Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
‹‹የሴቶች ተሳትፎ በሌለበት የሀገርን ብልጽግና ማረጋገጥ አይቻልም›› ወይዘሮ ልዕልቲ ግደይ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የሴቶች ተሳትፎ በሌለበት የሀገርን ብልጽግና ማረጋገጥ አይቻልም ሲሉ በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ልዕልቲ ግደይ ገለጹ።
ወይዘሮ ልዕልቲ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት ሀገር እንድትበለፅግ ሀገራዊ ሁኔታዎችን ለማረጋጋት የሴቶችን ተሳትፎ ከፍተኛ መሆን አለበት ሲሉ ገልፀዋል።

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93905
የሴቶችንመብትናእኩልነትበተመለከተ እንደ ሀገር የተደረሰበትን ርቀት ማሰብ ያስፈልጋል
**************
(ኢ ፕ ድ )
ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን ሲከበር እንደ ሀገር የሴቶችን መብትና እኩልነት በማክበርና በማስከበር በኩል የተደረሰበት ርቀት የት መሄድ ችሏል የሚለው ሊታሰብበት እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ ዶክተር ራሔል ባፌ ተናገሩ።
ዶክተር ራሔል ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳሉት፤ ፖለቲካ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93900
ከእሁድ ዕለት ከሰዓት ጀምሮ ለሜቄዶኒያ የተካሄደው የቀጥታ ስርጭት የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር የታሰበውን አሳክቶ ተጠናቋል
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከሰባት ሺህ በላይ አረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማንን በውስጡ በመያዝ አገልግሎት እየሰጠ ለሚገኘው ሜቄዶኒያ አዲስ ላስገነባው ህንጻ በርና መስኮት ለማሟላት የተካሄደው የቀጥታ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር የታሰበውን አሳክቶ ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ ተጠናቋል።
ሜቄዶኒያ ያስጀመረው ባለ 12 ወለል ሕንፃ ከሁለት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ ሲሆን፤ በርና መስኮት ለመግጠም 151 ሚሊየን ብር ያስፈልግ ነበር።
በኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አስተባባሪነት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች ታዋቂ ግለሰቦች በተሳተፉበት የቀጥታ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ላይ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ድጋፍ አድርገዋል።
በተደረገው የገቢ ማሰባሰብ መርሀ ግብርም ለ888 በሮች እና ለ739 መስኮቶች የሚውል ገንዝብ የተገኘ ሲሆን፤ የአንድ በር ዋጋ 106 ሺህ ብር የአንድ መስኮት ዋጋ ደግሞ 80 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።
ማዕከሉ በቀጣይ 20 ሺህ ወገኖችን ለመድረስ አቅዷል።
ኢፕድ የሴት ሠራተኞቹን ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ ነው
**************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) የተቋሙን ሴት ሠራተኞች ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን አስታወቀ። ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8 ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በሴት ጋዜጠኞች እየተዘጋጀ የሚወጣው ጋዜጣ መጠናከሩ የሚያበረታታ መሆኑንም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ፤ “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ 112ተኛ እንዲሁም በሀገራችን ለ47 ተኛ ጊዜ የሚከበረውን የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ሴት ሠራተኞችን የእኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፣ የአመራር ሚናቸው ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93903
ከ20 ሚሊዮን በላይ ሴቶች የወር አበባ ንጽሕና መጠበቂያ አያገኙም ተባለ
**************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የወር አበባ ከሚያዩ ከ35 ሚሊዮን ሴቶች ውስጥ 22 ሚሊዮን ወይም 75 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች የወር አበባ ንጽሕና መጠበቂያ እንደማያገኙ የአደይ የሴቶች የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ መሥራች አስታወቁ።
የአደይ የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ መሥራች ወይዘሮ ሚካል ማሞ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የአደይ የሴቶች የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ (ፓድ) ምርት በኢትዮጵያ ያለውን የሴቶች የወር አበባ የንጽሕና መጠበቂያ አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ይረዳል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93904
"የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ በሀሳብ የበላይነት ማመን ያስፈልጋል"
-የአውራምባ ማኅበረሰብ መሥራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ ጾታን ሳይሆን ሀሳብን የሚመዝን በሀሳብ የበላይነት የሚያምን ማኅበረሰብ መፍጠር እንደሚገባ የአውራምባ ማኅበረሰብ መሥራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ ገለጹ።
