጊዜ ጠርተው ይጠፋሉ ማለት አይቻለም። ነገር ግን በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ከአሁን በኋላ ፈተናዎች እየቀነሱ ይሄዳሉ፤
• ህብረተሰቡ የሰላሙም የልማቱም ባለቤት እንዲሆን ካደረግነው በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው ችግሮችን ማቃለል ይቻላል፤ ችግሮች ቢፈጠሩ እንኳን መቋቋም ይቻላል።
• ከቀበሌና ወረዳ ጀምሮ በትልልቅ ከተሞች ላይ ነው ማጥራት ያደረግነው። እንደገናም ወደ 11 የሚሆኑ ዞኖች ላይ የማጥራትና መልሶ የማደራጀት ስራ ሰርተናል።
• ሰፋ ያለ ቁጥር ያለው አመራር ከታች እስከላይ የማጥራትና የማስተካከል ስራ ነው የተሰራው። ይህ ደግሞ አገር መቀጠል አለበት፤ ህዝብ መቀጠል አለበት፤ ፓርቲ መቀጠል አለበት በሚል የተከናወነ ነው።
• ብልጽግና ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝቦች በእኩልነት የሚሳተፉበት፤ በፍትሃዊነት የሚወከሉበትም ፓርቲ ነው። እንደገናም በአገራችን ፈተና እየገጠመው ዴሞክራሲ እንዲያብብ ለማድረግ ነው።
• ሀሳብ አለኝ የሚል አካል እዚህ መጥቶ ሀሳቡን ይዞ ሰላማዊ ትግል ማግረግ ይችላል ከዚህ ውጪ ከኦሮሞ ባህል፣ እሴትና ተፈጥሮ ውጪ ኦሮሞን መሳል የሚፈልጉ የኦሮሞ ጽንፈኞችን ህዝቡ በቃችሁ ሊላቸው ይገባል።
• ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ብሄር ብሄረሰቦችም ጋር አንድ ሆኖ ዋጋ የከፈለበትን ለውጥና በለውጡ የጀመረውን ጉዞ ማስቀጠል፤ አካባቢውንም ሰላም ማድረግ አለበት፤ የሚል መልዕክት አለኝ።
ምንጭ አዲስ ዘመን ነሐሴ 25/2012
የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ወደ ባንክ አደገ
**********************
(ኢፕድ)
የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም (አብቁተ)ወደ ባንክ ማደጉ ተገለጸ።
የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ዋና ሥራ አስፈፃሚ መኮንን የለውምወሰን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተቋሙ ወደ ባንክ መሸጋገሩን ተከትሎ ከ3 እስከ 6 ወር ባለ ጊዜ ውስጥ ሦራ ለመጀመር ሠራተኞችን በቂ ስልጠና የመስጠትና ቢሮዎችን በማደራጀት ሥራ እንደሚሠራ ተናግረዋል።
ከዚያም ባለፈ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በብቃት ለመጠቀም በቂ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አብራርተዋል።
ተቋሙ የባንክ አገልግሎቱን በ8 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መነሻ ካፒታል የሚጀምር ሲሆን በ53 ነባር የተቋሙ ቅርንጫፎች ተደራሽ እንደሚሆንም አስረድተዋል።
ከዚህ በፊት ብድር ለወሰዱ ደምበኞች ሁለት አማራጭ መቀመጡን የተናገሩት ኃላፊው የመጀመሪያው በውሉ መሠረት መጨረስ ሲሆን ሁለተኛው አማራጭ የወሰዱትን ብድር መልሰው በአዲስ ብድር መጠየቅ መሆኑንም ገልጸዋል።
የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ከዚህ በፊት የሠራቸውን መልካም ሥራዎች በመቀመር አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈጻሚው የሚስተዋሉ ችግሮችን በማረምና በማስተካከል የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ እንደሚሠራም አመልክተዋል።
የክልሉ መንግሥት ድርሻ 98 በመቶ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ወደ ባንክ ሲያድግ ከ70 በመቶ መብለጥ እንደሌለበት መመሪያው ሲለሚገድብ 30 በመቶው ለግል አክሲዮን እንደሚሸጥ መናገራቸውን ከአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
**********************
(ኢፕድ)
የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም (አብቁተ)ወደ ባንክ ማደጉ ተገለጸ።
የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ዋና ሥራ አስፈፃሚ መኮንን የለውምወሰን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተቋሙ ወደ ባንክ መሸጋገሩን ተከትሎ ከ3 እስከ 6 ወር ባለ ጊዜ ውስጥ ሦራ ለመጀመር ሠራተኞችን በቂ ስልጠና የመስጠትና ቢሮዎችን በማደራጀት ሥራ እንደሚሠራ ተናግረዋል።
ከዚያም ባለፈ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በብቃት ለመጠቀም በቂ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አብራርተዋል።
ተቋሙ የባንክ አገልግሎቱን በ8 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር መነሻ ካፒታል የሚጀምር ሲሆን በ53 ነባር የተቋሙ ቅርንጫፎች ተደራሽ እንደሚሆንም አስረድተዋል።
