በምሽቱ የዲያመንድሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተወዳደሩ ሲሆን አትሌት ለተሰንበት ግደይ በ5ሺ ሜ ሴቶች 14:26.57 በሆነ ጊዜ ኬንያዊቷን ሄለን ኦቢሪን ተከትላ 2ኛ በመሆን ድሏን አጣጥማለች።
በ1,500 ሜ የተወዳደረው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ 5ኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ፣ የ3,000 ሜ መሠናክል ተሰላፊዎች አትሌት ለሜቻ ግርማ 8ኛ እና አትሌት ጌትነት ዋለ ደግሞ 10ኛ በመሆን እኤአ የ2020ን ዲያመንድሊግ ውድድር ሀ ብለው ጀምረዋል።
በ5ሺ ሜ ኡጋንዳዊው ጆሽዋ ቸፕተጌ 12:35.36 በሆነ ጊዜ ቀዳሚ ሲሆን በጀግናው ኢትዮጵያዊ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የነበረውን የ16 አመት የ5ሺ ሜ ሪከርድ 12:37.35 በመስበር ማሸነፍ ችሏል።
ቀጣዩ የዲያመንድሊግ ውድድር ከ9ቀናት በኋላ በስዊድን ስቶኮልም ይካሄዳል ተብሎም ይጠበቃል።
በ1,500 ሜ የተወዳደረው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ 5ኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ፣ የ3,000 ሜ መሠናክል ተሰላፊዎች አትሌት ለሜቻ ግርማ 8ኛ እና አትሌት ጌትነት ዋለ ደግሞ 10ኛ በመሆን እኤአ የ2020ን ዲያመንድሊግ ውድድር ሀ ብለው ጀምረዋል።
በ5ሺ ሜ ኡጋንዳዊው ጆሽዋ ቸፕተጌ 12:35.36 በሆነ ጊዜ ቀዳሚ ሲሆን በጀግናው ኢትዮጵያዊ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የነበረውን የ16 አመት የ5ሺ ሜ ሪከርድ 12:37.35 በመስበር ማሸነፍ ችሏል።
ቀጣዩ የዲያመንድሊግ ውድድር ከ9ቀናት በኋላ በስዊድን ስቶኮልም ይካሄዳል ተብሎም ይጠበቃል።
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ግምገማ መጀመሩ ተገለጸ
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ በየክልሉ ሥራ አስፈጻሚዎች የቀረቡትን ሪፖርቶች ለመገምገም ስብሰባ መጀመሩ ተገለጸ።
ሥራ አስፈጻሚው ዛሬ በጀመረው በዚሁ ስብሠባው በተጨማሪም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ጠቅላይ ሚኒስር ዶ/ር አብይ አህመድ በፌሥቡክ ገጻቸው ላይ አስታውቀዋል።
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ በየክልሉ ሥራ አስፈጻሚዎች የቀረቡትን ሪፖርቶች ለመገምገም ስብሰባ መጀመሩ ተገለጸ።
ሥራ አስፈጻሚው ዛሬ በጀመረው በዚሁ ስብሠባው በተጨማሪም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ጠቅላይ ሚኒስር ዶ/ር አብይ አህመድ በፌሥቡክ ገጻቸው ላይ አስታውቀዋል።
በጋምቤላ ክልል የሚገነባው የሶላር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት አፈፃፀም 74 ከመቶ ደረሰ
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በጋምቤላ ክልል በአኝዋ ዞን ጆር ወረዳ እንጎጊ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የሶላር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ 74 ከመቶ አፈፃፀም ላይ መድረሱን የጋምቤላ ክልል የአገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፅ/ቤት አስታወቀ፡፡
በ5ሺ 950 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው ይህ የሶላር ፕሮጀክት፤ በ425 ሺህ 746 የአሜሪካን ዶላር ወጪ "CET & NR Consotrium" በተባለ የቻይና ኩባንያ እየተገነባ ይገኛል፡፡ የግንባታው ሥራ ክትትል የሚያደርገው ደግሞ የሪጅኑ አገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም ፅ/ቤት ነው፡፡
እስካሁን 5.9 ኪሜ የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ የተከናወነ ሲሆን፤ የሶላር ፕሮጀክቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ ከ175KW በላይ ኃይል ማመንጨት የሚችል ነው ተብሏል፡፡
ፕሮጀክቱ ከ150 እስከ 200 ለሚጠጉ ደንበኞች እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት መስጠት ይችላል፡፡
የሶላር ኃይል ማመንጫው ከአንድ ወር በኋላ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሲል ያስታወቀው የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ነው።
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በጋምቤላ ክልል በአኝዋ ዞን ጆር ወረዳ እንጎጊ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የሶላር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ 74 ከመቶ አፈፃፀም ላይ መድረሱን የጋምቤላ ክልል የአገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፅ/ቤት አስታወቀ፡፡
በ5ሺ 950 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው ይህ የሶላር ፕሮጀክት፤ በ425 ሺህ 746 የአሜሪካን ዶላር ወጪ "CET & NR Consotrium" በተባለ የቻይና ኩባንያ እየተገነባ ይገኛል፡፡ የግንባታው ሥራ ክትትል የሚያደርገው ደግሞ የሪጅኑ አገር አቀፍ ኤሌክትሪክ አቅርቦት ፕሮግራም ፅ/ቤት ነው፡፡
እስካሁን 5.9 ኪሜ የመካከለኛ መስመር ዝርጋታ የተከናወነ ሲሆን፤ የሶላር ፕሮጀክቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ ከ175KW በላይ ኃይል ማመንጨት የሚችል ነው ተብሏል፡፡
ፕሮጀክቱ ከ150 እስከ 200 ለሚጠጉ ደንበኞች እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት መስጠት ይችላል፡፡
የሶላር ኃይል ማመንጫው ከአንድ ወር በኋላ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ሲል ያስታወቀው የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት ነው።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የቀዳሚ ምርመራ ሂደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
**************************************************************
በዛሬው እለት አቶ ጃዋር መሃመድ ጨምሮ ስምንት ተጠርጣሪዎች ላይ የዐቃቤ ሕግ የቀዳሚ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት የተያዘው ቀጠሮ አቶ ጃዋር መሃመድ አሞኛል በማለታቸው ተሰተጓጉላል። ከዚህም የተነሳ ፍርድ ቤቱ ምስክሮቹን የመስማት ሂደቱን ለማካሄድ ለሶስተኛ ጊዜ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶዋል።
በዚህ አጋጣሚ ለህዝብ እና ጉዳዩን ለሚከታተሉ ሁሉ ግልጽ ለማድረግ የምንፈልገው እነ አቶ ጃዋር መሃመድ በከባድ ወንጀል ተጠርጥረው በሕግ ቁጥጥር ስር እንደመሆናቸው ጤናቸውን ለመጠበቅ ባለው አሰራር አስፈላጊውን የጤና ክትትል እና አገልግሎት የሚያገኙ እና እያገኙ ያሉ ሲሆን ጤናቸውም በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል።
ለዚህም ማሳያ ከተደረገላቸው የህክምና በተጨማሪ ዛሬ በዋለው ችሎት ምስክር መሰማት እንዳይጀምር የተለያዩ ምክንያቶችን እያነሱ ለረጀም ሰዓት ሲከራከሩ ከቆዩ በኃላ በክርክሩ ላይ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቶ ምስክር መሰሚያ ሰዓት ሲደርስ ወጣ ገባ ማለታቸው የሚፈለገው የምስክሮችን የማሰማት ሂደቱን ለማስተጓጎል እና በግብረአበሮቻቸው ሁከት እና አመጽ ለመቀስቀስ ነው።
የተጠርጣሪው ግብረ አበሮች በተለያየ መንገድ ምስክሮችን በማስፈራራት የፍትህ ሂደቱ እንዲስተጓጎል ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑም ታውቆዋል። ከዚህም በተጨማሪ ፍጹም አግባብነት በሌላቸው መነሻዎች እና በተለያየ ሰበቦች ምስክሮች በቀዳሚ ምርመራ የሚሰሙበተ ሂደት እንዲራዘም እና እንዲሰናከል ለማድረግ ጥረት እያደረጉ በመሆኑ እንደ ወትሮም ሁሉ ተቋማችን ለምስክሮች ተገቢውን የህግ ጥበቃና ከለላ የሚያደረግ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ እንፈልጋለን።
ከምንም በላይ በተለያዩ ጥቃቅን ጉዳዮች አላግባብ ከሚቀርቡ አቤቱታ እና ይግባኞች ጀምሮ፣ አልተዘጋጀንም ተለዋጭ ቀጠሮ ይሰጠን፣ ዳኛው ፌገግ ብሏል እና ይቀየርልን በማለት በሰበብ አስባቡ የፍርድ ሂደቱን ለማደናቀፍ በተጠርጣሪዎቹ በኩል የሚደረግ ጥረት እንዳለ ግልጽ ሆኖዋል። ይህን እውነታ ህዝቡም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት እንዲገነዘቡ እና በአፋጣኝ ፍትህ እንዲረጋገጥ ከምናደርገው ጥረት ጎን እንዲሰለፉ ጥሪያችንን እያቀረብን ማንም ይሁን ማን ከህግ በላይ መሆን የማይቻል መሆኑን በአጽኖት ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
ነሐሴ 11 ቀን 2012 ዓ.ም
አዲስ አበባ
በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ የቀዳሚ ምርመራ ሂደት በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
**************************************************************
በዛሬው እለት አቶ ጃዋር መሃመድ ጨምሮ ስምንት ተጠርጣሪዎች ላይ የዐቃቤ ሕግ የቀዳሚ ምርመራ ምስክሮችን ለመስማት የተያዘው ቀጠሮ አቶ ጃዋር መሃመድ አሞኛል በማለታቸው ተሰተጓጉላል። ከዚህም የተነሳ ፍርድ ቤቱ ምስክሮቹን የመስማት ሂደቱን ለማካሄድ ለሶስተኛ ጊዜ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶዋል።
በዚህ አጋጣሚ ለህዝብ እና ጉዳዩን ለሚከታተሉ ሁሉ ግልጽ ለማድረግ የምንፈልገው እነ አቶ ጃዋር መሃመድ በከባድ ወንጀል ተጠርጥረው በሕግ ቁጥጥር ስር እንደመሆናቸው ጤናቸውን ለመጠበቅ ባለው አሰራር አስፈላጊውን የጤና ክትትል እና አገልግሎት የሚያገኙ እና እያገኙ ያሉ ሲሆን ጤናቸውም በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል።
ለዚህም ማሳያ ከተደረገላቸው የህክምና በተጨማሪ ዛሬ በዋለው ችሎት ምስክር መሰማት እንዳይጀምር የተለያዩ ምክንያቶችን እያነሱ ለረጀም ሰዓት ሲከራከሩ ከቆዩ በኃላ በክርክሩ ላይ ፍርድ ቤቱ ብይን ሰጥቶ ምስክር መሰሚያ ሰዓት ሲደርስ ወጣ ገባ ማለታቸው የሚፈለገው የምስክሮችን የማሰማት ሂደቱን ለማስተጓጎል እና በግብረአበሮቻቸው ሁከት እና አመጽ ለመቀስቀስ ነው።
የተጠርጣሪው ግብረ አበሮች በተለያየ መንገድ ምስክሮችን በማስፈራራት የፍትህ ሂደቱ እንዲስተጓጎል ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑም ታውቆዋል። ከዚህም በተጨማሪ ፍጹም አግባብነት በሌላቸው መነሻዎች እና በተለያየ ሰበቦች ምስክሮች በቀዳሚ ምርመራ የሚሰሙበተ ሂደት እንዲራዘም እና እንዲሰናከል ለማድረግ ጥረት እያደረጉ በመሆኑ እንደ ወትሮም ሁሉ ተቋማችን ለምስክሮች ተገቢውን የህግ ጥበቃና ከለላ የሚያደረግ መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለመግለጽ እንፈልጋለን።
ከምንም በላይ በተለያዩ ጥቃቅን ጉዳዮች አላግባብ ከሚቀርቡ አቤቱታ እና ይግባኞች ጀምሮ፣ አልተዘጋጀንም ተለዋጭ ቀጠሮ ይሰጠን፣ ዳኛው ፌገግ ብሏል እና ይቀየርልን በማለት በሰበብ አስባቡ የፍርድ ሂደቱን ለማደናቀፍ በተጠርጣሪዎቹ በኩል የሚደረግ ጥረት እንዳለ ግልጽ ሆኖዋል። ይህን እውነታ ህዝቡም ሆነ የሚመለከታቸው አካላት እንዲገነዘቡ እና በአፋጣኝ ፍትህ እንዲረጋገጥ ከምናደርገው ጥረት ጎን እንዲሰለፉ ጥሪያችንን እያቀረብን ማንም ይሁን ማን ከህግ በላይ መሆን የማይቻል መሆኑን በአጽኖት ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
ነሐሴ 11 ቀን 2012 ዓ.ም
አዲስ አበባ
አምንስቲ ኢንተርናሽናል ሰሞኑን ኢትዮጵያን በተመለከተ ያሰራጨው ዜና ስህተት መሆኑን አምኖ ይቅርታ ጠየቀ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
አምንስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው ድርጅት የታዋቂውን አርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኢትዮጵያ በተከሰተው ቀውስ ሳቢያ "መንግስት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጽሟል" በሚል ያሰራጨው ዘገባ ስህተት መሆኑን በይፋዊ የቲዊተር ገጹ ላይ አምኖ ይቅርታ ጠየቀ።
