Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያን የማጓጓዝ ሥራ ተጀምሯል
*************
(ኢ ፕ ድ)
ለ2015/16 የምርት ዘመን 1,287,500 ሜትሪክ ቶን የአፈር ማዳበሪያ ለማጓጓዝ ከግብርና ሚኒስቴር ጋር ውል ገብቶ ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት አስታወቀ። እስካሁን ጅቡቲ ወደብ ከደረሰው የአፈር ማዳበሪያ 388ሺ 206 ሜትሪክ ቶን መጓጓዙም ተገልጿል።
የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ድርጅት (ኢባትሎአድ) ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚና የጭነት አስተላላፊ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሲራጅ አብዱላሂ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93857
የሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት እያደረገ ነው
**************
(ኢ ፕ ድ)
ራስ ገዝ ለመሆን የሚያስችል ዝግጅት በማድረግ ላይ መሆኑን የሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ። የዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ መሆኑ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን እንደሚያሳድገው ተገልጿል።
የሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል ዩሱፍ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋሟት ራስ ገዝ እንዲሆኑ የተጀመረውን ጥረት ታሳቢ በማድረግ ዩኒቨርሲቲው የራሱን ዝግጅት እያከናወነ ይገኛል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93862
የኦሮሞ አርቲስቶች በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች ድጋፍ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ገለጹ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች ርዳታ የማሰባሰብ እንቅስቃሴ መጀመራቸውን የኦሮሞ አርቲስቶች ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ አስታወቀ። ኮሚቴው “ዜጋ ለዜጋው ጋሻ ነው” በሚል መሪ ቃል ድጋፍ የማሰባሰብ ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል ።
በድርቅ ለተጎዱ ዜጎችን ለመርዳት በአርቲስቶች የተቋቋመው ኮሚቴ ሰብሳቢ አርቲስት ቀመር የሱፍ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የክልሉ አርቲስቶች አንድ ላይ በመሆን በድርቅ ለተጎዱ የቦረና ፣ ጉጂ እና ባሌ ቆላማ አካባቢዎች ለሚኖሩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን እርዳታ የማሰባሰብ ሥራ ጀምሯል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93858
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የቦንጋ ከተማ ቀላል የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን አስጀመሩ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የቦንጋ ከተማ ቀላል የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን አሰጀመሩ።
ቀዳማዊት እመቤተ ዝናሽ ታያቸው ከጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ጋር በመሆን ቦንጋ ከተማ ገብተዋል።
ቦንጋ ከተማ ሲደርሱ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ወደ ቦንጋ የመጡት የቦንጋ ከተማ ቀላል የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለማስጀመርና በቀዳማዊት እመቤት ፅህፈት ቤት ከመቶ ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በቦንጋ ከተማ የተገነባውን የዳቦና ዱቄት ፋብሪካ ለማስመረቅ ነው።
ኢትዮጵያ ያስመዘገበቻቸው የልማት ስኬቶችን በተመድ ዓለምአቀፍ የአዳጊ ሀገራት ጉባዔ ላይ አካፈለች
***************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን የልማት ስኬቶች በኳታር ዶሃ እየተካሄደ በሚገኘው 5ኛው የተመድ ዓለምአቀፍ የአዳጊ ሀገራት ጉባዔ ላይ ማካፈሏን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዶ/ር ፍጹም አሠፋ ኢትዮጵያ በመስኖ ልማት፣ በስንዴ ምርታማነት፣ በአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄና በተለያዩ የልማት መሥኮች ያስመዘገበቻቸውን ውጤቶች ለጉባኤው አቅርበዋል፡፡
በግብርናው ዘርፍ ያስመዘገበቻቸውን የልማት ስኬቶች በ5ኛው የተመድ ዓለምአቀፍ የአዳጊ ሀገራት ጉባዔ ላይ አካፍላለች።