ከዚህ በፊት ብድር ለወሰዱ ደምበኞች ሁለት አማራጭ መቀመጡን የተናገሩት ኃላፊው የመጀመሪያው በውሉ መሠረት መጨረስ ሲሆን ሁለተኛው አማራጭ የወሰዱትን ብድር መልሰው በአዲስ ብድር መጠየቅ መሆኑንም ገልጸዋል።
የአማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ከዚህ በፊት የሠራቸውን መልካም ሥራዎች በመቀመር አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን የተናገሩት ዋና ሥራ አስፈጻሚው የሚስተዋሉ ችግሮችን በማረምና በማስተካከል የክልሉን ኢኮኖሚ ለማሳደግ እንደሚሠራም አመልክተዋል።
የክልሉ መንግሥት ድርሻ 98 በመቶ የነበረ ሲሆን አሁን ግን ወደ ባንክ ሲያድግ ከ70 በመቶ መብለጥ እንደሌለበት መመሪያው ሲለሚገድብ 30 በመቶው ለግል አክሲዮን እንደሚሸጥ መናገራቸውን ከአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በግል ትምህርት ቤቶች ምንም አይነት ተጨማሪ ክፍያ ማድረግ እንደማይቻል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
************
(ኢ ፕ ድ)
በግል ትምህርት ቤት በሚከናወነው የትምህርት ቤት ምዝገባም ሆነ የትምህርት ክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደማይቻል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የ 2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ ከ ነሃሴ 20/2012 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከናወን ትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁን ተከትሎ ከተማሪዎች ምዝገባ እና ከትምህርት ክፍያ ጋር ተያይዞ ወላጆች ቅሬታን እያቀረቡ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ አሊ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን የትምህርት ቤት ምዝገባ ክፍያ መመሪያን ተላልፈው ምዝገባ እያከናወኑ ያሉ ትምህርት ቤቶች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና ከመመሪያ ውጪ የሰበሰቡትን ገንዘብ ለወላጆች ተመላሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
ሚኒስተር ዴኤታዋ የ2013 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ላይም ምንም አይነት የክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደማይቻል እና እንደሚያስጠይቅም ተናግረዋል፡፡
ትምህርት ቤቶችም ምዝገባ ሲያከናውኑ ከዚህ በፊት ይጠቀሙበት የነበረውን የክፍያ አቀባበል ዘዴ መቀየር የማይችሉ መሆኑን እና ከዚህ በፊት በነበረው የክፍያ ስርዓት መቀጠል እንዳለባቸውም ገልጸዋል።፡
በተጨማሪም ትምህርት ቤቶች ከመደበኛ የትምህርት ክፍያ እና ከመመዝገቢያ ክፍያ ውጪ ሌሎች ተጨማሪ ክፍያ ማስከፈል ማይቻል መሆኑ ተነግሯል፡፡
የቀጣይ አመት ትምህርት የሚጀመርበትን ቀን በተመለከተም ትምህርት ሚኒስቴር እስከሚያሳውቅ ድረስ ማንኛውም ትምህርት ቤት ትምህርት መጀመር እንደማይችል ሚኒስትር ዴኤታዋ አስታውቀዋል፡፡
************
(ኢ ፕ ድ)
በግል ትምህርት ቤት በሚከናወነው የትምህርት ቤት ምዝገባም ሆነ የትምህርት ክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደማይቻል ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የ 2013 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ ከ ነሃሴ 20/2012 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከናወን ትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁን ተከትሎ ከተማሪዎች ምዝገባ እና ከትምህርት ክፍያ ጋር ተያይዞ ወላጆች ቅሬታን እያቀረቡ መሆኑ ተገልጿል፡፡
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ አሊ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የትምህርት ሚኒስቴር ያወጣውን የትምህርት ቤት ምዝገባ ክፍያ መመሪያን ተላልፈው ምዝገባ እያከናወኑ ያሉ ትምህርት ቤቶች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ እና ከመመሪያ ውጪ የሰበሰቡትን ገንዘብ ለወላጆች ተመላሽ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡
ሚኒስተር ዴኤታዋ የ2013 የትምህርት ዘመን ምዝገባ ላይም ምንም አይነት የክፍያ ጭማሪ ማድረግ እንደማይቻል እና እንደሚያስጠይቅም ተናግረዋል፡፡
ትምህርት ቤቶችም ምዝገባ ሲያከናውኑ ከዚህ በፊት ይጠቀሙበት የነበረውን የክፍያ አቀባበል ዘዴ መቀየር የማይችሉ መሆኑን እና ከዚህ በፊት በነበረው የክፍያ ስርዓት መቀጠል እንዳለባቸውም ገልጸዋል።፡
በተጨማሪም ትምህርት ቤቶች ከመደበኛ የትምህርት ክፍያ እና ከመመዝገቢያ ክፍያ ውጪ ሌሎች ተጨማሪ ክፍያ ማስከፈል ማይቻል መሆኑ ተነግሯል፡፡
