አትሌት መሠረት ደፋር በናጉያ ማራቶን ነገ ትሮጣለች
****************************
(ኢ.ፕ.ድ)
አትሌት መሠረት ደፋር በናጉያ ማራቶን ነገ መጋቢት 1/2011 ዓ. ም. ጃፓን ላይ ትሮጣለች፡፡
በባርሴሎና ማራቶን፣ በፈረንሳይና በጣሊያን በሮም ደግሞ የግማሽ ማራቶን ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን አትሌቶች በሳምንቱ ማብቂያ ይወዳደራሉ፡፡
ከእነዚህ መካከል ደግሞ፡- አትሌት አበበ ነገዎ፣ አትሌት ልመንህ፣ አትሌት ቁፍቱ፣ አትሌት ደራራ ደሳለኝ፣ አትሌት ሌንጮ ተስፋዬና ሌሎችም በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እንደሚወዳደሩ ከኢትዮጵ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
****************************
(ኢ.ፕ.ድ)
አትሌት መሠረት ደፋር በናጉያ ማራቶን ነገ መጋቢት 1/2011 ዓ. ም. ጃፓን ላይ ትሮጣለች፡፡
በባርሴሎና ማራቶን፣ በፈረንሳይና በጣሊያን በሮም ደግሞ የግማሽ ማራቶን ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያን አትሌቶች በሳምንቱ ማብቂያ ይወዳደራሉ፡፡
ከእነዚህ መካከል ደግሞ፡- አትሌት አበበ ነገዎ፣ አትሌት ልመንህ፣ አትሌት ቁፍቱ፣ አትሌት ደራራ ደሳለኝ፣ አትሌት ሌንጮ ተስፋዬና ሌሎችም በርካታ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች እንደሚወዳደሩ ከኢትዮጵ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
የዓለም ጤና ድርጅት በኬፕ ቨርዴ እያካሄደ ባለው ሁለተኛው የአፍሪካ የጤና ፎረም ላይ ባወጣው ሪፖርት አፍሪካ በበሽታ ምክንያት በየዓመቱ 2 ነጥብ 4 ትሪሊየን ዶላር እንደምታጣ ገልጿል፡፡
የኦል አፍሪካን ዘገባ እንደሚያመለክተው እ.አ.አ. በ2015 በ 47 ቱ የአፍሪካ ሀገራት 630 ሚሊዮን ሰዎች በተለያዩ በሽታዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ በሪፖርቱ መሰረት እንደ የልብ ህመም፣ ካንሰር፣ ስትሮክና ስኳር ያሉ በሽታዎች በዓለም ላይ ቀዳሚ ገዳዮች ሆነዋል፡፡ በበሽታ ምክንያት ከሚከሰቱ አስር ሞቶች ሰባቱ በእነዚህ በሽታዎች ምክንያት የሚከሰቱም ናቸው፡፡
በአፍሪካም ከፍተኛ ጫና በመፍጠር 37 በመቶ ድርሻ ያላቸው ተላላፊ ያልሆኑ በሽዎች ሲሆኑ ተላላፊ በሽታዎች ደግሞ 36 በመቶ ድርሻ በመያዝና ከፍተኛ ወጪ በማስወጣት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ የእናቶችና ሕፃናት በሽታዎች እንዲሁም ከአመጋገብ ጋር የተያያዙ የጤና እክሎች ደግሞ ቀሪውን ድርሻ ይይዛሉ ተብሏል።
በሪፖርቱ እ.አ.አ. በ 2030 የሚጠናቀቀው የዘላቂ ልማት ግብ እቅድ የሚሳካ ከሆነ አፍሪካ 47 በመቶ ወጪዋን በመቀነስ ኪሳራዋን ማስቀረት እንደምትችል ተገልጿል፡፡ ሆኖም በዘላቂ ልማት ግብ የተቀመጠው ዓለም አቀፍ የጤና ተደራሽነት የአራት ዓመት አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆኑን የጤና ድርጅቱ የአፍሪካ ዳይሬክተር ዶክተር ማትሺዲሶ ሞይቲ ገልጸዋል፡፡
በጤናው ዘርፍ በዘላቂ የልማት ግብ የተቀመጠውን ዓለም አቀፍ የጤና ተደራሸነትን ለማሳካት የአፍሪካ ሀገራት በየዓመቱ በትንሹ 271 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከሀገራቱ አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢ ሰባት ነጥብ አምስት በመቶ በጀት ለጤናው ዘርፍ መመደብ እንዳለበት ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