ድርጅቱ በይፋዊ የቲዊተር ገጹ ላይ እንዳሰፈረው አምንስቲ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሰብዓዊ መብት እኩል እንዲከበር ድጋፉን ያደርጋል። አሁን ያለውን የአገሪቱን ውስብስብ የፖለቲካ ሁኔታም ድርጅቱ ይረዳል ብሏል።
የታዋቂውን አርቲስት ግድያ ተከትሎ በአገሪቱ በተነሳው ሁከት ሳቢያ "መንግስት የሰብዓዊ ምብት ጥሰት ፈጽሟል፤ በርካቶች ለተቃውሞ ወጥተዋል" የሚል ይዘት ያለው ዘገባ በአምኒስቲ በኩል መሠራጨቱ ስህተት ነው ሲል በይፋ አምኗል።
አምንስቲ አክሎም በተሰራጨው የተሳሳተ መረጃ ሳቢያ ለተከሰተው አሉታዊ ውጤት ይቅርታ እንጠይቃለን ብሏል።
አምንስቲ በወቅቱ የለቀቀውን መረጃ ከትዊተር ገጹ ላይ ማጥፋቱ ታውቋል።
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
አምንስቲ ኢንተርናሽናል የተባለው ድርጅት የታዋቂውን አርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኢትዮጵያ በተከሰተው ቀውስ ሳቢያ "መንግስት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ፈጽሟል" በሚል ያሰራጨው ዘገባ ስህተት መሆኑን በይፋዊ የቲዊተር ገጹ ላይ አምኖ ይቅርታ ጠየቀ።
ድርጅቱ በይፋዊ የቲዊተር ገጹ ላይ እንዳሰፈረው አምንስቲ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሰብዓዊ መብት እኩል እንዲከበር ድጋፉን ያደርጋል። አሁን ያለውን የአገሪቱን ውስብስብ የፖለቲካ ሁኔታም ድርጅቱ ይረዳል ብሏል።
የታዋቂውን አርቲስት ግድያ ተከትሎ በአገሪቱ በተነሳው ሁከት ሳቢያ "መንግስት የሰብዓዊ ምብት ጥሰት ፈጽሟል፤ በርካቶች ለተቃውሞ ወጥተዋል" የሚል ይዘት ያለው ዘገባ በአምኒስቲ በኩል መሠራጨቱ ስህተት ነው ሲል በይፋ አምኗል።
አምንስቲ አክሎም በተሰራጨው የተሳሳተ መረጃ ሳቢያ ለተከሰተው አሉታዊ ውጤት ይቅርታ እንጠይቃለን ብሏል።
አምንስቲ በወቅቱ የለቀቀውን መረጃ ከትዊተር ገጹ ላይ ማጥፋቱ ታውቋል።
የተወሰኑ የምግብ ሸቀጦች ሙሉ ለሙሉ ከቀረጥ ነፃ እየገቡ መሆናቸው ተገለጸ
************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- መንግሥት የሸቀጦችን ዋጋ በማረጋጋት ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በአምስት መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረውን ቀረጥ ሙሉ ለሙሉ ማንሳቱ ተገለጸ።
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ መንግሥት በምግብ ሸቀጦች ላይ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት የምግብ ዘይት፣ ስኳር፣ የዳቦ ስንዴ፣ ሩዝና የታሸጉ የሕፃናት ምግቦችን ሙሉ ለሙሉ ከቀረጥና ታክስ ነፃ አድርጓል፡፡
መንግሥት ከእነዚህ ምርቶች ያገኝ የነበረውን ገቢ ሙሉ ለሙሉ በመሰረዝ ምግቦቹን ከውጭ ለሚያስገቡ ነጋዴዎች ቀረጥና ታክሱን ነፃ አድርጎ ኅብረተሰቡ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ማግኘት ያለበትን መሠረታዊ የምግብ ሸቀጥ በቀላሉ እንዲያገኝ እገዛ እያደረገ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ከዚሁ ጎን ለጎንም አቅርቦቱ እንዲሻሻልና ጥራቱ እንዲጨምር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የምግብ ዘይትን በተመለከተ ከዚህ በፊት በመንግሥት ድጎማ ይገባ የነበረው ፓልም ወይም በተለምዶ የሚረጋው ዘይት መሆኑን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ፤ በአሁኑ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ይዘታቸው ፈሳሽ የሆኑ እና በቫይታሚን ኤ እና ዲ የበለፀጉ የዘይት ምርቶች ከዚህ በፊት በተመረጡ 24 አስመጪዎች እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ማንኛውም አስመጪና የግል ነጋዴ እነዚህን ምርቶች ከውጭ ሲያስገባ ከቀረጥ ነፃ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ስርጭቱንና ዋጋውን በተመለከተ መንግሥት የሚቆጣጠራቸው መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
እንደ አቶ ወንድሙ ገለጻ፤ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በአብዛኛው የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑና የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር በሚል በመንግሥት ድጎማ ብቻ ይገቡ የነበሩ ምርቶች በግል ነጋዴዎች ጭምር እንዲገቡ ተደርጓል።ይህ የሆነው አቅርቦቱ እንዳይቋረጥና ነጋዴውም ተገቢውን ትርፍ እንዲያገኝ ለማስቻል ነው።
ነገር ግን ከዚህ ባለፈ ነጋዴው ባልተገባ መንገድ እንዳይጠቀምና ምርቱ ወደ ግለሰቦች እጅ እንዳይገባ መንግሥት ጥብቅ ክትትል ያደርጋል።
በአገሪቱ ከሚያስፈልገው የምግብ ዘይት ስድስት በመቶ በአገር ውስጥ የሚመረት መሆኑን ጠቅሰው፣ ቀሪው ከውጭ የሚገባ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። በአጠቃላይ በአገር ውስጥ የሚመረተውን የምግብ ዘይት ጨምሮ በግለሰብ ነጋዴዎችና በአስመጪዎች በየወሩ እስከ 42 ሚሊዮን ሌትር የምግብ ዘይት እየገባ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 12/2012
************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- መንግሥት የሸቀጦችን ዋጋ በማረጋጋት ኅብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በአምስት መሠረታዊ የምግብ ሸቀጦች ላይ ተጥሎ የነበረውን ቀረጥ ሙሉ ለሙሉ ማንሳቱ ተገለጸ።
የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድሙ ፍላቴ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ መንግሥት በምግብ ሸቀጦች ላይ እየታየ ያለውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋት የምግብ ዘይት፣ ስኳር፣ የዳቦ ስንዴ፣ ሩዝና የታሸጉ የሕፃናት ምግቦችን ሙሉ ለሙሉ ከቀረጥና ታክስ ነፃ አድርጓል፡፡
መንግሥት ከእነዚህ ምርቶች ያገኝ የነበረውን ገቢ ሙሉ ለሙሉ በመሰረዝ ምግቦቹን ከውጭ ለሚያስገቡ ነጋዴዎች ቀረጥና ታክሱን ነፃ አድርጎ ኅብረተሰቡ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ማግኘት ያለበትን መሠረታዊ የምግብ ሸቀጥ በቀላሉ እንዲያገኝ እገዛ እያደረገ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ከዚሁ ጎን ለጎንም አቅርቦቱ እንዲሻሻልና ጥራቱ እንዲጨምር እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የምግብ ዘይትን በተመለከተ ከዚህ በፊት በመንግሥት ድጎማ ይገባ የነበረው ፓልም ወይም በተለምዶ የሚረጋው ዘይት መሆኑን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ፤ በአሁኑ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ይዘታቸው ፈሳሽ የሆኑ እና በቫይታሚን ኤ እና ዲ የበለፀጉ የዘይት ምርቶች ከዚህ በፊት በተመረጡ 24 አስመጪዎች እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚሁ ጋር በተያያዘም ማንኛውም አስመጪና የግል ነጋዴ እነዚህን ምርቶች ከውጭ ሲያስገባ ከቀረጥ ነፃ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ስርጭቱንና ዋጋውን በተመለከተ መንግሥት የሚቆጣጠራቸው መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
እንደ አቶ ወንድሙ ገለጻ፤ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በአብዛኛው የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑና የአቅርቦት እጥረት እንዳይፈጠር በሚል በመንግሥት ድጎማ ብቻ ይገቡ የነበሩ ምርቶች በግል ነጋዴዎች ጭምር እንዲገቡ ተደርጓል።ይህ የሆነው አቅርቦቱ እንዳይቋረጥና ነጋዴውም ተገቢውን ትርፍ እንዲያገኝ ለማስቻል ነው።
ነገር ግን ከዚህ ባለፈ ነጋዴው ባልተገባ መንገድ እንዳይጠቀምና ምርቱ ወደ ግለሰቦች እጅ እንዳይገባ መንግሥት ጥብቅ ክትትል ያደርጋል።
በአገሪቱ ከሚያስፈልገው የምግብ ዘይት ስድስት በመቶ በአገር ውስጥ የሚመረት መሆኑን ጠቅሰው፣ ቀሪው ከውጭ የሚገባ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። በአጠቃላይ በአገር ውስጥ የሚመረተውን የምግብ ዘይት ጨምሮ በግለሰብ ነጋዴዎችና በአስመጪዎች በየወሩ እስከ 42 ሚሊዮን ሌትር የምግብ ዘይት እየገባ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 12/2012
ተጨማሪ 1 ሺህ 386 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተገለጸ
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
በለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 22,101 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 1,386 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 32,722 ደርሷል።
በሌላ በኩል 414 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ስሆን በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ 12,938 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
**********
(ኢ.ፕ.ድ)
በለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 22,101 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 1,386 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 32,722 ደርሷል።
በሌላ በኩል 414 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ስሆን በአጠቃላይ እስካሁን ድረስ 12,938 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
”የአመጽ ጥሪ አቅራቢዎች ቅጥረኛና ከሀዲዎች በመሆናቸው ህዝቡ ጆሮ ነስቷቸዋል" - ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- የአመጽ ጥሪ አቅራቢዎች ቅጥረኛ እና ከሀዲዎች መሆናቸው ስለሚታወቅ ህዝቡ በተደጋጋሚ ጆሮ እንደነሳቸው የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አስታወቁ። ህዝቡ በተለይም ወጣቱ ለጸረ ሰላም ሃይሎች ጥሪ ጆሮ ባለመስጠት ላሳየው የሰላም አጋርነት ምስጋና አቅርበዋል ።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ለትናንት ተላልፎ የነበረው አይነት ተመሳሳይ የአመጽ ጥሪዎች በተደጋጋሚ አልተሳኩም ፣ ያልተሳኩት ደግሞ የአመጹ ጥሪ አቅራቢዎች ቅጥረኛ እና ከሀዲዎች መሆናቸው ህዝቡ ስለሚያውቅ እንደሆነ አስታውቀዋል ።
እንደ ኮሚሽነር አራርሳ ገለጻ፤ ህዝቡ ትላንት ሲታገል ለምን አደባባይ ይወጣ እንደነበር በደንብ ስለሚያውቅና ዛሬ የሚተላለፈው ተመሳሳይ ጥሪ ደግሞ ለምንና ለማን ፍጆታ እንደሆነ ይረዳል። በመሆኑም ትናንት በኦሮሚያ ክልል የተጠራው የአመጽ ጥሪ ከሽፎ ህዝቡ በተለመደው የእለት ተእለት ስራው ላይ ውሏል።
“በጸጥታው መዋቅር ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ለውጥ አምጥቷል፡፡ በገንዘብ ድጋፍ የአመጽ ጥሪን ለማስፈጸም የሚጥሩ የጸጥታ ኃይል አካላት ነበሩ። እነዚህ ወገኖች ከስልጣን በተባረረው ከጥፋት ኃይል ጋር ሆነው ችግር ሲፈጽሙ ቢቆዩም ተለይተውና ተጣርቶ እርምጃ በመወሰዱ አሁን እየታየ ላለው የሰላምና የጸጥታ ለውጥ የራሱን አስተዋጾ አበርክቷል። ለትናንቱ ጥሪ አለመሳካትም የተወሰደው እርምጃ ትልቅ አስተዋጾ አድርጓል”ብለዋል ፡፡
ሰኞ እለት በምዕራብ አርሲ እና በምዕራብ ሀረርጌ አካባቢ የተወሰኑ እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም የጸጥታ አካላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት ወዲያውኑ መቆጣጠር ተችሏል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ አመጹ በተጠራበት እለት ትናንት ግን በሁሉም የክልሉ ዞኖችና ከተሞች ምንም አይነት የጸጥታ ችግር አልታየባቸውም፤ በአንጻሩ መደበኛ ሥራ ሲከናወን መዋሉን አመልክተዋል።
በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲደረግ የነበረው የአመጽ ጥሪ የወደቀ ሃሳብ በመሆኑ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም ያሉት ኮሚሽነሩ፤ በተደጋጋሚ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚደረጉ ጥሪዎች ተቀባይነት እያገኙ አይደለም፤ ይህም ህዝቡ “ለሽፍታ እና ለተላላኪ እጅ አንሰጥም” የማለቱ አብይ ማሳያ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
“እነዚህ ሃይሎች ጥሪውን ለምን እንደሚያደርጉት በግልጽ ይታወቃል፡፡ ከስልጣን የተባረረው ኃይል በሚሰጠው ገንዘብ የሚከናወን ሥራ ነው፤ ጥሪውን የሚያደርጉት አካላት ገንዘቡን ተቀብለው ሂሳቡን ለማወራረድ የሚሰሩ ተቀጣሪዎች ናቸው” ብለዋል።
ከሰኞ እለት ማታ ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ እንደተነሳ ግጭት እንደተፈጠረ በማስመስል ከዚህ በፊት የነበሩ የተቃውሞ ምስሎችን በመጠቀም ቅስቀሳ ለማድረግ መሞከሩን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ፤ ነገር ግን በክልሉ ትናንት ምንም አይነት ግጭት እንዳልነበረና የተጎዳ ሰውም እንደሌለ ገልፀዋል።
ችግር ቢኖር ኖሮ የክልሉ መንግስት ከዚህ በፊት በአርቲስት ሀጫሉ ግድያ ወቅት የተፈጠረውን ሳይደብቅ በሙሉ እንዳሳወቀው ሁሉ ያሳውቅ ነበር ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ዛሬም ሆነ ወደፊት ችግር ከተፈጠረ የምንደብቅበት ምንም አይነት ምክንያት የለም፤ ከተፈጠረም ወንጀለኞችን ፈልገን ለህግ እናቀርባለን እንጂ የምንደብቀው ጉዳይ አይኖርም ብለዋል።
የአመጽ ጥሪ በተደረገበት እለት በተቃራኒው በአምቦ፣ በጎባ እና በሌሎች ከተሞች ላይ ወጣቶች በጽዳትና መሰል የልማት ስራዎች ላይ ተሰማርተው መዋላቸውን ጠቁመዋል።
ህዝቡ በተለይም ወጣቱ ለጸረ ሰላም ሃይሎች ጥሪ ጆሮ ባለመስጠት ላሳየው የሰላም አጋርነት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ በቀጣይም በተመሳሳይ ለሰላምና ለልማት ያለውን አቋምና ጽኑ ፍላጎት አጠናክሮ እንዲቀጥል ፤ ከጸጥታ ሃይሉ ጋርም ተባብሮ እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል ።
አዲስ ዘመን ነሐሴ13/2012
በጋዜጣው ሪፖርተር
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- የአመጽ ጥሪ አቅራቢዎች ቅጥረኛ እና ከሀዲዎች መሆናቸው ስለሚታወቅ ህዝቡ በተደጋጋሚ ጆሮ እንደነሳቸው የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አስታወቁ። ህዝቡ በተለይም ወጣቱ ለጸረ ሰላም ሃይሎች ጥሪ ጆሮ ባለመስጠት ላሳየው የሰላም አጋርነት ምስጋና አቅርበዋል ።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ለትናንት ተላልፎ የነበረው አይነት ተመሳሳይ የአመጽ ጥሪዎች በተደጋጋሚ አልተሳኩም ፣ ያልተሳኩት ደግሞ የአመጹ ጥሪ አቅራቢዎች ቅጥረኛ እና ከሀዲዎች መሆናቸው ህዝቡ ስለሚያውቅ እንደሆነ አስታውቀዋል ።
እንደ ኮሚሽነር አራርሳ ገለጻ፤ ህዝቡ ትላንት ሲታገል ለምን አደባባይ ይወጣ እንደነበር በደንብ ስለሚያውቅና ዛሬ የሚተላለፈው ተመሳሳይ ጥሪ ደግሞ ለምንና ለማን ፍጆታ እንደሆነ ይረዳል። በመሆኑም ትናንት በኦሮሚያ ክልል የተጠራው የአመጽ ጥሪ ከሽፎ ህዝቡ በተለመደው የእለት ተእለት ስራው ላይ ውሏል።
“በጸጥታው መዋቅር ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ለውጥ አምጥቷል፡፡ በገንዘብ ድጋፍ የአመጽ ጥሪን ለማስፈጸም የሚጥሩ የጸጥታ ኃይል አካላት ነበሩ። እነዚህ ወገኖች ከስልጣን በተባረረው ከጥፋት ኃይል ጋር ሆነው ችግር ሲፈጽሙ ቢቆዩም ተለይተውና ተጣርቶ እርምጃ በመወሰዱ አሁን እየታየ ላለው የሰላምና የጸጥታ ለውጥ የራሱን አስተዋጾ አበርክቷል። ለትናንቱ ጥሪ አለመሳካትም የተወሰደው እርምጃ ትልቅ አስተዋጾ አድርጓል”ብለዋል ፡፡
ሰኞ እለት በምዕራብ አርሲ እና በምዕራብ ሀረርጌ አካባቢ የተወሰኑ እንቅስቃሴዎች ቢኖሩም የጸጥታ አካላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የተቀናጀ ጥረት ወዲያውኑ መቆጣጠር ተችሏል ያሉት ኮሚሽነሩ፤ አመጹ በተጠራበት እለት ትናንት ግን በሁሉም የክልሉ ዞኖችና ከተሞች ምንም አይነት የጸጥታ ችግር አልታየባቸውም፤ በአንጻሩ መደበኛ ሥራ ሲከናወን መዋሉን አመልክተዋል።
በማህበራዊ ሚዲያዎች ሲደረግ የነበረው የአመጽ ጥሪ የወደቀ ሃሳብ በመሆኑ በህዝቡ ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም ያሉት ኮሚሽነሩ፤ በተደጋጋሚ በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚደረጉ ጥሪዎች ተቀባይነት እያገኙ አይደለም፤ ይህም ህዝቡ “ለሽፍታ እና ለተላላኪ እጅ አንሰጥም” የማለቱ አብይ ማሳያ ነው ሲሉም ተናግረዋል።
“እነዚህ ሃይሎች ጥሪውን ለምን እንደሚያደርጉት በግልጽ ይታወቃል፡፡ ከስልጣን የተባረረው ኃይል በሚሰጠው ገንዘብ የሚከናወን ሥራ ነው፤ ጥሪውን የሚያደርጉት አካላት ገንዘቡን ተቀብለው ሂሳቡን ለማወራረድ የሚሰሩ ተቀጣሪዎች ናቸው” ብለዋል።
ከሰኞ እለት ማታ ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ እንደተነሳ ግጭት እንደተፈጠረ በማስመስል ከዚህ በፊት የነበሩ የተቃውሞ ምስሎችን በመጠቀም ቅስቀሳ ለማድረግ መሞከሩን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ፤ ነገር ግን በክልሉ ትናንት ምንም አይነት ግጭት እንዳልነበረና የተጎዳ ሰውም እንደሌለ ገልፀዋል።
ችግር ቢኖር ኖሮ የክልሉ መንግስት ከዚህ በፊት በአርቲስት ሀጫሉ ግድያ ወቅት የተፈጠረውን ሳይደብቅ በሙሉ እንዳሳወቀው ሁሉ ያሳውቅ ነበር ያሉት ኮሚሽነሩ፤ ዛሬም ሆነ ወደፊት ችግር ከተፈጠረ የምንደብቅበት ምንም አይነት ምክንያት የለም፤ ከተፈጠረም ወንጀለኞችን ፈልገን ለህግ እናቀርባለን እንጂ የምንደብቀው ጉዳይ አይኖርም ብለዋል።
የአመጽ ጥሪ በተደረገበት እለት በተቃራኒው በአምቦ፣ በጎባ እና በሌሎች ከተሞች ላይ ወጣቶች በጽዳትና መሰል የልማት ስራዎች ላይ ተሰማርተው መዋላቸውን ጠቁመዋል።
ህዝቡ በተለይም ወጣቱ ለጸረ ሰላም ሃይሎች ጥሪ ጆሮ ባለመስጠት ላሳየው የሰላም አጋርነት ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን፤ በቀጣይም በተመሳሳይ ለሰላምና ለልማት ያለውን አቋምና ጽኑ ፍላጎት አጠናክሮ እንዲቀጥል ፤ ከጸጥታ ሃይሉ ጋርም ተባብሮ እንዲሰራ ጥሪ አቅርበዋል ።
አዲስ ዘመን ነሐሴ13/2012
በጋዜጣው ሪፖርተር
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስካሁን 120 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉ ተገለጸ
********************************
- የግድቡ አጠቃላይ የግንባታ አፈጻጸሙም 78 በመቶ ደርሷል
(ኢ ፕ ድ)
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስካሁን 120 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉ ተገለጸ። የግድቡ አጠቃላይ ግንባታም 75 በመቶ መድረሱ ተጠቁሟል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ዛሬ ከህዳሴው ግድብ የቦርድ አመራሮች እና ከሚመለከታቸው የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ መድረክ ላይ እንደተገለጸው የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ 75 በመቶ የደረሰ ሲሆን፤ የአሌሌክትሮ ሜካኒካል ስራው 46 ነጥብ 5 በመቶ፤ የሲቪል ስራው ደግሞ 88 ነጥብ 8 በመቶ ደርሷል።
ከወጪም አኳያ ለግድቡ በኮንትራት ደረጃ የተያዘው አጠቃላይ በጀት 78 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ቢሆንም፤ እስካሁን ድረስ ለግድቡ ግንባታ 120 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን የግድቡ ግንባታ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ አስታውቀዋል።
ግድቡን ለማጠናቀቅም 160 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ ኢንጅነሩ ተናግረዋል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ግድቡ በመጪው አመት አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል ሁሉ ተደርጎለት ነሀሴ 2013 ላይ 18 ነጥብ 4 ቢሊዮን ሜትር ኪዩቢክ ውሃ በመያዝ ለህዝቡ ይበሰራል ብለዋል።
ከመስከረም እስከ ነሀሴ 2013 የሚሰሩ ስራዎች ለግድቡ ግንባታ ስኬታማነት ወሳኝ መሆናቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዚህ አግባብ መስራት ከተቻለ “በ2015 ዓ.ም የግደቡን የምረቃ ሪባን እንቆርጣለን” ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
********************************
- የግድቡ አጠቃላይ የግንባታ አፈጻጸሙም 78 በመቶ ደርሷል
(ኢ ፕ ድ)
ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ እስካሁን 120 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉ ተገለጸ። የግድቡ አጠቃላይ ግንባታም 75 በመቶ መድረሱ ተጠቁሟል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ዛሬ ከህዳሴው ግድብ የቦርድ አመራሮች እና ከሚመለከታቸው የፌዴራል መንግስት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት አድርገዋል።
በዚሁ መድረክ ላይ እንደተገለጸው የግድቡ አጠቃላይ ግንባታ 75 በመቶ የደረሰ ሲሆን፤ የአሌሌክትሮ ሜካኒካል ስራው 46 ነጥብ 5 በመቶ፤ የሲቪል ስራው ደግሞ 88 ነጥብ 8 በመቶ ደርሷል።
ከወጪም አኳያ ለግድቡ በኮንትራት ደረጃ የተያዘው አጠቃላይ በጀት 78 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ቢሆንም፤ እስካሁን ድረስ ለግድቡ ግንባታ 120 ቢሊዮን ብር ወጪ መደረጉን የግድቡ ግንባታ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ አስታውቀዋል።
ግድቡን ለማጠናቀቅም 160 ቢሊዮን ብር እንደሚፈጅ ኢንጅነሩ ተናግረዋል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ግድቡ በመጪው አመት አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል ሁሉ ተደርጎለት ነሀሴ 2013 ላይ 18 ነጥብ 4 ቢሊዮን ሜትር ኪዩቢክ ውሃ በመያዝ ለህዝቡ ይበሰራል ብለዋል።
ከመስከረም እስከ ነሀሴ 2013 የሚሰሩ ስራዎች ለግድቡ ግንባታ ስኬታማነት ወሳኝ መሆናቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዚህ አግባብ መስራት ከተቻለ “በ2015 ዓ.ም የግደቡን የምረቃ ሪባን እንቆርጣለን” ብለዋል።
በጌትነት ምህረቴ
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 1778 ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ የ 20 ሰዎች ህይወት አለፈ
****************************
(ኢፕድ)
በ24 ሰዓታት ለ21 ሺህ 456 ሰዎች በተደረገው የላብራቶሪ ምርመራ 1778ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋግጧል።
20 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ሲያልፍ በቫይረሱ የሞቱት ቁጥር 620 ደርሷል።
በዛሬው እለትም 228 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን አጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች
ቁጥር 13 ሺህ 536 መድረሱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በፌስቡክ ገጻቸው አስታውቀዋል።
ሌሎች 248 ሰዎች በፅኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ እንደሚገኙም ተገልጿል።
አጠቃላይ እስካሁን ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 35 ሺህ 836 ሲሆኑ በአሁኑ ሰአት ቫይረሱ ያለባቸው
ሰዎች ቁጥር 21 ሺህ 678ደርሷል።
****************************
(ኢፕድ)
በ24 ሰዓታት ለ21 ሺህ 456 ሰዎች በተደረገው የላብራቶሪ ምርመራ 1778ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋግጧል።
