Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
24.8K subscribers
41.2K photos
343 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
በመላው ኢትዮጵያ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል መርሃ ግብር ተጀመረ
****************
(ኢ.ፕ.ድ)

በአገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኞችን የመተከል መርሃ ግብር በይፋ ተጀምሯል።

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ሰላማዊት ካሳ እንደገለፁት፤ ኢትዮጵያዊ ን ከጫፍ እስከ ጫፋ በመነሳት በአካባቢያቸው የአረጓዴ አሻራቸውን እያኖሩ ነው።

በአንድ ጀንበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከጠዋቱ 12ሰዓት ጀምሮ በመላ አገሪቱ በይፋ መጀመሩን ገልፀዋል።

ይህ አረንጓዴ ዐሻራ የዛሬን ትውልድ ህይወቱን የሚድስ ለነገው ተስፋ የሚጭር መሆኑን ገልፀዋል።

ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበሱን ሁነት ከሶስት ሺህ በላይ የሚዲያ ባለሙያዎች እየዘገቡ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።

ከዘጠኝ ሺህ በላይ ቦታዎች የሚተከሉ ችግኞች በሳተላይት መከታተል የሚስችል ዝግጅትም ተደርጓል ብለዋል።

መላው ህዝብ በዚህ ታሪካዊ ዕለት የራሱን ዐሻራ በማኖር ዜጋዊ ድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

በአንድ ጀንበር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳድሮች ጨምሮ 500 ሚሊዮን ችግኞች ከንጋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት 500ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉ ይሆናል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአንድ ጀምበር 500ሚሊዮን ችግኞችን ተክለን የራሳችንን ሪከርድ እንስበር ሲሉ ለመላው ህዝብ ጥሪ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ችግኞችን የሚተከሉበት አካባቢዎች ሁሉ መረጃ የሚሰበሰብበት ሲችዌሽን ክፍል ተዝጋጅቶ ሥራውን እያከናወነም ይገኛል።

ሐምሌ 10 ቀን 2015 ዓ.ም
በጌትነት ምሕረቴ
#አረንጓዴዐሻራ_በጅማ‼️

በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት የአረንጓዴ ዐሻራ ዝግጅት በጅማ በኢፕድ ዐይን‼️
#አረንጓዴዐሻራ_በአዳማ‼️

በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኞች የሚተከሉበት የአረንጓዴ ዐሻራ ዝግጅት በአዳማ በኢፕድ ዐይን‼️