የቀጣይ አመት ትምህርት የሚጀመርበትን ቀን በተመለከተም ትምህርት ሚኒስቴር እስከሚያሳውቅ ድረስ ማንኛውም ትምህርት ቤት ትምህርት መጀመር እንደማይችል ሚኒስትር ዴኤታዋ አስታውቀዋል፡፡
የካንሰር፣ ከፍተኛ ደም ግፊት፣ የስኳር በሽታ፣ የልብ ህመም፣ አስምና ለረጅም ጊዜ የሚቆይ የመተንፈሻ አካል ህመም ያለባቸው ህመምተኖች በኮቪድ19 በሽታ እንዳይጠቁ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ምክንያቱም በዚህ በሽታ ከተጠቁ በሽታው ከሌሎች ሰዎች በበለጠ ሊጠናባቸው ይችላል፡፡
በመሆኑም:-
1. ወደ ጤና ተቋም የሚያደርጉትን ምልልስ በመቀነስ የቀጠሮ ጊዜ በሶስት ወራት እንዲራዘም ተደርጓል።
2. መድሃኒታቸውን በትክክልና ሳያቋርጡ መውሰድ ይጠበቅባቸዋል።
3. እራስን አለማጨናነቅ፣ በቤት ውስጥ ቀላል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ
4. ለኮቪድ 19 መከላከያዎችን ማለትም መሸፈን መራራቅ መታጠብን በሚገባ መተግበር
5. ህመም ከተሰማ ወዲያውኑ ወደ አቅራቢያ ጤና ተቋም መሄድ እና ሪፖርት ማድረግ፡፡
6. ህክምና የምናገኝበትንና መድሃኒት የምንወስድበትን ጤና ተቋም እንዲሁም የባለሙያ ስልክ ቁጥር መያዝ፣ በስልክ የጤና ባለሙያዎችን ምክር መጠየቅ፣ ማማከር ተገቢ ነው።
ተጨማሪ መረጃ ወይም ምክር ከፈለጉ በ952 በነፃ ይደውሉ።
በመሆኑም:-
1. ወደ ጤና ተቋም የሚያደርጉትን ምልልስ በመቀነስ የቀጠሮ ጊዜ በሶስት ወራት እንዲራዘም ተደርጓል።
2. መድሃኒታቸውን በትክክልና ሳያቋርጡ መውሰድ ይጠበቅባቸዋል።
3. እራስን አለማጨናነቅ፣ በቤት ውስጥ ቀላል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ
4. ለኮቪድ 19 መከላከያዎችን ማለትም መሸፈን መራራቅ መታጠብን በሚገባ መተግበር
5. ህመም ከተሰማ ወዲያውኑ ወደ አቅራቢያ ጤና ተቋም መሄድ እና ሪፖርት ማድረግ፡፡
6. ህክምና የምናገኝበትንና መድሃኒት የምንወስድበትን ጤና ተቋም እንዲሁም የባለሙያ ስልክ ቁጥር መያዝ፣ በስልክ የጤና ባለሙያዎችን ምክር መጠየቅ፣ ማማከር ተገቢ ነው።
ተጨማሪ መረጃ ወይም ምክር ከፈለጉ በ952 በነፃ ይደውሉ።
ፓርቲዎች ፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ጠንካራ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ ጠየቁ
*************************
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዛሬ በሚያካሂደው አስቸኳይ ስብሰባ የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ጠንካራ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ የተለያዩ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ፡፡
የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፤ ህብር ኢትዮጵያና ኢዜማ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በትግራይ ክልል ለማካሄድ በታቀደው ክልላዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ በገዢው ፓርቲና በሕወሓት መካከል ያለው ውጥረት በዘለቄታዊ መንገድ መፍታት የሚያስችል ውሳኔ ማስተላለፍ ይጠበቅበታል።
የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር አረጋዊ በርሔ እንደተናገሩት፤ ህወሓት ለማካሄድ ያሰበው ምርጫ ህገመንግስቱን የጣሰና ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ያስተላለፈውን ውሳኔ ያፈነገጠ ነው።በተለይም መላው አለም በኮረና ወረርሽኝ በተናወጠበትና ምርጫ ባስተላለፈበት በዚህ ወቅት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫው እንዲራዘም ያስተላለፈውን ውሳኔ የጣሰ ተግባር ነው።ሕወሓት ምርጫውን ለማካሄድ ህገ መንግስታዊ የጊዜ ገደብ ምክንያት ቢያደርግም ዋና አላማውም ትግራይን ከሌላው ህዝብ ለመገንጠል ያለመ ነው።
«ይህ ምርጫ ላለፉት 27ዓመታት በመላው አገሪቱ ያደረሱትን ጥፋትና ጉዳት ተጠያቂነት ለማምለጥ የሚያደርጉት ሽሽት ነው» ያሉት ሊቀመንበሩ፤ የህውሓት አመራሮች ምርጫውን የሚያካሂዱት ለእውነተኛ ዲሞክራሲ መስፈን ከማሰብ ሳይሆን በተገነጠለች ትግራይ ተዝናንተው ለመኖር ያቀዱት ሴራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ይህ ሁኔታ ትግራይን ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ክፍል የሚያናጋ ስራ መሆኑን ገልፀው፤ «የትግራይ ህዝብ ወንድም እህት ከሆነው ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያጋጩት ነው» ብለዋል።
የትግራይ ህዝብ እስካሁን ድረስ የደረሰበት ችግር አልበቃ ብሎ ተጨማሪ መከራ እንዲመጣበት የሕወሓት አመራሮች ሩጫ ላይ መሆናቸውን የጠቀሱት ዶክተር አረጋዊ ፤ ይህም ትልቅና ዘላቂ ችግር ያመጣል የሚል ስጋት እንዳላቸው አስረድተዋል። «ሕወሓት የሚከተለው አካሄድ አደገኛ በመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምርጫውን የሚያስቆም ጠንከር ያለ ውሳኔ ማስተላለፍ ይገባዋል» ብለዋል።