አዲስ ዘመን መጋቢት 20/2011
የትናየት ፈሩ
የኦል አፍሪካን ዘገባ እንደሚያመለክተው እ.አ.አ. በ2015 በ 47 ቱ የአፍሪካ ሀገራት 630 ሚሊዮን ሰዎች በተለያዩ በሽታዎች ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ በሪፖርቱ መሰረት እንደ የልብ ህመም፣ ካንሰር፣ ስትሮክና ስኳር ያሉ በሽታዎች በዓለም ላይ ቀዳሚ ገዳዮች ሆነዋል፡፡ በበሽታ ምክንያት ከሚከሰቱ አስር ሞቶች ሰባቱ በእነዚህ በሽታዎች ምክንያት የሚከሰቱም ናቸው፡፡
በአፍሪካም ከፍተኛ ጫና በመፍጠር 37 በመቶ ድርሻ ያላቸው ተላላፊ ያልሆኑ በሽዎች ሲሆኑ ተላላፊ በሽታዎች ደግሞ 36 በመቶ ድርሻ በመያዝና ከፍተኛ ወጪ በማስወጣት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል፡፡ የእናቶችና ሕፃናት በሽታዎች እንዲሁም ከአመጋገብ ጋር የተያያዙ የጤና እክሎች ደግሞ ቀሪውን ድርሻ ይይዛሉ ተብሏል።
በሪፖርቱ እ.አ.አ. በ 2030 የሚጠናቀቀው የዘላቂ ልማት ግብ እቅድ የሚሳካ ከሆነ አፍሪካ 47 በመቶ ወጪዋን በመቀነስ ኪሳራዋን ማስቀረት እንደምትችል ተገልጿል፡፡ ሆኖም በዘላቂ ልማት ግብ የተቀመጠው ዓለም አቀፍ የጤና ተደራሽነት የአራት ዓመት አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆኑን የጤና ድርጅቱ የአፍሪካ ዳይሬክተር ዶክተር ማትሺዲሶ ሞይቲ ገልጸዋል፡፡
በጤናው ዘርፍ በዘላቂ የልማት ግብ የተቀመጠውን ዓለም አቀፍ የጤና ተደራሸነትን ለማሳካት የአፍሪካ ሀገራት በየዓመቱ በትንሹ 271 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከሀገራቱ አጠቃላይ ዓመታዊ ገቢ ሰባት ነጥብ አምስት በመቶ በጀት ለጤናው ዘርፍ መመደብ እንዳለበት ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
አዲስ ዘመን መጋቢት 20/2011
የትናየት ፈሩ
❤1👍1
‘ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፎ የሚሰጥ ውይይት ፈጽሞ አላደረገችም፣ ወደፊትም አታደርግም’
~~~~~~~~~~
[ኢ.ፕ.ድ]
በትናንትናው እለት የኢትዮጵያ፣ የግብጽ እና የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የውሃ ሃብት ሚኒስትሮች እና የልዑካን ቡድኖቻቸው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ እኤአ ከጃንዋሪ 13 እስከ 15 ቀን 2020 በዋሽንግተን ዲሲ ሲያካሂዱት የነበረው ውይይት በጥሩ ውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል።
የውይይቱን ውጤት እና የኢትዮጵያን አቋም አስመልክቶ ክቡር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የተነሱ ዋና ዋና ሃሳቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል።
• ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድቡ ጋር በተያያዘ ትናንት በተደረገው የመግባቢያ ነጥብ ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፎ የሚሰጥ አንዳችም ውይይት ፈጽሞ አላደረገችም፣ ይሄ ወደፊትም የኢትዮጵያ ቀዳሚው መርህ ሆኖ ይቀጥላል።