20 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ሲያልፍ በቫይረሱ የሞቱት ቁጥር 620 ደርሷል።
በዛሬው እለትም 228 ሰዎች ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን አጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች
ቁጥር 13 ሺህ 536 መድረሱን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ በፌስቡክ ገጻቸው አስታውቀዋል።
ሌሎች 248 ሰዎች በፅኑ ህሙማን ክፍል ውስጥ እንደሚገኙም ተገልጿል።
አጠቃላይ እስካሁን ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 35 ሺህ 836 ሲሆኑ በአሁኑ ሰአት ቫይረሱ ያለባቸው
ሰዎች ቁጥር 21 ሺህ 678ደርሷል።
ተጨማሪ 1 ሺህ 368 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ 25 ሰዎች ሕይወትም አልፏል
********
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገው 19 ሺህ 776 የላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 368 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዚህም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 39ሺህ 33 ደርሷል።
የተጨማሪ 25 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን ፤በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 662 መድረሱ ታውቋል።
በአሁኑ ወቅት 251ሰዎች በጽኑ ሕክምና ላይ ይገኛሉ፤ 23ሺህ 889 ደግሞ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ቁጥር እንደሆነ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 567 ሰዎች ከቫይረሱ ያገገሙ ሲሆን፤ በአጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 14ሺህ 480 ደርሷል፡፡
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካዛሬ ድረስ 736ሺህ 904 የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል።
********
(ኢ.ፕ.ድ)
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገው 19 ሺህ 776 የላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 368 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዚህም በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 39ሺህ 33 ደርሷል።
የተጨማሪ 25 ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን ፤በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 662 መድረሱ ታውቋል።
በአሁኑ ወቅት 251ሰዎች በጽኑ ሕክምና ላይ ይገኛሉ፤ 23ሺህ 889 ደግሞ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ቁጥር እንደሆነ ተገልጿል።
በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 567 ሰዎች ከቫይረሱ ያገገሙ ሲሆን፤ በአጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 14ሺህ 480 ደርሷል፡፡
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካዛሬ ድረስ 736ሺህ 904 የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል።
አዲስ የተጀመሩት ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ነባር የተፈጥሮ ሀብቶችን ለማጉላት የታለሙ ናቸው - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
ሥነ-ምኅዳርን አማክለው አዲስ የተጀመሩት ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ነባር የተፈጥሮ ሀብቶችን ለማጉላት፣ የአገልግሎት ዘርፍን ለማስጀመር እና ለአካባቢው ነዋሪዎች ቋሚ ሥራን ለመፍጠር የታለሙ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያስታወቁት በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ስለፕሮጀክቶቹ በሰጡት ገለጻ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በኮይሻ ስለሚሠራው ፕሮጀክት በሰጡት ገለጻ፣ “ሥነ ምኅዳርን ያማከለው አዲሱ ፕሮጀክታችን ነባር የተፈጥሮ ሀብቶችን ለማጉላት፣ የአገልግሎት ዘርፍን ለማስጀመር እና ለአካባቢው ነዋሪዎች ሥራን ለመፍጠር የታለመ ነው።” ብለዋል።
ኮይሻ በለምለም ኮረብታዎች፣ እንደ ምንጣፍ በተዘረጉ መስኮች እና በጥቅጥቅ ደን የታደለች መሆኗን እንዲሁም በመጠናቀቅ ላይ ያለው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ እና የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክም በአቅራቢያው እንደሚገኙ ነው የገለጹት።
ወንጪ ላይ የሚከናወነውን ፕሮጀክት በተመለከተ ደግሞ፣ “ወንጪ ተጨማሪ የቱሪዝም መስሕብነት ዐቅም እንዲኖራት፣ ቋሚ የሥራ ዕድሎች እንዲፈጠሩ እና የአካባቢው ነዋሪዎች በቂ መተዳደሪያ ለማግኘት እንዲችሉ” የታለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን ለማበልጸግ ቆርጦ የተነሳውን የደፋሮቹን የ‘ገበታ ለሀገር’ ቤተሰብን በመቀላቀል ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
ሥነ-ምኅዳርን አማክለው አዲስ የተጀመሩት ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ነባር የተፈጥሮ ሀብቶችን ለማጉላት፣ የአገልግሎት ዘርፍን ለማስጀመር እና ለአካባቢው ነዋሪዎች ቋሚ ሥራን ለመፍጠር የታለሙ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያስታወቁት በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ስለፕሮጀክቶቹ በሰጡት ገለጻ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በኮይሻ ስለሚሠራው ፕሮጀክት በሰጡት ገለጻ፣ “ሥነ ምኅዳርን ያማከለው አዲሱ ፕሮጀክታችን ነባር የተፈጥሮ ሀብቶችን ለማጉላት፣ የአገልግሎት ዘርፍን ለማስጀመር እና ለአካባቢው ነዋሪዎች ሥራን ለመፍጠር የታለመ ነው።” ብለዋል።
ኮይሻ በለምለም ኮረብታዎች፣ እንደ ምንጣፍ በተዘረጉ መስኮች እና በጥቅጥቅ ደን የታደለች መሆኗን እንዲሁም በመጠናቀቅ ላይ ያለው የኮይሻ ኃይል ማመንጫ እና የጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክም በአቅራቢያው እንደሚገኙ ነው የገለጹት።
ወንጪ ላይ የሚከናወነውን ፕሮጀክት በተመለከተ ደግሞ፣ “ወንጪ ተጨማሪ የቱሪዝም መስሕብነት ዐቅም እንዲኖራት፣ ቋሚ የሥራ ዕድሎች እንዲፈጠሩ እና የአካባቢው ነዋሪዎች በቂ መተዳደሪያ ለማግኘት እንዲችሉ” የታለመ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያን ለማበልጸግ ቆርጦ የተነሳውን የደፋሮቹን የ‘ገበታ ለሀገር’ ቤተሰብን በመቀላቀል ድጋፍ እንዲያደርጉም ጠይቀዋል።
ባንኩ በኮቪድ-19 ምክንያት ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ብድር ሰጥቶት የነበረውን ወርሃዊ የክፍያ እፎይታ ጊዜ ማጠናቀቁን ገለጸ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርኝሽ ምክንያት ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ብድር ተበዳሪዎች ሰጥቶት የነበረውን ወርሃዊ የክፍያ እፎይታ ጊዜ ማጠናቀቁን አስታወቀ።
የኮቪድ -19 ወረርሽኝ በዜጎች ላይ የሚያስከትለውን የኢኮኖሚ ጫና ታሳቢ በማድረግ ባንኩ ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ብድር ተበዳሪዎች ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር 2012 ዓ.ም የቆየ የሶስት ወር የእፎይታ ጊዜ መስጠቱ ይታወሳል።
በመሆኑም የእፎይታ ጊዜው በሰኔ ወር 2012 ዓ.ም መጠናቀቁንና ደንበኞች ክፍያቸውን ከሐምሌ ወር 2012 ዓ.ም ጀምሮ መክፈል መጀመር እንዳለባቸው ባንኩ አሳስቧል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሶስት ወር የብድር እፎይታ ጊዜ መሰጠቱን አስመልክቶ አውጥቶት በነበረው መግለጫ የእፎይታ ጊዜ ቢሰጥም የብድር መክፈያ ጣሪያው እንደማይራዘም ገልጾ ነበር።
”ወርሃዊ ክፍያውን መክፈል አቅም ያላቸው ደንበኞች የወርሃዊ ብድር ክፍያቸውን እንዲከፍሉ ይበረታታሉ” ሲል ባንኩ ማስታወቁ አይዘነጋም።
ባንኩ በሰጠው የእፎይታ ጊዜ ውስጥ 542 ሚሊዮን ብር ገንዘብ መሰብሰብ ይችል እንደነበር በመግለጽ፤ ”በወረርሽኙ ምክንያትም ወደቀጣይ ጊዜ አራዝሚያለሁ” ማለቱ የሚታወስ ነው።
ምንጭ ኢዜአ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ወረርኝሽ ምክንያት ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ብድር ተበዳሪዎች ሰጥቶት የነበረውን ወርሃዊ የክፍያ እፎይታ ጊዜ ማጠናቀቁን አስታወቀ።
የኮቪድ -19 ወረርሽኝ በዜጎች ላይ የሚያስከትለውን የኢኮኖሚ ጫና ታሳቢ በማድረግ ባንኩ ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ብድር ተበዳሪዎች ከሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር 2012 ዓ.ም የቆየ የሶስት ወር የእፎይታ ጊዜ መስጠቱ ይታወሳል።
በመሆኑም የእፎይታ ጊዜው በሰኔ ወር 2012 ዓ.ም መጠናቀቁንና ደንበኞች ክፍያቸውን ከሐምሌ ወር 2012 ዓ.ም ጀምሮ መክፈል መጀመር እንዳለባቸው ባንኩ አሳስቧል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሶስት ወር የብድር እፎይታ ጊዜ መሰጠቱን አስመልክቶ አውጥቶት በነበረው መግለጫ የእፎይታ ጊዜ ቢሰጥም የብድር መክፈያ ጣሪያው እንደማይራዘም ገልጾ ነበር።
”ወርሃዊ ክፍያውን መክፈል አቅም ያላቸው ደንበኞች የወርሃዊ ብድር ክፍያቸውን እንዲከፍሉ ይበረታታሉ” ሲል ባንኩ ማስታወቁ አይዘነጋም።
ባንኩ በሰጠው የእፎይታ ጊዜ ውስጥ 542 ሚሊዮን ብር ገንዘብ መሰብሰብ ይችል እንደነበር በመግለጽ፤ ”በወረርሽኙ ምክንያትም ወደቀጣይ ጊዜ አራዝሚያለሁ” ማለቱ የሚታወስ ነው።
ምንጭ ኢዜአ
የአማራ ክልል በ2012 በጀት ዓመት ከ158 ቢሊዮን ብር በላይ ኢንቨስትመንት መሳቡን አስታወቀ
***************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- አማራ ክልል ባለፈው በጀት ዓመት 158 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በክልሉ ኢንቨስት ለማድረግ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።
ኢንቨስትመንቶችን ከጥፋት ቡድኖች ለመጠበቅም የኢንቨስትመንት ፖሊሶች ተመድበው ተገቢው ጥበቃ እየተደረገ እንደሆነ ተገልጿል።
የአማራ ክልል የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈራ ወንድምአገኘሁ የክልሉን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በተመለከተ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በክልሉ በ2012 በጀት ዓመት ለሁለት ሺህ 222 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 158 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ካፒታል ላስመዘገቡ ሁለት ሺህ 908 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሰጥቷል። ይህም ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል። በ2012 በጀት ዓመት የኮቪድ -19 ተጽእኖ ቢኖርም በክልሉ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰት መመዝገቡን አመልክተዋል።
የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ ባለሀብቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ መግባት ሲችሉም 395 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩ አመልክተው፣ ባለሀብቶቹ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና በግብርና ዘርፎች መሰማራታቸውንና፤ የኢንቨስትመንት ፈቃዱን ከወሰዱት ከ70 በመቶ የሚሆኑት በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ እንደሚሰማሩ ተናግረዋል።
