የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞች አነስተኛ ደመወዝ ላላቸው ባልደረቦቻቸው ድጋፍ አደረጉ
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞች እና አመራሮች በተቋሙ ውስጥ ለሚሰሩና የወር ደመወዛቸው አነስተኛ ለሆኑ የስራ ባልደረቦቻቸው የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።
“እኛው ለእኛው” በሚል መርህ የተደረገው ይሄው ድጋፍ የተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮች ከወር ደሞዛቸው በመቀነስ ከለገሱት የተገኘ መሆኑን የድርጅቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድም ተክሉ አስታውቀዋል።
እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ፤ ይህ ድጋፍ ትልቅ ስራ ነው ተብሎ የታሰበ አይደለም፤ ነገር ግን በአንድ ተቋም ውስጥ ሊኖር የሚገባውን የእርስ በእርስ መተሳሰብን ለማጠናከር ታስቦ የተደረገና ሌሎች መሰል ተቋማትም ይሄንኑ ተግባር እንዲያከናውኑ ለማነሳሳት ነው።
የዚህ አይነቱ እርስ በእርስ የመተሳሰብና የመረዳዳት ባህልን በተቋም ውስጥ መገንባት ከተቻለ ተቋሙ ሊያሳከው የሚፈልገውን ግብ ከዳር ለማድረስ እንደ አንድ ግብአት የሚረዳ ይሆናል ያሉት አቶ ወንድም፤ በሰራተኞች መካከልም መዋደድና መተሳሰብን የሚፈጥር ነው ብለዋል።
በቀጣይም በተቋሙ የሚታሰበው ትልቁ ስራ እነዚህ ሰራተኞች እራሳቸውን በኢኮኖሚ የሚጠቅሙበትን ሁኔታ ማመቻቸት መሆኑን የጠቆሙት አቶ ወንድም፤ የሰራተኛውን ችግር በቋሚነት ሊፈቱ የሚችሉ ስራዎች በተቋሙ እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ለሰራተኞቹ የተደረገውን ድጋፍ ያስተባበሩት ወ/ሮ ብርሃኔ ደመቀ እንደተናጉት፤ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ ከተከሰተ ወዲህ በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የኑሮ ጫናው በርትቶባቸዋል፤ ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ውስጥ የሚገኙና የወር ገቢያቸው አነስተኛ የሆኑ ሰራተኞችን መደገፍ አስፈላጊ ሆኗል።
ይህንን የተቀደሰ ተግባር ከዳር ለማድረስም የድርጅቱ ሰራተኞችና አመራሮች ከወር ደመወዛቸው የሚቀነስ ገንዘብ በማዋጣት ለ43 የስራ ባልደረቦቻቸው ከጎናቸው መቆማቸውን በተግባር ማሳየት መቻላቸውን ወ/ሮ ብርሃኔ አብራርተዋል።
እንደ ወ/ሮ ብርሃኔ ገለፃ፤ እርስበርስ መረዳዳቱ በጣም አስፈላጊና ፈጣሪም የሚወደው ስራ ስለሆነ ድጋፍ የተደረገላቸውም ብቻ ሳይሆኑ ድጋፍ ያደረጉ ሰራተኞችም ደስተኛ ሆነዋል።
በእለቱ ድጋፍ ከተደረገላቸው ሰራተኞች መካከል የሆኑት ወ/ሮ ፀሀይ ደበሌ እና ወ/ሮ አበበች አስፋው እንደተናገሩት፤ የድርጅቱ ሰራተኞች ይህን መልካም ተግባር አስበው ድጋፍ በማድረጋቸው በእጅጉ ተደስተዋል። ይህ ክፉ ጊዜ እስኪያልፍ ድረስ እርስ በርስ እየተረዳዱ ማለፉን ፈጣሪ የሚወደው ተግባር ነው በሚል የስራ ባልደረቦቻቸው ያደረጉላቸው ድጋፍ ያልጠበቁት በመሆኑ ትልቅ ደስታን ፈጥሮላቸዋል። ለተደረገላቸው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞችና አመራሮች ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ የወር ደመወዛቸው አነስተኛ ለሆኑ ሰራተኞች ተመሳሳይ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል።
አዲስ ዘመን ሐምሌ 30/2012
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞች እና አመራሮች በተቋሙ ውስጥ ለሚሰሩና የወር ደመወዛቸው አነስተኛ ለሆኑ የስራ ባልደረቦቻቸው የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።
“እኛው ለእኛው” በሚል መርህ የተደረገው ይሄው ድጋፍ የተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮች ከወር ደሞዛቸው በመቀነስ ከለገሱት የተገኘ መሆኑን የድርጅቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድም ተክሉ አስታውቀዋል።
እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ፤ ይህ ድጋፍ ትልቅ ስራ ነው ተብሎ የታሰበ አይደለም፤ ነገር ግን በአንድ ተቋም ውስጥ ሊኖር የሚገባውን የእርስ በእርስ መተሳሰብን ለማጠናከር ታስቦ የተደረገና ሌሎች መሰል ተቋማትም ይሄንኑ ተግባር እንዲያከናውኑ ለማነሳሳት ነው።
የዚህ አይነቱ እርስ በእርስ የመተሳሰብና የመረዳዳት ባህልን በተቋም ውስጥ መገንባት ከተቻለ ተቋሙ ሊያሳከው የሚፈልገውን ግብ ከዳር ለማድረስ እንደ አንድ ግብአት የሚረዳ ይሆናል ያሉት አቶ ወንድም፤ በሰራተኞች መካከልም መዋደድና መተሳሰብን የሚፈጥር ነው ብለዋል።
በቀጣይም በተቋሙ የሚታሰበው ትልቁ ስራ እነዚህ ሰራተኞች እራሳቸውን በኢኮኖሚ የሚጠቅሙበትን ሁኔታ ማመቻቸት መሆኑን የጠቆሙት አቶ ወንድም፤ የሰራተኛውን ችግር በቋሚነት ሊፈቱ የሚችሉ ስራዎች በተቋሙ እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ለሰራተኞቹ የተደረገውን ድጋፍ ያስተባበሩት ወ/ሮ ብርሃኔ ደመቀ እንደተናጉት፤ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ ከተከሰተ ወዲህ በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የኑሮ ጫናው በርትቶባቸዋል፤ ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ውስጥ የሚገኙና የወር ገቢያቸው አነስተኛ የሆኑ ሰራተኞችን መደገፍ አስፈላጊ ሆኗል።
ይህንን የተቀደሰ ተግባር ከዳር ለማድረስም የድርጅቱ ሰራተኞችና አመራሮች ከወር ደመወዛቸው የሚቀነስ ገንዘብ በማዋጣት ለ43 የስራ ባልደረቦቻቸው ከጎናቸው መቆማቸውን በተግባር ማሳየት መቻላቸውን ወ/ሮ ብርሃኔ አብራርተዋል።
እንደ ወ/ሮ ብርሃኔ ገለፃ፤ እርስበርስ መረዳዳቱ በጣም አስፈላጊና ፈጣሪም የሚወደው ስራ ስለሆነ ድጋፍ የተደረገላቸውም ብቻ ሳይሆኑ ድጋፍ ያደረጉ ሰራተኞችም ደስተኛ ሆነዋል።
በእለቱ ድጋፍ ከተደረገላቸው ሰራተኞች መካከል የሆኑት ወ/ሮ ፀሀይ ደበሌ እና ወ/ሮ አበበች አስፋው እንደተናገሩት፤ የድርጅቱ ሰራተኞች ይህን መልካም ተግባር አስበው ድጋፍ በማድረጋቸው በእጅጉ ተደስተዋል። ይህ ክፉ ጊዜ እስኪያልፍ ድረስ እርስ በርስ እየተረዳዱ ማለፉን ፈጣሪ የሚወደው ተግባር ነው በሚል የስራ ባልደረቦቻቸው ያደረጉላቸው ድጋፍ ያልጠበቁት በመሆኑ ትልቅ ደስታን ፈጥሮላቸዋል። ለተደረገላቸው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞችና አመራሮች ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ የወር ደመወዛቸው አነስተኛ ለሆኑ ሰራተኞች ተመሳሳይ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል።
አዲስ ዘመን ሐምሌ 30/2012
« የወንጀለኞች ቡድን በአገር ጥቅም ከመደራደር ወደ ኋላ አይልም » - ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የለውጡ አመራር ወደ ሥልጣን ከመጣ ማግስት ጀምሮ ወንጀል እየሰራ ያለው የወንጀለኞች ቡድን ወደ ሕግ የሚያቀርበው በመጥፋቱ ሥልጣን ይዞ እንደፈለገው ለመሆን ምንጊዜም በአገር ጥቅም ከመደራደር ወደ ኋላ እንደማይል ተገለጸ፡፡
ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በወቅታዊ አገራዊ ሁኔታ ላይ ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የለውጡ አመራር ወደ ሥልጣን ከመጣ ማግስት ጀምሮ ወንጀል እየሰራ ያለው የወንጀለኞች ቡድን ወደ ሕግ የሚያቀርበው በመጥፋቱ ሥልጣን ይዞ እንደፈልገው ለመሆን በአገር ጥቅም ከመደራደር ምንጊዜም ወደ ኋላ የሚል አይደለም።ሁሉም ወንጀለኞች የአገርን ጥቅም አሳልፈው አይሰጡም።የአገርን ጥቅም አሳልፈው የሚሸጡ ግን ሁሌም ወንጀለኞች ናቸው፡፡
መፈንቅለ መንግሥት የማድረግ ፍላጎት ያለው ይህ የወንጀለኞች ቡድን የለውጡ መንግሥት ሥልጣን ላይ እንዲቆይ እንደማይፈልግ አመልክተው፤ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል የደንቆሮዎች ፖሊሲ የአገርን ሉዓላዊነትና ነፃነት ለግብጽ አሳልፈው መስጠት የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያው የውሃ ሙሌት በሚጀመርበት ጊዜ ሀጫሉን በመግደል ለዜጎች ሞትና ለንብረት ውድመት እንዲከሰት ማድረጉን ተናግረዋል።
ይህ የወንጀለኞች ቡድን ኦሮሞና አማራን ማጋጨት በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ መቀልበስ ይቻላል ብሎ እንደሚያምን አመልክተው፤ ለዚህም ሲባል ሀጫሉ እንዲገደል ማድረጉ የቡድኑ የሴራ ፖለቲካ ውጤት መሆኑንም አስረድተዋል።
በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የተፈጠሩት የጸጥታ ችግሮች በጸረ ለውጡ ቡድን የተቀነባበሩ መሆናቸውን አውስተው፤ ከሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም በፊት መፈንቀለ መንግሥት ተሞከረ፣ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ቦምብ ተወረወረ፣ ቡራዮ በተከሰተው ችግር መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ ኮማንዶ ቤተ መንግሥት መግባት፣በጥቅምትና ኅዳር ወራቶች 2011 ዓ.ም አካባቢ በኦሮሚያና በጌዲዮ፣ በኦሮሚያ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልል፣ በአማራ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በአማራና በቅማንት ግጭቶች ተከስተው በርካታ ሰዎች መፈናቀላቸው አመልክተዋል።
እንዲሁም የእስልምና እና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮችን እንዲጋጩ መደረጉን፣ ቤተ ክርስቲያንና መስኪዶች መቃጠላቸውና ይህ መፈንቅለ መንግሥት መደረግ አለበት ብሎ ሲጎተጉት በነበረውና በተለያየ መንገድ ለውጡን እየመራ ያለ መንግሥት ደካማ ነው፤ ጸጥታ ማስከበር አይችልም የሚለውን ነገር ለማስረገጥ በማሰብም ሴት ልጆችን መጥለፉንና ጠለፍኩ ብሎ መናገር ያልቻለው በሕጋዊነት በአገር ላይ ስለሚኖር መሆኑንም ተናግረዋል።
ጸረ ለውጥ ቡድኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካ ተቀባይነት እንዳያገኙ ብዙ ሴራዎች መፈጸሙን አመልክተው፤ ይህ ጸረ ለውጥ ቡድን ህዳሴ ግድብ ተሸጠ አለ፣ ሌላም ሌላም የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ነዛ ያቀደው ግን ሊሳካለት አለመቻሉና ወደፊትም እንደማይሳካት ገልጸዋል፡፡
መንግሥት የወንጀለኛውን ቡድን አባላት የትም ይሁን የትም የገቡበት ገብቶ ይዞ ፍርድ ቤት ማቅረብ አለበት የሚል እምነት እንዳላቸው አመልክተው፤ እስካሁንም መንግሥት በጣም ትዕግስት አድርጓል፤ ትዕግስት ማድረጉ ትክክል ቢሆንም ወንጀል በተለይም ልታልፈው በማይገባ ወንጀል ላይ ትዕግስት ማድረግ የለበትም፤ ምክንያቱም የኔት ወርክ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ማግስት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ወንጀል የሚፈጸመው በተመሳሳይ ቡድን ነው ብለዋል፡፡
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የለውጡ አመራር ወደ ሥልጣን ከመጣ ማግስት ጀምሮ ወንጀል እየሰራ ያለው የወንጀለኞች ቡድን ወደ ሕግ የሚያቀርበው በመጥፋቱ ሥልጣን ይዞ እንደፈለገው ለመሆን ምንጊዜም በአገር ጥቅም ከመደራደር ወደ ኋላ እንደማይል ተገለጸ፡፡
ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በወቅታዊ አገራዊ ሁኔታ ላይ ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የለውጡ አመራር ወደ ሥልጣን ከመጣ ማግስት ጀምሮ ወንጀል እየሰራ ያለው የወንጀለኞች ቡድን ወደ ሕግ የሚያቀርበው በመጥፋቱ ሥልጣን ይዞ እንደፈልገው ለመሆን በአገር ጥቅም ከመደራደር ምንጊዜም ወደ ኋላ የሚል አይደለም።ሁሉም ወንጀለኞች የአገርን ጥቅም አሳልፈው አይሰጡም።የአገርን ጥቅም አሳልፈው የሚሸጡ ግን ሁሌም ወንጀለኞች ናቸው፡፡
መፈንቅለ መንግሥት የማድረግ ፍላጎት ያለው ይህ የወንጀለኞች ቡድን የለውጡ መንግሥት ሥልጣን ላይ እንዲቆይ እንደማይፈልግ አመልክተው፤ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል የደንቆሮዎች ፖሊሲ የአገርን ሉዓላዊነትና ነፃነት ለግብጽ አሳልፈው መስጠት የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያው የውሃ ሙሌት በሚጀመርበት ጊዜ ሀጫሉን በመግደል ለዜጎች ሞትና ለንብረት ውድመት እንዲከሰት ማድረጉን ተናግረዋል።
ይህ የወንጀለኞች ቡድን ኦሮሞና አማራን ማጋጨት በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ መቀልበስ ይቻላል ብሎ እንደሚያምን አመልክተው፤ ለዚህም ሲባል ሀጫሉ እንዲገደል ማድረጉ የቡድኑ የሴራ ፖለቲካ ውጤት መሆኑንም አስረድተዋል።
በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የተፈጠሩት የጸጥታ ችግሮች በጸረ ለውጡ ቡድን የተቀነባበሩ መሆናቸውን አውስተው፤ ከሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም በፊት መፈንቀለ መንግሥት ተሞከረ፣ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ቦምብ ተወረወረ፣ ቡራዮ በተከሰተው ችግር መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ ኮማንዶ ቤተ መንግሥት መግባት፣በጥቅምትና ኅዳር ወራቶች 2011 ዓ.ም አካባቢ በኦሮሚያና በጌዲዮ፣ በኦሮሚያ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልል፣ በአማራ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በአማራና በቅማንት ግጭቶች ተከስተው በርካታ ሰዎች መፈናቀላቸው አመልክተዋል።
እንዲሁም የእስልምና እና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮችን እንዲጋጩ መደረጉን፣ ቤተ ክርስቲያንና መስኪዶች መቃጠላቸውና ይህ መፈንቅለ መንግሥት መደረግ አለበት ብሎ ሲጎተጉት በነበረውና በተለያየ መንገድ ለውጡን እየመራ ያለ መንግሥት ደካማ ነው፤ ጸጥታ ማስከበር አይችልም የሚለውን ነገር ለማስረገጥ በማሰብም ሴት ልጆችን መጥለፉንና ጠለፍኩ ብሎ መናገር ያልቻለው በሕጋዊነት በአገር ላይ ስለሚኖር መሆኑንም ተናግረዋል።
ጸረ ለውጥ ቡድኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካ ተቀባይነት እንዳያገኙ ብዙ ሴራዎች መፈጸሙን አመልክተው፤ ይህ ጸረ ለውጥ ቡድን ህዳሴ ግድብ ተሸጠ አለ፣ ሌላም ሌላም የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ነዛ ያቀደው ግን ሊሳካለት አለመቻሉና ወደፊትም እንደማይሳካት ገልጸዋል፡፡
መንግሥት የወንጀለኛውን ቡድን አባላት የትም ይሁን የትም የገቡበት ገብቶ ይዞ ፍርድ ቤት ማቅረብ አለበት የሚል እምነት እንዳላቸው አመልክተው፤ እስካሁንም መንግሥት በጣም ትዕግስት አድርጓል፤ ትዕግስት ማድረጉ ትክክል ቢሆንም ወንጀል በተለይም ልታልፈው በማይገባ ወንጀል ላይ ትዕግስት ማድረግ የለበትም፤ ምክንያቱም የኔት ወርክ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ማግስት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ወንጀል የሚፈጸመው በተመሳሳይ ቡድን ነው ብለዋል፡፡
የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በመጥለፍ የተከሰሱ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ
***************************
በእነ ከሊፋ አብዱረህማን የክስ መዝገብ የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ህዳር 24 እና 25/2012 ዓ.ም በመጥለፍ በሽብር ወንጀል ከተከሰሱት 17 ግለሰቦች መካከል ዘጠኙ በዛሬው ዕለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
በሦስት የሽብር ወንጀል የተከሰሱት ተከሳሾቹ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው የተከሰሱበት ወንጀል ተነቦላቸዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ተከሳሾቹ በበኩላቸው ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት መቃወሚያ በጽሁፍ አቅርበዋል።
ከሳሽ ዐቃቤ ህግ በመቃወሚያው ላይ ምላሽ እንዲሰጥና ትእዛዝ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለነሐሴ 25/2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። EBC
***************************
በእነ ከሊፋ አብዱረህማን የክስ መዝገብ የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ህዳር 24 እና 25/2012 ዓ.ም በመጥለፍ በሽብር ወንጀል ከተከሰሱት 17 ግለሰቦች መካከል ዘጠኙ በዛሬው ዕለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
በሦስት የሽብር ወንጀል የተከሰሱት ተከሳሾቹ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው የተከሰሱበት ወንጀል ተነቦላቸዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ተከሳሾቹ በበኩላቸው ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት መቃወሚያ በጽሁፍ አቅርበዋል።
ከሳሽ ዐቃቤ ህግ በመቃወሚያው ላይ ምላሽ እንዲሰጥና ትእዛዝ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለነሐሴ 25/2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። EBC
“ቄሮ የለውጥ እንጂ የጥፋት ኃይል አይደለም” - ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ፣ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የኦሮሚያ ክልል ወጣት(ቄሮ) የለውጥ እንጂ የጥፋት ኃይል እንዳልሆነ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ አስታወቁ፡፡ ለዚህም የታገለለትንና ዋጋ የከፈለበትን ለውጥ ወደኋላ የሚመልሱ አክራሪ ጽንፈኞችን የሁከት ጥሪ በእምቢታ በማክሸፍ የለውጥ ኃይል መሆኑን በድጋሚ በግልጽ ማረጋገጡን አመልክተዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ቄሮ ለውጡን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍሎ ያመጣው መሆኑን በማስታወስ ጽንፈኛ ኃይሎች ይህንን ኃይል የከንቱ ፍላጎታቸው ማስፈጸሚያ ለማድረግ የሁከትና የአመጽ ጥሪዎችን በተለያዩ ጊዜያት ቢያስተላልፉለትም ለጥሪያቸው እምቢተኝነቱን በመግለጽ የለውጥ ኃይልነቱን በአደባባይ በተጨባጭ አስመስክሯል ብለዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ገለጻ፤ አሁን የሚደረጉ የሁከትና የአመጽ ጥሪዎች ባለፈው የተፈጠረውን ችግር ማስቀጠል የሚፈልጉ ኃይሎች ጥሪ ነው፤ ሰዎቹ የቀደመውን ሁከት ያቀነባበሩ ናቸው፡፡ በሕዝብ የተተፉ፣ ሌሎችም በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ የተደረጉ ናቸው፡፡
እነዚህ ኃይሎች አንድ እግራቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ፤ አንድ እግራቸውን ደግሞ ውጪ አድርገው የሚጫወቱ መሆናቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፣ ብሔርንና ሃይማኖትን መሰረት ያደረጉ ጥፋቶች እንዲቀጥሉ የሚፈልጉና ይሄንን ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ እንደሆኑም አስታውቀዋል ።
ከዚህ በፊት ወጣቱ ለለውጥ ሲያደርግ የነበረው እንቅስቃሴ በእነሱ የተፈጠረ አጀንዳ እንደሆነ በማስመሰል እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጠቁመው፣ እነዚህ ሰዎች ዛሬ ላይ የሚያደርጉት ጥሪ እና እንቅስቃሴ፤ ትናንት ወጣቱ ሲያደርገው ከነበረው ትግልና እንቅስቃሴ ጋር በጣም የተለያየ ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ የማይገናኝ ሆድና ጀርባ መሆኑን አመልክተዋል ።
ለዚህ እኩይ ተግባራቸው መሳካት እነሱ ቄሮ እያሉ የሚጣሩ ቢሆንም፤ ቄሮ የተፈጠረው ለእኩልነት ነው፣ ለፍትህ ነው የታገለው፤ ሕይወትም የከፈለው ለዚህ ነው ብለዋል ። ለሕዝቦች እኩልነትና ለፍትህ የታገለው ቄሮ ለእኩይ አላማቸው ጆሮውን በመንፈግ በኦሮሚያ ያለው ቄሮ የለውጥ ኃይል እንጂ የጥፋት ኃይል አለመሆኑን አሳይቷቸዋል ሲሉም ተናግረዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ እንደሚሉት፤ ቄሮ የታገለው የኦሮሞን ህዝብ ከሌላ ብሔር ጋር እኩል እንዲኖር፤ እኩል ተጠቃሚ እንዲሆን ነው። ሁሉም ሃይማኖት እኩል እንዲሆንና በእኩል እንዲከበር ነው። ከዚህ በተቃራኒው አንዱ የበላይ፣ ሌላው የበታች እንዲሆን፤ ጨቋኝና ተጨቋኝ እንዲኖር አይደለም።
ከውጪም ከውስጥም ሆነው ለእኩይ አላማ የሚንቀሳቀሱ እነዚህ ኃይሎች ትናንትና ቄሮ ጠይቆና ታግሎ ያመጣው ለውጥ በእነርሱ አጀንዳ እንደተፈጠረ አድርገው ለመሳል የሚያደርጉት ጥረት ከጅምሩም ትክክል አልነበረም፤ አሁን ደግሞ በተጨባጭ ትክክል እንዳልሆነ ከተግባራቸው ተረጋግጧል። ጉዞው ለየቅል መሆኑን ማየት ተችሏል፤ አሁንም መመልከት ይቻላል።
እነዚህ ኃይሎች እየተደረጉ ያሉት ቅስቀሳ ሆነ ጥሪ አገር የሚያጠፉ ነው ፤ ይሄን ለውጥ ወደኋላ እንዲመለስ የሚያደርግ ነው ፤ ይሄን የሚያደርጉ ቅጥረኞች ናቸው፤ ትናንትና እኛ ሞተን ያመጣነውን ለውጥ፣ ያመጣነውን እኩልነት ለመቀየር የሚደረጉ ጥረቶች ናቸው። ይሄን ጥረታቸውን ለማሳካትም በወጣቱ ስም የሚነግዱ መሆናቸውን አመልክተዋል።
“አሁንም የሚደረጉ ጥሪዎች እንዲከሽፉ፤ ሲቀሰቅሱ የነበሩት የጥፋት አጀንዳዎች ተግባራዊ እንዳይሆኑ ያደረገው ወጣቱ ራሱ ነው። በመሆኑም ይሄ ቅስቀሳና ጥሪ የወጣቱ አጀንዳ አይደለም። የጥቂት አክራሪዎች አጀንዳ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ደግሞ ወጣቱ የአክራሪነት ዝንባሌ የለውም። ጥያቄው ለሁሉም ሕዝቦች የእኩልነት፣ የፍትህና የማንነት ጥያቄ እንዲረጋገጥ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ቄሮ ትግል ሲጀምር ለኦሮሞ ብቻ አይደለም፤ ለሁሉም ነው የታገለው። ለሁሉም ነው የሞተው። አሁንም ይሄው አስተሳሰብ ነው ወጣቱ ውስጥ ያለው” ብለዋል ።
አሁን ያለው የብሔር አክራሪነትና የሃይማኖት አክራሪነት ኦሮሚያ ውስጥ ያለው ቄሮ አመለካከት አይደለም። ይሄንን የሚገልጽም አይደለም። አሁን የተደረገው ጥሪ የወደቀውም ከዚህ አንጻር ነው። አጀንዳቸውን የወጣቱ አጀንዳ ማድረግ ያልቻሉትም ከዚህ አንጻር ነው።
አሁን ወጣቱና የጸጥታ ኃይሉ አብሮ እየሰራ ነው። በዚህም በቅርቡ በተፈጠረው ግርግር ምንም ውስጥ የሌሉ ወጣቶች ችግሩን ለማስቀረት ሲሰሩ አካላቸውን ሕይወታቸውን ከፍለዋል። የብሔር ግጭት እንዳይፈጠር፤ የሃይማኖት ግጭት እንዳይፈጠር ከማድረግ አኳያ፤ አሁን እየሆነ ያለው ነገር ክፋት ነው በማለት ከፖሊስ ጎን ሆነው እንደ መንግስት ምንም ኃላፊነት ሳይኖራቸው ሕይወታቸውን የገበሩ ጥቂት እንዳልሆኑ አስታውቀዋል ።
ይሄ ደግሞ ትናንት የታገለለት የፍትህና ለእኩልነትና ዓላማ ወደኋላ እንዳይመለስ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። ሌሎች ጓደኞቻቸው ቀድመው የሞቱለት ዓላማ ወደኋላ እንዳይቀለበስ ለማድረግ እንደሆነ አስታውቀዋል። እዚም እዛም የሚታየውም ጥቂት ቅጥረኞች የሚያደርጉት እንጂ የወጣቱ አጀንዳና ተግባር አይደለም ብለዋል።
ለምሳሌ፣ ድንጋይ የሚያስቀምጡ ቅጥረኛ ኃይሎች አሉ፤ ወያኔም አሰልጥኖ የሚልካቸው ኃይሎች አሉ። እነዚህን ደግሞ ከጸጥታ ኃይሉ በተጓዳኝ ወጣቶች ናቸው ይዘው ለህግ እያቀረቧቸው ያሉት። በዚህም አሁን ኦሮሚያ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሰላም እንደሆነ አስታውቀዋል።
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የኦሮሚያ ክልል ወጣት(ቄሮ) የለውጥ እንጂ የጥፋት ኃይል እንዳልሆነ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ አስታወቁ፡፡ ለዚህም የታገለለትንና ዋጋ የከፈለበትን ለውጥ ወደኋላ የሚመልሱ አክራሪ ጽንፈኞችን የሁከት ጥሪ በእምቢታ በማክሸፍ የለውጥ ኃይል መሆኑን በድጋሚ በግልጽ ማረጋገጡን አመልክተዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ቄሮ ለውጡን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍሎ ያመጣው መሆኑን በማስታወስ ጽንፈኛ ኃይሎች ይህንን ኃይል የከንቱ ፍላጎታቸው ማስፈጸሚያ ለማድረግ የሁከትና የአመጽ ጥሪዎችን በተለያዩ ጊዜያት ቢያስተላልፉለትም ለጥሪያቸው እምቢተኝነቱን በመግለጽ የለውጥ ኃይልነቱን በአደባባይ በተጨባጭ አስመስክሯል ብለዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ገለጻ፤ አሁን የሚደረጉ የሁከትና የአመጽ ጥሪዎች ባለፈው የተፈጠረውን ችግር ማስቀጠል የሚፈልጉ ኃይሎች ጥሪ ነው፤ ሰዎቹ የቀደመውን ሁከት ያቀነባበሩ ናቸው፡፡ በሕዝብ የተተፉ፣ ሌሎችም በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ የተደረጉ ናቸው፡፡
እነዚህ ኃይሎች አንድ እግራቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ፤ አንድ እግራቸውን ደግሞ ውጪ አድርገው የሚጫወቱ መሆናቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፣ ብሔርንና ሃይማኖትን መሰረት ያደረጉ ጥፋቶች እንዲቀጥሉ የሚፈልጉና ይሄንን ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ እንደሆኑም አስታውቀዋል ።
ከዚህ በፊት ወጣቱ ለለውጥ ሲያደርግ የነበረው እንቅስቃሴ በእነሱ የተፈጠረ አጀንዳ እንደሆነ በማስመሰል እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጠቁመው፣ እነዚህ ሰዎች ዛሬ ላይ የሚያደርጉት ጥሪ እና እንቅስቃሴ፤ ትናንት ወጣቱ ሲያደርገው ከነበረው ትግልና እንቅስቃሴ ጋር በጣም የተለያየ ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ የማይገናኝ ሆድና ጀርባ መሆኑን አመልክተዋል ።
ለዚህ እኩይ ተግባራቸው መሳካት እነሱ ቄሮ እያሉ የሚጣሩ ቢሆንም፤ ቄሮ የተፈጠረው ለእኩልነት ነው፣ ለፍትህ ነው የታገለው፤ ሕይወትም የከፈለው ለዚህ ነው ብለዋል ። ለሕዝቦች እኩልነትና ለፍትህ የታገለው ቄሮ ለእኩይ አላማቸው ጆሮውን በመንፈግ በኦሮሚያ ያለው ቄሮ የለውጥ ኃይል እንጂ የጥፋት ኃይል አለመሆኑን አሳይቷቸዋል ሲሉም ተናግረዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ እንደሚሉት፤ ቄሮ የታገለው የኦሮሞን ህዝብ ከሌላ ብሔር ጋር እኩል እንዲኖር፤ እኩል ተጠቃሚ እንዲሆን ነው። ሁሉም ሃይማኖት እኩል እንዲሆንና በእኩል እንዲከበር ነው። ከዚህ በተቃራኒው አንዱ የበላይ፣ ሌላው የበታች እንዲሆን፤ ጨቋኝና ተጨቋኝ እንዲኖር አይደለም።
