በአርቲስት ዓሊ ቢራ ስም በቢሾፍቱ ከተማ አዲስ የባንክ ቅርንጫፍ ተከፈተ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቢሾፍቱ ከተማ ድሬ ጂቱ ቀበሌ በክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ ስም ‘’ዓሊ ቢራ ቅርንጫፍ’’ በይፋ አስመርቆ ስራ አሰጀመረ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ወጋየሁ ገብረማርያም፣ የባንኩ ማዕከላዊ ሪጅን የዲስትርክቶች ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ግዛቸውና አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ በጋራ ቅርንጫፉን መርቀው ስራ አሰጀምረዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማዕከላዊ ሪጅን የዲስትርክት ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ግዛቸው እንደተናገሩት፤ አርቲስት አሊ ቢራ ከዚህ በላይ ይገበዋል፤ ተሰጦውን ሳይሰስት ለኢትዮጵያውያን ያበረከተና ለጥበብ የተሰጠ ሰው እንደሆነ ተናግረዋል።
በአሁኑ ትውልድ ይበልጥ እንዲታወቅና በመጪው ትውልድ እንዳይዘነጋ ታስቦ ቅርንጫፉ እንደተከፈተ ጠቁመዋል።
ለክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ የህይወት ዘመን ትሩፋቶች የተዘጋጀ መታሰቢያ እንደሆነም ተገልጿል።
በምረቃ ሥነሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተለያዩ ቅርንጫፍ ማናጀሮች፣ የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ ተወካይ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎችና በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቢሾፍቱ ከተማ ድሬ ጂቱ ቀበሌ በክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ ስም ‘’ዓሊ ቢራ ቅርንጫፍ’’ በይፋ አስመርቆ ስራ አሰጀመረ።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የደንበኞች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ወጋየሁ ገብረማርያም፣ የባንኩ ማዕከላዊ ሪጅን የዲስትርክቶች ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ግዛቸውና አባ ገዳ በየነ ሰንበቶ በጋራ ቅርንጫፉን መርቀው ስራ አሰጀምረዋል።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ማዕከላዊ ሪጅን የዲስትርክት ኦፕሬሽን ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ግዛቸው እንደተናገሩት፤ አርቲስት አሊ ቢራ ከዚህ በላይ ይገበዋል፤ ተሰጦውን ሳይሰስት ለኢትዮጵያውያን ያበረከተና ለጥበብ የተሰጠ ሰው እንደሆነ ተናግረዋል።
በአሁኑ ትውልድ ይበልጥ እንዲታወቅና በመጪው ትውልድ እንዳይዘነጋ ታስቦ ቅርንጫፉ እንደተከፈተ ጠቁመዋል።
ለክቡር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ የህይወት ዘመን ትሩፋቶች የተዘጋጀ መታሰቢያ እንደሆነም ተገልጿል።
በምረቃ ሥነሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተለያዩ ቅርንጫፍ ማናጀሮች፣ የቢሾፍቱ ከተማ ከንቲባ ተወካይ፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎችና በርካታ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ያልተጠናቀቁ የጋራ መኖርያ ቤቶች ግምባታ እስከ ሰኔ ወር ድረስ እንዲጠናቀቅ ከንቲባ አዳነች አሳሰቡ
****************
(ኢ ፕ ድ)
የጋራ መኖርያ ቤቶችን ግንባታ በተያዘላቸው ጊዜ ያለማጠናቀቅ ክፍተት መኖሩን የገመገሙት ከንቲባ አዳነች፣ ለዚህ ክፍተት የሲሚንቶ እጥረት፣ የተለያዩ የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ ልዩነት እንዲሁም የወሰን ማስከበር ችግር መኖሩን ተገንዝበናል ብለዋል