• ከግድቡ ጋር የሚደረጉ ድርድሮች እና ውይይቶች ኢትዮጵያ ሌሎች ግድቦችን የመገንባት መብቷን የማይጋፋ ነው።
• ከዚህ ቀደም ለውይይቱ መጓተት እንደምክንያት ሲነሳ የነበረውን የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ከታችኛው ተፋሰስ አገራት ግድቦች የማያያዝ ውኔታ እንደቀር ማድረግ ተችሏል።
• ግድቡ ሲጠናቀቅ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የቱሪዝምና የአሳ እርባታ ልማቶችን ይኖሩታል።
• የቴክኒክ ውይይቱ ብሎም ከህግ ጋር የሚያያዙት ጉዳዮች አሁንም በዘርፉ ልምድና ክህሎቱ ባላቸው፣ በሐገር ፍቅር እንዲሁም በከፍተኛ ኃላፊነት ብቁ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች እየተመራ ነው።
[ኢ.ፕ.ድ]
በትናንትናው እለት የኢትዮጵያ፣ የግብጽ እና የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የውሃ ሃብት ሚኒስትሮች እና የልዑካን ቡድኖቻቸው በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ እኤአ ከጃንዋሪ 13 እስከ 15 ቀን 2020 በዋሽንግተን ዲሲ ሲያካሂዱት የነበረው ውይይት በጥሩ ውጤት መጠናቀቁ ይታወሳል።
የውይይቱን ውጤት እና የኢትዮጵያን አቋም አስመልክቶ ክቡር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው እና የውሃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ስለሺ በቀለ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም የተነሱ ዋና ዋና ሃሳቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል።
• ኢትዮጵያ ከህዳሴ ግድቡ ጋር በተያያዘ ትናንት በተደረገው የመግባቢያ ነጥብ ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፎ የሚሰጥ አንዳችም ውይይት ፈጽሞ አላደረገችም፣ ይሄ ወደፊትም የኢትዮጵያ ቀዳሚው መርህ ሆኖ ይቀጥላል።
• ከግድቡ ጋር የሚደረጉ ድርድሮች እና ውይይቶች ኢትዮጵያ ሌሎች ግድቦችን የመገንባት መብቷን የማይጋፋ ነው።
• ከዚህ ቀደም ለውይይቱ መጓተት እንደምክንያት ሲነሳ የነበረውን የህዳሴ ግድብ የውሃ ሙሌት ከታችኛው ተፋሰስ አገራት ግድቦች የማያያዝ ውኔታ እንደቀር ማድረግ ተችሏል።
• ግድቡ ሲጠናቀቅ ከኃይል ማመንጨት ባሻገር የቱሪዝምና የአሳ እርባታ ልማቶችን ይኖሩታል።
• የቴክኒክ ውይይቱ ብሎም ከህግ ጋር የሚያያዙት ጉዳዮች አሁንም በዘርፉ ልምድና ክህሎቱ ባላቸው፣ በሐገር ፍቅር እንዲሁም በከፍተኛ ኃላፊነት ብቁ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች እየተመራ ነው።
ፖሊስ ባደረገው ድንገተኛ አሰሳ በርካታ የስልክ ገመዶችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ጋዝ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአዲስ ከተማ ፖሊስ ጥር 6 ቀን 2012 ዓ.ም. በአካባቢው ላይ በተደረገ ድንገተኛ አሰሳ በርካታ የስልክ ገመዶች በሸራ ተሸፍኖ መገኘቱን አስታወቀ።
በተመሳሳይ ጥር 05 ቀን 2012 ዓ/ም በዚሁ አካባቢ በርካታ የስልክ ገመዶችን አከማችተው የተገኙ 2 ተጠርጣሪዎች ከነንብረቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ይታወሳል ሲል የአዲስ አበባ ፓሊስ አስታውቋል።