ይሁንና ጦርነት ማወጅም ሆነ የትግራይ ህዝብ ለሞት የሚዳርግ ማንኛውም እርምጃ ፓርቲያቸው መኖር አለበት ብሎ እንደማያምን ጠቁመው፤ ይልቁንም የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል።ይህም ማለት ፋይናንስ ከመከልከል ጀምሮ የኮምዩኒኬሽንና የትራንፖርት አማራጮችን በመዝጋት ህውሃትን ከጥፋት ጎዳናው መመለስ እንደሚገባ አስገንዝብዋል።ከዚህም ባለፈ ህዝቡን ለተጨማሪ የጦርነት ስጋትም ሆነ በምርጫ ሰበብ ለባከነው ገንዘብ የህውሃትን አመራሮች ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የትግራይ ክልልን የሚያስተዳድረው የሕወሓት መንግስት ምርጫን ለማካሄድ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ህገመንግስቱንም ሆነ ፓርቲዎች የፈረሙትን የጋራ የቃልኪዳን ሰነድ የሚጣረስ ነው።የክልሉ መንግስት እስካሁንም ድረስ ምክር ቤቱ የሚያስተላልፋቸውን ውሳኔዎች ወደ ጎን በመተው የራሱን መንገድ መምረጡን አስታውሰው፤ አሁንም የምክር ቤቱን ውሳኔ ይቀበለዋል የሚል እምነት እንደሌላቸው አመልክተዋል።በመሆኑም የሕወሓትን አቋም ሊያስቀይር የሚችል ውሳኔ ማስተላለፍ ከምክር ቤቱ እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል፡፡
«በእኛ እምነት የፌዴራል መንግስቱን በሚያስተዳድረው ብልፅግና እና በህወሃት መካከል ያለው ልዩነት ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ነው መፈታት ያለበት» ያሉት አቶ ናትናኤል፤ የፌዴራል መንግስት ህገመንግስቱን የማስከበር ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ይህንን ኃላፊነቱን በሰላማዊ መንገድ ሊወጣው እንደሚገባ አስገንዝበዋል። «ሕወሃትንም ጨምሮ 107 የፖለቲካ ፓርቲዎች የፈረሙበት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ቃልኪዳን ሰነድ መሰረት ምርጫ ተደርጎ ህገመንግስቱ እስከሚቀየር ድረስ አሁን ያለውን ህገመንግስት የማክበር ግዴታ ሁሉም ሃይሎች ለመወጣት ቁርጠኝነታቸውን ማሳየት አለባቸው» ብለዋል።
በሌላ በኩል ሕወሓት የፌዴራል መንግስት ምርጫውን ለማስተጓጎል ጥረት ቢያደርግ በህግ እንደሚጠይቀው መግለፁን በሚመለከትም ተጠይቀው « በአንድ በኩል ህግን እየጣሱ በሌላ በኩልም ተጠያቂነትን አሰፍናለሁ የሚለው ነገር የሚያስኬድ አይመስለኝም» ብለዋል፡፡ የፌዴራል መንግስቱን ስልጣን የሚጋፉ ከሆነና የሚወስደውንም እርምጃዎች አንቀበልም የሚሉ ከሆነ እነሱም በህግ ማንንም ተጠያቂ ሊያደርጉ የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገቡ ተናግረዋል።
የህብር ኢትዮጵያ ሊቀመንበር አቶ ግርማ በቀለም «የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤው ከትግራይ ክልል ምርጫ ጋር በተያያዘ ጠንካራ ውሳኔ ያስተላልፋል ብለን እንጠብቃለን»ብለዋል።
በተለይም በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ያለውን የፖለቲካ ውጥረት የሚያረግብ ውሳኔ ማስተላለፍ እንደሚገባው አሳስበዋል። ሁሉንም አካላት ያማከለ የፖለቲካ ድርድር ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል። ለዚህም አንዱ ሌላውን ለማሸነፍ ከማሰብ ብቻ ሳይሆን በቅንነትና በቁርጠኝነት አገርን ከትርምስ የማዳን ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚገባው አመልክተዋል።
«አሁንም ቢሆን በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ችግሮች መስማትና ማድመጥ የማይፈልገውን ነገር ሁሉ መስማትና ማድመጥ የማይፈልገውን ነገር ሁሉ ሊያደምጥበት የሚገባ ነገር መፈጠር አለበት» ያሉት ሊቀመንበሩ ፣ መንግስት ወይም የፌደሬሽን ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ ቁርጠኛ መሆናቸውን ካሳወቁ ሁሉም ዜጋ ሊተባበር እንደሚችል አስረድተዋል።
በፓርቲዎች መካከል ያለው ግንኙነት ጤናማ እና ልዩነቶች ያለግጭት የሚስተናገዱበት ሁኔታ መፈጠር እንደሚገባው አመልክተው፣ በተለይም ሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች የገባነውን ቃል መተግበር ይጠበቅብናል ብለዋል ። «ይህን ቃልኪዳን ለማክበር መንግስት ቁርጠኝነቱን ካሳየና ሕወሓት ለማክበር ካልፈለገ ጉዳዩ በሁለቱ ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን የመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ጉዳይ ነው» በማለት ገልፀዋል።