ከውጪም ከውስጥም ሆነው ለእኩይ አላማ የሚንቀሳቀሱ እነዚህ ኃይሎች ትናንትና ቄሮ ጠይቆና ታግሎ ያመጣው ለውጥ በእነርሱ አጀንዳ እንደተፈጠረ አድርገው ለመሳል የሚያደርጉት ጥረት ከጅምሩም ትክክል አልነበረም፤ አሁን ደግሞ በተጨባጭ ትክክል እንዳልሆነ ከተግባራቸው ተረጋግጧል። ጉዞው ለየቅል መሆኑን ማየት ተችሏል፤ አሁንም መመልከት ይቻላል።
እነዚህ ኃይሎች እየተደረጉ ያሉት ቅስቀሳ ሆነ ጥሪ አገር የሚያጠፉ ነው ፤ ይሄን ለውጥ ወደኋላ እንዲመለስ የሚያደርግ ነው ፤ ይሄን የሚያደርጉ ቅጥረኞች ናቸው፤ ትናንትና እኛ ሞተን ያመጣነውን ለውጥ፣ ያመጣነውን እኩልነት ለመቀየር የሚደረጉ ጥረቶች ናቸው። ይሄን ጥረታቸውን ለማሳካትም በወጣቱ ስም የሚነግዱ መሆናቸውን አመልክተዋል።
“አሁንም የሚደረጉ ጥሪዎች እንዲከሽፉ፤ ሲቀሰቅሱ የነበሩት የጥፋት አጀንዳዎች ተግባራዊ እንዳይሆኑ ያደረገው ወጣቱ ራሱ ነው። በመሆኑም ይሄ ቅስቀሳና ጥሪ የወጣቱ አጀንዳ አይደለም። የጥቂት አክራሪዎች አጀንዳ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ደግሞ ወጣቱ የአክራሪነት ዝንባሌ የለውም። ጥያቄው ለሁሉም ሕዝቦች የእኩልነት፣ የፍትህና የማንነት ጥያቄ እንዲረጋገጥ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ቄሮ ትግል ሲጀምር ለኦሮሞ ብቻ አይደለም፤ ለሁሉም ነው የታገለው። ለሁሉም ነው የሞተው። አሁንም ይሄው አስተሳሰብ ነው ወጣቱ ውስጥ ያለው” ብለዋል ።
አሁን ያለው የብሔር አክራሪነትና የሃይማኖት አክራሪነት ኦሮሚያ ውስጥ ያለው ቄሮ አመለካከት አይደለም። ይሄንን የሚገልጽም አይደለም። አሁን የተደረገው ጥሪ የወደቀውም ከዚህ አንጻር ነው። አጀንዳቸውን የወጣቱ አጀንዳ ማድረግ ያልቻሉትም ከዚህ አንጻር ነው።
አሁን ወጣቱና የጸጥታ ኃይሉ አብሮ እየሰራ ነው። በዚህም በቅርቡ በተፈጠረው ግርግር ምንም ውስጥ የሌሉ ወጣቶች ችግሩን ለማስቀረት ሲሰሩ አካላቸውን ሕይወታቸውን ከፍለዋል። የብሔር ግጭት እንዳይፈጠር፤ የሃይማኖት ግጭት እንዳይፈጠር ከማድረግ አኳያ፤ አሁን እየሆነ ያለው ነገር ክፋት ነው በማለት ከፖሊስ ጎን ሆነው እንደ መንግስት ምንም ኃላፊነት ሳይኖራቸው ሕይወታቸውን የገበሩ ጥቂት እንዳልሆኑ አስታውቀዋል ።
ይሄ ደግሞ ትናንት የታገለለት የፍትህና ለእኩልነትና ዓላማ ወደኋላ እንዳይመለስ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። ሌሎች ጓደኞቻቸው ቀድመው የሞቱለት ዓላማ ወደኋላ እንዳይቀለበስ ለማድረግ እንደሆነ አስታውቀዋል። እዚም እዛም የሚታየውም ጥቂት ቅጥረኞች የሚያደርጉት እንጂ የወጣቱ አጀንዳና ተግባር አይደለም ብለዋል።
ለምሳሌ፣ ድንጋይ የሚያስቀምጡ ቅጥረኛ ኃይሎች አሉ፤ ወያኔም አሰልጥኖ የሚልካቸው ኃይሎች አሉ። እነዚህን ደግሞ ከጸጥታ ኃይሉ በተጓዳኝ ወጣቶች ናቸው ይዘው ለህግ እያቀረቧቸው ያሉት። በዚህም አሁን ኦሮሚያ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሰላም እንደሆነ አስታውቀዋል።
👍1
ከ8ኛና 12ኛ ክፍል ውጭ ላሉ ተማሪዎች የነፃ ዝውውር መደረጉ ትምህርት ጥራት ላይ የሚፈጥረው ችግር እንደማይኖር የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
*************************
የትምህርት ሚኒስቴር ከ8ኛ እና 12 ኛ ክፍል ውጭ ያሉ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል ካለፈተና እንዲዛወሩ መወሰኑን ተከትሎ የትምህርት ጥራት ላይ ጥያቄዎች እየተነሱ ነው።
የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ) የነፃ ዝውውር መደረጉ ተማሪዎች ላይ የሚፈጠረውን ጫና መንግስት እንዲሸከም በማድረግ ከትምህርት ውጭ የቆዩ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማድረግ ታስቦ ነው ብለዋል።
አሁን በምንከተለው ስርዓተ ትምህርት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ አንችልም ያሉት ሚኒስትሩ 2014 ላይ ወደ ተግባር የሚገባ ስረዓተ ትምህርት የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል።
የትምህርት ጥራት ችግርን በዘላቂነት የሚፈታው ይህ ስርዓተ ትምህርት እንጂ ፈተና በመፈተንና ባለመፈተን የሚረጋገት የትምህርት ጥራት አይኖርም ነው ያሉት።
የትምህርት ሚኒስቴር የነፃ ዝውውር ውሳኔን ሲወስን የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮ በመውሰድና በተለያየ ምክንያት
የኮቪድ 19ኝ ወረርሽኝን ተከትሎ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ስለቆዩ በዚያው እንዳይቀሩ ለማድረግ ታስቦም ጭምር ነው።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትምህርት ሚኒስቴር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።
*************************
የትምህርት ሚኒስቴር ከ8ኛ እና 12 ኛ ክፍል ውጭ ያሉ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል ካለፈተና እንዲዛወሩ መወሰኑን ተከትሎ የትምህርት ጥራት ላይ ጥያቄዎች እየተነሱ ነው።
የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ) የነፃ ዝውውር መደረጉ ተማሪዎች ላይ የሚፈጠረውን ጫና መንግስት እንዲሸከም በማድረግ ከትምህርት ውጭ የቆዩ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማድረግ ታስቦ ነው ብለዋል።
አሁን በምንከተለው ስርዓተ ትምህርት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ አንችልም ያሉት ሚኒስትሩ 2014 ላይ ወደ ተግባር የሚገባ ስረዓተ ትምህርት የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል።
የትምህርት ጥራት ችግርን በዘላቂነት የሚፈታው ይህ ስርዓተ ትምህርት እንጂ ፈተና በመፈተንና ባለመፈተን የሚረጋገት የትምህርት ጥራት አይኖርም ነው ያሉት።
የትምህርት ሚኒስቴር የነፃ ዝውውር ውሳኔን ሲወስን የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮ በመውሰድና በተለያየ ምክንያት
የኮቪድ 19ኝ ወረርሽኝን ተከትሎ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ስለቆዩ በዚያው እንዳይቀሩ ለማድረግ ታስቦም ጭምር ነው።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትምህርት ሚኒስቴር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።
ለ12ኛ ክፍል አይነ ስውራን ተማሪዎች እየተሰጠ ያለው የተስማሚ ቴክኖሎጂ ስልጠና በታሰበለት ደረጃ እየሄደ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
----------------------------------------------------
ሚኒስቴሩ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ሁሉም አይነሰውራን ተማሪዎች በኦንላይን እንዲፈተኑ ለማድረግ በሙሉ አቅም እየተሰራ መሆኑን አስታወቋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ ዓሊ ተማሪዎቹ ፈተናውን በኦንላይን ለመፈተን የሚያስችላቸውን መሰረታዊ እውቀት እየያዙ መሆኑን ተናግረዋል።
ገና ስልጠናው ሳይጀመር ለፈተና ብቁ ሊሆኑ አይችሉም ብሎ መገመት ለተማሪዎቹ ዝቅ ያለ ግምት መስጠት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ በተቻለ መጠን ለፈተና ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
እንደ አስፈላጊነቱ አጋዥ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎችም ለመመደብ እቅድ መያዙን አብራርተዋል።
ተማሪዎቹ እንደየ አካባቢያቸው ሁኔታ ከዚህ ቀደም የኮምፒውተር እውቀት ያላቸውና የሌላቸው በመሆናቸው ተመሳሳይ አቀባበል የላቸውም ያሉት የተስማሚ ቴክኖሎጂ ለአይነስውራን በኢትዮጵያ ዳይሬክተርና አሰልጣኝ ታምሩ እውነቱ (ዶ/ር) ይህንን ታሳቢ በማድረግ ተማሪዎችን በመለየት ለፈተና ዝግጁ ለማድረግ ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል።
ተማሪዎቹ በበኩላቸው አብዛኞቻችን ከዚህ ቀደም የኮምፒውተር እውቀት ስለሌለን የስልጠናው ጊዜ ቢራዘም የሚል ጥያቄ አንስተዋል።
ከመላ ሃገሪቱ የተውጣጡ 250 ዓይነስውራን ተማሪዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተስማሚ ቴክኖሎጂ ስልጠና እየወሰዱ ነው።
ስልጠናው ለፈተና ዝግጁ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በቀጣይ ለሚኖራቸው የስራ ጊዜ ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታሰባል።
----------------------------------------------------
ሚኒስቴሩ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ሁሉም አይነሰውራን ተማሪዎች በኦንላይን እንዲፈተኑ ለማድረግ በሙሉ አቅም እየተሰራ መሆኑን አስታወቋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ ዓሊ ተማሪዎቹ ፈተናውን በኦንላይን ለመፈተን የሚያስችላቸውን መሰረታዊ እውቀት እየያዙ መሆኑን ተናግረዋል።
ገና ስልጠናው ሳይጀመር ለፈተና ብቁ ሊሆኑ አይችሉም ብሎ መገመት ለተማሪዎቹ ዝቅ ያለ ግምት መስጠት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ በተቻለ መጠን ለፈተና ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
እንደ አስፈላጊነቱ አጋዥ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎችም ለመመደብ እቅድ መያዙን አብራርተዋል።
ተማሪዎቹ እንደየ አካባቢያቸው ሁኔታ ከዚህ ቀደም የኮምፒውተር እውቀት ያላቸውና የሌላቸው በመሆናቸው ተመሳሳይ አቀባበል የላቸውም ያሉት የተስማሚ ቴክኖሎጂ ለአይነስውራን በኢትዮጵያ ዳይሬክተርና አሰልጣኝ ታምሩ እውነቱ (ዶ/ር) ይህንን ታሳቢ በማድረግ ተማሪዎችን በመለየት ለፈተና ዝግጁ ለማድረግ ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል።
ተማሪዎቹ በበኩላቸው አብዛኞቻችን ከዚህ ቀደም የኮምፒውተር እውቀት ስለሌለን የስልጠናው ጊዜ ቢራዘም የሚል ጥያቄ አንስተዋል።
ከመላ ሃገሪቱ የተውጣጡ 250 ዓይነስውራን ተማሪዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተስማሚ ቴክኖሎጂ ስልጠና እየወሰዱ ነው።
ስልጠናው ለፈተና ዝግጁ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በቀጣይ ለሚኖራቸው የስራ ጊዜ ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታሰባል።
በየካ ክፍለ ከተማ የጎረቤቷን የኤቲኤም ካርድ በመስረቅ ከ5መቶ 80 ሺ ብር በላይ ወጪ አድርጋ ለግል ጥቅሟ ያዋለች ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ገለፀ፡፡
***
የግልተበዳይ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ እና ወንጀሉን ፈፅማለች የተባለችው ግለሰብ የቅርብ ግንኙነት እና ጉርብትና አላቸው፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮተቤ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መርማሪ ረዳት ሳጅን እስጢፋኖስ ገ/ታቲዎስ እንደገለፁት ተጠርጣሪዋ ከግል ተበዳይ ጋር ያላትን ቅርበት ተጠቅማ ወደ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ መኝታ ክፍል በመግባት ቁም ሳጥን ውስጥ ተቀምጦ የነበረ የዘመን ባንክ ኤቲኤም ካርድ ከነ ሚስጥር ቁጥሩ ሰርቃ በመውሰድ እና በተለያዩ ጊዜያት ከ5መቶ 80 ሺ ብር በላይ ከባንኩ ወጪ በማድረግ ለግል ጥቅሟ አውላች፡፡
የግል ተበዳይ ከሀገር ውጭ የሚኖሩ መሆናቸውን የገለፁት ተወካያቸው አቶ ወርቁ ለገሰ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ የኤቲኤም ካርዱን ከባንኩ ከወሰዱበት ጊዜ ጀምሮ ተጠቅመውበት እንደማያውቁ እና ባላወቁት ሁኔታ ገንዘቡ ከባንክ ወጪ መደረጉን ባወቁ ጊዜ ለፖሊስ ማመልከታቸውን የተናገሩ ሲሆን ግለሰቧ የፈፀመችው ተግባር በመተማመን መካከል መልካም ግንኙነትን የሚያጠለሽ ክስተት ሊፈጠር እንደሚችል በመገንዘብ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ያየንበት ነው ብለዋል፡፡
ፖሊስ ከባንኩ ባገኘው መረጃ መሰረት በተጠርጣሪዋ ላይ ክትትል በማድረግ በየካ ክፍለ ከተማ ክልል ውስጥ በቁጥጥር ስር እንዳዋላት እና በአሁኑ ወቅትም ምርመራ እየተጣራባት እንደሚገኝ ያስረዱት ረዳት ሳጅን እስጢፋኖስ ገ/ታቲዎስ የኤቲኤም ካርድ የሚጠቀሙ ግለሰቦች የሚስጥር ቁጥራቸውን ከተቻለ በቃላቸው መዝግበው በመያዝ ወረቀቱን ማስወገድ ይህ ካልተቻለም ሚስጥራዊ ቦታ በማስቀመጥ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