‹‹የሴቶች ተሳትፎ በሌለበት የሀገርን ብልጽግና ማረጋገጥ አይቻልም›› ወይዘሮ ልዕልቲ ግደይ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የሴቶች ተሳትፎ በሌለበት የሀገርን ብልጽግና ማረጋገጥ አይቻልም ሲሉ በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ልዕልቲ ግደይ ገለጹ።
ወይዘሮ ልዕልቲ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት ሀገር እንድትበለፅግ ሀገራዊ ሁኔታዎችን ለማረጋጋት የሴቶችን ተሳትፎ ከፍተኛ መሆን አለበት ሲሉ ገልፀዋል።

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93905
የሴቶችንመብትናእኩልነትበተመለከተ እንደ ሀገር የተደረሰበትን ርቀት ማሰብ ያስፈልጋል
**************
(ኢ ፕ ድ )
ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን ሲከበር እንደ ሀገር የሴቶችን መብትና እኩልነት በማክበርና በማስከበር በኩል የተደረሰበት ርቀት የት መሄድ ችሏል የሚለው ሊታሰብበት እንደሚገባ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጸሐፊ ዶክተር ራሔል ባፌ ተናገሩ።
ዶክተር ራሔል ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳሉት፤ ፖለቲካ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93900
ከእሁድ ዕለት ከሰዓት ጀምሮ ለሜቄዶኒያ የተካሄደው የቀጥታ ስርጭት የገንዘብ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር የታሰበውን አሳክቶ ተጠናቋል
****************
(ኢ.ፕ.ድ)
ከሰባት ሺህ በላይ አረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማንን በውስጡ በመያዝ አገልግሎት እየሰጠ ለሚገኘው ሜቄዶኒያ አዲስ ላስገነባው ህንጻ በርና መስኮት ለማሟላት የተካሄደው የቀጥታ ገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር የታሰበውን አሳክቶ ትናንት እኩለ ሌሊት ላይ ተጠናቋል።
ሜቄዶኒያ ያስጀመረው ባለ 12 ወለል ሕንፃ ከሁለት ነጥብ ሶስት ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ ሲሆን፤ በርና መስኮት ለመግጠም 151 ሚሊየን ብር ያስፈልግ ነበር።
በኮሜዲያን እሸቱ መለሰ አስተባባሪነት የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች ታዋቂ ግለሰቦች በተሳተፉበት የቀጥታ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ ግብር ላይ በአገር ውስጥና በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች ድጋፍ አድርገዋል።
በተደረገው የገቢ ማሰባሰብ መርሀ ግብርም ለ888 በሮች እና ለ739 መስኮቶች የሚውል ገንዝብ የተገኘ ሲሆን፤ የአንድ በር ዋጋ 106 ሺህ ብር የአንድ መስኮት ዋጋ ደግሞ 80 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።
ማዕከሉ በቀጣይ 20 ሺህ ወገኖችን ለመድረስ አቅዷል።
ኢፕድ የሴት ሠራተኞቹን ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ ነው
**************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት (ኢፕድ) የተቋሙን ሴት ሠራተኞች ሁለተናዊ ተጠቃሚነት ለማሳደግ እየሠራ መሆኑን አስታወቀ። ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8 ምክንያት በማድረግ በየዓመቱ በሴት ጋዜጠኞች እየተዘጋጀ የሚወጣው ጋዜጣ መጠናከሩ የሚያበረታታ መሆኑንም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጌትነት ታደሰ፤ “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ” በሚል መሪ ቃል በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ 112ተኛ እንዲሁም በሀገራችን ለ47 ተኛ ጊዜ የሚከበረውን የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ ባስተላለፉት መልዕክት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት በተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ሴት ሠራተኞችን የእኩል ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ፣ የአመራር ሚናቸው ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93903
ከ20 ሚሊዮን በላይ ሴቶች የወር አበባ ንጽሕና መጠበቂያ አያገኙም ተባለ
**************
(ኢ ፕ ድ)
በኢትዮጵያ የወር አበባ ከሚያዩ ከ35 ሚሊዮን ሴቶች ውስጥ 22 ሚሊዮን ወይም 75 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች የወር አበባ ንጽሕና መጠበቂያ እንደማያገኙ የአደይ የሴቶች የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ መሥራች አስታወቁ።