በተያያዘ ዜና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የሆኑ የትግራይ ክልል ተወላጆች ምክር ቤቱ ዛሬ የሚካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ አጀንዳ ያልተገለፀላቸው በመሆኑ በስብሰባው እንደማይሳተፉ በደብዳቤ ገልፀዋል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 30/2012
*************************
የፌዴሬሽን ምክር ቤት ዛሬ በሚያካሂደው አስቸኳይ ስብሰባ የትግራይ ክልል ምርጫን በሚመለከት ጠንካራ ውሳኔ እንዲያስተላልፍ የተለያዩ ፓርቲዎች ጥሪ አቀረቡ፡፡
የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ፤ ህብር ኢትዮጵያና ኢዜማ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ የፌዴሬሽን ምክር ቤት በትግራይ ክልል ለማካሄድ በታቀደው ክልላዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ በገዢው ፓርቲና በሕወሓት መካከል ያለው ውጥረት በዘለቄታዊ መንገድ መፍታት የሚያስችል ውሳኔ ማስተላለፍ ይጠበቅበታል።
የትግራይ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሊቀመንበር ዶክተር አረጋዊ በርሔ እንደተናገሩት፤ ህወሓት ለማካሄድ ያሰበው ምርጫ ህገመንግስቱን የጣሰና ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ያስተላለፈውን ውሳኔ ያፈነገጠ ነው።በተለይም መላው አለም በኮረና ወረርሽኝ በተናወጠበትና ምርጫ ባስተላለፈበት በዚህ ወቅት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምርጫው እንዲራዘም ያስተላለፈውን ውሳኔ የጣሰ ተግባር ነው።ሕወሓት ምርጫውን ለማካሄድ ህገ መንግስታዊ የጊዜ ገደብ ምክንያት ቢያደርግም ዋና አላማውም ትግራይን ከሌላው ህዝብ ለመገንጠል ያለመ ነው።
«ይህ ምርጫ ላለፉት 27ዓመታት በመላው አገሪቱ ያደረሱትን ጥፋትና ጉዳት ተጠያቂነት ለማምለጥ የሚያደርጉት ሽሽት ነው» ያሉት ሊቀመንበሩ፤ የህውሓት አመራሮች ምርጫውን የሚያካሂዱት ለእውነተኛ ዲሞክራሲ መስፈን ከማሰብ ሳይሆን በተገነጠለች ትግራይ ተዝናንተው ለመኖር ያቀዱት ሴራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ይህ ሁኔታ ትግራይን ብቻ ሳይሆን መላውን የኢትዮጵያ ክፍል የሚያናጋ ስራ መሆኑን ገልፀው፤ «የትግራይ ህዝብ ወንድም እህት ከሆነው ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያጋጩት ነው» ብለዋል።
የትግራይ ህዝብ እስካሁን ድረስ የደረሰበት ችግር አልበቃ ብሎ ተጨማሪ መከራ እንዲመጣበት የሕወሓት አመራሮች ሩጫ ላይ መሆናቸውን የጠቀሱት ዶክተር አረጋዊ ፤ ይህም ትልቅና ዘላቂ ችግር ያመጣል የሚል ስጋት እንዳላቸው አስረድተዋል። «ሕወሓት የሚከተለው አካሄድ አደገኛ በመሆኑ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ምርጫውን የሚያስቆም ጠንከር ያለ ውሳኔ ማስተላለፍ ይገባዋል» ብለዋል።
ይሁንና ጦርነት ማወጅም ሆነ የትግራይ ህዝብ ለሞት የሚዳርግ ማንኛውም እርምጃ ፓርቲያቸው መኖር አለበት ብሎ እንደማያምን ጠቁመው፤ ይልቁንም የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ እርምጃዎችን መውሰድ እንደሚገባ ተናግረዋል።ይህም ማለት ፋይናንስ ከመከልከል ጀምሮ የኮምዩኒኬሽንና የትራንፖርት አማራጮችን በመዝጋት ህውሃትን ከጥፋት ጎዳናው መመለስ እንደሚገባ አስገንዝብዋል።ከዚህም ባለፈ ህዝቡን ለተጨማሪ የጦርነት ስጋትም ሆነ በምርጫ ሰበብ ለባከነው ገንዘብ የህውሃትን አመራሮች ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ናትናኤል ፈለቀ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ የትግራይ ክልልን የሚያስተዳድረው የሕወሓት መንግስት ምርጫን ለማካሄድ እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ህገመንግስቱንም ሆነ ፓርቲዎች የፈረሙትን የጋራ የቃልኪዳን ሰነድ የሚጣረስ ነው።የክልሉ መንግስት እስካሁንም ድረስ ምክር ቤቱ የሚያስተላልፋቸውን ውሳኔዎች ወደ ጎን በመተው የራሱን መንገድ መምረጡን አስታውሰው፤ አሁንም የምክር ቤቱን ውሳኔ ይቀበለዋል የሚል እምነት እንደሌላቸው አመልክተዋል።በመሆኑም የሕወሓትን አቋም ሊያስቀይር የሚችል ውሳኔ ማስተላለፍ ከምክር ቤቱ እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል፡፡
«በእኛ እምነት የፌዴራል መንግስቱን በሚያስተዳድረው ብልፅግና እና በህወሃት መካከል ያለው ልዩነት ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ነው መፈታት ያለበት» ያሉት አቶ ናትናኤል፤ የፌዴራል መንግስት ህገመንግስቱን የማስከበር ኃላፊነት ያለበት በመሆኑ ይህንን ኃላፊነቱን በሰላማዊ መንገድ ሊወጣው እንደሚገባ አስገንዝበዋል። «ሕወሃትንም ጨምሮ 107 የፖለቲካ ፓርቲዎች የፈረሙበት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ቃልኪዳን ሰነድ መሰረት ምርጫ ተደርጎ ህገመንግስቱ እስከሚቀየር ድረስ አሁን ያለውን ህገመንግስት የማክበር ግዴታ ሁሉም ሃይሎች ለመወጣት ቁርጠኝነታቸውን ማሳየት አለባቸው» ብለዋል።