***
የግልተበዳይ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ እና ወንጀሉን ፈፅማለች የተባለችው ግለሰብ የቅርብ ግንኙነት እና ጉርብትና አላቸው፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮተቤ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መርማሪ ረዳት ሳጅን እስጢፋኖስ ገ/ታቲዎስ እንደገለፁት ተጠርጣሪዋ ከግል ተበዳይ ጋር ያላትን ቅርበት ተጠቅማ ወደ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ መኝታ ክፍል በመግባት ቁም ሳጥን ውስጥ ተቀምጦ የነበረ የዘመን ባንክ ኤቲኤም ካርድ ከነ ሚስጥር ቁጥሩ ሰርቃ በመውሰድ እና በተለያዩ ጊዜያት ከ5መቶ 80 ሺ ብር በላይ ከባንኩ ወጪ በማድረግ ለግል ጥቅሟ አውላች፡፡
የግል ተበዳይ ከሀገር ውጭ የሚኖሩ መሆናቸውን የገለፁት ተወካያቸው አቶ ወርቁ ለገሰ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ የኤቲኤም ካርዱን ከባንኩ ከወሰዱበት ጊዜ ጀምሮ ተጠቅመውበት እንደማያውቁ እና ባላወቁት ሁኔታ ገንዘቡ ከባንክ ወጪ መደረጉን ባወቁ ጊዜ ለፖሊስ ማመልከታቸውን የተናገሩ ሲሆን ግለሰቧ የፈፀመችው ተግባር በመተማመን መካከል መልካም ግንኙነትን የሚያጠለሽ ክስተት ሊፈጠር እንደሚችል በመገንዘብ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ያየንበት ነው ብለዋል፡፡
ፖሊስ ከባንኩ ባገኘው መረጃ መሰረት በተጠርጣሪዋ ላይ ክትትል በማድረግ በየካ ክፍለ ከተማ ክልል ውስጥ በቁጥጥር ስር እንዳዋላት እና በአሁኑ ወቅትም ምርመራ እየተጣራባት እንደሚገኝ ያስረዱት ረዳት ሳጅን እስጢፋኖስ ገ/ታቲዎስ የኤቲኤም ካርድ የሚጠቀሙ ግለሰቦች የሚስጥር ቁጥራቸውን ከተቻለ በቃላቸው መዝግበው በመያዝ ወረቀቱን ማስወገድ ይህ ካልተቻለም ሚስጥራዊ ቦታ በማስቀመጥ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በኳታር ዶሃ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው የቦንድ ግዥ ለመፈጸም ቃል ገቡ
*********^
በኳታር ዶሃ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት ሰሞኑን በኤምባሲው በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመገኘት ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው የቦንድ ግዥ ለመፈጸም ቃል ገብተዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት በኳታር የኢፌዲሪ አምባሳደር አምባሳደር ሳሚያ ዘካሪያ በእለቱ ባደረጉት ንግግር አገራችን ይህንን ታሪካዊ ድል ማስመዝገብ በመቻሏ ለሁሉም የአገራችን ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል።
አምባሳደሯ አገራችን የውሃ ሃብቷን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ለፈለገችው ልማት የመጠቀም ተፈጥሯዊ እና ህጋዊ መብቷን በተግባር ያረጋገጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪመ የግድቡ ግንባታ ከፍጻሜ እስኪደርስ ድረስ እያንዳንዱ ዜጋ የአቅሙን ድጋፍ በማድረግ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
በፕሮግራሙ የታደሙ የዳያስፖራ ተወካዮች እና የሚሲዮኑ የሥራ ባልደረቦችም የግድቡ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሙሌት በስኬት መጠናቀቅ ለአገራችን እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን አኩሪ ድል እንደሆነ እና የዚህ አኩሪ ታሪካዊ ስኬት አካል በመሆናቸውም ታላቅ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል። የግድቡ የግንባታ ስራ ከተጀመረበት እለት ጀምሮ ሲያደርጉ የቆዩትን ድጋፍ የበለጠ አጠናክረው ለማስቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡ ሲሆን፣ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ (575,000 ብር) ዋጋ ያለው የቦንድ ግዥ ለመፈጸምም ቃል ገብተዋል። ሌሎችንም የየማህበር አባሎቻቸውን እንዲሁም መላ የዳያስፖራ አባላትን ለመቀስቀስና ቦንድ ለማስገዛት እንደሚንቀሳቀሱም ቃል ገብተዋል።
በዶሃ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና ወዳጆች የግድብ ግንባታው ከተበሰረበት ጊዜ ጀምሮ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ዋጋ ያለው የቦንድ ግዥ ፈጽመዋል::
ከገንዘብ ድጋፍ ባለፈም በግድቡ ዙሪያ የሕዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ለመስራት ያለመ እና ከአስራ አምስት በላይ አባላት ያሉት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድንም ተመስርቶ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል። በዚህው በርካታ የዳያስፖራ አባላት በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎቻቸው አማካኝነት ስለ ህዳሴው ግድባችን በአርብኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎችን በመጠቀም ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ በመስራት ላይ ይገኛል።
*********^
በኳታር ዶሃ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት ሰሞኑን በኤምባሲው በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ በመገኘት ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያለው የቦንድ ግዥ ለመፈጸም ቃል ገብተዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር ሙሌት በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት በኳታር የኢፌዲሪ አምባሳደር አምባሳደር ሳሚያ ዘካሪያ በእለቱ ባደረጉት ንግግር አገራችን ይህንን ታሪካዊ ድል ማስመዝገብ በመቻሏ ለሁሉም የአገራችን ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላለፈዋል።
አምባሳደሯ አገራችን የውሃ ሃብቷን ፍትሃዊ እና ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ለፈለገችው ልማት የመጠቀም ተፈጥሯዊ እና ህጋዊ መብቷን በተግባር ያረጋገጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪመ የግድቡ ግንባታ ከፍጻሜ እስኪደርስ ድረስ እያንዳንዱ ዜጋ የአቅሙን ድጋፍ በማድረግ የዜግነት ግዴታውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
በፕሮግራሙ የታደሙ የዳያስፖራ ተወካዮች እና የሚሲዮኑ የሥራ ባልደረቦችም የግድቡ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሙሌት በስኬት መጠናቀቅ ለአገራችን እና ለመላው ኢትዮጵያዊያን አኩሪ ድል እንደሆነ እና የዚህ አኩሪ ታሪካዊ ስኬት አካል በመሆናቸውም ታላቅ ደስታ እንደተሰማቸው ገልጸዋል። የግድቡ የግንባታ ስራ ከተጀመረበት እለት ጀምሮ ሲያደርጉ የቆዩትን ድጋፍ የበለጠ አጠናክረው ለማስቀጠል ያላቸውን ቁርጠኝነት ያረጋገጡ ሲሆን፣ በተዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ብቻ ከግማሽ ሚሊዮን ብር በላይ (575,000 ብር) ዋጋ ያለው የቦንድ ግዥ ለመፈጸምም ቃል ገብተዋል። ሌሎችንም የየማህበር አባሎቻቸውን እንዲሁም መላ የዳያስፖራ አባላትን ለመቀስቀስና ቦንድ ለማስገዛት እንደሚንቀሳቀሱም ቃል ገብተዋል።
በዶሃ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና ወዳጆች የግድብ ግንባታው ከተበሰረበት ጊዜ ጀምሮ ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር በላይ ዋጋ ያለው የቦንድ ግዥ ፈጽመዋል::
ከገንዘብ ድጋፍ ባለፈም በግድቡ ዙሪያ የሕዝብ ግንኙነት ሥራዎችን ለመስራት ያለመ እና ከአስራ አምስት በላይ አባላት ያሉት የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ቡድንም ተመስርቶ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል። በዚህው በርካታ የዳያስፖራ አባላት በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎቻቸው አማካኝነት ስለ ህዳሴው ግድባችን በአርብኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎችን በመጠቀም ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ በመስራት ላይ ይገኛል።
"አንድ ክልል ከፌዴራል መንግስት ጋር ጦርነት እገጥማለሁ ብሎ ለጦርነት ቢነሳ መጀመሪያ ከራሱ ክልል ጋር ነው የሚጋጨው፤ ሁለተኛ ከመላ ኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ይጋጫል" - ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ
• አንድ ክልል ከፌዴራል መንግስቱ ጋር በስምምነት ነው መስራት ያለበት። ህገ መንግስቱን በመጣስ ከህግ ውጭ የሚሄድ ከሆነ ደግሞ በህገ መንግስቱ ውስጥ መፍትሄ አለው።
• አንድ ክልል ተነስቶ የፌዴራል መንግስትን በጦርነት አፈሙዝ አሸንፌ የሆነ ነገር አደርጋለሁ የሚል ካለ የእሳት ራት ነው የሚሆነው። ጦርነት ይመጣል ብዬ አንድ ቀንም ሰግቼ አላውቅም።
• ክላሽን አሸክመህ ከታንክና ከሚሳኤሎች ጋር የምታጋጥመው ሰው አይኖርም። እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ የሚገባ ወጣትም ያለም አይመስለኝም።
• የፌዴራል መንግስቱን አስተሳሰብ አውቃለሁ፣ የክልሎችንም አቅም አውቃለሁ፤ የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ውስጣዊ አቋም አውቃለሁ።
• ግብጾች የመጨረሻ ርብርብ ያደረጉት፣ መፈንቀለ መንግስት አድራጊው ወንጀለኛ ቡድን የተኮሰው የመጨረሻዋ ጥይት ሀጫሉን የገደለበትና ያን ተከትሎ የመጣውን ግጭት ነው
• ይህ ማለት ግን ትንኮሳ ያቆማሉ ማለት አይደለም። ነገር ግን ስጋቱ በግብጽ በኩልም በእኛ በኩልም ውሃ መያዝ ስለጀመርን እየቀነሰ ይሄዳል።
• የህዳሴው ግድብን ፈጥነን ስራችንን በጨረስን ቁጥር ስጋታችን ይቀንሳል። ከተጠናቀቀ በኋላ ግን ስጋቱ መቶ በመቶ ባይጠፋም ትርጉም ያለው አይሆንም። ግብጾችም ፋይናንስ አያደርጉትም።
• አሁን ያለውን የለውጥ አመራር ቤተ መንግስት ያስገባው ማንም ግለሰብ ወይም ቡድን ሳይሆን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው።
• ለውጡ ከመጣ በኋላ ፖለቲከኛ፣ ተንታኝ፣ ያልሆነ የለም። ያልተከፈተ የሚዲያ አይነት የለም።
• መንግስት ትግስት ማድረጉ ትክክል ቢሆንም የሚታገሰውና የማይታገሰውን ነገር መምረጥ አለበት። ወንጀልን በፍጹም መታገስ የለበትም። ወንጀል ከሆነ የወንጀል ትንሽ የለውም።
• የኔት ወርክ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ወንጀል የሚፈጸመው ተመሳሳይ ቡድን ነው።
• ምንጊዜም ቢሆን ለውጥ ካለ ጸረ ለውጥ አለ። ሀጫሉ ለውጡን ካመጡት፤ ለውጡ እንዲመጣ ካቀነቀኑት፣ከታገሉት ሰዎች የመጀመሪያው ረድፋ ላይ የሚሰለፍ ነው።
• ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካ ተቀባይነት እንዳያገኙ ብዙ ሴራዎች ተፈጽመዋል። ለውጡን ወደ ኋላ ለመመለስ የተደረጉ ጥረቶችን ለመገንዘብ ሶስቱን ሰኔዎችንና ሌሎች ክስተቶችን ወደ ኋላ ማየት ነው።
• በየአካባቢው ግጭት፣ የዜጎች መፈናቀል፣ ግድብ ተሸጠ፣ ሌላም ሌላም የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ተነዛ ፤
• ይህን ሁሉ ከሞከረ በኋላ ከተላላኪዎቹ ጋር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጦርነቱን አዲስ አበባ ጀምረን አዲስ አበባ እንጨርሳለን ብለው ወሰኑ።
• አዲስ አበባ ጀምረው አዲስ አበባ ለመጨረስ ትስስር ተፈጠረ።
• ኦሮሞና አማራን ማጋጨት በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ መቀልበስም፤ አሁን ያለውን የለውጥ መንግስትም ከስልጣን ማስወገድ ይቻላል የሚል መደምደሚያ ላይ ስለተደረሰ ለሀጫሉ በኦኤምኤን ቴሌቪዥን ቃለ ምልልስ ተዘጋጀለት።
• ለሀጫሉ የሚዘጋጅለት ጥያቄ የኦሮሞንና የአማራን ግንኙነት የሚበጥስና የሚያጋጭ እንዲሆን ታስቦ ነው።
• ሀጫሉ የተገደለው የአማራና የኦሮሞ ግጭት ለማምጣት ነው። የሴራ ዕቅድ የለውጡን አመራሮች በቀላሉና በሰከንድ አራት ኪሎ ቤተ መንግስት ገብተን እናስወጣለን በሚል ስሌት ነው።
• ሀጫሉ ስለ አጼ ምኒልክ ተናገረ ፤ በምኒልክ ጉዳይ ደግሞ አማራ ይነሳል። ሀጫሉን አማራ ነው የገደለው የሚል አስተሳሰብ በኦሮሞ ይፈጠራል። ኦሮሞ በአማራ ላይ ይነሳል።
• አጼ ምኒልክ የአንድ ኢትዮጵያን የመሩ መሆኑ ቀርቶ የአማራ ንጉስ ተደርገዋል። ልክ አሁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ መላው ኢትዮጵያን ህዝብ የሚያገለግሉ እንጂ ለኦሮሞ ብቻ የቆሙ አይደሉም።
• ሀጫሉ በኦነግ ሸኔ ዛቻ እየመጣበት እንዳለና ለምን ያ ዛቻ እንደሚመጣበትም በግልጸ የተናገረው ነገር ግን ተቆርጦ ሳይተላለፍ ቀርቷል።
• ሀጫሉ የተመረጠው ምክንያት በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ታዋቂና የትግል ምልክት ተደርጎ የሚቆጠር ስለሆነ ነው።
• የሚገርመው ሀጫሉን እነሱ ገለውት መልሰው ያዝኑለታል። ስለዚህ አሁንም ለውጥ አለ፤ ጸረ ለውጥም አለ።