በተለይ ባለፈው በጀት ዓመት በክልሉ እስካሁን ልማት ላይ ውሎ የማያውቅ 60ሺህ ሄክታር መሬት በግብርና ኢንቨስትመንት እንዲለማ መደረጉን ገልጸዋል።
በክልሉ ሁሉም ዞኖች ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ዕድገት የተመዘገበ መሆኑን አመልክተው፤ የኢንቨስትመን ፈቃድ የወሰዱት ባለሀብቶች ከቁጥራቸው ብዛትና ባስመዘገቡት ካፒታል አንጻር ሲታይ ባህር ዳር ከተማ፤ ሰሜን ሸዋ፣ ምሥራቅ ጎጃም፣ አዊን ዞን ጨምሮ ምዕራብ ጎጃምና ጎንደር ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ክልሉ ቀደም ሲል በነበሩት ዓመታት በቂ የመሠረተ ልማቶች ያልተዘረጉለት መሆኑን አውስተው፣ በተለይ በክልሉ ውስጥ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ማሰራጫና ማከፋፈያ ጣቢያ ባለመኖራቸው ምክንያት የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ለኢንቨስትመንትና ግንባታቸው
ለተጠናቀቁት ኢንዱስትሪዎች ቀዳሚ እንቅፋት መሆኑን ጠቅሰዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረቱን ለመቅረፍም አሁንም ገና ብዙ ሥራዎችን የሚጠይቅ ቢሆንም በደብረ ብርሃን፣ በደብረ ታቦር ቋሚና ተንቀሳቃሽ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያና ማሰራጫ ጣቢያዎች መተከላቸውን አመልክተዋል።
በቡሬና ደብረማርቆስ ከተሞች ኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ መምጣታቸውን ተከትሎ በፌዴራል መንግሥት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ (ሰብስቴሽን) ለመገንባት ዕቅድ ቢይዝም ቶሎ ወደ ተግባር አለመግባቱንአመልክተው ኢንዱስትሪዎች ግንባታቸውን ጨርሰው ወደ ማምረት ቢገቡም በሙሉ አቅም ለማምረት የኃይል እጥረት ስጋት ውስጥ ከቷቸዋል ብለዋል።
ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅፋት የሆኑ ችግሮችን ስልታዊ በሆነ መንገድ በመፍታት፣ የመሬት አቅርቦት በማመቻቸትና ያልተንዛዛ አገልግሎት በመስጠት ረገድ አሁንም በክልሉ በሚገኙ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች የአመለካከት ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ እነዚህን ችግሮች ማረም ከተቻለ የክልሉን የኢንቨስትመንት ፍሰት በእጅጉ መጨመር እንደሚቻል ተናግረዋል።
«ክልሉ ለኢንዱስትሪና ለኢንቨስትመንት ዋስትና የሚሰጥና የተመቸ እንዲሆን እየሰራን ነው» ያሉት የቢሮ ኃላፊው፣ በአጭር ጊዜ በኢንቨስትመንቶች ላይ የጥፋት ኃይሎች ጉዳት እንዳያደርሱ ለመጠበቅ ኢንቨስትመንቶች ባሉባቸው አካባቢዎች የሰለጠኑ የኢንቨስትመንት ፖሊሶችን መድበናል፣በረጅም ጊዜ ደግሞ ኅብረተሰቡም ሆነ አመራሩ ኢንቨስትመንት ዕድል መሆኑን ተገንዝቦ እንዲጠቀምበትና እንዲጠብቀው የሚያደርጉ ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል።
አቶ ተፈራ እንዳሉት የኢንቨስትመንት ፖሊስ የሚል መዋቅር ዘርግተን በኢንቨስትመንቶች ላይ ተገቢ ጥበቃ እየተደረገ ነው። ስለዚህ የክልሉ የኢንቨስትመንት ሥራ አስተማማኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በአዲሱ በጀት ዓመትም ኮቪድ-19 የሚያሳድረው ተጸእኖ እንደተጠበቀ ሆኖ በክልሉ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ ዕቅድ መያዙን አመልክተው፤ እስካሁንም ሆነ ወደፊት በኢንቨስትመንት ስም መሬት አጥረው እንዳይቀመጡና በአግባቡ እንዲያለሙ አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
«በክልሉ የልማት ሥራዎችን ለማደናቀፍና ከግራም ሆነ ከቀኝ ክልሉን ለማተራመስ፣ ግርግርና ግጭት ለመፍጠር እየጣሩ ያሉ ግለሰቦችና ቡድኖች አሉ፤ » ያሉት አቶ ተፈራ፤ የክልሉን መልማት የማይፈልጉ አካላትን የአማራ ሕዝብ ጠንቅቆ ስላወቃቸው መቼም ቢሆን አይሳካላቸውም፤ በበጀት ዓመቱም የተመዘገበው ኢንቨስትመንትም በሕዝቡ፣በመንግሥትና በጸጥታ ኃይሉ የተገኘ የተቀናጀ ሥራ ውጤት መሆኑንና ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ የሚገኙት፤ ኮምቦልቻና አረርቲ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ሙሉ በሙሉ ሥራ የጀመሩ መሆኑን አውስተው በደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ አንድ ሼድ ሥራ የጀመረ ሲሆን ቀሪዎቹ ሼዶችና የባህዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጭር ጊዜ የሚሟሉ ነገሮች ተሟልተው ወደ ሥራ እንደሚገቡ አብራርተዋል።
ኢንዱስትሪዎቹ ግንባታቻው ተጠናቆ ማምረት ሲጀምሩም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካትና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ረገድ ከፍተኛ ድርሻ ይኖራቸዋል ብለዋል። ክልሉን ሆነ አገሪቱን ወደ ብልጽግና ለማሸጋገር ድርሻቸው የጎላ ነው ያሉት አቶ ተፈራ፣ በቀጣይም ክልሉ ለልማት የተመቸና የኢንቨስተሮችን ቀልብ የሚስብ እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነም አስታውቀዋል።
አዲስ ዘመን ነሃሴ 18/2012
በጌትነት ምህረቴ
***************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- አማራ ክልል ባለፈው በጀት ዓመት 158 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ካፒታል ያስመዘገቡ ባለሀብቶች በክልሉ ኢንቨስት ለማድረግ የኢንቨስትመንት ፈቃድ መውሰዳቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪና የኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።
ኢንቨስትመንቶችን ከጥፋት ቡድኖች ለመጠበቅም የኢንቨስትመንት ፖሊሶች ተመድበው ተገቢው ጥበቃ እየተደረገ እንደሆነ ተገልጿል።
የአማራ ክልል የኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ አቶ ተፈራ ወንድምአገኘሁ የክልሉን የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በተመለከተ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ በክልሉ በ2012 በጀት ዓመት ለሁለት ሺህ 222 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት ታቅዶ 158 ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ካፒታል ላስመዘገቡ ሁለት ሺህ 908 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ሰጥቷል። ይህም ከዕቅድ በላይ ማሳካት ተችሏል። በ2012 በጀት ዓመት የኮቪድ -19 ተጽእኖ ቢኖርም በክልሉ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰት መመዝገቡን አመልክተዋል።
የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ ባለሀብቶች ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ መግባት ሲችሉም 395 ሺህ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥሩ አመልክተው፣ ባለሀብቶቹ በኢንዱስትሪ፣ በአገልግሎትና በግብርና ዘርፎች መሰማራታቸውንና፤ የኢንቨስትመንት ፈቃዱን ከወሰዱት ከ70 በመቶ የሚሆኑት በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ እንደሚሰማሩ ተናግረዋል።
በተለይ ባለፈው በጀት ዓመት በክልሉ እስካሁን ልማት ላይ ውሎ የማያውቅ 60ሺህ ሄክታር መሬት በግብርና ኢንቨስትመንት እንዲለማ መደረጉን ገልጸዋል።
በክልሉ ሁሉም ዞኖች ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ዕድገት የተመዘገበ መሆኑን አመልክተው፤ የኢንቨስትመን ፈቃድ የወሰዱት ባለሀብቶች ከቁጥራቸው ብዛትና ባስመዘገቡት ካፒታል አንጻር ሲታይ ባህር ዳር ከተማ፤ ሰሜን ሸዋ፣ ምሥራቅ ጎጃም፣ አዊን ዞን ጨምሮ ምዕራብ ጎጃምና ጎንደር ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ያስመዘገቡ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።
ክልሉ ቀደም ሲል በነበሩት ዓመታት በቂ የመሠረተ ልማቶች ያልተዘረጉለት መሆኑን አውስተው፣ በተለይ በክልሉ ውስጥ በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ማሰራጫና ማከፋፈያ ጣቢያ ባለመኖራቸው ምክንያት የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረት ለኢንቨስትመንትና ግንባታቸው
ለተጠናቀቁት ኢንዱስትሪዎች ቀዳሚ እንቅፋት መሆኑን ጠቅሰዋል።
የኤሌክትሪክ ኃይል እጥረቱን ለመቅረፍም አሁንም ገና ብዙ ሥራዎችን የሚጠይቅ ቢሆንም በደብረ ብርሃን፣ በደብረ ታቦር ቋሚና ተንቀሳቃሽ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያና ማሰራጫ ጣቢያዎች መተከላቸውን አመልክተዋል።
በቡሬና ደብረማርቆስ ከተሞች ኢንዱስትሪዎች እየተስፋፉ መምጣታቸውን ተከትሎ በፌዴራል መንግሥት የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ (ሰብስቴሽን) ለመገንባት ዕቅድ ቢይዝም ቶሎ ወደ ተግባር አለመግባቱንአመልክተው ኢንዱስትሪዎች ግንባታቸውን ጨርሰው ወደ ማምረት ቢገቡም በሙሉ አቅም ለማምረት የኃይል እጥረት ስጋት ውስጥ ከቷቸዋል ብለዋል።
ለኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት እንቅፋት የሆኑ ችግሮችን ስልታዊ በሆነ መንገድ በመፍታት፣ የመሬት አቅርቦት በማመቻቸትና ያልተንዛዛ አገልግሎት በመስጠት ረገድ አሁንም በክልሉ በሚገኙ በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች የአመለካከት ችግር መኖሩን ጠቁመው፤ እነዚህን ችግሮች ማረም ከተቻለ የክልሉን የኢንቨስትመንት ፍሰት በእጅጉ መጨመር እንደሚቻል ተናግረዋል።
«ክልሉ ለኢንዱስትሪና ለኢንቨስትመንት ዋስትና የሚሰጥና የተመቸ እንዲሆን እየሰራን ነው» ያሉት የቢሮ ኃላፊው፣ በአጭር ጊዜ በኢንቨስትመንቶች ላይ የጥፋት ኃይሎች ጉዳት እንዳያደርሱ ለመጠበቅ ኢንቨስትመንቶች ባሉባቸው አካባቢዎች የሰለጠኑ የኢንቨስትመንት ፖሊሶችን መድበናል፣በረጅም ጊዜ ደግሞ ኅብረተሰቡም ሆነ አመራሩ ኢንቨስትመንት ዕድል መሆኑን ተገንዝቦ እንዲጠቀምበትና እንዲጠብቀው የሚያደርጉ ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል።
አቶ ተፈራ እንዳሉት የኢንቨስትመንት ፖሊስ የሚል መዋቅር ዘርግተን በኢንቨስትመንቶች ላይ ተገቢ ጥበቃ እየተደረገ ነው። ስለዚህ የክልሉ የኢንቨስትመንት ሥራ አስተማማኝ መሆኑን ተናግረዋል።
በአዲሱ በጀት ዓመትም ኮቪድ-19 የሚያሳድረው ተጸእኖ እንደተጠበቀ ሆኖ በክልሉ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን ለመሳብ ዕቅድ መያዙን አመልክተው፤ እስካሁንም ሆነ ወደፊት በኢንቨስትመንት ስም መሬት አጥረው እንዳይቀመጡና በአግባቡ እንዲያለሙ አስፈላጊው ክትትልና ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።
«በክልሉ የልማት ሥራዎችን ለማደናቀፍና ከግራም ሆነ ከቀኝ ክልሉን ለማተራመስ፣ ግርግርና ግጭት ለመፍጠር እየጣሩ ያሉ ግለሰቦችና ቡድኖች አሉ፤ » ያሉት አቶ ተፈራ፤ የክልሉን መልማት የማይፈልጉ አካላትን የአማራ ሕዝብ ጠንቅቆ ስላወቃቸው መቼም ቢሆን አይሳካላቸውም፤ በበጀት ዓመቱም የተመዘገበው ኢንቨስትመንትም በሕዝቡ፣በመንግሥትና በጸጥታ ኃይሉ የተገኘ የተቀናጀ ሥራ ውጤት መሆኑንና ወደፊትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰዋል።
በሌላ በኩል በክልሉ የሚገኙት፤ ኮምቦልቻና አረርቲ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ሙሉ በሙሉ ሥራ የጀመሩ መሆኑን አውስተው በደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ አንድ ሼድ ሥራ የጀመረ ሲሆን ቀሪዎቹ ሼዶችና የባህዳር ኢንዱስትሪ ፓርክ በአጭር ጊዜ የሚሟሉ ነገሮች ተሟልተው ወደ ሥራ እንደሚገቡ አብራርተዋል።