በሌላ በኩል ሕወሓት የፌዴራል መንግስት ምርጫውን ለማስተጓጎል ጥረት ቢያደርግ በህግ እንደሚጠይቀው መግለፁን በሚመለከትም ተጠይቀው « በአንድ በኩል ህግን እየጣሱ በሌላ በኩልም ተጠያቂነትን አሰፍናለሁ የሚለው ነገር የሚያስኬድ አይመስለኝም» ብለዋል፡፡ የፌዴራል መንግስቱን ስልጣን የሚጋፉ ከሆነና የሚወስደውንም እርምጃዎች አንቀበልም የሚሉ ከሆነ እነሱም በህግ ማንንም ተጠያቂ ሊያደርጉ የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገቡ ተናግረዋል።
የህብር ኢትዮጵያ ሊቀመንበር አቶ ግርማ በቀለም «የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስቸኳይ ጉባኤው ከትግራይ ክልል ምርጫ ጋር በተያያዘ ጠንካራ ውሳኔ ያስተላልፋል ብለን እንጠብቃለን»ብለዋል።
በተለይም በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል ያለውን የፖለቲካ ውጥረት የሚያረግብ ውሳኔ ማስተላለፍ እንደሚገባው አሳስበዋል። ሁሉንም አካላት ያማከለ የፖለቲካ ድርድር ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል። ለዚህም አንዱ ሌላውን ለማሸነፍ ከማሰብ ብቻ ሳይሆን በቅንነትና በቁርጠኝነት አገርን ከትርምስ የማዳን ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚገባው አመልክተዋል።
«አሁንም ቢሆን በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ችግሮች መስማትና ማድመጥ የማይፈልገውን ነገር ሁሉ መስማትና ማድመጥ የማይፈልገውን ነገር ሁሉ ሊያደምጥበት የሚገባ ነገር መፈጠር አለበት» ያሉት ሊቀመንበሩ ፣ መንግስት ወይም የፌደሬሽን ምክር ቤት በጉዳዩ ላይ ቁርጠኛ መሆናቸውን ካሳወቁ ሁሉም ዜጋ ሊተባበር እንደሚችል አስረድተዋል።
በፓርቲዎች መካከል ያለው ግንኙነት ጤናማ እና ልዩነቶች ያለግጭት የሚስተናገዱበት ሁኔታ መፈጠር እንደሚገባው አመልክተው፣ በተለይም ሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች የገባነውን ቃል መተግበር ይጠበቅብናል ብለዋል ። «ይህን ቃልኪዳን ለማክበር መንግስት ቁርጠኝነቱን ካሳየና ሕወሓት ለማክበር ካልፈለገ ጉዳዩ በሁለቱ ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን የመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ጉዳይ ነው» በማለት ገልፀዋል።
በተያያዘ ዜና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባል የሆኑ የትግራይ ክልል ተወላጆች ምክር ቤቱ ዛሬ የሚካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ አጀንዳ ያልተገለፀላቸው በመሆኑ በስብሰባው እንደማይሳተፉ በደብዳቤ ገልፀዋል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 30/2012
የፌዴሬሽን ምክር ቤት የትግራይ ክልል የምርጫ እንቅስቃሴን በተመለከተ እየመከረ ነው
---------------------------------
የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ የትግራይ ክልላዊ መንግስት አካሂደዋለሁ ባለው ምርጫ ዙሪያ የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦችን ለፌደሬሽን ምክር ቤት ማቅረቡን አስታውቋል፡፡
በኮሮና ስጋት ምክንያት በአገር ደረጃ ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ የተወሰነውን ምርጫ በተለይም ክልሉ ለማካሄድ ወስኖ የምርጫ ቦርድ ማቋቋሙ ህገ መንግስትን የሚጥስ ጉዳይ መሆኑን አመላክቷል፡፡
በሌላ በኩል በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም እንደ ራያ ዴሞክራሲያው ፓርቲና የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ምርጫውን በሙሉ ዝግጅት ለመሳተፍ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታ ሳይኖር በዚህ ወቅት ምርጫ መደረጉ አግባብነት የለውም ብለው ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነት ያለው መሆኑን ጉባኤው በውሳኔ ሀሳብነት አካቶታል፡፡
እንደ ወልቃይትና ራያ ባሉ አካባቢዎች ከማንነት ጉዳይ ጋር የተነሱ ቅሬታዎች ከምርጫው ጋር ተያይዞ በአካባቢዎቹ የሰብዊ መብት ጥሰት እየተፈፀመ ነው በሚል የቀረቡ አቤቱታዎችም ህገ መንግስታዊ መሰረት ያላቸው በመሆኑ ሊጤኑ እንደሚገባ ጉባኤው አመልክቷል፡፡
የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ያቀረባቸውን የውሳኔ ሀሳቦችን ተከትሎ የፌደሬሽን ምክር ቤት ይበጃል ይበጃል ያለውን ውሳኔ እንዲያሳልፍ ጠይቋል፡፡