• እነዚህ ቡድኖች አዲስ አበባ ጀምረን አዲስ አበባ እንጨርሳለን የሚለው መርሀ ግብርና ዕቅድ ሲቀርጹ በተለያየ ቦታ መዋቅር አላቸው። በየቦታው የሚያስተባብሩ ሰዎች አሏቸው።
• ለማስተባበር ደግሞ የግድ የዚያ አካባቢ ነዋሪ ሊሆንም፤ ላይሆንም ይችላል። የሚያስፈልገው ገንዘብ ብቻ ነው።
• የሀጫሉን ሞት ተከትሎ ሰዎች ሞተዋል። ዜጎች 30ና 40 ዓመታት የለፉበት ንብረት ወድሟል። ሻሸመኔና መስል ከተሞች እንዳልነበሩ ሆነዋል። ግን እነሱ እንደፈለጉት ኦሮሞና አማራ ተነስቶ አልተዋጋም። ሁሉም ህዝብ ለምን እንደተደረገ ገብቶታል።
• ወቅቱ የህዳሴው ግድብ ሙሌት የተጀመረበት ነው። የግብጽ መንግስት እነዚህን ቡድኖች ፋይናንስ ያደርጋል።
• ሁሌም በወንጀል ውስጥ የሚኖር የአገርን ጥቅም አሳልፎ ይሻጣል። ምክንያቱም እነዚህ የወንጀለኛ ቡድኖች ምንጊዜም ወደ ህግ ፊት የሚያቀርባቸውን ሀይል በማጥፋት ስልጣን ይዘው እንደፈለጉት ለመሆን በአገር ጥቅም ከመደራደር ወደ ኋላ የሚሉ አይደሉም።
• ግብጾችን ወክለው የሚዋጉ ተላላኪዎች ስላሏቸው ለእነሱ ፋይናንስ ማድረግ ብቻ ይጠበቅባቸዋል።
• የህዳሴው ግድብ የስጋት ምንጫችን ሆኖ የሚቀጥለው ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ ነው። ይህ ደግሞ በእኛ የመገደብ ፍጥነት ላይ ይወሰናል። ከዚያ በኋላ ነገሩ ይቀየራል።
• በትግራይ ክልል ምርጫ እናደርጋለን የሚለው ነገር ከጸጥታም ከህግም አኳያ በአግባቡ መታየት አለበት የሚል እምነት አለኝ።
ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ሐምሌ 30/2012 ዓ.ም ዕትም ጋር ከደደረጉት ቃለምልልስ የተወሰደ
• አንድ ክልል ከፌዴራል መንግስቱ ጋር በስምምነት ነው መስራት ያለበት። ህገ መንግስቱን በመጣስ ከህግ ውጭ የሚሄድ ከሆነ ደግሞ በህገ መንግስቱ ውስጥ መፍትሄ አለው።
• አንድ ክልል ተነስቶ የፌዴራል መንግስትን በጦርነት አፈሙዝ አሸንፌ የሆነ ነገር አደርጋለሁ የሚል ካለ የእሳት ራት ነው የሚሆነው። ጦርነት ይመጣል ብዬ አንድ ቀንም ሰግቼ አላውቅም።
• ክላሽን አሸክመህ ከታንክና ከሚሳኤሎች ጋር የምታጋጥመው ሰው አይኖርም። እንደዚህ አይነት ነገር ውስጥ የሚገባ ወጣትም ያለም አይመስለኝም።
• የፌዴራል መንግስቱን አስተሳሰብ አውቃለሁ፣ የክልሎችንም አቅም አውቃለሁ፤ የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ውስጣዊ አቋም አውቃለሁ።
• ግብጾች የመጨረሻ ርብርብ ያደረጉት፣ መፈንቀለ መንግስት አድራጊው ወንጀለኛ ቡድን የተኮሰው የመጨረሻዋ ጥይት ሀጫሉን የገደለበትና ያን ተከትሎ የመጣውን ግጭት ነው
• ይህ ማለት ግን ትንኮሳ ያቆማሉ ማለት አይደለም። ነገር ግን ስጋቱ በግብጽ በኩልም በእኛ በኩልም ውሃ መያዝ ስለጀመርን እየቀነሰ ይሄዳል።
• የህዳሴው ግድብን ፈጥነን ስራችንን በጨረስን ቁጥር ስጋታችን ይቀንሳል። ከተጠናቀቀ በኋላ ግን ስጋቱ መቶ በመቶ ባይጠፋም ትርጉም ያለው አይሆንም። ግብጾችም ፋይናንስ አያደርጉትም።
• አሁን ያለውን የለውጥ አመራር ቤተ መንግስት ያስገባው ማንም ግለሰብ ወይም ቡድን ሳይሆን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው።
• ለውጡ ከመጣ በኋላ ፖለቲከኛ፣ ተንታኝ፣ ያልሆነ የለም። ያልተከፈተ የሚዲያ አይነት የለም።
• መንግስት ትግስት ማድረጉ ትክክል ቢሆንም የሚታገሰውና የማይታገሰውን ነገር መምረጥ አለበት። ወንጀልን በፍጹም መታገስ የለበትም። ወንጀል ከሆነ የወንጀል ትንሽ የለውም።
• የኔት ወርክ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ወንጀል የሚፈጸመው ተመሳሳይ ቡድን ነው።
• ምንጊዜም ቢሆን ለውጥ ካለ ጸረ ለውጥ አለ። ሀጫሉ ለውጡን ካመጡት፤ ለውጡ እንዲመጣ ካቀነቀኑት፣ከታገሉት ሰዎች የመጀመሪያው ረድፋ ላይ የሚሰለፍ ነው።
• ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካ ተቀባይነት እንዳያገኙ ብዙ ሴራዎች ተፈጽመዋል። ለውጡን ወደ ኋላ ለመመለስ የተደረጉ ጥረቶችን ለመገንዘብ ሶስቱን ሰኔዎችንና ሌሎች ክስተቶችን ወደ ኋላ ማየት ነው።
• በየአካባቢው ግጭት፣ የዜጎች መፈናቀል፣ ግድብ ተሸጠ፣ ሌላም ሌላም የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ተነዛ ፤
• ይህን ሁሉ ከሞከረ በኋላ ከተላላኪዎቹ ጋር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጦርነቱን አዲስ አበባ ጀምረን አዲስ አበባ እንጨርሳለን ብለው ወሰኑ።
• አዲስ አበባ ጀምረው አዲስ አበባ ለመጨረስ ትስስር ተፈጠረ።
• ኦሮሞና አማራን ማጋጨት በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ መቀልበስም፤ አሁን ያለውን የለውጥ መንግስትም ከስልጣን ማስወገድ ይቻላል የሚል መደምደሚያ ላይ ስለተደረሰ ለሀጫሉ በኦኤምኤን ቴሌቪዥን ቃለ ምልልስ ተዘጋጀለት።
• ለሀጫሉ የሚዘጋጅለት ጥያቄ የኦሮሞንና የአማራን ግንኙነት የሚበጥስና የሚያጋጭ እንዲሆን ታስቦ ነው።
• ሀጫሉ የተገደለው የአማራና የኦሮሞ ግጭት ለማምጣት ነው። የሴራ ዕቅድ የለውጡን አመራሮች በቀላሉና በሰከንድ አራት ኪሎ ቤተ መንግስት ገብተን እናስወጣለን በሚል ስሌት ነው።
• ሀጫሉ ስለ አጼ ምኒልክ ተናገረ ፤ በምኒልክ ጉዳይ ደግሞ አማራ ይነሳል። ሀጫሉን አማራ ነው የገደለው የሚል አስተሳሰብ በኦሮሞ ይፈጠራል። ኦሮሞ በአማራ ላይ ይነሳል።
• አጼ ምኒልክ የአንድ ኢትዮጵያን የመሩ መሆኑ ቀርቶ የአማራ ንጉስ ተደርገዋል። ልክ አሁን ጠቅላይ ሚኒስትሩ መላው ኢትዮጵያን ህዝብ የሚያገለግሉ እንጂ ለኦሮሞ ብቻ የቆሙ አይደሉም።
• ሀጫሉ በኦነግ ሸኔ ዛቻ እየመጣበት እንዳለና ለምን ያ ዛቻ እንደሚመጣበትም በግልጸ የተናገረው ነገር ግን ተቆርጦ ሳይተላለፍ ቀርቷል።
• ሀጫሉ የተመረጠው ምክንያት በኦሮሞ ህዝብ ዘንድ ታዋቂና የትግል ምልክት ተደርጎ የሚቆጠር ስለሆነ ነው።
• የሚገርመው ሀጫሉን እነሱ ገለውት መልሰው ያዝኑለታል። ስለዚህ አሁንም ለውጥ አለ፤ ጸረ ለውጥም አለ።
• እነዚህ ቡድኖች አዲስ አበባ ጀምረን አዲስ አበባ እንጨርሳለን የሚለው መርሀ ግብርና ዕቅድ ሲቀርጹ በተለያየ ቦታ መዋቅር አላቸው። በየቦታው የሚያስተባብሩ ሰዎች አሏቸው።
• ለማስተባበር ደግሞ የግድ የዚያ አካባቢ ነዋሪ ሊሆንም፤ ላይሆንም ይችላል። የሚያስፈልገው ገንዘብ ብቻ ነው።
• የሀጫሉን ሞት ተከትሎ ሰዎች ሞተዋል። ዜጎች 30ና 40 ዓመታት የለፉበት ንብረት ወድሟል። ሻሸመኔና መስል ከተሞች እንዳልነበሩ ሆነዋል። ግን እነሱ እንደፈለጉት ኦሮሞና አማራ ተነስቶ አልተዋጋም። ሁሉም ህዝብ ለምን እንደተደረገ ገብቶታል።
• ወቅቱ የህዳሴው ግድብ ሙሌት የተጀመረበት ነው። የግብጽ መንግስት እነዚህን ቡድኖች ፋይናንስ ያደርጋል።
• ሁሌም በወንጀል ውስጥ የሚኖር የአገርን ጥቅም አሳልፎ ይሻጣል። ምክንያቱም እነዚህ የወንጀለኛ ቡድኖች ምንጊዜም ወደ ህግ ፊት የሚያቀርባቸውን ሀይል በማጥፋት ስልጣን ይዘው እንደፈለጉት ለመሆን በአገር ጥቅም ከመደራደር ወደ ኋላ የሚሉ አይደሉም።
• ግብጾችን ወክለው የሚዋጉ ተላላኪዎች ስላሏቸው ለእነሱ ፋይናንስ ማድረግ ብቻ ይጠበቅባቸዋል።
• የህዳሴው ግድብ የስጋት ምንጫችን ሆኖ የሚቀጥለው ግድቡ እስኪጠናቀቅ ድረስ ነው። ይህ ደግሞ በእኛ የመገደብ ፍጥነት ላይ ይወሰናል። ከዚያ በኋላ ነገሩ ይቀየራል።
• በትግራይ ክልል ምርጫ እናደርጋለን የሚለው ነገር ከጸጥታም ከህግም አኳያ በአግባቡ መታየት አለበት የሚል እምነት አለኝ።
ሌተናል ጄነራል ባጫ ደበሌ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ሐምሌ 30/2012 ዓ.ም ዕትም ጋር ከደደረጉት ቃለምልልስ የተወሰደ
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 1 ሺህ 86 ሰዎች የኮኖና ቫይረስ ሲገኝባቸው የ16 ሰዎች ሕይወት አለፈ።
ባለፉት 24 ሰዓታት በኢትዮጵያ በተደረገ 14 ሺህ 688 የላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 86 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአጠቃላይ በአገሪቱ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥርም 26 ሺህ 204 ደርሷል።
በሌላ በኩል ትናንት 394 ሰዎች በማገገማቸው በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 11 ሺህ 428 ሆኗል።
ባለፉት 24 ሰዓታት የ16 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ ይህም በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ቁጥር 479 አድርሶታል።
በአሁኑ ጊዜ 14 ሺህ 295 ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ሕክምና እየተከታተሉ ነው፤ 193 ሰዎች ደግሞ በጽኑ ሕክምና ላይ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካዛሬ ድረስ 550 ሺህ 119 የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል።
ባለፉት 24 ሰዓታት በኢትዮጵያ በተደረገ 14 ሺህ 688 የላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሺህ 86 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአጠቃላይ በአገሪቱ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥርም 26 ሺህ 204 ደርሷል።
በሌላ በኩል ትናንት 394 ሰዎች በማገገማቸው በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 11 ሺህ 428 ሆኗል።
ባለፉት 24 ሰዓታት የ16 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ ይህም በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ቁጥር 479 አድርሶታል።
በአሁኑ ጊዜ 14 ሺህ 295 ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ሕክምና እየተከታተሉ ነው፤ 193 ሰዎች ደግሞ በጽኑ ሕክምና ላይ ይገኛሉ።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካዛሬ ድረስ 550 ሺህ 119 የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል።
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 1,038 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው
------------------------------
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 17ሺህ 323 የላቦራቶሪ ምርመራ 1038 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 27 ሺህ 242 ደርሷል።
በትናንትናው ዕለት 232 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 11 ሺህ 660 ሆኗል።
ካለፉት 24 ሰዓታት ምርመራ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ በኮሮናቫይረስ የተነሣ የሟቾች ቁጥር 492 ደርሷል።
በአሁኑ ወቅት 195 ሰዎች በጽኑ ሕክምና ላይ ሲገኙ፣ 15 ሺህ 088 ደግሞ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች መሆናቸው ተገልጿል።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካዛሬ ድረስ 567 ሺህ 442 የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል።
------------------------------
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገው 17ሺህ 323 የላቦራቶሪ ምርመራ 1038 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 27 ሺህ 242 ደርሷል።
በትናንትናው ዕለት 232 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን፣ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 11 ሺህ 660 ሆኗል።
ካለፉት 24 ሰዓታት ምርመራ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ተከትሎ በኮሮናቫይረስ የተነሣ የሟቾች ቁጥር 492 ደርሷል።
በአሁኑ ወቅት 195 ሰዎች በጽኑ ሕክምና ላይ ሲገኙ፣ 15 ሺህ 088 ደግሞ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች መሆናቸው ተገልጿል።
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካዛሬ ድረስ 567 ሺህ 442 የላቦራቶሪ ምርመራ ተከናውኗል።
መቄዶኒያ የአረጋውያንና አዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ከሁለት ሺህ በላይ በጎዳና የወደቁ አረጋዊያንን አዕምሮ ህሙማን ለማንሳት ህብረተሰቡ ጥቆማ እንዲሰጠው ጥሪ አቀረበ።
ማዕከሉን ለመርዳት ቃል የገቡ ወገኖችም ቃላቸውን እንዲፈጽሙ ጠይቋል።
ማዕከሉ በአንድ ጊዜ ወር ውስጥ በጀመረው አረጋዊያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና እያነሳ መሆኑን ገልጿል።
የማዕከሉ ፕሮጀክት ኃላፊ አቶ ራጁ ዲንሳ ለኢዜአ እንዳሉት ማዕከሉ በአዲስ አበባና ሐረር ከተሞች ከሁለት ሺህ በላይ አረጋውያንና አዕምሮ ህሙማንን ከጎዳና ለማንሳት እየሰራ ነው።
በዚህም በአዲስ አበባ ከሁለት ሺህ በላይ አረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማንን ለማንሳት ማቀዱንና እስካሁን ከአንድ ሺህ በላይ ከጎዳና መነሳታቸውን ተናግረዋል።
