ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደህንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንገነባለን- ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
“ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደህንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንገነባለን” ሲሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ ገለጹ።
በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው መርሐ-ግብር መሰረት ኢትዮጵያዊያን በነቂስ ወጥተው ችግኝ እየተከሉ ነው።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያዊያን ዝናቡ ሳይበግራቸው ችግኝ በመትከል ላይ ይገኛሉ።
ችግኝ መትከል የሕልውና ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በድርቅ የምትጠቃ አገር በመሆኗ አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ከመትከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጉዳይ ነው ብለዋል።
“ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደህንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንገነባለን” ብለዋል ሚኒስትሩ።
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓም
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
“ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደህንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንገነባለን” ሲሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ ገለጹ።
በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል በተያዘው መርሐ-ግብር መሰረት ኢትዮጵያዊያን በነቂስ ወጥተው ችግኝ እየተከሉ ነው።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት ኢትዮጵያዊያን ዝናቡ ሳይበግራቸው ችግኝ በመትከል ላይ ይገኛሉ።
ችግኝ መትከል የሕልውና ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ በተደጋጋሚ በድርቅ የምትጠቃ አገር በመሆኗ አረንጓዴ አሻራ ችግኝ ከመትከል ባለፈ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ጉዳይ ነው ብለዋል።
“ችግኞችን በጋራ እንደተከልን ሁሉ ሰላማችንን በጋራ በመጠበቅ ደህንነቷ የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት አገር እንገነባለን” ብለዋል ሚኒስትሩ።
ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓም
አብሮ ታሪክ መስራት ትልቅ ድል ነው-አቶ ደመቀ መኮንን
***************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሃግብርን በአዲስ አበባ አስጀምረዋል፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ባደረጉት ንግግር የዛሬው ቀን ኢትዮጵያን ፀጋ በማልበስ ትልቅ ታሪክ እየተሰራበት ያለ ቀን መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኝ በመትከል ሀገራችን ለማልበስ ለትውልድ የተመቸ ሁኔታ ለመፍጠር በመላ ሀገሪቱ ታሪክ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ካሳካነው በላይ ሪከርዳችንን በማሻሻል ውጤት የምናሳይበት ቀን ነውም ብለዋል፡፡
500 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀንበር መትከል ማለት የመስራት አቅማችንን የበለጠ የሚያነሳሳ እና ለተሻለ እንድንዘጋጅ የሚያደርገን ነው ብለዋል አቶ ደመቀ፡፡
ትውልዱ የራሱን ታሪክ የሚሰራና ለመጪው ትውልድ የተመቸች ኢትዮጵያን ለማስረከብ እየሰራ ነው ያሉት አቶ ደመቀ በዚህም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡
እንደ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘገባ “ስናብር ያምርብናል፤ አብሮ ታሪክ መስራት ትልቅ ድል ነው ”ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ እንትጋ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
***************
(ኢ ፕ ድ)
ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሃግብርን በአዲስ አበባ አስጀምረዋል፡፡
ምክትል ጠቅላይ ሚንስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ባደረጉት ንግግር የዛሬው ቀን ኢትዮጵያን ፀጋ በማልበስ ትልቅ ታሪክ እየተሰራበት ያለ ቀን መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኝ በመትከል ሀገራችን ለማልበስ ለትውልድ የተመቸ ሁኔታ ለመፍጠር በመላ ሀገሪቱ ታሪክ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡
ባለፉት ዓመታት ካሳካነው በላይ ሪከርዳችንን በማሻሻል ውጤት የምናሳይበት ቀን ነውም ብለዋል፡፡
500 ሚሊየን ችግኝ በአንድ ጀንበር መትከል ማለት የመስራት አቅማችንን የበለጠ የሚያነሳሳ እና ለተሻለ እንድንዘጋጅ የሚያደርገን ነው ብለዋል አቶ ደመቀ፡፡
ትውልዱ የራሱን ታሪክ የሚሰራና ለመጪው ትውልድ የተመቸች ኢትዮጵያን ለማስረከብ እየሰራ ነው ያሉት አቶ ደመቀ በዚህም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡
እንደ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዘገባ “ስናብር ያምርብናል፤ አብሮ ታሪክ መስራት ትልቅ ድል ነው ”ሲሉም ገልጸዋል፡፡ የተተከሉ ችግኞችን በመንከባከብ እንትጋ ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