የኢቢሲ ዘገባ እንዳመለከተው የፌደሬሽን ምክር ቤትም ዛሬ በጠራው አስቸኳይ ስብሰባው የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ባቀረበለት የውሳኔ ሀሳቦች ዙሪያ በዝግ እየመከረ ይገኛል፤ ይህን ተከትሎም የምክር ውይይት ካደረገበት በኋላ ውሳኔም ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
---------------------------------
የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ የትግራይ ክልላዊ መንግስት አካሂደዋለሁ ባለው ምርጫ ዙሪያ የተለያዩ የውሳኔ ሀሳቦችን ለፌደሬሽን ምክር ቤት ማቅረቡን አስታውቋል፡፡
በኮሮና ስጋት ምክንያት በአገር ደረጃ ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ የተወሰነውን ምርጫ በተለይም ክልሉ ለማካሄድ ወስኖ የምርጫ ቦርድ ማቋቋሙ ህገ መንግስትን የሚጥስ ጉዳይ መሆኑን አመላክቷል፡፡
በሌላ በኩል በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም እንደ ራያ ዴሞክራሲያው ፓርቲና የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ምርጫውን በሙሉ ዝግጅት ለመሳተፍ የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታ ሳይኖር በዚህ ወቅት ምርጫ መደረጉ አግባብነት የለውም ብለው ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነት ያለው መሆኑን ጉባኤው በውሳኔ ሀሳብነት አካቶታል፡፡
እንደ ወልቃይትና ራያ ባሉ አካባቢዎች ከማንነት ጉዳይ ጋር የተነሱ ቅሬታዎች ከምርጫው ጋር ተያይዞ በአካባቢዎቹ የሰብዊ መብት ጥሰት እየተፈፀመ ነው በሚል የቀረቡ አቤቱታዎችም ህገ መንግስታዊ መሰረት ያላቸው በመሆኑ ሊጤኑ እንደሚገባ ጉባኤው አመልክቷል፡፡
የሕገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ያቀረባቸውን የውሳኔ ሀሳቦችን ተከትሎ የፌደሬሽን ምክር ቤት ይበጃል ይበጃል ያለውን ውሳኔ እንዲያሳልፍ ጠይቋል፡፡
የኢቢሲ ዘገባ እንዳመለከተው የፌደሬሽን ምክር ቤትም ዛሬ በጠራው አስቸኳይ ስብሰባው የህገ መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ባቀረበለት የውሳኔ ሀሳቦች ዙሪያ በዝግ እየመከረ ይገኛል፤ ይህን ተከትሎም የምክር ውይይት ካደረገበት በኋላ ውሳኔም ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የሩሲያ የኮሮና ቫይረስ ክትባት የኮቪድ 19 በሽታን የመቋቋም ምልክት እያሳየ ነው
የሩሲያ የኮሮና ቫይረስ ክትባት የኮቪድ 19 በሽታን የመቋቋም ምልክት እያሳየ መሆኑን የአገሪቱ ሳይንቲስቶች
አስታወቁ።
ቢ ቢ ሲ እንደዘገበው የሩሲያ ሳይንቲስቶች የኮሮና ቫይረስ ክትባት ውጤት በተመለከተ የመጀመሪያውን ሪፖርት
ለህትመት አብቅተዋል።
በህክምና መጽሄት ላይ የወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው ክትባቱ የተሰጣቸው እያንዳንዶቹ ሰዎች ቫይረሱን ለመዋጋት
የሚያስችላቸው የመከላከል አቅም (አንቲቦዲ) አጎልብተዋል።
ሩሲያ ክትባቱ በአገር ውስጥ ስራ ላይ እንዲውል በነሀሴ ወር ፍቃድ የሰጠች ብቸኛ አገር መሆኗም ተገልጿል።
ኤክስፐርቶች የክትባቱን ብቃትና ደህንነት ለማረጋገጥ የተደረገው ሙከራ በጣም አነሰተኛ ነው ማለታቸውም
ተጠቅሷል።
ሆኖም የተገኘው ውጤት የክትባቱ ውጤታማነት የሚያመላክት መሆኑ በአገሪቱ እየተገለጸ ነው።
የክትባቱ ሙከራ በሰኔና ሀምሌ ወራት ሁለት ጊዜ መካሄዱ በሪፖርቱ የተጠቀሰ ሲሆን፤ በእያንዳንዱ ሙከራ ለ38 ፈቃደኛ
ለሆኑ ጤነኛ ሰዎች ክትባቱ መሰጠቱ ተመልክቷል።
ከ18 እስከ 60 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ሰዎች ላይ ለ42 ቀናት ክትትል መደረጉና በሶስት ሳምንታት ውስጥ
የመከላከል አቅም (አንቲቦዲ) ማጎልበታቸው ነው የተገለጸው።
በአብዛኛው የታየው የክትባቱ የጎንዮሽ ጉዳትም የእራስ ምታት ህመምና የመገጣጠሚያ ህመም መሆኑ ተጠቁሟል።
የኮቪድ 19 በሽታን ከመከላከል አንጻር የክትባቱን ደህንነትና ውጤታማነት የበለጠ ለማረጋገጥ የክትባቱን ሙከራ
በስፋትና ለረጅም ጊዜ በሚቆይ መልኩ ማካሄድና ተጨማሪ ክትትል እንደሚያስፈልግ በሪፖርቱ መጠቀሱ ተመልክቷል።
በክትባቱ የ3ኛ ዙር ሙከራ ከተለያዩ የዕድሜ ክልሎች የሆኑ 40 ሺህ ፈቃደኞች እንደሚሳተፉም ተጠቅሷል።
የሩሲያ የኮሮና ቫይረስ ክትባት የኮቪድ 19 በሽታን የመቋቋም ምልክት እያሳየ መሆኑን የአገሪቱ ሳይንቲስቶች
አስታወቁ።
ቢ ቢ ሲ እንደዘገበው የሩሲያ ሳይንቲስቶች የኮሮና ቫይረስ ክትባት ውጤት በተመለከተ የመጀመሪያውን ሪፖርት
ለህትመት አብቅተዋል።
በህክምና መጽሄት ላይ የወጣው ሪፖርት እንዳመለከተው ክትባቱ የተሰጣቸው እያንዳንዶቹ ሰዎች ቫይረሱን ለመዋጋት
የሚያስችላቸው የመከላከል አቅም (አንቲቦዲ) አጎልብተዋል።
ሩሲያ ክትባቱ በአገር ውስጥ ስራ ላይ እንዲውል በነሀሴ ወር ፍቃድ የሰጠች ብቸኛ አገር መሆኗም ተገልጿል።
ኤክስፐርቶች የክትባቱን ብቃትና ደህንነት ለማረጋገጥ የተደረገው ሙከራ በጣም አነሰተኛ ነው ማለታቸውም
ተጠቅሷል።
ሆኖም የተገኘው ውጤት የክትባቱ ውጤታማነት የሚያመላክት መሆኑ በአገሪቱ እየተገለጸ ነው።