ሆኖም እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ፣ የጋራ መኖርያ ቤቶችን መሰረታዊ ግንባታ መንግስት በአፋጣኝ በማጠናቀቅ፣ ቀሪውን ተጠቃሚው እንዲያሟላ የሚደረግ ሲሆን የመሰረተ ልማት አቅራቢ ተቋማት ቀሪ ስራዎችን በቅንጅትና በፍጥነት እንዲያጠናቅቁ አቅጣጫ የሰጡ ሲሆን ይህንንም የሚከታተሉ ተቋማትና ኮሚቴዎች በየሳምንቱ የግንባታውን ሂደት ይከታተላሉ ብለዋል።
የተነሱት የግብዓት እጥረትና የዋጋ ልዩነቶችም አፋጣኝ እልባት አግኝተው እስከ ሰኔ ወር ባለው ግዜ ግንባታዎች ተጠናቅቀው ለተጠቃሚው ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ አቅጣጫ መቀመጡን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ገልጸዋል።
****************
(ኢ ፕ ድ)
የጋራ መኖርያ ቤቶችን ግንባታ በተያዘላቸው ጊዜ ያለማጠናቀቅ ክፍተት መኖሩን የገመገሙት ከንቲባ አዳነች፣ ለዚህ ክፍተት የሲሚንቶ እጥረት፣ የተለያዩ የግንባታ ግብዓቶች ዋጋ ልዩነት እንዲሁም የወሰን ማስከበር ችግር መኖሩን ተገንዝበናል ብለዋል
ሆኖም እነዚህን ችግሮች በመቅረፍ፣ የጋራ መኖርያ ቤቶችን መሰረታዊ ግንባታ መንግስት በአፋጣኝ በማጠናቀቅ፣ ቀሪውን ተጠቃሚው እንዲያሟላ የሚደረግ ሲሆን የመሰረተ ልማት አቅራቢ ተቋማት ቀሪ ስራዎችን በቅንጅትና በፍጥነት እንዲያጠናቅቁ አቅጣጫ የሰጡ ሲሆን ይህንንም የሚከታተሉ ተቋማትና ኮሚቴዎች በየሳምንቱ የግንባታውን ሂደት ይከታተላሉ ብለዋል።
የተነሱት የግብዓት እጥረትና የዋጋ ልዩነቶችም አፋጣኝ እልባት አግኝተው እስከ ሰኔ ወር ባለው ግዜ ግንባታዎች ተጠናቅቀው ለተጠቃሚው ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ አቅጣጫ መቀመጡን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት ገልጸዋል።
የጠቅላይ ሚነስትር ዶከተር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት‼️
ዛሬ ከሼክ ተሚም ኢብን ሀማድ አልታኒ ጋር በመገናኘታችን ደስተኛ ነኝ። የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን ጨምሮ በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም ተወያይተናል። #ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ዘርፎች ለኳታር ኢንቨስትመንቶች ብዙ ዕድሎች አሉ።
ዛሬ ከሼክ ተሚም ኢብን ሀማድ አልታኒ ጋር በመገናኘታችን ደስተኛ ነኝ። የሁለትዮሽ ግንኙነታችንን ጨምሮ በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይም ተወያይተናል። #ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ዘርፎች ለኳታር ኢንቨስትመንቶች ብዙ ዕድሎች አሉ።
በቶክዮ ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል
******
(ኢ.ፕ.ድ)
ሌሊት በተካሄደው የ2023 የቶክዮ ማራቶን ላይ የተሳተፉ ወንድና ሴት ኢትዮጵያዊን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል።
በወንዶች ውድድር አትሌት ደሶ ገልሚሲ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ፤ አትሌት መሀመድ ኢሳ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል። አትሌት ፀጋዬ ጌታቸው ደግሞ የሶስተኛ ደረጃን ይዞ ፉክክሩን ጨርሷል ።
በሴቶች በተደረገው ውድድር አትሌት ፀሀይ ገመቹ በኬንያዊቷ ሮዝመሪ ዋንጂሩ ተቀድማ በሁለተኝነት ውድድሯን ስታጠናቅቅ አሸቴ በከሬ ሶስተኛ አትሌት ወርቅነሽ ኢዶሳ ደግሞ በአራተኝነት ውድድራቸውን ፈፅመዋል።
******
(ኢ.ፕ.ድ)
ሌሊት በተካሄደው የ2023 የቶክዮ ማራቶን ላይ የተሳተፉ ወንድና ሴት ኢትዮጵያዊን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል።
በወንዶች ውድድር አትሌት ደሶ ገልሚሲ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ፤ አትሌት መሀመድ ኢሳ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል። አትሌት ፀጋዬ ጌታቸው ደግሞ የሶስተኛ ደረጃን ይዞ ፉክክሩን ጨርሷል ።