በተመሳሳይ በሐረር ከተማ ለማንሳት ከታቀደው 110 አረጋውያንንና አዕምሮ ሕሙማን መካከል 60ዎቹን ማንሳቱን አስታውቀዋል።
በመሆኑም በከተሞቹ ዕድሚያቸው ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ አረጋዊያንንና ጎዳና ላይ የወደቁ ፣ ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን ጥቆማ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ጥቆማ ለመስጠት በ90-49-49-49-49 ወይንም በ90-70-70-70-70 ስልክ ቁጥሮች ደውሎ ማሳወቅ እንደሚቻል አቶ ራጁ አስረድተዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ማዕከሉን መጎብኘት ባለመቻሉ የሚደረገለት ድጋፍ ተቀዛቅዟል።
በወረርሽኙ ምክንያት መጋቢት 6 ቀን 2012 በሚሌኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ቃል የገቡ ግለሰቦችና ድርጅቶች ቃላቸውን እንዳልፈጸሙ ተናግረዋል።
በወቅቱ ቃል ከተገባው ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን እስካሁን የተሰበሰበው ከ15 ሚሊዮን ብር እንደማይበልጥ ነው የተናገሩት።
በመሆኑም በተሰጡት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ቃል የገቡበትን ገልጸው ሕጋዊ በሆነ ደረሰኝ ያሉበት ድረስ በመሄድ መቀበል እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
በማዕከሉ የአረጋዊያን ተጠሪ መምህር ሳሙኤል ከበደ በማዕከሉ የሚገኙ አረጋዊያን የሚጦሩት ድጋፍ በሚያደርጉ ወገኖች በመሆኑ ቃል የገቡ አካላት ቃላቸውን አክብረው ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
በኮቪድ-19 ምክንያት አረጋዊያንን መጎብኘት ባይቻልም፤ የማዕከሉ መግቢያ በር ላይ በሚገኘው ገንዘብ ቤት ድጋፍ ማድረግ እንደሚቻል ተገልጿል።
አልባሳትና ሌሎች ድጋፍ የሚፈልጉ ወገኖች በማዕከሉ ተገኝተው መለገስ ካልቻሉ፥ ያሉበት ድረስ በመሄድ መቀበል እንደሚቻልም ተጠቁሟል።
መቄዶኒያ የአረጋዊያንና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል ከሶስት ሺህ ለሚበልጡ አረጋዊያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና በማንሳት የምግብ፣ የሕክምና፣ መጠለያና ሌሎች አገልግሎት ይሰጣል።
በቀጣይ ሁለት ዓመታት ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖች ቁጥር 10 ሺህ ለማድረስ እየሰራ ነው።
ማዕከሉ በአዲስ አበባ አያት አካባቢ በ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ ዘመናዊ ሆስፒታልና ለአረጋዊያን መኖሪያ የሚውል ባለ 11 ወለል ህንጻ እያስገነባ መሆኑም ታውቋል። ምንጭ...ኢዜአ
ማዕከሉን ለመርዳት ቃል የገቡ ወገኖችም ቃላቸውን እንዲፈጽሙ ጠይቋል።
ማዕከሉ በአንድ ጊዜ ወር ውስጥ በጀመረው አረጋዊያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና እያነሳ መሆኑን ገልጿል።
የማዕከሉ ፕሮጀክት ኃላፊ አቶ ራጁ ዲንሳ ለኢዜአ እንዳሉት ማዕከሉ በአዲስ አበባና ሐረር ከተሞች ከሁለት ሺህ በላይ አረጋውያንና አዕምሮ ህሙማንን ከጎዳና ለማንሳት እየሰራ ነው።
በዚህም በአዲስ አበባ ከሁለት ሺህ በላይ አረጋዊያንና የአእምሮ ህሙማንን ለማንሳት ማቀዱንና እስካሁን ከአንድ ሺህ በላይ ከጎዳና መነሳታቸውን ተናግረዋል።
በተመሳሳይ በሐረር ከተማ ለማንሳት ከታቀደው 110 አረጋውያንንና አዕምሮ ሕሙማን መካከል 60ዎቹን ማንሳቱን አስታውቀዋል።
በመሆኑም በከተሞቹ ዕድሚያቸው ከ60 ዓመት በላይ የሆኑ አረጋዊያንንና ጎዳና ላይ የወደቁ ፣ ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን ጥቆማ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
ጥቆማ ለመስጠት በ90-49-49-49-49 ወይንም በ90-70-70-70-70 ስልክ ቁጥሮች ደውሎ ማሳወቅ እንደሚቻል አቶ ራጁ አስረድተዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ማዕከሉን መጎብኘት ባለመቻሉ የሚደረገለት ድጋፍ ተቀዛቅዟል።
በወረርሽኙ ምክንያት መጋቢት 6 ቀን 2012 በሚሌኒየም አዳራሽ በተዘጋጀው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ቃል የገቡ ግለሰቦችና ድርጅቶች ቃላቸውን እንዳልፈጸሙ ተናግረዋል።
በወቅቱ ቃል ከተገባው ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን እስካሁን የተሰበሰበው ከ15 ሚሊዮን ብር እንደማይበልጥ ነው የተናገሩት።
በመሆኑም በተሰጡት የስልክ ቁጥሮች በመደወል ቃል የገቡበትን ገልጸው ሕጋዊ በሆነ ደረሰኝ ያሉበት ድረስ በመሄድ መቀበል እንደሚችሉ ጠቁመዋል።
በማዕከሉ የአረጋዊያን ተጠሪ መምህር ሳሙኤል ከበደ በማዕከሉ የሚገኙ አረጋዊያን የሚጦሩት ድጋፍ በሚያደርጉ ወገኖች በመሆኑ ቃል የገቡ አካላት ቃላቸውን አክብረው ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።
በኮቪድ-19 ምክንያት አረጋዊያንን መጎብኘት ባይቻልም፤ የማዕከሉ መግቢያ በር ላይ በሚገኘው ገንዘብ ቤት ድጋፍ ማድረግ እንደሚቻል ተገልጿል።
አልባሳትና ሌሎች ድጋፍ የሚፈልጉ ወገኖች በማዕከሉ ተገኝተው መለገስ ካልቻሉ፥ ያሉበት ድረስ በመሄድ መቀበል እንደሚቻልም ተጠቁሟል።
መቄዶኒያ የአረጋዊያንና አዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል ከሶስት ሺህ ለሚበልጡ አረጋዊያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከጎዳና በማንሳት የምግብ፣ የሕክምና፣ መጠለያና ሌሎች አገልግሎት ይሰጣል።
በቀጣይ ሁለት ዓመታት ድጋፍ የሚደረግላቸውን ወገኖች ቁጥር 10 ሺህ ለማድረስ እየሰራ ነው።
ማዕከሉ በአዲስ አበባ አያት አካባቢ በ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ ዘመናዊ ሆስፒታልና ለአረጋዊያን መኖሪያ የሚውል ባለ 11 ወለል ህንጻ እያስገነባ መሆኑም ታውቋል። ምንጭ...ኢዜአ
“የትግራይ ህዝብ በታሪኩ የተዋረደበት፣ ባህሉ የጠፋበት፣ ቤተእምነቱ የተደፈረበት ያለፉት 27 ዓመታት ናቸው” አቶ ሊላይ ኃይለማርያም የህወሓት ነባር ታጋይ
*********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ የትግራይ ህዝብ በታሪኩ የተዋረደበት፣ ባህሉ የጠፋበት፣ ቤተ ክርስቲያኑ እና መስጂዱ የተደፈረበት ጊዜ ቢኖር ያለፉት 27 ዓመታት መሆናቸውን የህወሓት ነባር ታጋይ አቶ ሊላይ ኃይለማርያም አመለከቱ። ህወሓትን እየመሩ ያሉ አመራሮች ምን ያህል የወደቁ መሆናቸውን የሚያሳየው ተሳዳቢ ቡድን በማህበራዊ ሚዲያው ውስጥ ማደራጀታቸው እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት ፣ በትግራይ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ሰቆቃ ተነግሮም፣ ተሰምቶም የማይታወቅ ነው። በትግራይ ታሪክም እንዲህ አይነት ክፉ ጊዜ አጋጥሞ አያውቅም። የትግራይ ህዝብ የተዋረደበት፣ ባህሉ የጠፋበት፣ ቤተ ክርስቲያኑ እና መስጂዱ የተደፈረበት ጊዜ ቢኖር ያለፈው 27 ዓመታት ናቸው።
“የትግራይ ህዝብ ከ1967 ትግል ከመውጣቱ በፊት ነጭ ጋቢ ይለብስ ነበር። አሁን ጆንያ ለብሶ ነው የሚያድረው። ቀድሞ ነጭ ማር፣ ነጭ ወተት፣ ነጭ አምባሻ ይመገብ ነበር። አሁን ግን በእርዳታ ስንዴ ነው የሚኖረው። የትግራይ ህዝብ አሁን ምኒሊክና ኃይለስላሴን ቀርቶ ደርግን ረስቷል። እነዛ ሥርዓቶች ካደረሱበት በላይ ፍጹም ድህነትና ፍጹም ባርነት ውስጥ ነው ያለው” ብለዋል፡፡
በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በትግራይ ታሪክ የተሰደዱበት፣ ሰው የታሰረበት፣ የተገደለበት ዘመን ቢኖር ያለፉት 27 ዓመታት ናቸው ያሉት አቶ ሊላይ፤ የህውሃት ሰዎች እንደ ገቡ አስር ትልልቅ እስር ቤቶች እና ሰባት የዜሮ ስድስት የድብቅ እስር ቤት እንደሰሩም አመልክተዋል።
የሰማዕታት እናቶች በረሃብ የሞቱበት፣ ህዝቡ በፍጹም ድህነት እንዲኖር የተፈረደበት ዘመን እንደነበረም አመልክተዋል። በዚህ ዘመን የትግራይ ህዝብ በልመና ኑሮውን እንዲገፋ፣ እንዳይሰራና ከ50 በመቶ በላይ ሴፍቲኔት ጠባቂ እንዲሆንም መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
ህውሀት ይህን ሁሉ የሚያደርገው ‹‹ወደ ስልጣን ያመጣው የትግራይ ህዝብ እንደሆነ ሁሉ ከስልጣን የሚያወረደውም የትግራይ ህዝብ እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው›› ያሉት ነባር ታጋዩ፤ ህዝቡ ካመጸ የሚሰጠውን ድጋፍ በማቋረጥ ዝም ለማስባል የተደረገ ሴራ እንደሆነም ጠቁመዋል። ስልጣናቸውን ለማቆየት ሲሉ ትግራይን ወደ ፍጹም ድህነት አስገብተውታል ብለዋል።
እንደርሳቸው ማብራሪያ፤ በትግራይ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ሰቆቃ ተነግሮም፣ ተሰምቶም የማይታወቅ ነው። በትግራይ ታሪክም እንዲህ አይነት ክፉ ጊዜ አጋጥሞን አያውቅም። አሁን እኮ ስለ ደርግ፣ ኃይለስላሴ እና ምኒልክ የሚያወራ የለም። ምክንያቱም እነዚህ ሶስቱ ያጠፉት ተጨምቆ የስብሃት ነጋ ኔትዎርክ የሚሰራውን በደል አንድ መቶኛ ቢሆን ነው።
አሁን በትግራይ ያለው ፍጹም ባርነት ነው። ስራ ለመቀጠርና የትምህርት እድል ለማግኘት እንኳን የእነርሱ ኔትወርክ መሆን ወይም ንግስተ ሳባ ትምህርት ቤት መማር ዋና መመዘኛ ሆኖ እንደሚቀርብ አቶ ሊላይ አመልክተዋል፡፡
“ወያኔ የጀግኖች ስም እንጂ የተሳዳቢዎች ስም አይደለም። በጣም የሚያሳዝነው በአሁኑ ሰዓት ህወሓትን እየመሩ ያሉ አመራሮች ምን ያህል የወደቁ መሆናቸውን የሚያሳየው ተሳዳቢ ቡድን በማህበራዊ ሚዲያው ውስጥ ማደራጀታቸው ነው ብለዋል። ይህ ደግሞ ከትግራይ ህዝብ ማህበራዊ ሥነ ልቡና እና ከትግራይ ባህል ውጪ ነው። ለምሳሌ፣ አሁን አንተ ከእኔ ጋር አውርተህ የምትጽፈውን ስታይ አንድ ሚሊዮን ተሳዳቢ ይወጣል። እናም በጣም የሚያሳዝነው መሪዎቹ ሚዲያ ላይ ወጥተው ላደረጋችሁት ተጋድሎ እናመሰግናለን ሲሉ ነው የምትሰማው” ብለዋል፡፡
ይሄ የሚያሳየው አመራሩ ብቃት እንደሌለው ነው።
የምትሳደበው ጉልበትና ሃሳብ ስታጣ ነው። ትግራይ ውስጥ ስድብ ጸያፍም ነውርም ነው። አይደለም መሳደብ ጮኾ መናገር ነውር ነው። ይህም እነዚህ ሃይሎች ከትግራይ ህዝብ ሥነልቡና ውጪ መሆናቸውን አመላካች እንደሆነም አስታውቀዋል።
“ለህወሓቶች ይሄን አይነት ማደናገሪያ ባህላቸው እንደሆነ ጠቁመው ፣ ባለፉት 27 ዓመታት በክልሉ ውስጥ ልማት አልተሰራም። ለምን ብትላቸው ሻዕቢያ መጥቶ ያፈርሰዋል ይሉሀል። ይህ ደግሞ ህዝቡ ደህንነት እንዳይሰማው ለማድረግ ነው። በዚህ መልኩ የትግራይን ህዝብ እየፈሩ ግን ሳያስቡት ቄሮ አባረራቸው። ምንም እንኳን ትግራይ ድረስ ሄደው ነጻ ባያወጡንም ዱላ ይዞ ታግሎ ላባረራቸው ለቄሮ የወጣት ንቅናቄ ትልቅ ክብር አለኝ። እናም ህወሓት አሁን ያለው የመጨረሻ አማራጭ ያለበትን ቦታ ላለማጣት እንደለመደው ህዝቡን የደህንነት ስጋት እንዳለበት አድርጎ ለማሳመን መስራት ነው” ብለዋል፡፡
ሰሞኑን ወታደራዊ ሰልፍ ሲያሳዩ ነበር። የሚገርመው አር.ቢጂ ክላሽ እናቶችን አሸክመው ነበር። እነዚህ ሰዎች በዚህ መልኩ ጦር በሰልፍ ለማሳየት መጣራቸው ምን ያህል ወደ ኋላ የቀሩና አንድ ቦታ ተተክለው የቀሩ መሆናቸውን የሚያመላክት ነው። አር.ቢጂ ክላሽ ይዘህ የምታሸንፈው ጦርነት አሁን ዓለም ላይ አለመኖሩን እንኳን አልተገነዘቡትም። ይህ ይቅር፣ ለመሆኑ ያንን ጦርነት ከማን ጋር ነው የሚያደርጉት? ሲሉም ጠይቀዋል።
ማዕከላዊ መንግስት ይሄን እንዲያደርጉ የሚደግፋቸው ነው የሚመስለው። ምክንያቱም እነዚህ አካላት ይሄ ሁሉ ጥፋት እንዲጠፋ በአሁኑ ሰዓት የኤርትራን ተቃዋሚ ትግራይ ውስጥ እያሰለጠኑ ነው። አማራን ለመውጋት ቅማንትን እያሰለጠኑ ነው። አርዱፍ አፋርን ለመውጋት እያሰለጠኑ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ በጀት እየጨመረ እየሰጠ ነው። ማዕከላዊ መንግስቱ ከሰባት ቢሊዮን አስር ቢሊዮን ጨምሬላችኋለሁ ይላል። በዚህ ደግሞ ማዕከላዊ መንግስት ወደፊት በታሪክ ተጠያቂ ሊሆን እንደሚችል አሳስበዋል ፡፡
አሁንም ሌላ 200 ሺህ ጦር እንዲያሰለጥኑ ባጀቱን ከሰባት ቢሊዮን ወደ አስር ቢሊዮን አሳድጌያለሁ ብሎ ይነግረናል። ከአዲስ አበባ ሸሽተው የሄዱት ግን በዓመት ውስጥ እኮ ሶስት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ነው ለሆቴልና ለሌላም ወጪ የወጣላቸው። ከግማሽ ሚሊዮን ወጣት ግን እዛ ስራ የለውም። ከዚህ ባለፈ ከኤርትራ ጋር የመጣውን ሰላም በቀላል ማየት የለብንም። ያንን ሰላም እኮ ከየትኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ በላይ የትግራይ ህዝብ አብዝቶ የሚፈልገውና አብዝቶ ሲናፍቀው የነበረ ነው።
ከሰላሙ በአንደኝነት የሚጠቀመው የትግራይ ህዝብ ነው። ሆኖም ያ ሰላም ከተፈጠረ እነዚህ ህወሓቶች መኖር ስለማይችሉ፤ አሁን ላይ ስትራቴጂያቸው ሻቢያ ወረረህ፣ አማራ ሊወርህ ነው፣ ዐብይ ሊወርህ ነው የሚል እንደሆነም አመልክተዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 9/2012
