በዞኑ ባለፉት ስምንት ወራት ከቱሪዝም ዘርፉ ከ94 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ባለፉት ስምንት ወራት ከሀገር ውስጥና ከውጭ ጎብኚዎች ከ94 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ፡፡
በዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የቱሪዝም መስኮች ጥናትና ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ከተማ አለሙ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፣ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት የውጭ ገብኚዎች ቁጥር የቀነሰ ቢሆንም የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ቁጥር ጥሩ መሻሻል ያሳየ ነው፡፡
በዞኑ ባለፉት ስድስት ወራት ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች እንዲሁም ከሁለት ሺ በላይ የውጭ ሀገር ገብኚዎች ወደ ዞኑ ሄደው የጎበኙ ሲሆን በዘርፉ ከ94 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘት እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡ ጉራጌ ዞን ብዙ ለሀገር ውስጥና...
https://www.press.et/?p=94333
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ባለፉት ስምንት ወራት ከሀገር ውስጥና ከውጭ ጎብኚዎች ከ94 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን የጉራጌ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ፡፡
በዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ የቱሪዝም መስኮች ጥናትና ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ከተማ አለሙ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፣ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ምክንያት የውጭ ገብኚዎች ቁጥር የቀነሰ ቢሆንም የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች ቁጥር ጥሩ መሻሻል ያሳየ ነው፡፡
በዞኑ ባለፉት ስድስት ወራት ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን በላይ የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች እንዲሁም ከሁለት ሺ በላይ የውጭ ሀገር ገብኚዎች ወደ ዞኑ ሄደው የጎበኙ ሲሆን በዘርፉ ከ94 ሚሊዮን ብር በላይ ማግኘት እንደተቻለ ገልጸዋል፡፡ ጉራጌ ዞን ብዙ ለሀገር ውስጥና...
https://www.press.et/?p=94333
ጉዳት የደረሰበት የደሴ ሙዚየም የመልሶ ግንባታ ስራ ተጀመረ
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ጉዳት የደረሰበት የደሴ ሙዚየም የመልሶ ግንባታ ስራ መጀመሩን የደሴ ከተማ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።
የደሴ ከተማ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትዕግስት አበበ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በእንግሊዝ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የደሴ ሙዚየምን የማደስና የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ተጀምሯል።
የደሴ ሙዚየም መልሶ ግንባታ ስራ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የመምሪያ ኃላፊዋ ጠቁመዋል። በቱሪዝም ዘርፍ የወደሙ መሰረተ ልማቶችንና ቅርሶችን መልሶ የመገንባት ስራ በተደራጀ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል።
ስራው በቀጣይ የቱሪዝም ዘርፍ ገቢን ለማሳደግ ይረዳል ሲሉም ወ/ሮ ትዕግስት ተናግረዋል። ለመልሶ ግንባታና....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=94330
************
(ኢ.ፕ.ድ)
በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ጉዳት የደረሰበት የደሴ ሙዚየም የመልሶ ግንባታ ስራ መጀመሩን የደሴ ከተማ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታወቀ።
የደሴ ከተማ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ትዕግስት አበበ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በእንግሊዝ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ የደሴ ሙዚየምን የማደስና የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ተጀምሯል።
