Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
343 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
#አረንጓዴዐሻራ

በአዳማ በከሰዓት በኋላ መርሀ ግብሩ ችግኝ ተከላው ቀጥሏል
***********
(ኢ.ፕ.ድ)

በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከሉ መርሀ ግብር በአዳማ ከተማ ቀጥሏል።

በኢሬቻ ቀበሌ እየተካሄደ የሚገኘውን መርሀ ግብር የኢፕድ ዘጋቢ እየተመለከተ ይገኛል።

ሕብረተሰቡ በበራሱ ወጪ ሳይቀር የገዛውን ችግኝ በመትከል ላይ ይገኛሉ።

ችግኝ መትከል ብቻውን በቂ እንዳልሆነ ተናግረው አስፈላጊውን እንክብካቤ ለማድረግም በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።

በዋሲሁን ተክሌ (አዳማ)
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
#አረንጓዴዐሻራ

የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በጅማ ከተማ በተለያዩ ቀበሌዎች ከሰአትም ቀጥሏል

በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመተከል መርሃ ግብር በጅማ ከተማ ቀጥሏል።

በከሰአት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በግንጆ ጉዱሩ ፣ በህርማታ መንቲና እና እግንጆ ቀበሌዎች ቀጥሏል።

በዳግማዊት አበበ (ጅማ)
#አረንጓዴዐሻራ በኢትዮጵያ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ፣በዕለቱ ለሦስተኛ ጊዜ ከአረጋውያን እናቶችና አባቶች ጋር አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አሰታወቀ።
#አረንጓዴዐሻራ በኢትዮጵያ ‼️
በአንድ ጀንበር የ500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ ግብር በአየር ሃይል ጠቅላይ መምሪያ ተከናወነ
*****
(ኢ.ፕ.ድ)

በአንድ ጀምበር የ500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሐ-ግብር በአየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ተከናውኗል።

በአየር ኃይል ደረጃ በተከናወነው ችግኝ የመትከል መርሐግብር የፌዴራልና የክልል የስራ ኃላፊዎች ከቢሾፍቱ ከተማ የተውጣጡ የማህበረሰብ ክፍሎችና የአየር ኃይል አባላት ተገኝተዋል።

በችግኝ ተከላው ላይ ተገኙት የትምህርት ሚንስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንደተናገሩት ለነገው ትውልድ የምትሆን የለማች ጠንካራ ሀገር ለመገንባት ለተያዘው ራዕይና ግብ የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ፍቃዱ ተሠማ በበኩላቸው አለም በአየር ንብረት መዛባት በጦርነት በወረርሽኝና በሌሎች ችግሮች መወጠሯንና ይህም ከበረሃማነት ጋር ተያይዞ የሚከሰት ችግር መሆኑን ጠቅሰው ችግሩን ከምንጩ ለማድረቅ ለተያዘው ሀገራዊ የአረንጓዴ ልማት ንቅናቄ ችግኝ መትከል አሥፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል።

አቶ ፍቃዱ ሰራዊቱ ችግኞችን መትከል ብቻ ሳይሆን ተንከባክበው ለታለመለት ዓላማ ከግብ በማድረሱ ረገድም እንደ ከዚህ ቀደሙ ጥረታቸውን መቀጠል አለበት ማለታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።