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ጋዝ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአዲስ ከተማ ፖሊስ ጥር 6 ቀን 2012 ዓ.ም. በአካባቢው ላይ በተደረገ ድንገተኛ አሰሳ በርካታ የስልክ ገመዶች በሸራ ተሸፍኖ መገኘቱን አስታወቀ።
በተመሳሳይ ጥር 05 ቀን 2012 ዓ/ም በዚሁ አካባቢ በርካታ የስልክ ገመዶችን አከማችተው የተገኙ 2 ተጠርጣሪዎች ከነንብረቱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውም ይታወሳል ሲል የአዲስ አበባ ፓሊስ አስታውቋል።
በኢትዮጵያ በየዓመቱ ስምንት ሺህ ሰዎች ራሳቸውን እንደሚያጠፉ ተጠቆመ
**************************************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ በየዓመቱ ስምንት ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ራሳቸውን እንደሚያጠፉ ጥናት አመለከተ። ራስን በራስ የማጥፋት ድርጊት የሥነ ልቦና ጫና ከማሳደሩም በላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስን እንደሚያባብስም ተገልጿል።
በጤና ሚኒስቴር የአዕምሮ ጤና ፕሮግራም ቡድን መሪ ዶክተር ደረጀ አሰፋ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መረጃ፤ አንድ የማህበረሰብ አባል ራስን በማጥፋት ለህልፈት መዳረጉ ማህበራዊ ቀውስን እንደሚያስከትልና ለአገር ብዙ ጥቅም ሊሰጡ የሚችሉ ሰዎች ራሳቸውን ሲያጠፉ በሚባክነው ሀብት ምክንያት በቤተሰብም ሆነ በአገር ደረጃ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንደሚያስከትል ጠቁመዋል።
ወቅታዊ የሆኑ ሰፊ ጥናቶች ባይጠኑም ትንንሽ ጥናቶችና ዓለም አቀፍ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት፤ በኢትዮጵያ ቢያንስ ከአንድ ሚሊዮን ሰዎች 80ዎቹ ራሳቸውን ያጠፋሉ የሚሉት ዶክተር ደረጀ ለማህበረሰቡ ዕድገትና ሌሎች በጎ መስተጋብሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሰው ማጣት ለማህበረሰቡም ብቻ ሳይሆን ለተቀሩት የቤተሰብ አባላትም የስነ ልቦና ጫና እያሳደረ ይገኛል ብለዋል።
ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/Ama/?p=25733
**************************************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ በየዓመቱ ስምንት ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ራሳቸውን እንደሚያጠፉ ጥናት አመለከተ። ራስን በራስ የማጥፋት ድርጊት የሥነ ልቦና ጫና ከማሳደሩም በላይ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስን እንደሚያባብስም ተገልጿል።
በጤና ሚኒስቴር የአዕምሮ ጤና ፕሮግራም ቡድን መሪ ዶክተር ደረጀ አሰፋ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መረጃ፤ አንድ የማህበረሰብ አባል ራስን በማጥፋት ለህልፈት መዳረጉ ማህበራዊ ቀውስን እንደሚያስከትልና ለአገር ብዙ ጥቅም ሊሰጡ የሚችሉ ሰዎች ራሳቸውን ሲያጠፉ በሚባክነው ሀብት ምክንያት በቤተሰብም ሆነ በአገር ደረጃ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንደሚያስከትል ጠቁመዋል።
