#አረንጓዴዐሻራ
የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አርሶ አደሮች በአረንጓዴ አሻራ ላሳዩት ተሳትፎ አመሰገኑ
********************
(ኢ ፕ ድ)
በዘንድሮው የአረንግዴ ዐሻራ መርሀ ግብር 500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር የመትከል መርሀ ግብር ላይ ለተሳተፉ የአማራ ክልል አርሶአደሮች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ምስጋና አቀረቡ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ዛሬ በክልሉ በተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፤ “ነገን ዛሬ እንትከል የሚለው መልዕክት ለአርሶ አደሮቻችን እጥፍ ድርብ መልዕክት አለው” ብለዋል።
አርሶ አደሮቻችን ምርታማ እንዲሆኑ የመሬቱ ለምነት እንዲጠበቅ በየአከባቢው ዛፎች መኖራቸው ከፍተኛ ዋጋ እንዳለው አርሶ አደሮቻችን ብለዋል፤ ርዕሰ መስተዳድሩ።
"ችግኝ መትከል ከግብርና ስራችን ጋር የተቆራኘ የማይለያይ ተግባር ነው፤ ይህን ተግባር አርሶ አደሮች በነቂስ ወጥታችሁ አብራችሁን በመሳተፋችሁ በዋናነትም የእናንተ ስራ ጠቃሚ መሆኑን ተገንዝባችሁ የዚህ በአል ተሳታፊ በመሆናችሁ አመሰግናለሁ” ብለዋል።
ይህን ችግኝ በዘመቻ እንተክላላን፤ መትከል አንድ ነገር ነው፤ የመጨረሻውና ዋናው ነገር የተከልነው ችግኝ ፀድቆ ለአከባቢው ጥቅምና አገልግሎት የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ማድረስ ነውም ብለዋል።
“የፍራፍሬ ከሆነ ከፍሬው ለመቋደስ መስራት መቻል አለብን፤ የተከልነው ዛፍ ከሆነም የአከባቢውን ስነ ምህዳር እንዲጠብቅ ማድረግ አለብን፤ ይህ ካልሆነ ከንቱ ልፋት ነው” ሲሉም ነው የተናገሩት።
“ችግኞቹን ከብዙ ንክኪ በመጠበቅ እንክብካቤ ተደርጎላቸው ፀድቀው እናንተን እንዲጠቅሙ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታደርጉ አደራ እላላሁ” ሲሉም ነው መልዕክታቸውን ያስተላለፉት።
በሀይማኖት ከበደ
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓም
የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አርሶ አደሮች በአረንጓዴ አሻራ ላሳዩት ተሳትፎ አመሰገኑ
********************
(ኢ ፕ ድ)
በዘንድሮው የአረንግዴ ዐሻራ መርሀ ግብር 500 ሚሊዮን ችግኝ በአንድ ጀምበር የመትከል መርሀ ግብር ላይ ለተሳተፉ የአማራ ክልል አርሶአደሮች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ምስጋና አቀረቡ።
ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር ይልቃል ከፋለ ዛሬ በክልሉ በተካሄደው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር ላይ ባደረጉት ንግግር፤ “ነገን ዛሬ እንትከል የሚለው መልዕክት ለአርሶ አደሮቻችን እጥፍ ድርብ መልዕክት አለው” ብለዋል።
አርሶ አደሮቻችን ምርታማ እንዲሆኑ የመሬቱ ለምነት እንዲጠበቅ በየአከባቢው ዛፎች መኖራቸው ከፍተኛ ዋጋ እንዳለው አርሶ አደሮቻችን ብለዋል፤ ርዕሰ መስተዳድሩ።
"ችግኝ መትከል ከግብርና ስራችን ጋር የተቆራኘ የማይለያይ ተግባር ነው፤ ይህን ተግባር አርሶ አደሮች በነቂስ ወጥታችሁ አብራችሁን በመሳተፋችሁ በዋናነትም የእናንተ ስራ ጠቃሚ መሆኑን ተገንዝባችሁ የዚህ በአል ተሳታፊ በመሆናችሁ አመሰግናለሁ” ብለዋል።
ይህን ችግኝ በዘመቻ እንተክላላን፤ መትከል አንድ ነገር ነው፤ የመጨረሻውና ዋናው ነገር የተከልነው ችግኝ ፀድቆ ለአከባቢው ጥቅምና አገልግሎት የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ማድረስ ነውም ብለዋል።
“የፍራፍሬ ከሆነ ከፍሬው ለመቋደስ መስራት መቻል አለብን፤ የተከልነው ዛፍ ከሆነም የአከባቢውን ስነ ምህዳር እንዲጠብቅ ማድረግ አለብን፤ ይህ ካልሆነ ከንቱ ልፋት ነው” ሲሉም ነው የተናገሩት።
“ችግኞቹን ከብዙ ንክኪ በመጠበቅ እንክብካቤ ተደርጎላቸው ፀድቀው እናንተን እንዲጠቅሙ የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታደርጉ አደራ እላላሁ” ሲሉም ነው መልዕክታቸውን ያስተላለፉት።
በሀይማኖት ከበደ