የአውራምባ ማኅበረሰብ መሥራቹ የክብር ዶክተር ዙምራ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ የፆታ እኩልነት ያስፈልጋል ሲባል አንዱ አብሮ የሚነሳው ነገር የሥራ ክፍፍል ነው። አትዮጵያ ውስጥ የጾታ ልዩነት ለሥራ ክፍፍል የማይውልበት ማኅበረሰብ አለ። በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ የአውራምባ ማኅበረሰብ ወንድ ወይም ሴት መሆን አንድን ነገር ማድረግ ከመቻል ጋር ቁርኝት የለውም ብለው ያምናሉ።

መሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93912
መንግስት አራት ድርጅቶችን ወደግል ለማዛወር ማቀዱ ተገለጸ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
መንግስት የተወሰኑ ተቋማትን ወደግል የማዛወር እቅድ እንዳለው የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታወቀ፡፡
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃብታሙ ኃይለሚካኤል ለኢፕድ በሰጡት ማብራሪያ፤ በመንግስት የአክሲዮን ድርሻ ተይዘው ያሉ ተቋማት አሉ፡፡ እነርሱን ባለሃብቶች እንዲገቡበት ይፈለጋል ብለዋል፡፡
በመንግስትና በግል አጋርነት ያሉ እንደ ቢ.ኤም ጨርቃጨርቅ፣ አፍሪካ ጁስ፣ አብያታ ሶዳ አሽ እና አምቼ በሂደት ወደግል ባለሀብቶች ለማዛወር መታቀዱን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
መንግስት ባለፉት ዓመትት 300 በላይ ድርጅቶችን ወደግል ማዛወሩን ጠቁመው፤በአሁኑ ወቅትም የመንግስትን እና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረገ መልኩ የነበረው አሰራር የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ፣ ብሔራዊ እንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት፣ ዕዳና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ተጠሪ የሆኑ የልማት ድርጅቶች መሆናቸው ይታወቃል፡፡
በክፍለዮሃንስ አንበርብር
«መሪነት ለሴት ልጅ ችሮታ ሳይሆን ችሎታ ነው»
-ዶክተር አዲስ ዓለም አባትሁን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ካምፓስ ዲን
******************
(ኢ ፕ ድ)
መሪነት ለሴት ልጅ ችሮታ ሳይሆን ችሎታ ነው›› ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ካምፓስ ዲን ዶክተር አዲስዓለም አባትሁን ገለጹ።
ዶክተር አዲስዓለም ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ ሴት ልጅ በተለያየ የሥልጣን ደረጃ ላይ ሆና የመሪነት መንበር ላይ ብትቀመጥም ከፈተና ማምለጥ አትችልም።
መሪነት ላይ መሆን እርሷን ካለችበት ከፍታ ሊያወርዳት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93928
በኦቢቻ ወረዳ ለማዋለጃ አገልግሎት የሚውል ክሊኒክ ግንባታ ሥራ መጀመሩ ተገለጸ
****************
(ኢ ፕ ድ)
በረከት ወርቁ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ የእርሻ ሥራ በሚያከናውንበት በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ኦቢቻ ወረዳ የሚስተዋለውን የእናቶች የጤና አገልግሎት መስጫ ችግር ለመፍታት የተሟላ የቤተሙከራ (ላቦራቶሪ)ያለው የወሊድ አገልግሎት መስጫ ክሊኒክ ግንባታ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ።
‹‹ገበሬ›› በሚል ቅጽል ስም የምትታወቀው የኢንዱስትሪው ባለቤት በረከት ወርቁ ‹‹እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ›› በሚል መሪ ሐሳብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ112ኛ ጊዜ፤ በሀገራችን ደግሞ ለ47ኛ ጊዜ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93940
በሆርቲካልቸር ሴክተር ባላፉት ሰባት ወራት ከ400 ሚሊየን ዶላር ባላይ ገቢ ተገኝቷል
👉 8ኛው አለም አቀፍ የሆርቲካልቸር ኤክስፖ ተከፈተ
****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር አምራች ላኪዎች ማኅበር ያዘጋጀው 8ኛው የሆርቲካልቸር ኤክስፖ በሚሊኒየም አደራሽ ተከፈቷል
የግብርና ሚኒስትር ዶክተር ግርማ አመንቴ በኤክስፖ መክፈቻ ስነስርአቱ፣ ዘርፉ ለበርካቶች የስራ እድል የፈጠረና የውጭ ምንዛሬን እያስገኘ ያለ እንደሆነ በመጠቀስ በተያዘው በጀት አመት ባላፉት ሰባት ወራት ውስጥ ከ400 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልጸዋል።
ሆርቲካልቸር አገራዊ ኢኮኖሚውን ከሚደግፍ አንጻር ጥሩ ውጤት ከታየባቸው ዘርፎች አንዱ እንደሆነ ተናግረዋል።
በአክስፖው አለም አቀፍ የገብያ ትስስርን ለመፍጠርና የተወዳዳሪነትን አቅም ለማሳድግ ትልቅ ሚና እንዳለው ተጠቅሷል።
በአዲሱ ገረመው
ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ በከተማ ፅዳት ስራ ለተሰማሩ 353 ሴቶች ዘመናዊ የስልክ ቀፎ ሸለመ
****************************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮ ቴሌኮም አለማቀፉን የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ ለ353 የአዲስ አበባ ከተማ የጽዳት አገልግሎት የላቀ አፈጻጸም ላላቸዉ ሴት ሰራተኞች ዘመናዊ የስልክ ቀፎ ሸለመ።
ኩባንያዉ '' የዲጂታል አካታችነት ለፆታ እኩልነት'' በሚል መሪ ቃል አለም አቀፍ የሴቶችን ቀንን አክብሯል።
የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ እንደተናገሩት ሽልማቱ ሴቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂና ፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው።
የዲጂታል ኢኮኖሚ ተካታችነትንና እኩልነትን ለማረጋገጥ ትልቅ ፋይዳ አለውም ገልጸዋል።
ሴቶችን ማካተትና ማብቃት የኩባንያዉ አንዱ እሴት በመሆኑ ለዘመናዊ የስልክ ቀፎዎቹ ከ3 ሚሊየን ብር በላይ መወጪ ማድረጉን ተናግረዋል።
ባለፉት 3 ዓመታት ብቻ ሴቶች የመረጃ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለመደገፍ 54.4 ሚሊየን ብር ወጪ በማድረግ ከ70ሺ በላይ የሞባይል ቀፎዎችን አበርክቷል።