የደሴ ሙዚየም መልሶ ግንባታ ስራ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የመምሪያ ኃላፊዋ ጠቁመዋል። በቱሪዝም ዘርፍ የወደሙ መሰረተ ልማቶችንና ቅርሶችን መልሶ የመገንባት ስራ በተደራጀ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል።
ስራው በቀጣይ የቱሪዝም ዘርፍ ገቢን ለማሳደግ ይረዳል ሲሉም ወ/ሮ ትዕግስት ተናግረዋል። ለመልሶ ግንባታና....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=94330
ፓርኩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ አድኗል
***************
(ኢ ፕ ድ)
የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ባለፉት ስምንት ወራት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ማዳኑን አስታወቀ። ባለፉት ስምንት ወራት ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከ48 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማግኘቱንም አስታውቋል።
በፓርኩ እያለሙ የሚገኙ ባለሀብቶች ከሀገር ውስጥ ምርትና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በፈጠሩት የገበያ ትስስር፤ በስምንት ወራት የሁለት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር የምርትና አገልግሎት ትስስር መፈጠሩንም አስታውቋል። የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ትንሳኤ ይማም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በተያዘው በጀት ዓመት የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት በርካታ ሥራዎችን ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ፓርኩ ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ምርትን በሀገር ውስጥ መተካት ችሏል።
ለዚህም ሱፍሌት ማልት የብቅል ፋብሪካ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ይህ ፋብሪካ ከውጭ የሚገባውን የብቅል ምርት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካት ችሏል። ይህም 54 ሺህ ለሚሆኑ አነስተኛ የእርሻ መሬት ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=94324
(ፎቶ ኢፕድ ፋይል)
***************
(ኢ ፕ ድ)
የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ባለፉት ስምንት ወራት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ማዳኑን አስታወቀ። ባለፉት ስምንት ወራት ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከ48 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ማግኘቱንም አስታውቋል።
በፓርኩ እያለሙ የሚገኙ ባለሀብቶች ከሀገር ውስጥ ምርትና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር በፈጠሩት የገበያ ትስስር፤ በስምንት ወራት የሁለት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር የምርትና አገልግሎት ትስስር መፈጠሩንም አስታውቋል። የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ትንሳኤ ይማም ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በተያዘው በጀት ዓመት የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት በርካታ ሥራዎችን ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም ፓርኩ ከሁለት ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባ ምርትን በሀገር ውስጥ መተካት ችሏል።
ለዚህም ሱፍሌት ማልት የብቅል ፋብሪካ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል። ይህ ፋብሪካ ከውጭ የሚገባውን የብቅል ምርት ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ምርት መተካት ችሏል። ይህም 54 ሺህ ለሚሆኑ አነስተኛ የእርሻ መሬት ያላቸው አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እንዲሆኑ
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=94324
(ፎቶ ኢፕድ ፋይል)