የአደይ የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ መሥራች ወይዘሮ ሚካል ማሞ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የአደይ የሴቶች የሚታጠብ ንጽሕና መጠበቂያ (ፓድ) ምርት በኢትዮጵያ ያለውን የሴቶች የወር አበባ የንጽሕና መጠበቂያ አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ይረዳል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93904
"የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ በሀሳብ የበላይነት ማመን ያስፈልጋል"
-የአውራምባ ማኅበረሰብ መሥራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የጾታ እኩልነትን ለማረጋገጥ ጾታን ሳይሆን ሀሳብን የሚመዝን በሀሳብ የበላይነት የሚያምን ማኅበረሰብ መፍጠር እንደሚገባ የአውራምባ ማኅበረሰብ መሥራች የክብር ዶክተር ዙምራ ኑሩ ገለጹ።
የአውራምባ ማኅበረሰብ መሥራቹ የክብር ዶክተር ዙምራ ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ የፆታ እኩልነት ያስፈልጋል ሲባል አንዱ አብሮ የሚነሳው ነገር የሥራ ክፍፍል ነው። አትዮጵያ ውስጥ የጾታ ልዩነት ለሥራ ክፍፍል የማይውልበት ማኅበረሰብ አለ። በደቡብ ጎንደር ዞን ፎገራ ወረዳ ውስጥ የሚገኙ የአውራምባ ማኅበረሰብ ወንድ ወይም ሴት መሆን አንድን ነገር ማድረግ ከመቻል ጋር ቁርኝት የለውም ብለው ያምናሉ።

መሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93912
መንግስት አራት ድርጅቶችን ወደግል ለማዛወር ማቀዱ ተገለጸ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
መንግስት የተወሰኑ ተቋማትን ወደግል የማዛወር እቅድ እንዳለው የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታወቀ፡፡
የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር አቶ ሃብታሙ ኃይለሚካኤል ለኢፕድ በሰጡት ማብራሪያ፤ በመንግስት የአክሲዮን ድርሻ ተይዘው ያሉ ተቋማት አሉ፡፡ እነርሱን ባለሃብቶች እንዲገቡበት ይፈለጋል ብለዋል፡፡
በመንግስትና በግል አጋርነት ያሉ እንደ ቢ.ኤም ጨርቃጨርቅ፣ አፍሪካ ጁስ፣ አብያታ ሶዳ አሽ እና አምቼ በሂደት ወደግል ባለሀብቶች ለማዛወር መታቀዱን ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
መንግስት ባለፉት ዓመትት 300 በላይ ድርጅቶችን ወደግል ማዛወሩን ጠቁመው፤በአሁኑ ወቅትም የመንግስትን እና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረገ መልኩ የነበረው አሰራር የሚቀጥል ይሆናል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ፣ ብሔራዊ እንስሳት ጤና ጥበቃ ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት፣ ዕዳና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን፣ የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን እና የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ተጠሪ የሆኑ የልማት ድርጅቶች መሆናቸው ይታወቃል፡፡
በክፍለዮሃንስ አንበርብር
«መሪነት ለሴት ልጅ ችሮታ ሳይሆን ችሎታ ነው»
-ዶክተር አዲስ ዓለም አባትሁን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ካምፓስ ዲን
******************
(ኢ ፕ ድ)
መሪነት ለሴት ልጅ ችሮታ ሳይሆን ችሎታ ነው›› ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አራት ኪሎ ካምፓስ ዲን ዶክተር አዲስዓለም አባትሁን ገለጹ።
ዶክተር አዲስዓለም ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደተናገሩት፤ ሴት ልጅ በተለያየ የሥልጣን ደረጃ ላይ ሆና የመሪነት መንበር ላይ ብትቀመጥም ከፈተና ማምለጥ አትችልም።
መሪነት ላይ መሆን እርሷን ካለችበት ከፍታ ሊያወርዳት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93928
በኦቢቻ ወረዳ ለማዋለጃ አገልግሎት የሚውል ክሊኒክ ግንባታ ሥራ መጀመሩ ተገለጸ
****************
(ኢ ፕ ድ)
በረከት ወርቁ ኢንተግሬትድ አግሮ ኢንዱስትሪ የእርሻ ሥራ በሚያከናውንበት በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ኦቢቻ ወረዳ የሚስተዋለውን የእናቶች የጤና አገልግሎት መስጫ ችግር ለመፍታት የተሟላ የቤተሙከራ (ላቦራቶሪ)ያለው የወሊድ አገልግሎት መስጫ ክሊኒክ ግንባታ ሥራ መጀመሩን አስታወቀ።
‹‹ገበሬ›› በሚል ቅጽል ስም የምትታወቀው የኢንዱስትሪው ባለቤት በረከት ወርቁ ‹‹እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ›› በሚል መሪ ሐሳብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ112ኛ ጊዜ፤ በሀገራችን ደግሞ ለ47ኛ ጊዜ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93940