ወቅታዊ የሆኑ ሰፊ ጥናቶች ባይጠኑም ትንንሽ ጥናቶችና ዓለም አቀፍ ጥናቶች እንደሚያመለክቱት፤ በኢትዮጵያ ቢያንስ ከአንድ ሚሊዮን ሰዎች 80ዎቹ ራሳቸውን ያጠፋሉ የሚሉት ዶክተር ደረጀ ለማህበረሰቡ ዕድገትና ሌሎች በጎ መስተጋብሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሰው ማጣት ለማህበረሰቡም ብቻ ሳይሆን ለተቀሩት የቤተሰብ አባላትም የስነ ልቦና ጫና እያሳደረ ይገኛል ብለዋል።
ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/Ama/?p=25733
27 የምግብ አይነቶች ከገበያ መታገዳቸው ተገለጸ
#Ethiopia : አዲስ አበባ፡- አድራሻቸው የማይታወቁና ተጭበርብረው የተሠሩ 27 የምግብ ምርት ዓይነቶች በሁለተኛው ሩብ ዓመት ከገበያ መታገዳቸውን የኢትዮጵያ የምግብ ፣የመድሐኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥር ባለስልጣን ገለጸ፡፡
ባለስልጣኑ ለአዲስ ዘመን በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጸው፤ በሁለተኛው ሩብ ዓመት በመላው አገሪቱ ለሕብረተሰቡ በብዛት በሚቀርቡ የምግብ ምርቶች ላይ ቁጥጥር ተደርጓል፡፡ በመሆኑም የአምራች ድርጅቶቻቸው አድራሻ የማይታወቁ፣ ተመሳስለውና ተጭበርብረው የተሠሩ የምግብ ምርቶች ገበያ ላይ እየዋሉ ስለመሆናቸው ማረጋገጥ እንደተቻለ ጠቁሟል፡፡
በተደረገው የገበያ ቅኝት የተሟላ ገላጭ ጽሑፍ የሌላቸው፣ አስገዳጅ ብሔራዊ ደረጃን ያላሟሉ፣ አምራች ድርጅቶቻቸውም ሆነ አድራሻቸው የማይታወቁ፣ መለያ ቁጥር የሌላቸው፣ የመጠቀሚያቸውና የተመረቱበት ጊዜ በትክክል ያልታተመባቸውና የታሸጉ ምግቦች መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡
ከገበያ የታገዱት የምግብ ዓይነቶችም ንጹህ የኑግ ዘይት፣ ኢዛና ዘይት፣ ጣና ዘይት፣ ኦሊያድ ዘይት፣ ስኬት የተጣራ ዘይት፣ በቅሳ የምግብ ዘይት፣ አሚን የምግብ ዘይት፣ቀመር የምግብ ዘይት፣ ሎዛ የምግብ ዘይት፣ ዘቢብ ቃህ የምግብ ዘይት፣ ዘመን የኑግ እና የለውዝ ዘይት፣ ማኢዳ የለውዝ ቂቤ፣ ሮዛ ክሬሚ ለውዝ ቅቤም፣ ዳና ቪንቶ፣ ቪንቶ፣አዋሽ የገበታ ጨው፣ሳራ እና ኑስራ ጨው፣ሴፍ የገበታ ጨው፣ሽናጉ የገበታ ጨው፣ወዛቴ የአይወዲን ጨው፣ቃና የገበታ ጨው፣አስሊ የገበታ ጨው፣ ሲሳይ ንጹህ ማርና ቅቤ፣ ወለላ ማር፣ካርቶንስ ካንዲ ፍሩትስ፣ ሊዛ ሎሊፖፕ እና ክሬም ሎሊፖፕ ተጠቅሰዋል፡፡
የክልል ተቆጣጣሪዎችና በየደረጃው የሚገኙ የቁጥጥር አካላት ምርቶቹን ከገበያ ላይ የመሰብሰብ ሥራውን እንዲሠሩ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ ማቅረቡንም አስታውቋል፡፡
ሕብረተሰቡም የትኛውንም የምግብ ምርት ከገበያ ሲገዛ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ እንዲረዳው የተመረተበትንና የመጠቀሚያ የአገልግሎት ጊዜው ትክክለኛነት፣ የደረጃ ምልክት የለጠፈ፣ ያልተፋቀና ያልተሰረዘ መሆኑን፤ የአምራች ድርጅቱ ስምና ሙሉ አድራሻ፣ የምርት መለያ ቁጥር ያሟላ መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለበት ተገልጿል፡፡