ኢንዱስትሪዎቹ ግንባታቻው ተጠናቆ ማምረት ሲጀምሩም ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካትና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ረገድ ከፍተኛ ድርሻ ይኖራቸዋል ብለዋል። ክልሉን ሆነ አገሪቱን ወደ ብልጽግና ለማሸጋገር ድርሻቸው የጎላ ነው ያሉት አቶ ተፈራ፣ በቀጣይም ክልሉ ለልማት የተመቸና የኢንቨስተሮችን ቀልብ የሚስብ እንዲሆን ለማድረግ እየተሰራ እንደሆነም አስታውቀዋል።
አዲስ ዘመን ነሃሴ 18/2012
በጌትነት ምህረቴ
የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት ፀብ -ጫሪነትን በመሸሽ ወደ አማራ ክልል በመግባት ላይ መሆናቸው ተገለጸ
**********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የትግራይ ክልላዊ መንግሥትን ፀብ ጫሪነት በመሸሽ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ወደ አማራ ክልል የሚገቡ የክልሉ የልዩ ኃይል አባላት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ።
የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፣ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይሎች የትግራይ ክልላዊ መንግሥትን ፀባ ጫሪነት በመሸሽ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ወደ አማራ ክልል እየሸሹ ነው። ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው።
ከሰሞኑ ብቻ በሰሜን ጎንደር ከሰላሳ የሚበልጡ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የአጥፊነት መልዕክትን በመክዳት ወደ አማራ ክልል ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው መግባታቸውን ያስታወቁት ኃላፊው፤ ከነዚህ መካከል አንዳንዶች የማንነት እና የወሰን ጥያቄ ያለባቸው የክልሉ ነዋሪዎች ልጆች መሆናቸውን አመልክተዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ የትግራይ ክልል ተወላጆች መሆናቸውን ገልጸዋል።ይህም ክልሉልዩ ኃይሎች መካከል ከፍተኛ የሆነ መፈረካከስ እንዳለ አመላካች ነው ብለዋል።
ከትግራይ ክልል መንግሥት ሸሽተው የሚመጡት ዜጎቻችን በመሆናቸው ክልላችን በሚታወቅበት እንግዳን በአክብሮት የመቀበል ባህላችን ተቀብሎ እንክብካቤ እያደረገላቸው ነው ብለዋል።
ህወሃት በአሁኑ ወቅት በርካታ ወጣቶችን በወታደርነት በመመልመል ለጦርነት እያዘጋጀች መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው፣ የትግራይ ሕዝብ የክልሉ መንግሥት እያደረገ ያለው ትክክል አይደለም ብሎ እንደሚያምን በፈቃዳቸው ወደ አማራ ክልል ከገቡ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት መረዳት መቻሉን አስታውቀዋል።
በግዳጅ የሚታጠቁ ወጣቶች ከእነትጥቃቸው በተደጋጋሚ ወደ አማራ ክልል እየገቡ ናቸው።በአማራ ክልል በኩል በእንደዚህ ዓይነት መልኩ ሰው እንዲመጣ አንፈልግም።ምክንያቱም ጉዳዩ በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለበት ብለን እናምናለን ሲሉ ኃላፊው አመላክተዋል።
ከትግራይ ክልል ጋር በምንዋሰንበት አካባቢ ለእረጅም ጊዜ የቆየ የአማራ ክልል ጥያቄ የሆነ የማንነት እና የወሰን ጥያቄ መኖሩን የጠቆሙት ኃላፊው፣ ከዚህ ጋር ተያይዞ የህወሃት የአድዋ ቡድን የጦርነት ዝግጅት ለሀገር እድገት እና አንድነት ተገቢ አይደለም ብለዋል። በድንበር አካባቢ ወደ ጦርነት ለመግባት የማኮብኮብ ዓይነት እንቅስቃሴዎች መኖራቸውንም አመልክተዋል።
«የአማራ ክልል ወደ ጦርነት አይገባም። የአማራ እና የትግራይ ሕዝቦች ሁለት ወንድማማች ሕዝቦች ናቸው።በግልፅ እንደሚታወቀው አብረው ተጋብተው እና ተዋልደው የሚኖሩ ሕዝቦች ናቸው።ምንም ዓይነት ጉንተላ እና ፀብ-ጫሪነት በትግራይ ክልል መንግሥት በኩል ቢኖርም መቼም ቢሆን ሁለቱ ሕዝቦች ወደ ጦርነት ይገባሉ ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው» ብለዋል ።
ከአማራ ክልል በኩል እስከዛሬ ድረስ ምንም ዓይነት ትንኮሳ የለም ወደፊትም አይኖርም የሚሉት ኃላፊው፤ በእኛ በኩል እየጠየቅነው ያለው የሕዝብ ጥያቄ የሆነውን የማንነት እና የወሰን ጥያቄ ነው። ይህ ደግሞ ሕጋዊ ጥያቄ ስለሆነ ጉዳዩ የሚመለከተው የፌዴራሉ መንግሥት ሕጋዊ አሠራር ተከትሎ የራሱን እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል እንጠብቃለን ሲሉም ተናግረዋል።
አዲስ ዘመን ነሃሴ 18/2012
ሙሉቀን ታደገ
**********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የትግራይ ክልላዊ መንግሥትን ፀብ ጫሪነት በመሸሽ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ወደ አማራ ክልል የሚገቡ የክልሉ የልዩ ኃይል አባላት ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑ ተገለጸ።
የአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፣ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይሎች የትግራይ ክልላዊ መንግሥትን ፀባ ጫሪነት በመሸሽ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ወደ አማራ ክልል እየሸሹ ነው። ቁጥራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ነው።
ከሰሞኑ ብቻ በሰሜን ጎንደር ከሰላሳ የሚበልጡ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የአጥፊነት መልዕክትን በመክዳት ወደ አማራ ክልል ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው መግባታቸውን ያስታወቁት ኃላፊው፤ ከነዚህ መካከል አንዳንዶች የማንነት እና የወሰን ጥያቄ ያለባቸው የክልሉ ነዋሪዎች ልጆች መሆናቸውን አመልክተዋል። ቀሪዎቹ ደግሞ የትግራይ ክልል ተወላጆች መሆናቸውን ገልጸዋል።ይህም ክልሉልዩ ኃይሎች መካከል ከፍተኛ የሆነ መፈረካከስ እንዳለ አመላካች ነው ብለዋል።
ከትግራይ ክልል መንግሥት ሸሽተው የሚመጡት ዜጎቻችን በመሆናቸው ክልላችን በሚታወቅበት እንግዳን በአክብሮት የመቀበል ባህላችን ተቀብሎ እንክብካቤ እያደረገላቸው ነው ብለዋል።
ህወሃት በአሁኑ ወቅት በርካታ ወጣቶችን በወታደርነት በመመልመል ለጦርነት እያዘጋጀች መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው፣ የትግራይ ሕዝብ የክልሉ መንግሥት እያደረገ ያለው ትክክል አይደለም ብሎ እንደሚያምን በፈቃዳቸው ወደ አማራ ክልል ከገቡ የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል አባላት መረዳት መቻሉን አስታውቀዋል።
በግዳጅ የሚታጠቁ ወጣቶች ከእነትጥቃቸው በተደጋጋሚ ወደ አማራ ክልል እየገቡ ናቸው።በአማራ ክልል በኩል በእንደዚህ ዓይነት መልኩ ሰው እንዲመጣ አንፈልግም።ምክንያቱም ጉዳዩ በሰላማዊ መንገድ መፈታት አለበት ብለን እናምናለን ሲሉ ኃላፊው አመላክተዋል።
ከትግራይ ክልል ጋር በምንዋሰንበት አካባቢ ለእረጅም ጊዜ የቆየ የአማራ ክልል ጥያቄ የሆነ የማንነት እና የወሰን ጥያቄ መኖሩን የጠቆሙት ኃላፊው፣ ከዚህ ጋር ተያይዞ የህወሃት የአድዋ ቡድን የጦርነት ዝግጅት ለሀገር እድገት እና አንድነት ተገቢ አይደለም ብለዋል። በድንበር አካባቢ ወደ ጦርነት ለመግባት የማኮብኮብ ዓይነት እንቅስቃሴዎች መኖራቸውንም አመልክተዋል።
«የአማራ ክልል ወደ ጦርነት አይገባም። የአማራ እና የትግራይ ሕዝቦች ሁለት ወንድማማች ሕዝቦች ናቸው።በግልፅ እንደሚታወቀው አብረው ተጋብተው እና ተዋልደው የሚኖሩ ሕዝቦች ናቸው።ምንም ዓይነት ጉንተላ እና ፀብ-ጫሪነት በትግራይ ክልል መንግሥት በኩል ቢኖርም መቼም ቢሆን ሁለቱ ሕዝቦች ወደ ጦርነት ይገባሉ ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው» ብለዋል ።
ከአማራ ክልል በኩል እስከዛሬ ድረስ ምንም ዓይነት ትንኮሳ የለም ወደፊትም አይኖርም የሚሉት ኃላፊው፤ በእኛ በኩል እየጠየቅነው ያለው የሕዝብ ጥያቄ የሆነውን የማንነት እና የወሰን ጥያቄ ነው። ይህ ደግሞ ሕጋዊ ጥያቄ ስለሆነ ጉዳዩ የሚመለከተው የፌዴራሉ መንግሥት ሕጋዊ አሠራር ተከትሎ የራሱን እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል እንጠብቃለን ሲሉም ተናግረዋል።
አዲስ ዘመን ነሃሴ 18/2012
ሙሉቀን ታደገ
ነባሮቹን መዝናኛ ስፍራዎች በአዲስ መልክ ለመስራት ታቅዷል
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማን ነባር የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች ለማደስና ለህዝብ አገልግሎት ምቹ ለማድረግ መታቀዱን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዋለልኝ ደሳለኝ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የአዲስ አበባ ከተማ አብዛኛዎቹ ነባር መናፈሻ ቦታዎች ወንዝን ተከትለው የተሰሩ ናቸው።
ከአዲሶቹ መዝናኛ ስፍራዎች አንፃር ሲታይ ነባሮቹ መዝናኛ ስፍራዎች ሰዎች ሊጠቀሙባቸው የሚችሉባቸው ነገሮች እንደሌሏቸው የሚናገሩት አቶ ዋለልኝ፤ በቂ ማረፊያ ቦታ፣ የመብራት አገልግሎት፣ ፈጣን የሆነ የምግብ አገልግሎትና ሌሎች አዝናኝ ነገሮች እንደሚጎድላቸው አመልክተዋል። መዝናኛ ስፍዎቹ በትክክለኛ መንገድ እንዲገነቡ የማድረግ እቅድ እንዳለም አስረድተዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ ገለፃ፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አካባቢ የማልማት ስራ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። በተለይ ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን አረንጓዴ የልማት ቦታዎች አስፈላጊ ናቸው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስም ሁሉን ያማከሉ አረንጓዴ ቦታዎች አልነበሩም።
በተለያዩ ምክንያቶች ከተማዋ ተፈጥሮአዊ መስህቦ ቿን ሳትጠቀም መቆየቷንና የተፈጥሮ ሀብቶቿ እየባከኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተለይ ወንዞች ቀደም ባሉት ዘመናት አሳ ይለማባቸውና ሌሎች የግብርና ምርቶች ይመረቱባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። ለመዋኛና ለመዝናኛነትም ይውሉ እንደነበርም ገልፀዋል። ባለፉት አስርት ዓመታት ወንዞች ወደ ፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃነት ተቀይረው መቆየታቸውን ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ አባባል፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተደረገው ውጤታማ ስራ ለውጦች እየመጡ ነው። በቀጣይ ዓመታት የወንዝ ዳርቻዎችን ተከትሎ ሰፋፊ የአረንጓዴ ቦታ በመፍጠር ለከተማዋ ህዝብ ምቹ መዝናኛ እንዲሁም ጎብኚዎቿን ሳቢ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው። አጠቃላይ 56 ኪሎ ሜትር በቀበና፣ ቁርጥሜ፣ በቀጨኔ እንዲሁም በሌሎች ወንዞች ላይ የአረንጓዴ ፕሮጀክት ተጀምሯል።
ከዚህም ውስጥ ለማሳያነት ከሸራተን እስከ እሪ በከንቱ ድረስ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ጠቅሰዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ በፍጥነት እንደተሰራና መናፈሻ ቦታው ሰፊ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ በፍጥነት መሰራት ለሌሎች ስራዎች እንደ ተሞክሮ እየጠቀመ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ከእንጦጦ አናት ጀምሮ መጀመሩን አመልክተው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የእንጦጦ ፓርክ ግንባታም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኖ ለማየት መቻሉንም አመልክተዋል። በቀጣይ ዓመታትም በወንዝ መዳረሻ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ወንዞችን በማጣራት፣ ግራና ቀኝ የአረንጓዴ ቦታዎችን ሳቢ ማድረግ ሰዎች በስፍራዎቹ እንዲዝናኑ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናቀቁም አብራተዋል።
መርድ ክፍሉ
አዲስ ዘመን ነሐሴ 19/2012
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማን ነባር የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች ለማደስና ለህዝብ አገልግሎት ምቹ ለማድረግ መታቀዱን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዋለልኝ ደሳለኝ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የአዲስ አበባ ከተማ አብዛኛዎቹ ነባር መናፈሻ ቦታዎች ወንዝን ተከትለው የተሰሩ ናቸው።