የክትባቱ ሙከራ በሰኔና ሀምሌ ወራት ሁለት ጊዜ መካሄዱ በሪፖርቱ የተጠቀሰ ሲሆን፤ በእያንዳንዱ ሙከራ ለ38 ፈቃደኛ
ለሆኑ ጤነኛ ሰዎች ክትባቱ መሰጠቱ ተመልክቷል።
ከ18 እስከ 60 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙት ሰዎች ላይ ለ42 ቀናት ክትትል መደረጉና በሶስት ሳምንታት ውስጥ
የመከላከል አቅም (አንቲቦዲ) ማጎልበታቸው ነው የተገለጸው።
በአብዛኛው የታየው የክትባቱ የጎንዮሽ ጉዳትም የእራስ ምታት ህመምና የመገጣጠሚያ ህመም መሆኑ ተጠቁሟል።
የኮቪድ 19 በሽታን ከመከላከል አንጻር የክትባቱን ደህንነትና ውጤታማነት የበለጠ ለማረጋገጥ የክትባቱን ሙከራ
በስፋትና ለረጅም ጊዜ በሚቆይ መልኩ ማካሄድና ተጨማሪ ክትትል እንደሚያስፈልግ በሪፖርቱ መጠቀሱ ተመልክቷል።
በክትባቱ የ3ኛ ዙር ሙከራ ከተለያዩ የዕድሜ ክልሎች የሆኑ 40 ሺህ ፈቃደኞች እንደሚሳተፉም ተጠቅሷል።
በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ሊመረት ነው
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ከአንድ ወር በኋላ ማምረት እንደሚጀመር የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለኢዜአ እንደተናገሩት ኮሮናቫይረስን የመመርመር አቅምን ከፍ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው።
በአሁኑ ወቅትም ከአንድ ወር በኋላ ከቻይና መንግሥት ጋር በመተባበር የመመርመሪያ ኪት ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
ለእዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ድጋፉን ከምታደርገው የቻይና መንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል።
“የመመርመሪያ ኪቱን በአገር ውስጥ ማምረት ሲጀመር ከውጭ የሚገባውን ኪት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል” ያሉት ዶክተር ደረጀ፣ ምርቱ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት እንደሚዳረስም ተናግረዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የመመርመር አቅም በእጅጉ ከፍ እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል በአሁኑ ወቅት የኢንፌክሽን መከላከያ ግብዓቶች በኢትዮጵያ በስፋት መመረት መጀመራቸውን ጠቁመው፣ የኮሮናቫይረስ መከላከያ ቁሶችን ወደ ውጭ አገራት መላክ መጀመሩንም ገልጸዋል።
እንድ ኢዜአ ዘገባ፤ በሐዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እነዚህን ቁሶች የሚያመርቱ ኩባንያዎች ቀዳሚ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 52 የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት የሚገኙ ሲሆን በእነዚህም በቀን ከ20 ሺህ በላይ ናሙናዎችን መመርመር ተችሏል።
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ከአንድ ወር በኋላ ማምረት እንደሚጀመር የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ ለኢዜአ እንደተናገሩት ኮሮናቫይረስን የመመርመር አቅምን ከፍ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው።
በአሁኑ ወቅትም ከአንድ ወር በኋላ ከቻይና መንግሥት ጋር በመተባበር የመመርመሪያ ኪት ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
ለእዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ድጋፉን ከምታደርገው የቻይና መንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል።
“የመመርመሪያ ኪቱን በአገር ውስጥ ማምረት ሲጀመር ከውጭ የሚገባውን ኪት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል” ያሉት ዶክተር ደረጀ፣ ምርቱ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት እንደሚዳረስም ተናግረዋል።
ከእዚህ በተጨማሪ በየጊዜው እያደገ የመጣውን የመመርመር አቅም በእጅጉ ከፍ እንደሚያደርገው ጠቁመዋል።
በሌላ በኩል በአሁኑ ወቅት የኢንፌክሽን መከላከያ ግብዓቶች በኢትዮጵያ በስፋት መመረት መጀመራቸውን ጠቁመው፣ የኮሮናቫይረስ መከላከያ ቁሶችን ወደ ውጭ አገራት መላክ መጀመሩንም ገልጸዋል።
እንድ ኢዜአ ዘገባ፤ በሐዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እነዚህን ቁሶች የሚያመርቱ ኩባንያዎች ቀዳሚ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አመልክተዋል።
በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 52 የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት የሚገኙ ሲሆን በእነዚህም በቀን ከ20 ሺህ በላይ ናሙናዎችን መመርመር ተችሏል።