ሕብረተሰቡ አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲገጥሙትም ለአካባቢው ፖሊስ ወይም ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በነፃ ስልክ መስመር 8482 ላይ እንዲያሳውቁ ጠይቋል፡፡
አዲስ ዘመን ጥር 8/2012
#Ethiopia : አዲስ አበባ፡- አድራሻቸው የማይታወቁና ተጭበርብረው የተሠሩ 27 የምግብ ምርት ዓይነቶች በሁለተኛው ሩብ ዓመት ከገበያ መታገዳቸውን የኢትዮጵያ የምግብ ፣የመድሐኒትና ጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥር ባለስልጣን ገለጸ፡፡
ባለስልጣኑ ለአዲስ ዘመን በላከው ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጸው፤ በሁለተኛው ሩብ ዓመት በመላው አገሪቱ ለሕብረተሰቡ በብዛት በሚቀርቡ የምግብ ምርቶች ላይ ቁጥጥር ተደርጓል፡፡ በመሆኑም የአምራች ድርጅቶቻቸው አድራሻ የማይታወቁ፣ ተመሳስለውና ተጭበርብረው የተሠሩ የምግብ ምርቶች ገበያ ላይ እየዋሉ ስለመሆናቸው ማረጋገጥ እንደተቻለ ጠቁሟል፡፡
በተደረገው የገበያ ቅኝት የተሟላ ገላጭ ጽሑፍ የሌላቸው፣ አስገዳጅ ብሔራዊ ደረጃን ያላሟሉ፣ አምራች ድርጅቶቻቸውም ሆነ አድራሻቸው የማይታወቁ፣ መለያ ቁጥር የሌላቸው፣ የመጠቀሚያቸውና የተመረቱበት ጊዜ በትክክል ያልታተመባቸውና የታሸጉ ምግቦች መገኘታቸውን ገልጸዋል፡፡
ከገበያ የታገዱት የምግብ ዓይነቶችም ንጹህ የኑግ ዘይት፣ ኢዛና ዘይት፣ ጣና ዘይት፣ ኦሊያድ ዘይት፣ ስኬት የተጣራ ዘይት፣ በቅሳ የምግብ ዘይት፣ አሚን የምግብ ዘይት፣ቀመር የምግብ ዘይት፣ ሎዛ የምግብ ዘይት፣ ዘቢብ ቃህ የምግብ ዘይት፣ ዘመን የኑግ እና የለውዝ ዘይት፣ ማኢዳ የለውዝ ቂቤ፣ ሮዛ ክሬሚ ለውዝ ቅቤም፣ ዳና ቪንቶ፣ ቪንቶ፣አዋሽ የገበታ ጨው፣ሳራ እና ኑስራ ጨው፣ሴፍ የገበታ ጨው፣ሽናጉ የገበታ ጨው፣ወዛቴ የአይወዲን ጨው፣ቃና የገበታ ጨው፣አስሊ የገበታ ጨው፣ ሲሳይ ንጹህ ማርና ቅቤ፣ ወለላ ማር፣ካርቶንስ ካንዲ ፍሩትስ፣ ሊዛ ሎሊፖፕ እና ክሬም ሎሊፖፕ ተጠቅሰዋል፡፡
የክልል ተቆጣጣሪዎችና በየደረጃው የሚገኙ የቁጥጥር አካላት ምርቶቹን ከገበያ ላይ የመሰብሰብ ሥራውን እንዲሠሩ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ ማቅረቡንም አስታውቋል፡፡
ሕብረተሰቡም የትኛውንም የምግብ ምርት ከገበያ ሲገዛ ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ እንዲረዳው የተመረተበትንና የመጠቀሚያ የአገልግሎት ጊዜው ትክክለኛነት፣ የደረጃ ምልክት የለጠፈ፣ ያልተፋቀና ያልተሰረዘ መሆኑን፤ የአምራች ድርጅቱ ስምና ሙሉ አድራሻ፣ የምርት መለያ ቁጥር ያሟላ መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለበት ተገልጿል፡፡
ሕብረተሰቡ አጠራጣሪ ጉዳዮች ሲገጥሙትም ለአካባቢው ፖሊስ ወይም ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በነፃ ስልክ መስመር 8482 ላይ እንዲያሳውቁ ጠይቋል፡፡
አዲስ ዘመን ጥር 8/2012
በስድስት ቢሊዮን ብር ወጪ ዘመናዊ ተርሚናልና ዴፖ ሊገነባ ነው
-የመርካቶ መናኸሪያ ግንባታ 80 በመቶ ተጠናቅቋል
********************************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
አዲስ አበባ፡- በአዲስ አበባ ከተማ የመገናኛ የብዙሃን ትራንስፖርት ተርሚናልና የየካ የአውቶብስ ዲፖ ስድስት ቢሊዮን ብር በሚደርስ ወጪ ለማስገንባት በጨረታ ሂደት ላይ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የመርካቶ አውቶብስ ተርሚናል ግንባታ 80 በመቶ መጠናቀቁም ተገልጿል፡፡