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓም
#አረንጓዴዐሻራ በኢትዮጵያ ‼
እስካሁን በአገር አቀፍ ደረጃ 372 ሚሊዮን 500 ሺህ ችግኞች መተከላቸው ተገለጸ።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ አዲስ አበባ ከሚገኘው የሁነት መከታተያ ማዕከል ሆነው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ከጠዋቱ 12 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ባለው መረጃ 372 ሚሊዮን 500 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓም
እስካሁን በአገር አቀፍ ደረጃ 372 ሚሊዮን 500 ሺህ ችግኞች መተከላቸው ተገለጸ።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ አዲስ አበባ ከሚገኘው የሁነት መከታተያ ማዕከል ሆነው በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ ከጠዋቱ 12 ጀምሮ እስካሁን ድረስ ባለው መረጃ 372 ሚሊዮን 500 ሺህ ችግኞች ተተክለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓም
#አረንጓዴዐሻራ
በአዳማ በከሰዓት በኋላ መርሀ ግብሩ ችግኝ ተከላው ቀጥሏል
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከሉ መርሀ ግብር በአዳማ ከተማ ቀጥሏል።
በኢሬቻ ቀበሌ እየተካሄደ የሚገኘውን መርሀ ግብር የኢፕድ ዘጋቢ እየተመለከተ ይገኛል።
ሕብረተሰቡ በበራሱ ወጪ ሳይቀር የገዛውን ችግኝ በመትከል ላይ ይገኛሉ።
ችግኝ መትከል ብቻውን በቂ እንዳልሆነ ተናግረው አስፈላጊውን እንክብካቤ ለማድረግም በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
በዋሲሁን ተክሌ (አዳማ)
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
በአዳማ በከሰዓት በኋላ መርሀ ግብሩ ችግኝ ተከላው ቀጥሏል
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሀ ግብር በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከሉ መርሀ ግብር በአዳማ ከተማ ቀጥሏል።
በኢሬቻ ቀበሌ እየተካሄደ የሚገኘውን መርሀ ግብር የኢፕድ ዘጋቢ እየተመለከተ ይገኛል።
ሕብረተሰቡ በበራሱ ወጪ ሳይቀር የገዛውን ችግኝ በመትከል ላይ ይገኛሉ።
ችግኝ መትከል ብቻውን በቂ እንዳልሆነ ተናግረው አስፈላጊውን እንክብካቤ ለማድረግም በቁርጠኝነት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
በዋሲሁን ተክሌ (አዳማ)
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
#አረንጓዴዐሻራ
የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በጅማ ከተማ በተለያዩ ቀበሌዎች ከሰአትም ቀጥሏል
በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመተከል መርሃ ግብር በጅማ ከተማ ቀጥሏል።
በከሰአት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በግንጆ ጉዱሩ ፣ በህርማታ መንቲና እና እግንጆ ቀበሌዎች ቀጥሏል።
በዳግማዊት አበበ (ጅማ)
የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በጅማ ከተማ በተለያዩ ቀበሌዎች ከሰአትም ቀጥሏል
በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመተከል መርሃ ግብር በጅማ ከተማ ቀጥሏል።
በከሰአት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በግንጆ ጉዱሩ ፣ በህርማታ መንቲና እና እግንጆ ቀበሌዎች ቀጥሏል።
በዳግማዊት አበበ (ጅማ)
#አረንጓዴዐሻራ በኢትዮጵያ ‼
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ፣በዕለቱ ለሦስተኛ ጊዜ ከአረጋውያን እናቶችና አባቶች ጋር አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አሰታወቀ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሐ ግብር ፣በዕለቱ ለሦስተኛ ጊዜ ከአረጋውያን እናቶችና አባቶች ጋር አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አሰታወቀ።