በአፍሪካ ቀንድ የሚታየውን የሰራተኞች ፍልሰት ለመቆጣጠር የሚያስችል የቀጠናው አገራት የሚኒስትሮች ፎረም እየተካሄደ ነው
******************
(ኢ ፕ ድ)
በምስራቅና በአፍሪካ ቀንድ የሚታየውን የሰራተኞች ፍልሰት ለመቆጣጠር የሚያስችለው አራተኛው የቀጠናው አገራት የሚኒስትሮች ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
የአለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት በኢትዮጵያ ምክትል ሃላፊ ጂያን ዣን በፎረሙ መክፈቻ ላይ እነዳሉት፤ ፍልሰትን ለመቆጣጠር እና የስደተኛ ሰራተኞችን ደህንነት ለመጠበቅ ፖሊሲዎችን እና ልምዶችን ለማስማማት ጠቃሚ መድረክ ነው።
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ድኤታ አቶ አሰግድ ጌታቸው በበኩላቸው አራተኛው የሚኒስትሮች ፈረም በሰራተኞች መብት አያያዝ፣ ጉልበት ብዝበዛን በመከላከል፣ ህገወጥ ፍልሰትን ለመቆጣጠር አገራት ያላቸው ልምዶችና ተሞክሮዎችን የሚለዋወጡበት ነው።
ኢትዮጵያ በሰራተኞች አያያዝና በስራ እድል ፈጠራ ላይ ያላትን ልምድና ትሞክሮ እንደምታካፍል ገልጸዋል።
ፎረሙ 11 አገራትን ማለትም ኢትዮጵያ፣ ኬንያያ፣ ብሩንዲ፣ ኤርትራ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ሩዋንዳ፣ ሶማሊያ፣ ታንዛኒያና ኡጋንዳን የያዘ ሲሆን በአለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ ተወካዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ፎረሙ ለሚቀጥሉት አራት ቀናት የሚቆይ ነው።
በሞገስ ተስፋ
******************
(ኢ ፕ ድ)
በምስራቅና በአፍሪካ ቀንድ የሚታየውን የሰራተኞች ፍልሰት ለመቆጣጠር የሚያስችለው አራተኛው የቀጠናው አገራት የሚኒስትሮች ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።
የአለም አቀፍ የፍልሰተኞች ድርጅት በኢትዮጵያ ምክትል ሃላፊ ጂያን ዣን በፎረሙ መክፈቻ ላይ እነዳሉት፤ ፍልሰትን ለመቆጣጠር እና የስደተኛ ሰራተኞችን ደህንነት ለመጠበቅ ፖሊሲዎችን እና ልምዶችን ለማስማማት ጠቃሚ መድረክ ነው።
የስራና ክህሎት ሚኒስትር ድኤታ አቶ አሰግድ ጌታቸው በበኩላቸው አራተኛው የሚኒስትሮች ፈረም በሰራተኞች መብት አያያዝ፣ ጉልበት ብዝበዛን በመከላከል፣ ህገወጥ ፍልሰትን ለመቆጣጠር አገራት ያላቸው ልምዶችና ተሞክሮዎችን የሚለዋወጡበት ነው።
ኢትዮጵያ በሰራተኞች አያያዝና በስራ እድል ፈጠራ ላይ ያላትን ልምድና ትሞክሮ እንደምታካፍል ገልጸዋል።
ፎረሙ 11 አገራትን ማለትም ኢትዮጵያ፣ ኬንያያ፣ ብሩንዲ፣ ኤርትራ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ሩዋንዳ፣ ሶማሊያ፣ ታንዛኒያና ኡጋንዳን የያዘ ሲሆን በአለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት፣ የአፍሪካ ልማት ባንክ ተወካዮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ፎረሙ ለሚቀጥሉት አራት ቀናት የሚቆይ ነው።
በሞገስ ተስፋ
ክልሎች ለውሃ ልማት የተበደሩትን አምስት ቢሊዮን ብር ለመመለስ ፈቃደኛ አልሆኑም
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ውሃ ለማልማት የተበደሩትን አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በንጹህ የመጠጥ ውሃ ተደራሽነት ላይ እንቅፋት መፍጠሩ ተገለጸ።
መመለስ ከነበረባቸውም የመለሱት ገንዘብም አንድ ከመቶ በታች መሆኑም ተገልጿል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ ለኢትዮጵያ ፕሬሰ ድርጅት እንደገለጹት፤ የውሃ ልማት ፈንድ በሚኒስቴሩ ስር ሲቋቋም የተገኘውን ገንዘብ ከተሞች ተበድረው የመጠጥ ውሃ ግንባታ አከናውነው ለህብረተሰቡ ከሚሰጡት የመጠጥ ውሃ ደግሞ የሚገኘውን ገቢ በመሰብሰብ እዳቸውን የሚከፍሉበትን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=94373
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ውሃ ለማልማት የተበደሩትን አምስት ቢሊዮን ብር በላይ ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በንጹህ የመጠጥ ውሃ ተደራሽነት ላይ እንቅፋት መፍጠሩ ተገለጸ።
መመለስ ከነበረባቸውም የመለሱት ገንዘብም አንድ ከመቶ በታች መሆኑም ተገልጿል።
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ሃብታሙ ኢተፋ ለኢትዮጵያ ፕሬሰ ድርጅት እንደገለጹት፤ የውሃ ልማት ፈንድ በሚኒስቴሩ ስር ሲቋቋም የተገኘውን ገንዘብ ከተሞች ተበድረው የመጠጥ ውሃ ግንባታ አከናውነው ለህብረተሰቡ ከሚሰጡት የመጠጥ ውሃ ደግሞ የሚገኘውን ገቢ በመሰብሰብ እዳቸውን የሚከፍሉበትን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=94373