በቢሮው የፕሮጀክቱ ኃላፊ ኢንጅነር ናትናኤል ጫላ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለተሳፋሪዎችና ለተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚሰጡ ደረጃቸውን የጠበቁ መናኸሪያዎች (የተርሚናሎች)ና የአውቶብስ ዴፖዎች የሏትም፡፡ ይህንን ተግዳሮቶች ለመቅረፍም የመገናኛና የየካ ዘመናዊ የአውቶቡስ ዲፖዎችንና የብዙሃን ትራንስፖርት ተርሚናሎች ስድስት ቢሊዮን ብር በሚደርስ ወጪ ለማስገንባት በጨረታ ሂደት ላይ ናቸው፡፡
የመገናኛ የከተማ የብዙሃን ትራንስፖርት ተርሚናል በ11ሺህ 790 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፍ ሲሆን ስምንት ወለሎች እንደሚኖሩት ኢንጅነር ናትናኤል ገልጸው አራቱ ወለሎች ለአውቶቡሶች እና ለታክሲዎች አገልግሎት መስጫ፣ አንድ የንግድ ማዕከል ወለል፣ አንድ የመኪና ማቆሚያ ወለል፣ የአስተዳደር ቢሮ እና የብዙሃን ትራንስፖርት ስምሪት ሥርዓትን ያካተተ ወለል እንደሚኖሩት ጠቅሰዋል፡፡
ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/Ama/?p=25749
-የመርካቶ መናኸሪያ ግንባታ 80 በመቶ ተጠናቅቋል
********************************************************
(ኢ.ፕ.ድ)
አዲስ አበባ፡- በአዲስ አበባ ከተማ የመገናኛ የብዙሃን ትራንስፖርት ተርሚናልና የየካ የአውቶብስ ዲፖ ስድስት ቢሊዮን ብር በሚደርስ ወጪ ለማስገንባት በጨረታ ሂደት ላይ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ የትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የመርካቶ አውቶብስ ተርሚናል ግንባታ 80 በመቶ መጠናቀቁም ተገልጿል፡፡
በቢሮው የፕሮጀክቱ ኃላፊ ኢንጅነር ናትናኤል ጫላ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ከተማዋ ለተሳፋሪዎችና ለተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚሰጡ ደረጃቸውን የጠበቁ መናኸሪያዎች (የተርሚናሎች)ና የአውቶብስ ዴፖዎች የሏትም፡፡ ይህንን ተግዳሮቶች ለመቅረፍም የመገናኛና የየካ ዘመናዊ የአውቶቡስ ዲፖዎችንና የብዙሃን ትራንስፖርት ተርሚናሎች ስድስት ቢሊዮን ብር በሚደርስ ወጪ ለማስገንባት በጨረታ ሂደት ላይ ናቸው፡፡
የመገናኛ የከተማ የብዙሃን ትራንስፖርት ተርሚናል በ11ሺህ 790 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፍ ሲሆን ስምንት ወለሎች እንደሚኖሩት ኢንጅነር ናትናኤል ገልጸው አራቱ ወለሎች ለአውቶቡሶች እና ለታክሲዎች አገልግሎት መስጫ፣ አንድ የንግድ ማዕከል ወለል፣ አንድ የመኪና ማቆሚያ ወለል፣ የአስተዳደር ቢሮ እና የብዙሃን ትራንስፖርት ስምሪት ሥርዓትን ያካተተ ወለል እንደሚኖሩት ጠቅሰዋል፡፡
ለተጨማሪ ንባብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/Ama/?p=25749
www.press.et
በስድስት ቢሊዮን ብር ወጪ ዘመናዊ ተርሚናልና ዴፖ ሊገነባ ነው | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