ከአዲሶቹ መዝናኛ ስፍራዎች አንፃር ሲታይ ነባሮቹ መዝናኛ ስፍራዎች ሰዎች ሊጠቀሙባቸው የሚችሉባቸው ነገሮች እንደሌሏቸው የሚናገሩት አቶ ዋለልኝ፤ በቂ ማረፊያ ቦታ፣ የመብራት አገልግሎት፣ ፈጣን የሆነ የምግብ አገልግሎትና ሌሎች አዝናኝ ነገሮች እንደሚጎድላቸው አመልክተዋል። መዝናኛ ስፍዎቹ በትክክለኛ መንገድ እንዲገነቡ የማድረግ እቅድ እንዳለም አስረድተዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ ገለፃ፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አካባቢ የማልማት ስራ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። በተለይ ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን አረንጓዴ የልማት ቦታዎች አስፈላጊ ናቸው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስም ሁሉን ያማከሉ አረንጓዴ ቦታዎች አልነበሩም።
በተለያዩ ምክንያቶች ከተማዋ ተፈጥሮአዊ መስህቦ ቿን ሳትጠቀም መቆየቷንና የተፈጥሮ ሀብቶቿ እየባከኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተለይ ወንዞች ቀደም ባሉት ዘመናት አሳ ይለማባቸውና ሌሎች የግብርና ምርቶች ይመረቱባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። ለመዋኛና ለመዝናኛነትም ይውሉ እንደነበርም ገልፀዋል። ባለፉት አስርት ዓመታት ወንዞች ወደ ፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃነት ተቀይረው መቆየታቸውን ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ አባባል፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተደረገው ውጤታማ ስራ ለውጦች እየመጡ ነው። በቀጣይ ዓመታት የወንዝ ዳርቻዎችን ተከትሎ ሰፋፊ የአረንጓዴ ቦታ በመፍጠር ለከተማዋ ህዝብ ምቹ መዝናኛ እንዲሁም ጎብኚዎቿን ሳቢ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው። አጠቃላይ 56 ኪሎ ሜትር በቀበና፣ ቁርጥሜ፣ በቀጨኔ እንዲሁም በሌሎች ወንዞች ላይ የአረንጓዴ ፕሮጀክት ተጀምሯል።
ከዚህም ውስጥ ለማሳያነት ከሸራተን እስከ እሪ በከንቱ ድረስ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ጠቅሰዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ በፍጥነት እንደተሰራና መናፈሻ ቦታው ሰፊ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ በፍጥነት መሰራት ለሌሎች ስራዎች እንደ ተሞክሮ እየጠቀመ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ከእንጦጦ አናት ጀምሮ መጀመሩን አመልክተው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የእንጦጦ ፓርክ ግንባታም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኖ ለማየት መቻሉንም አመልክተዋል። በቀጣይ ዓመታትም በወንዝ መዳረሻ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ወንዞችን በማጣራት፣ ግራና ቀኝ የአረንጓዴ ቦታዎችን ሳቢ ማድረግ ሰዎች በስፍራዎቹ እንዲዝናኑ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናቀቁም አብራተዋል።
መርድ ክፍሉ
አዲስ ዘመን ነሐሴ 19/2012
በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ100 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል
**********************************
(ኢፕድ)
ቢሾፍቱ፡- ባለፈው በጀት ዓመት 2012ዓ.ም በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የነበሩ ከ 100ሺ በላይ ዜጎችን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ መስክም ውጤታማ ስራ መሰራቱን አመለከተ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ገዱ አንድአርጋቸው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የስራ ኃላፊዎችና የሚሲዮን መሪዎች ዓመታዊ ስብሰባ ትናንት " ዲፕሎማሲ ተልዕኮችን ለአገራዊ ብልጸግናችን" በሚል መሪ ቃል በቢሾፍቱ ከተማ ኩሪፍቱ ሪዞርት ሲጀመር እንደገለጹት፤ በ2012 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ ውጤታማ ስራዎችን አከናውናለች። በተለይ በዜጋ ተኮር የዲፕሎማሲ ስራዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የነበሩ ከ100ሺ በላይ ዜጎች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።
መንግስት በውጭ ለሚኖሩት ዜጎች ክብር የሚሰጥና ለመብታቸው መከበርም ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኘ የገለጹት አቶ ገዱ ፤ በ2012 በጀት ዓመትም በዜጋ ተኮር የዲፕሎማሲ በውጭ አገራት ለሚኖሩት ደግሞ መብትና ጥቅማቸው እንዲከበር ውጤታማ ስራዎች እንደተሰሩ ተናግረዋል።
በርካታ ቁጥር ያላቸው ዜጎችም ያጋጠሟቸው የተለያዩ ችግሮች ለማቃላል ሰፊ ጥረት መደረጉን ገልጸው፤ በተሰሩት ውጤታማ ስራዎች የዜጎችን መብቶችና ጥቅሞች በተቻለ መጠን ለማስጠበቅ የተደረገው ጥረት ውጤታማ ሊባል የሚችል መሆኑን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እንዲሳተፉ በማድረግ በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በድርድር ሂደት የተገኘውን ድል በፐብሊክ ዲፕሎማሲ በማጀብ የሀገራችን አቋም የሆነውን ፍትሀዊና ምክንያታዊ የተጠቃሚነት መርህን ለማስረዳት እና የዲፕሎማሲ ድጋፍ ለመሰብሰብ የረዳ ጠንካራ የገፅታ ግንባታ ስራ በመከናወን ላይ ይገኛልም ነው ያሉት።
በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በህዳሴ ግድብ የበኩላቸውን የገንዘብና የዲፕሎማሲ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የተሰራው ስራም ስኬታማ እንደነበር አመልክተው ፤ይህ ስራ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ መስክም ውጤታማ ስራ እንደተሰራ ጠቁመው፣ ለአብነትም ከ200 በላይ ከሚሆኑ የዓለም አቀፍ ኩባያዎችና ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸው ለማፍስስ የቅድመ ስምምነት መደረሱን ጠቁመዋል።
በሁሉም የዓለማችን ክፍሎች ከሚገኙ ሀገራት ብሔራዊ ጥቅምን መሰረት በማድረግ ነባር እና አዳዲስ ስትራቴጂክ አጋሮችን በማፍራት በሀገራችን እየተካሄደ ያለውን ሁሉን አቀፍ ለውጥ የፖለቲካ እና የዲፕሎማሲ ድጋፎች እንዲያገኝ በማድረግ አወንታዊ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል።
ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር፣ በኢጋድ ማዕቀፍ በክልሉ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ትስስርን በመፍጠር፣ በሀገራችን ሰላም፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንዲሁም የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የተፈረመው የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን፣ በሱዳን የተፈጠረው ቀውስ ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር እንዲኖር፣ በሶማሊያ ዘላቂ ሰላም እንዲፈጠር እንዲሁም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር የሰላም ስምምነት በመፈራረምና በቀጠናው ሰላም የማስከበር ስራዎች ረገድ የተሰሩ ስራዎች በበጎ የሚነሱ የዲፕሎማሲው ስራዎች ውጤቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በአሜሪካን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ፍጹም አረጋና በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ተሸመ ቶጋ እንደገለጹልን ስብሰባው የአገራችንን ጥቅም ለማስጠበቅ እንዲሁም ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ለመሳብ እና ሌሎች የዲፕሎማሲ ስራዎችን በትጋትና በውጤት ለማሳካት ስንቅ ይሆናል።
በተለይ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አምባሳደሮቹና ከፍተኛ ሃላፊዎቹ የሚሰጡትን አስተያየት እንደ ተጨማሪ ግብዓት በማካተት በመጪው ዓመት ፖሊሲው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ስራ ላይ ይውላል ተብሎ ይጠበቃል።
በስብሰባው ላይ የለውጥ ሥራዎች እና የመደመር ፍልስፍና መሰረታዊ ሃሳቦች፣ የፖለቲካ ብልጽግና እና የመደመር ገጽ፣ የኢኮኖሚ ብልጽግና እና የመደመር ገጽ፣ የሀገሪቱ የቀጣይ የአስር ዓመታት መሪ የልማት እቅድ፣ የመደመር የውጭ ግንኙነት እሳቤዎች በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ፣ ስትራቴጂክ አመራር እና የውጤት ተኮር ዕቅድ አስተቃቀድ ስልጠናዎች ይሰጣሉ።
እንዲሁም የእያንዳንዱ ኤምባሲ የ2012 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀምና ሪፖርት ግምገማና በልዩ ልዩ ሀገራዊ፣ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፋዊ የውጭ ግንኙነት ፈታኝ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የጋራ ግንዛቤ እንደሚያዝ ይጠበቃል።
ዓመታዊ ስብስባው ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከ160 በላይ የሚሲዮን መሪዎችና የውጭ ጉዳይ ከፍተኛ ኃላፊዎች ይሳተፉበታል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 19/2012
**********************************
(ኢፕድ)
ቢሾፍቱ፡- ባለፈው በጀት ዓመት 2012ዓ.ም በተለያዩ አገራት በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የነበሩ ከ 100ሺ በላይ ዜጎችን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ መስክም ውጤታማ ስራ መሰራቱን አመለከተ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ገዱ አንድአርጋቸው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የስራ ኃላፊዎችና የሚሲዮን መሪዎች ዓመታዊ ስብሰባ ትናንት " ዲፕሎማሲ ተልዕኮችን ለአገራዊ ብልጸግናችን" በሚል መሪ ቃል በቢሾፍቱ ከተማ ኩሪፍቱ ሪዞርት ሲጀመር እንደገለጹት፤ በ2012 በጀት ዓመት ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲው መስክ ውጤታማ ስራዎችን አከናውናለች። በተለይ በዜጋ ተኮር የዲፕሎማሲ ስራዎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ የነበሩ ከ100ሺ በላይ ዜጎች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።
መንግስት በውጭ ለሚኖሩት ዜጎች ክብር የሚሰጥና ለመብታቸው መከበርም ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኘ የገለጹት አቶ ገዱ ፤ በ2012 በጀት ዓመትም በዜጋ ተኮር የዲፕሎማሲ በውጭ አገራት ለሚኖሩት ደግሞ መብትና ጥቅማቸው እንዲከበር ውጤታማ ስራዎች እንደተሰሩ ተናግረዋል።
በርካታ ቁጥር ያላቸው ዜጎችም ያጋጠሟቸው የተለያዩ ችግሮች ለማቃላል ሰፊ ጥረት መደረጉን ገልጸው፤ በተሰሩት ውጤታማ ስራዎች የዜጎችን መብቶችና ጥቅሞች በተቻለ መጠን ለማስጠበቅ የተደረገው ጥረት ውጤታማ ሊባል የሚችል መሆኑን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያውያን በሀገራቸው ጉዳይ ላይ እንዲሳተፉ በማድረግ በታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ በድርድር ሂደት የተገኘውን ድል በፐብሊክ ዲፕሎማሲ በማጀብ የሀገራችን አቋም የሆነውን ፍትሀዊና ምክንያታዊ የተጠቃሚነት መርህን ለማስረዳት እና የዲፕሎማሲ ድጋፍ ለመሰብሰብ የረዳ ጠንካራ የገፅታ ግንባታ ስራ በመከናወን ላይ ይገኛልም ነው ያሉት።
በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በህዳሴ ግድብ የበኩላቸውን የገንዘብና የዲፕሎማሲ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የተሰራው ስራም ስኬታማ እንደነበር አመልክተው ፤ይህ ስራ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ መስክም ውጤታማ ስራ እንደተሰራ ጠቁመው፣ ለአብነትም ከ200 በላይ ከሚሆኑ የዓለም አቀፍ ኩባያዎችና ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ መዋዕለ ንዋያቸው ለማፍስስ የቅድመ ስምምነት መደረሱን ጠቁመዋል።
በሁሉም የዓለማችን ክፍሎች ከሚገኙ ሀገራት ብሔራዊ ጥቅምን መሰረት በማድረግ ነባር እና አዳዲስ ስትራቴጂክ አጋሮችን በማፍራት በሀገራችን እየተካሄደ ያለውን ሁሉን አቀፍ ለውጥ የፖለቲካ እና የዲፕሎማሲ ድጋፎች እንዲያገኝ በማድረግ አወንታዊ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቅሰዋል።
ለአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ዘላቂ ሰላምና መረጋጋት እንዲፈጠር፣ በኢጋድ ማዕቀፍ በክልሉ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ትስስርን በመፍጠር፣ በሀገራችን ሰላም፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንዲሁም የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ወገኖች የተፈረመው የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን፣ በሱዳን የተፈጠረው ቀውስ ሰላማዊ የፖለቲካ ሽግግር እንዲኖር፣ በሶማሊያ ዘላቂ ሰላም እንዲፈጠር እንዲሁም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር የሰላም ስምምነት በመፈራረምና በቀጠናው ሰላም የማስከበር ስራዎች ረገድ የተሰሩ ስራዎች በበጎ የሚነሱ የዲፕሎማሲው ስራዎች ውጤቶች መሆናቸውን አስታውቀዋል።
በአሜሪካን የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ፍጹም አረጋና በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር አምባሳደር ተሸመ ቶጋ እንደገለጹልን ስብሰባው የአገራችንን ጥቅም ለማስጠበቅ እንዲሁም ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ለመሳብ እና ሌሎች የዲፕሎማሲ ስራዎችን በትጋትና በውጤት ለማሳካት ስንቅ ይሆናል።
በተለይ በውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አምባሳደሮቹና ከፍተኛ ሃላፊዎቹ የሚሰጡትን አስተያየት እንደ ተጨማሪ ግብዓት በማካተት በመጪው ዓመት ፖሊሲው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ስራ ላይ ይውላል ተብሎ ይጠበቃል።
በስብሰባው ላይ የለውጥ ሥራዎች እና የመደመር ፍልስፍና መሰረታዊ ሃሳቦች፣ የፖለቲካ ብልጽግና እና የመደመር ገጽ፣ የኢኮኖሚ ብልጽግና እና የመደመር ገጽ፣ የሀገሪቱ የቀጣይ የአስር ዓመታት መሪ የልማት እቅድ፣ የመደመር የውጭ ግንኙነት እሳቤዎች በሁለትዮሽ እና በባለብዙ ወገን የዲፕሎማሲ፣ ስትራቴጂክ አመራር እና የውጤት ተኮር ዕቅድ አስተቃቀድ ስልጠናዎች ይሰጣሉ።
እንዲሁም የእያንዳንዱ ኤምባሲ የ2012 በጀት ዓመት የእቅድ አፈፃፀምና ሪፖርት ግምገማና በልዩ ልዩ ሀገራዊ፣ አካባቢያዊ እና ዓለም አቀፋዊ የውጭ ግንኙነት ፈታኝ ጉዳዮች ላይ በመወያየት የጋራ ግንዛቤ እንደሚያዝ ይጠበቃል።
ዓመታዊ ስብስባው ለ15 ቀናት የሚቆይ ሲሆን ከ160 በላይ የሚሲዮን መሪዎችና የውጭ ጉዳይ ከፍተኛ ኃላፊዎች ይሳተፉበታል።
አዲስ ዘመን ነሐሴ 19/2012
ነባሮቹን መዝናኛ ስፍራዎች በአዲስ መልክ ለመስራት ታቅዷል
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማን ነባር የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች ለማደስና ለህዝብ አገልግሎት ምቹ ለማድረግ መታቀዱን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዋለልኝ ደሳለኝ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የአዲስ አበባ ከተማ አብዛኛዎቹ ነባር መናፈሻ ቦታዎች ወንዝን ተከትለው የተሰሩ ናቸው።
ከአዲሶቹ መዝናኛ ስፍራዎች አንፃር ሲታይ ነባሮቹ መዝናኛ ስፍራዎች ሰዎች ሊጠቀሙባቸው የሚችሉባቸው ነገሮች እንደሌሏቸው የሚናገሩት አቶ ዋለልኝ፤ በቂ ማረፊያ ቦታ፣ የመብራት አገልግሎት፣ ፈጣን የሆነ የምግብ አገልግሎትና ሌሎች አዝናኝ ነገሮች እንደሚጎድላቸው አመልክተዋል። መዝናኛ ስፍዎቹ በትክክለኛ መንገድ እንዲገነቡ የማድረግ እቅድ እንዳለም አስረድተዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ ገለፃ፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አካባቢ የማልማት ስራ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። በተለይ ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን አረንጓዴ የልማት ቦታዎች አስፈላጊ ናቸው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስም ሁሉን ያማከሉ አረንጓዴ ቦታዎች አልነበሩም።
በተለያዩ ምክንያቶች ከተማዋ ተፈጥሮአዊ መስህቦ ቿን ሳትጠቀም መቆየቷንና የተፈጥሮ ሀብቶቿ እየባከኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተለይ ወንዞች ቀደም ባሉት ዘመናት አሳ ይለማባቸውና ሌሎች የግብርና ምርቶች ይመረቱባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። ለመዋኛና ለመዝናኛነትም ይውሉ እንደነበርም ገልፀዋል። ባለፉት አስርት ዓመታት ወንዞች ወደ ፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃነት ተቀይረው መቆየታቸውን ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ አባባል፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተደረገው ውጤታማ ስራ ለውጦች እየመጡ ነው። በቀጣይ ዓመታት የወንዝ ዳርቻዎችን ተከትሎ ሰፋፊ የአረንጓዴ ቦታ በመፍጠር ለከተማዋ ህዝብ ምቹ መዝናኛ እንዲሁም ጎብኚዎቿን ሳቢ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው። አጠቃላይ 56 ኪሎ ሜትር በቀበና፣ ቁርጥሜ፣ በቀጨኔ እንዲሁም በሌሎች ወንዞች ላይ የአረንጓዴ ፕሮጀክት ተጀምሯል።
ከዚህም ውስጥ ለማሳያነት ከሸራተን እስከ እሪ በከንቱ ድረስ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ጠቅሰዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ በፍጥነት እንደተሰራና መናፈሻ ቦታው ሰፊ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ በፍጥነት መሰራት ለሌሎች ስራዎች እንደ ተሞክሮ እየጠቀመ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ከእንጦጦ አናት ጀምሮ መጀመሩን አመልክተው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የእንጦጦ ፓርክ ግንባታም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኖ ለማየት መቻሉንም አመልክተዋል። በቀጣይ ዓመታትም በወንዝ መዳረሻ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ወንዞችን በማጣራት፣ ግራና ቀኝ የአረንጓዴ ቦታዎችን ሳቢ ማድረግ ሰዎች በስፍራዎቹ እንዲዝናኑ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናቀቁም አብራተዋል።
መርድ ክፍሉ
አዲስ ዘመን ነሐሴ 19/2012
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የአዲስ አበባ ከተማን ነባር የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች ለማደስና ለህዝብ አገልግሎት ምቹ ለማድረግ መታቀዱን የአዲስ አበባ አካባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት ኤጀንሲ አስታወቀ።
የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዋለልኝ ደሳለኝ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ የአዲስ አበባ ከተማ አብዛኛዎቹ ነባር መናፈሻ ቦታዎች ወንዝን ተከትለው የተሰሩ ናቸው።
ከአዲሶቹ መዝናኛ ስፍራዎች አንፃር ሲታይ ነባሮቹ መዝናኛ ስፍራዎች ሰዎች ሊጠቀሙባቸው የሚችሉባቸው ነገሮች እንደሌሏቸው የሚናገሩት አቶ ዋለልኝ፤ በቂ ማረፊያ ቦታ፣ የመብራት አገልግሎት፣ ፈጣን የሆነ የምግብ አገልግሎትና ሌሎች አዝናኝ ነገሮች እንደሚጎድላቸው አመልክተዋል። መዝናኛ ስፍዎቹ በትክክለኛ መንገድ እንዲገነቡ የማድረግ እቅድ እንዳለም አስረድተዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ ገለፃ፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአረንጓዴ አካባቢ የማልማት ስራ ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል። በተለይ ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀመጫ እንደመሆኗ መጠን አረንጓዴ የልማት ቦታዎች አስፈላጊ ናቸው። እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስም ሁሉን ያማከሉ አረንጓዴ ቦታዎች አልነበሩም።
በተለያዩ ምክንያቶች ከተማዋ ተፈጥሮአዊ መስህቦ ቿን ሳትጠቀም መቆየቷንና የተፈጥሮ ሀብቶቿ እየባከኑ መሆናቸውን ተናግረዋል። በተለይ ወንዞች ቀደም ባሉት ዘመናት አሳ ይለማባቸውና ሌሎች የግብርና ምርቶች ይመረቱባቸው እንደነበር አስታውሰዋል። ለመዋኛና ለመዝናኛነትም ይውሉ እንደነበርም ገልፀዋል። ባለፉት አስርት ዓመታት ወንዞች ወደ ፍሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃነት ተቀይረው መቆየታቸውን ጠቁመዋል።
እንደ አቶ ዋለልኝ አባባል፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተደረገው ውጤታማ ስራ ለውጦች እየመጡ ነው። በቀጣይ ዓመታት የወንዝ ዳርቻዎችን ተከትሎ ሰፋፊ የአረንጓዴ ቦታ በመፍጠር ለከተማዋ ህዝብ ምቹ መዝናኛ እንዲሁም ጎብኚዎቿን ሳቢ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው። አጠቃላይ 56 ኪሎ ሜትር በቀበና፣ ቁርጥሜ፣ በቀጨኔ እንዲሁም በሌሎች ወንዞች ላይ የአረንጓዴ ፕሮጀክት ተጀምሯል።
ከዚህም ውስጥ ለማሳያነት ከሸራተን እስከ እሪ በከንቱ ድረስ ያለው የወንዝ ዳርቻ ልማት ጠቅሰዋል። የወንዝ ዳርቻ ልማቱ በፍጥነት እንደተሰራና መናፈሻ ቦታው ሰፊ እንዲሆን መደረጉን ተናግረዋል። የፕሮጀክቱ በፍጥነት መሰራት ለሌሎች ስራዎች እንደ ተሞክሮ እየጠቀመ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ከእንጦጦ አናት ጀምሮ መጀመሩን አመልክተው፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችል የእንጦጦ ፓርክ ግንባታም በአጭር ጊዜ ውስጥ ተከናውኖ ለማየት መቻሉንም አመልክተዋል። በቀጣይ ዓመታትም በወንዝ መዳረሻ ቦታዎች ላይ የሚገኙ ወንዞችን በማጣራት፣ ግራና ቀኝ የአረንጓዴ ቦታዎችን ሳቢ ማድረግ ሰዎች በስፍራዎቹ እንዲዝናኑ ለማድረግ የተጀመሩ ስራዎች እንደሚጠናቀቁም አብራተዋል።
መርድ ክፍሉ
አዲስ ዘመን ነሐሴ 19/2012
ላለፉት 27 አመታት የተዘነጋው የህገ-መንግስቱ ቅርስ
የኢፌዲሪ ህገ መንግስት በህዳር ወር 1987 ዓ.ም ከመጽደቁ በፊት የህገ መንግስቱ አርቃቂ ኮሚሽን ስብሰባውን ያካሄደበት ታሪካዊው የመብራት ሃይል አዳራሽ አስታዋሽ አጥቶ እንዲህ በሚያሳዝን መልኩ ታሪክ ሆኗል።
ከህገ መንግስቱ ባሻገር ታሪካዊነቱ የጎላው ይህ አዳራሽ ላለፉት 27 አመታት አስታዋሽ አጥቶ ታሪኮ ደብዝዞ በምስሉ ላይ በሚታየው መልኩ ፈራርሶ ይገኛል።
ላለፉት 27 አመታት ስለ ህገ መንግስት ሲዘምሩ የነበሩት አካላት ቅርሱን በዚህ ሁኔታ ስለምን ተውት?
አሁንም የሚመለከተው አካል ለዚሁ ታሪካዊ አዳራሽ ትኩረት ይስጥ እንላለን!
የኢፌዲሪ ህገ መንግስት በህዳር ወር 1987 ዓ.ም ከመጽደቁ በፊት የህገ መንግስቱ አርቃቂ ኮሚሽን ስብሰባውን ያካሄደበት ታሪካዊው የመብራት ሃይል አዳራሽ አስታዋሽ አጥቶ እንዲህ በሚያሳዝን መልኩ ታሪክ ሆኗል።
ከህገ መንግስቱ ባሻገር ታሪካዊነቱ የጎላው ይህ አዳራሽ ላለፉት 27 አመታት አስታዋሽ አጥቶ ታሪኮ ደብዝዞ በምስሉ ላይ በሚታየው መልኩ ፈራርሶ ይገኛል።
ላለፉት 27 አመታት ስለ ህገ መንግስት ሲዘምሩ የነበሩት አካላት ቅርሱን በዚህ ሁኔታ ስለምን ተውት?
አሁንም የሚመለከተው አካል ለዚሁ ታሪካዊ አዳራሽ ትኩረት ይስጥ እንላለን!