*********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ የትግራይ ህዝብ በታሪኩ የተዋረደበት፣ ባህሉ የጠፋበት፣ ቤተ ክርስቲያኑ እና መስጂዱ የተደፈረበት ጊዜ ቢኖር ያለፉት 27 ዓመታት መሆናቸውን የህወሓት ነባር ታጋይ አቶ ሊላይ ኃይለማርያም አመለከቱ። ህወሓትን እየመሩ ያሉ አመራሮች ምን ያህል የወደቁ መሆናቸውን የሚያሳየው ተሳዳቢ ቡድን በማህበራዊ ሚዲያው ውስጥ ማደራጀታቸው እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡
አቶ ሊላይ ኃይለማርያም ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳመለከቱት ፣ በትግራይ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ሰቆቃ ተነግሮም፣ ተሰምቶም የማይታወቅ ነው። በትግራይ ታሪክም እንዲህ አይነት ክፉ ጊዜ አጋጥሞ አያውቅም። የትግራይ ህዝብ የተዋረደበት፣ ባህሉ የጠፋበት፣ ቤተ ክርስቲያኑ እና መስጂዱ የተደፈረበት ጊዜ ቢኖር ያለፈው 27 ዓመታት ናቸው።
“የትግራይ ህዝብ ከ1967 ትግል ከመውጣቱ በፊት ነጭ ጋቢ ይለብስ ነበር። አሁን ጆንያ ለብሶ ነው የሚያድረው። ቀድሞ ነጭ ማር፣ ነጭ ወተት፣ ነጭ አምባሻ ይመገብ ነበር። አሁን ግን በእርዳታ ስንዴ ነው የሚኖረው። የትግራይ ህዝብ አሁን ምኒሊክና ኃይለስላሴን ቀርቶ ደርግን ረስቷል። እነዛ ሥርዓቶች ካደረሱበት በላይ ፍጹም ድህነትና ፍጹም ባርነት ውስጥ ነው ያለው” ብለዋል፡፡
በሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በትግራይ ታሪክ የተሰደዱበት፣ ሰው የታሰረበት፣ የተገደለበት ዘመን ቢኖር ያለፉት 27 ዓመታት ናቸው ያሉት አቶ ሊላይ፤ የህውሃት ሰዎች እንደ ገቡ አስር ትልልቅ እስር ቤቶች እና ሰባት የዜሮ ስድስት የድብቅ እስር ቤት እንደሰሩም አመልክተዋል።
የሰማዕታት እናቶች በረሃብ የሞቱበት፣ ህዝቡ በፍጹም ድህነት እንዲኖር የተፈረደበት ዘመን እንደነበረም አመልክተዋል። በዚህ ዘመን የትግራይ ህዝብ በልመና ኑሮውን እንዲገፋ፣ እንዳይሰራና ከ50 በመቶ በላይ ሴፍቲኔት ጠባቂ እንዲሆንም መደረጉን አስታውቀዋል፡፡
ህውሀት ይህን ሁሉ የሚያደርገው ‹‹ወደ ስልጣን ያመጣው የትግራይ ህዝብ እንደሆነ ሁሉ ከስልጣን የሚያወረደውም የትግራይ ህዝብ እንደሆነ ስለሚያውቅ ነው›› ያሉት ነባር ታጋዩ፤ ህዝቡ ካመጸ የሚሰጠውን ድጋፍ በማቋረጥ ዝም ለማስባል የተደረገ ሴራ እንደሆነም ጠቁመዋል። ስልጣናቸውን ለማቆየት ሲሉ ትግራይን ወደ ፍጹም ድህነት አስገብተውታል ብለዋል።
እንደርሳቸው ማብራሪያ፤ በትግራይ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለው ሰቆቃ ተነግሮም፣ ተሰምቶም የማይታወቅ ነው። በትግራይ ታሪክም እንዲህ አይነት ክፉ ጊዜ አጋጥሞን አያውቅም። አሁን እኮ ስለ ደርግ፣ ኃይለስላሴ እና ምኒልክ የሚያወራ የለም። ምክንያቱም እነዚህ ሶስቱ ያጠፉት ተጨምቆ የስብሃት ነጋ ኔትዎርክ የሚሰራውን በደል አንድ መቶኛ ቢሆን ነው።
አሁን በትግራይ ያለው ፍጹም ባርነት ነው። ስራ ለመቀጠርና የትምህርት እድል ለማግኘት እንኳን የእነርሱ ኔትወርክ መሆን ወይም ንግስተ ሳባ ትምህርት ቤት መማር ዋና መመዘኛ ሆኖ እንደሚቀርብ አቶ ሊላይ አመልክተዋል፡፡
“ወያኔ የጀግኖች ስም እንጂ የተሳዳቢዎች ስም አይደለም። በጣም የሚያሳዝነው በአሁኑ ሰዓት ህወሓትን እየመሩ ያሉ አመራሮች ምን ያህል የወደቁ መሆናቸውን የሚያሳየው ተሳዳቢ ቡድን በማህበራዊ ሚዲያው ውስጥ ማደራጀታቸው ነው ብለዋል። ይህ ደግሞ ከትግራይ ህዝብ ማህበራዊ ሥነ ልቡና እና ከትግራይ ባህል ውጪ ነው። ለምሳሌ፣ አሁን አንተ ከእኔ ጋር አውርተህ የምትጽፈውን ስታይ አንድ ሚሊዮን ተሳዳቢ ይወጣል። እናም በጣም የሚያሳዝነው መሪዎቹ ሚዲያ ላይ ወጥተው ላደረጋችሁት ተጋድሎ እናመሰግናለን ሲሉ ነው የምትሰማው” ብለዋል፡፡
ይሄ የሚያሳየው አመራሩ ብቃት እንደሌለው ነው።
የምትሳደበው ጉልበትና ሃሳብ ስታጣ ነው። ትግራይ ውስጥ ስድብ ጸያፍም ነውርም ነው። አይደለም መሳደብ ጮኾ መናገር ነውር ነው። ይህም እነዚህ ሃይሎች ከትግራይ ህዝብ ሥነልቡና ውጪ መሆናቸውን አመላካች እንደሆነም አስታውቀዋል።
“ለህወሓቶች ይሄን አይነት ማደናገሪያ ባህላቸው እንደሆነ ጠቁመው ፣ ባለፉት 27 ዓመታት በክልሉ ውስጥ ልማት አልተሰራም። ለምን ብትላቸው ሻዕቢያ መጥቶ ያፈርሰዋል ይሉሀል። ይህ ደግሞ ህዝቡ ደህንነት እንዳይሰማው ለማድረግ ነው። በዚህ መልኩ የትግራይን ህዝብ እየፈሩ ግን ሳያስቡት ቄሮ አባረራቸው። ምንም እንኳን ትግራይ ድረስ ሄደው ነጻ ባያወጡንም ዱላ ይዞ ታግሎ ላባረራቸው ለቄሮ የወጣት ንቅናቄ ትልቅ ክብር አለኝ። እናም ህወሓት አሁን ያለው የመጨረሻ አማራጭ ያለበትን ቦታ ላለማጣት እንደለመደው ህዝቡን የደህንነት ስጋት እንዳለበት አድርጎ ለማሳመን መስራት ነው” ብለዋል፡፡
ሰሞኑን ወታደራዊ ሰልፍ ሲያሳዩ ነበር። የሚገርመው አር.ቢጂ ክላሽ እናቶችን አሸክመው ነበር። እነዚህ ሰዎች በዚህ መልኩ ጦር በሰልፍ ለማሳየት መጣራቸው ምን ያህል ወደ ኋላ የቀሩና አንድ ቦታ ተተክለው የቀሩ መሆናቸውን የሚያመላክት ነው። አር.ቢጂ ክላሽ ይዘህ የምታሸንፈው ጦርነት አሁን ዓለም ላይ አለመኖሩን እንኳን አልተገነዘቡትም። ይህ ይቅር፣ ለመሆኑ ያንን ጦርነት ከማን ጋር ነው የሚያደርጉት? ሲሉም ጠይቀዋል።
ማዕከላዊ መንግስት ይሄን እንዲያደርጉ የሚደግፋቸው ነው የሚመስለው። ምክንያቱም እነዚህ አካላት ይሄ ሁሉ ጥፋት እንዲጠፋ በአሁኑ ሰዓት የኤርትራን ተቃዋሚ ትግራይ ውስጥ እያሰለጠኑ ነው። አማራን ለመውጋት ቅማንትን እያሰለጠኑ ነው። አርዱፍ አፋርን ለመውጋት እያሰለጠኑ ነው። የኢትዮጵያ መንግስት ደግሞ በጀት እየጨመረ እየሰጠ ነው። ማዕከላዊ መንግስቱ ከሰባት ቢሊዮን አስር ቢሊዮን ጨምሬላችኋለሁ ይላል። በዚህ ደግሞ ማዕከላዊ መንግስት ወደፊት በታሪክ ተጠያቂ ሊሆን እንደሚችል አሳስበዋል ፡፡
አሁንም ሌላ 200 ሺህ ጦር እንዲያሰለጥኑ ባጀቱን ከሰባት ቢሊዮን ወደ አስር ቢሊዮን አሳድጌያለሁ ብሎ ይነግረናል። ከአዲስ አበባ ሸሽተው የሄዱት ግን በዓመት ውስጥ እኮ ሶስት መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ነው ለሆቴልና ለሌላም ወጪ የወጣላቸው። ከግማሽ ሚሊዮን ወጣት ግን እዛ ስራ የለውም። ከዚህ ባለፈ ከኤርትራ ጋር የመጣውን ሰላም በቀላል ማየት የለብንም። ያንን ሰላም እኮ ከየትኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ በላይ የትግራይ ህዝብ አብዝቶ የሚፈልገውና አብዝቶ ሲናፍቀው የነበረ ነው።
ከሰላሙ በአንደኝነት የሚጠቀመው የትግራይ ህዝብ ነው። ሆኖም ያ ሰላም ከተፈጠረ እነዚህ ህወሓቶች መኖር ስለማይችሉ፤ አሁን ላይ ስትራቴጂያቸው ሻቢያ ወረረህ፣ አማራ ሊወርህ ነው፣ ዐብይ ሊወርህ ነው የሚል እንደሆነም አመልክተዋል።
አዲስ ዘመን ነሀሴ 9/2012
በአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ተመሥገን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ ሰመራ ገባ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ተመሥገን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ በጎርፍ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ለመድረግ ዛሬ ጠዋት ሰመራ-አፋር ገብቷል፡፡
የልዑኩ አባላት ሰመራ-ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፍሬ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር አወል አርባን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
በጉዞው የገቢዎች ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌውን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸውን አመብድ ዘግቧል፡፡
በርዕሰ መሥተዳድር ተመስገን ጥሩነህ የተመራው ልዑክ ትናንት በኦሮሚያ ክልል ጉዳት ለደረሳባቸው ዜጎች ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
**********************
(ኢ ፕ ድ)
በአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ተመሥገን ጥሩነህ የተመራ ልዑክ በጎርፍ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ለመድረግ ዛሬ ጠዋት ሰመራ-አፋር ገብቷል፡፡
የልዑኩ አባላት ሰመራ-ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፍሬ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር አወል አርባን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡
በጉዞው የገቢዎች ሚኒስትሩ አቶ ላቀ አያሌውን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መገኘታቸውን አመብድ ዘግቧል፡፡
በርዕሰ መሥተዳድር ተመስገን ጥሩነህ የተመራው ልዑክ ትናንት በኦሮሚያ ክልል ጉዳት ለደረሳባቸው ዜጎች ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
ዘንድሮ በአዲስ አበባና ዙሪያዋ 520 የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ደርሰዋል
. በአደጋው የ 105 ሰዎች ህይወት አልፏል
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- እየተጠናቀቀ ባለው የ2012 ዓመት በአዲስ አበባ ከተማና በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች 520 የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መድረሳቸውንና የ 105 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ አስተዳደር የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ .አቶ ጉልላት ጌታነህ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፣ በዘንድሮው ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያና ኦሮሚያ ልዩ ዞኖች 520 የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ደርሰዋል፡፡
በዓመቱ በደረሱት የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች የ105 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን 132 የሚሆኑ ሰዎችም የመቁሰል ጉዳት አጋጥሟቸዋል። ከደረሱት 520 አደጋዎች ውስጥ 335 የእሳትና 185 የድንገተኛ አደጋዎች
ሲሆኑ 479ኙ በአዲስ አበባና 41 ያህሉ በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች የተመዘገቡ ናቸው ።
በአደጋዎቹ የደረሰው የንብረት ውድመት በገንዘብ ሲተመን 342 ሚሊዮን 236 ሺ 660 ብር መሆኑን የተናገሩት ባለሙያው በተመሳሳይ ሁኔታ በተደረገው ከፍተኛ የመከላከል ጥረት ከ7 ቢሊዮን 796 ሚሊዮን 284 ሺ 500 ብር በላይ የሚገመት ንብረትን ለመታደግ እንደተቻለ ተናግረዋል።
በተለያዩ ጊዜያት የደረሱ አደጋዎችን ለመቆጣጠር 150 የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና 440 አምቡላንሶች ከ 6 ሺ 635 የአደጋ መከላከል ሠራተኞች ጋር መሰማራታቸውን አክለው ገልጸዋል፡፡
በዚህ ዓመት 335 የእሳት አደጋዎች የደረሱ ሲሆን በቃጠሎው ያጋጠመው ጉዳትም ከሌሎች አደጋዎች ይበልጥ ከፍተኛው ቁጥር እንደተመዘገበበት ተናግረዋል፡፡በተመሳሳይ ሁኔታ 180 ድንገተኛ አደጋዎች መድረሳቸውን የጠቀሱት ባለሙያው በነዚህ አደጋዎችም ጉድጓድ ውስጥ መግባት፣ራስን ከፎቅ ላይ መወርወር ፣ታንቆ መሞትና መሰል ክስተቶች እንደሚያጋጥሙ ተናግረዋል ፡፡
ባለፈው ዓመት በእሳት ቃጠሎ የደረሱ አደጋዎች ቁጥር 397 እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጉልላት የዘንድሮው ዓመት ከአምናው ተመሳሳይ ሁኔታ ጋር ሲነጻጸር በ62 መቀነሱን ተናግረዋል ፡፡
እንደ ባለሙያው ገለጻ በ2011 ዓ.ም በድንገተኛ አደጋዎች የተመዘገበው ቁጥር 177 የነበረ ሲሆን ዘንድሮ ባለው ተመሳሳይ ሁኔታ ደግሞ ቁጥሩ በስምንት ጨምሮ 185 ሆኖ ተመዝግቧል። ዘንድሮ በተጠቀሱት አካባቢዎች የደረሱ የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥር ከአምናው ተመሳሳይ ሁኔታ ጋር ሲነጻጸርም በ54 ቅናሽ ማሳየቱን ተናግረዋል፡፡
በዘንድሮው ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖረውን የክረምት ተጽዕኖ ለመቀነስ አስቀድሞ ዝግጅት መደረጉን የጠቀሱት አቶ ጉልላት በከተማዋ ያሉ 261 የጎርፍ ተጋላጭ ቦታዎችን በመለየት በተሰጠው ህብረተሰብ አቀፍ ግንዛቤ ውጤታማ ሥራ መመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡
በኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በየጊዜው የሚሰጠው አደጋን የመቀነስ ጥንቃቄ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር አስተዋጽኦ አድርጓል ያሉት ባለሙያው ዘንድሮም ይህ ጥረት መቀጠሉ ችግሩን ለመቀነስ ድርሻ ነበረው ብለዋል።
ህብረተሰቡ ራሱንና ንብረቱን ለአደጋ ከሚያጋልጡ አደጋዎች ሊጠበቅ ይገባል ያሉት አቶ ጉልላት ከኮሚሽኑ በየጊዜው የሚሰጠውን ምክርና ማሳሰቢያን በመተግበርም ጥንቃቄን ባህል ማድረግ ግድ ይላል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አዲስ ዘመን ነሀሴ 9/2012
. በአደጋው የ 105 ሰዎች ህይወት አልፏል
******************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- እየተጠናቀቀ ባለው የ2012 ዓመት በአዲስ አበባ ከተማና በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች 520 የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መድረሳቸውንና የ 105 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ አስተዳደር የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ .አቶ ጉልላት ጌታነህ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፣ በዘንድሮው ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ ዙሪያና ኦሮሚያ ልዩ ዞኖች 520 የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ደርሰዋል፡፡
በዓመቱ በደረሱት የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች የ105 ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን 132 የሚሆኑ ሰዎችም የመቁሰል ጉዳት አጋጥሟቸዋል። ከደረሱት 520 አደጋዎች ውስጥ 335 የእሳትና 185 የድንገተኛ አደጋዎች
ሲሆኑ 479ኙ በአዲስ አበባና 41 ያህሉ በኦሮሚያ ልዩ ዞኖች የተመዘገቡ ናቸው ።
በአደጋዎቹ የደረሰው የንብረት ውድመት በገንዘብ ሲተመን 342 ሚሊዮን 236 ሺ 660 ብር መሆኑን የተናገሩት ባለሙያው በተመሳሳይ ሁኔታ በተደረገው ከፍተኛ የመከላከል ጥረት ከ7 ቢሊዮን 796 ሚሊዮን 284 ሺ 500 ብር በላይ የሚገመት ንብረትን ለመታደግ እንደተቻለ ተናግረዋል።
በተለያዩ ጊዜያት የደረሱ አደጋዎችን ለመቆጣጠር 150 የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና 440 አምቡላንሶች ከ 6 ሺ 635 የአደጋ መከላከል ሠራተኞች ጋር መሰማራታቸውን አክለው ገልጸዋል፡፡
በዚህ ዓመት 335 የእሳት አደጋዎች የደረሱ ሲሆን በቃጠሎው ያጋጠመው ጉዳትም ከሌሎች አደጋዎች ይበልጥ ከፍተኛው ቁጥር እንደተመዘገበበት ተናግረዋል፡፡በተመሳሳይ ሁኔታ 180 ድንገተኛ አደጋዎች መድረሳቸውን የጠቀሱት ባለሙያው በነዚህ አደጋዎችም ጉድጓድ ውስጥ መግባት፣ራስን ከፎቅ ላይ መወርወር ፣ታንቆ መሞትና መሰል ክስተቶች እንደሚያጋጥሙ ተናግረዋል ፡፡
ባለፈው ዓመት በእሳት ቃጠሎ የደረሱ አደጋዎች ቁጥር 397 እንደነበር ያስታወሱት አቶ ጉልላት የዘንድሮው ዓመት ከአምናው ተመሳሳይ ሁኔታ ጋር ሲነጻጸር በ62 መቀነሱን ተናግረዋል ፡፡
እንደ ባለሙያው ገለጻ በ2011 ዓ.ም በድንገተኛ አደጋዎች የተመዘገበው ቁጥር 177 የነበረ ሲሆን ዘንድሮ ባለው ተመሳሳይ ሁኔታ ደግሞ ቁጥሩ በስምንት ጨምሮ 185 ሆኖ ተመዝግቧል። ዘንድሮ በተጠቀሱት አካባቢዎች የደረሱ የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥር ከአምናው ተመሳሳይ ሁኔታ ጋር ሲነጻጸርም በ54 ቅናሽ ማሳየቱን ተናግረዋል፡፡
በዘንድሮው ዓመት በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖረውን የክረምት ተጽዕኖ ለመቀነስ አስቀድሞ ዝግጅት መደረጉን የጠቀሱት አቶ ጉልላት በከተማዋ ያሉ 261 የጎርፍ ተጋላጭ ቦታዎችን በመለየት በተሰጠው ህብረተሰብ አቀፍ ግንዛቤ ውጤታማ ሥራ መመዝገቡን ጠቅሰዋል፡፡
በኮሚሽኑ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች በየጊዜው የሚሰጠው አደጋን የመቀነስ ጥንቃቄ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር አስተዋጽኦ አድርጓል ያሉት ባለሙያው ዘንድሮም ይህ ጥረት መቀጠሉ ችግሩን ለመቀነስ ድርሻ ነበረው ብለዋል።
ህብረተሰቡ ራሱንና ንብረቱን ለአደጋ ከሚያጋልጡ አደጋዎች ሊጠበቅ ይገባል ያሉት አቶ ጉልላት ከኮሚሽኑ በየጊዜው የሚሰጠውን ምክርና ማሳሰቢያን በመተግበርም ጥንቃቄን ባህል ማድረግ ግድ ይላል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አዲስ ዘመን ነሀሴ 9/2012
የቤት ውስጥ ራስን ለይቶ ህክምና (ውሸባ) እና እንክብካቤ በኢትዮጵያ አገልግሎት መሰጠት ተጀመረ
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የቤት ውስጥ ራስን ለይቶ ህክምና (ውሸባ) እና እንክብካቤ (Home Based Isolation and Care) በኢትዮጵያ አገልግሎት መሰጠት ተጀመረ፡፡
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ በተደረጉ 567,442 የኮሮና ቫይረስ የላብራቶሪ ምርመራዎች 27,242 በቫይረሱ የተያዙ ታማሚዎች ሲገኙ ከዚህም ውስጥ እስከ ሰኔ 22/2012 ዓ.ም ከነበሩት 5,000 ታማሚዎች 76 በመቶ ምንም ምልክት የሌለባቸው እና 21 በመቶ መለስተኛ ህመም ያላቸው እና ቀሪውቹ ከባድ እና በፅኑ ህመም ውስጥ ያሉ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል ፡፡
በብሔራዊ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል የኮቪድ-19 ምላሽ ማስተባበሪያ የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ክፍል ሀላፊ ዶ/ር ታይካ አለሙ እንደገለጹት በአሁኑ ሠአት 2000 በላይ የቤት ውስጥ የውሸባ እና እንክብካቤ የሚደረግላቸው ታካሚዎች እንደሚገኙ እና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ፡፡በዚህም ከ400 በላይ የሚሆኑት አገግመው መውጣታቸውን ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም በቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ጊዜ ከታካሚው ጋር በሚኖር ግንኙነት ንክኪን ማስወገድ፣ እጅን ከአልኮል በተሰራ የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ማፅዳት፣ ከታካሚው ጋር በሚገናኙበት ጊዜ የህክምና የአፍና የአፍንጫ ጭንብል በአግባቡ እንዲደረግ ዶ/ር ታይካ አሳስበዋል፡፡
እንዲሁም ታካሚዎቹ ማንኛውም የህመም መባባስ ሲኖራቸው ወደ 8335/952 ወይም ለሚከታተላቸው ክፍል በመደወል ማሳወቅ ወይም አቅራቢያቸው ወደሚገኝ ጤና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን ህክምና ማግኝት እንደሚችሉም ተገልጿል፡፡
በቅድሚያ የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ለማግኘት ስለታካሚው ተገቢውን መረጃ መስጠት የሚችል የቤት ውስጥ ተንከባካቢ ወይም የማህበረሰብ በጎ ፍቃደኛ መኖር፣ ቫይረሱ እንዳይሰራጭ ቤቱ በተገቢው ሁኔታ የተዋቀረ መሆን፣ ለታካሚው ቤተሰብ በቂ የአፍና አፍንጫ ጭንብል፣ ጓንት መኖሩን ማረጋረጥ የምግብ እና መሰረታዊ አቅርቦቶች ሞሟላት በተጨማሪም ተንከባካቢው እንዲሁም ታማሚው ተጓዳኝ በሽታ እንደሌለበት ማረጋገጥ ይኖርብናል ተብሏል፡፡
ህብረተሰቡ የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ መጀመሩን አውቆ ከጤና ባለሞያዎች የሚሰጠውን ምክር በሚገባ መተግበር እንዳለበት እና ለቫይረሱ ስርጭት ምክንያት ባለመሆን እንዲጠነቀቁ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል፡፡
የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ማለት አንድ የኮቪድ-19 ታማሚ መሆኑ በላብራቶሪ ምርመራ የተረጋገጠ ሰው የህመም ምልክት ሳያሳይ ወይም ቀለል ያሉ የህመም ምልክቶች ያሉት እንዲሁም በቤት ውስጥ መሞላት ያለበትን መስፈርቶች የሚያሞሉ የህብረተሰብ ክፍል የቤት ውስጥ እንክብካቤ ማድረግ ሲጀምር በቤት ውስጥ ውሸባ እንክብካቤ ማድረግ ማለት እንደሆነ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
የቤት ውስጥ ራስን ለይቶ ህክምና (ውሸባ) እና እንክብካቤ (Home Based Isolation and Care) በኢትዮጵያ አገልግሎት መሰጠት ተጀመረ፡፡
በኢትዮጵያ በአጠቃላይ በተደረጉ 567,442 የኮሮና ቫይረስ የላብራቶሪ ምርመራዎች 27,242 በቫይረሱ የተያዙ ታማሚዎች ሲገኙ ከዚህም ውስጥ እስከ ሰኔ 22/2012 ዓ.ም ከነበሩት 5,000 ታማሚዎች 76 በመቶ ምንም ምልክት የሌለባቸው እና 21 በመቶ መለስተኛ ህመም ያላቸው እና ቀሪውቹ ከባድ እና በፅኑ ህመም ውስጥ ያሉ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል ፡፡
በብሔራዊ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል የኮቪድ-19 ምላሽ ማስተባበሪያ የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ክፍል ሀላፊ ዶ/ር ታይካ አለሙ እንደገለጹት በአሁኑ ሠአት 2000 በላይ የቤት ውስጥ የውሸባ እና እንክብካቤ የሚደረግላቸው ታካሚዎች እንደሚገኙ እና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል ፡፡በዚህም ከ400 በላይ የሚሆኑት አገግመው መውጣታቸውን ገልጸዋል፡፡
በተጨማሪም በቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ጊዜ ከታካሚው ጋር በሚኖር ግንኙነት ንክኪን ማስወገድ፣ እጅን ከአልኮል በተሰራ የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ማፅዳት፣ ከታካሚው ጋር በሚገናኙበት ጊዜ የህክምና የአፍና የአፍንጫ ጭንብል በአግባቡ እንዲደረግ ዶ/ር ታይካ አሳስበዋል፡፡
እንዲሁም ታካሚዎቹ ማንኛውም የህመም መባባስ ሲኖራቸው ወደ 8335/952 ወይም ለሚከታተላቸው ክፍል በመደወል ማሳወቅ ወይም አቅራቢያቸው ወደሚገኝ ጤና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን ህክምና ማግኝት እንደሚችሉም ተገልጿል፡፡
በቅድሚያ የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ለማግኘት ስለታካሚው ተገቢውን መረጃ መስጠት የሚችል የቤት ውስጥ ተንከባካቢ ወይም የማህበረሰብ በጎ ፍቃደኛ መኖር፣ ቫይረሱ እንዳይሰራጭ ቤቱ በተገቢው ሁኔታ የተዋቀረ መሆን፣ ለታካሚው ቤተሰብ በቂ የአፍና አፍንጫ ጭንብል፣ ጓንት መኖሩን ማረጋረጥ የምግብ እና መሰረታዊ አቅርቦቶች ሞሟላት በተጨማሪም ተንከባካቢው እንዲሁም ታማሚው ተጓዳኝ በሽታ እንደሌለበት ማረጋገጥ ይኖርብናል ተብሏል፡፡
ህብረተሰቡ የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ መጀመሩን አውቆ ከጤና ባለሞያዎች የሚሰጠውን ምክር በሚገባ መተግበር እንዳለበት እና ለቫይረሱ ስርጭት ምክንያት ባለመሆን እንዲጠነቀቁ ኢንስቲትዩቱ አሳስቧል፡፡
የቤት ውስጥ ውሸባ እና እንክብካቤ ማለት አንድ የኮቪድ-19 ታማሚ መሆኑ በላብራቶሪ ምርመራ የተረጋገጠ ሰው የህመም ምልክት ሳያሳይ ወይም ቀለል ያሉ የህመም ምልክቶች ያሉት እንዲሁም በቤት ውስጥ መሞላት ያለበትን መስፈርቶች የሚያሞሉ የህብረተሰብ ክፍል የቤት ውስጥ እንክብካቤ ማድረግ ሲጀምር በቤት ውስጥ ውሸባ እንክብካቤ ማድረግ ማለት እንደሆነ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡
በምሽቱ የዲያመንድሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተወዳደሩ ሲሆን አትሌት ለተሰንበት ግደይ በ5ሺ ሜ ሴቶች 14:26.57 በሆነ ጊዜ ኬንያዊቷን ሄለን ኦቢሪን ተከትላ 2ኛ በመሆን ድሏን አጣጥማለች።
በ1,500 ሜ የተወዳደረው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ 5ኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ፣ የ3,000 ሜ መሠናክል ተሰላፊዎች አትሌት ለሜቻ ግርማ 8ኛ እና አትሌት ጌትነት ዋለ ደግሞ 10ኛ በመሆን እኤአ የ2020ን ዲያመንድሊግ ውድድር ሀ ብለው ጀምረዋል።
በ5ሺ ሜ ኡጋንዳዊው ጆሽዋ ቸፕተጌ 12:35.36 በሆነ ጊዜ ቀዳሚ ሲሆን በጀግናው ኢትዮጵያዊ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የነበረውን የ16 አመት የ5ሺ ሜ ሪከርድ 12:37.35 በመስበር ማሸነፍ ችሏል።
ቀጣዩ የዲያመንድሊግ ውድድር ከ9ቀናት በኋላ በስዊድን ስቶኮልም ይካሄዳል ተብሎም ይጠበቃል።
በ1,500 ሜ የተወዳደረው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ 5ኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ፣ የ3,000 ሜ መሠናክል ተሰላፊዎች አትሌት ለሜቻ ግርማ 8ኛ እና አትሌት ጌትነት ዋለ ደግሞ 10ኛ በመሆን እኤአ የ2020ን ዲያመንድሊግ ውድድር ሀ ብለው ጀምረዋል።
በ5ሺ ሜ ኡጋንዳዊው ጆሽዋ ቸፕተጌ 12:35.36 በሆነ ጊዜ ቀዳሚ ሲሆን በጀግናው ኢትዮጵያዊ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ተይዞ የነበረውን የ16 አመት የ5ሺ ሜ ሪከርድ 12:37.35 በመስበር ማሸነፍ ችሏል።
ቀጣዩ የዲያመንድሊግ ውድድር ከ9ቀናት በኋላ በስዊድን ስቶኮልም ይካሄዳል ተብሎም ይጠበቃል።
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ግምገማ መጀመሩ ተገለጸ
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ በየክልሉ ሥራ አስፈጻሚዎች የቀረቡትን ሪፖርቶች ለመገምገም ስብሰባ መጀመሩ ተገለጸ።
ሥራ አስፈጻሚው ዛሬ በጀመረው በዚሁ ስብሠባው በተጨማሪም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ጠቅላይ ሚኒስር ዶ/ር አብይ አህመድ በፌሥቡክ ገጻቸው ላይ አስታውቀዋል።
***********
(ኢ.ፕ.ድ)
የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ በየክልሉ ሥራ አስፈጻሚዎች የቀረቡትን ሪፖርቶች ለመገምገም ስብሰባ መጀመሩ ተገለጸ።
ሥራ አስፈጻሚው ዛሬ በጀመረው በዚሁ ስብሠባው በተጨማሪም በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያይ ጠቅላይ ሚኒስር ዶ/ር አብይ አህመድ በፌሥቡክ ገጻቸው ላይ አስታውቀዋል።