በሴቶች በተደረገው ውድድር አትሌት ፀሀይ ገመቹ በኬንያዊቷ ሮዝመሪ ዋንጂሩ ተቀድማ በሁለተኝነት ውድድሯን ስታጠናቅቅ አሸቴ በከሬ ሶስተኛ አትሌት ወርቅነሽ ኢዶሳ ደግሞ በአራተኝነት ውድድራቸውን ፈፅመዋል።
የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ሀብት ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ ተሻግሯል
****************
(ኢ ፕ ድ )
የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ በማንቀሳቀስ በአገሪቱ ምጣኔ ሀብት ዕድገት ላይ ጉልህ ሚና እየተወጡ መሆኑን የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታወቀ፡፡
ቀደም ሲል በኪሣራ ውስጥ የነበሩ የልማት ድርጅቶች ወደ ትርፋማነት ተሸጋግረዋል ተብሏል፡፡ https://www.press.et/?p=93690
****************
(ኢ ፕ ድ )
የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ከአንድ ትሪሊዮን ብር በላይ በማንቀሳቀስ በአገሪቱ ምጣኔ ሀብት ዕድገት ላይ ጉልህ ሚና እየተወጡ መሆኑን የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር አስታወቀ፡፡
ቀደም ሲል በኪሣራ ውስጥ የነበሩ የልማት ድርጅቶች ወደ ትርፋማነት ተሸጋግረዋል ተብሏል፡፡ https://www.press.et/?p=93690
ማህበሩ በ52 ፓርኮች ከ24 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን እየተንከባከበ ነው
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
👉 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እየተዘጋጀ ነው
በ52 ፓርኮች ከ24 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን የኦሮሚያ ልማት ማህበር አስታወቀ፡፡
ማህበሩ በመጪው ክረምት ስድስት ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የዝግጅት ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አስታውቋል፡፡
የኦሮሚያ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ኢቲቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93759
***************
(ኢ.ፕ.ድ)
👉 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እየተዘጋጀ ነው
በ52 ፓርኮች ከ24 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን የኦሮሚያ ልማት ማህበር አስታወቀ፡፡
ማህበሩ በመጪው ክረምት ስድስት ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የዝግጅት ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አስታውቋል፡፡
የኦሮሚያ ልማት ማህበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ኢቲቻ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለፁት...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93759
ስንዴን ወደ ውጭ ገበያ መላክ ጠንካራ ኢኮኖሚን ለመገንባት ዕድል ይሰጣል
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ በስፋት ያለማችውን ስንዴን ኤክስፖርት ማድረግ መጀመሯ ጠንካራ ኢኮኖሚን መገንባት የሚያስችላት ትልቅ ጅማሮ እንደሆነ የምጣኔ ሀብት ምሁር ገለጹ፡፡
በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህርና በ‹‹ፍሮንቲየርአይ (Frontieri)›› ጥናትና አማካሪ ድርጅት ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር ሞላ አለማየሁ ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ አሁን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93762
************
(ኢ.ፕ.ድ)
ኢትዮጵያ በበጋ መስኖ በስፋት ያለማችውን ስንዴን ኤክስፖርት ማድረግ መጀመሯ ጠንካራ ኢኮኖሚን መገንባት የሚያስችላት ትልቅ ጅማሮ እንደሆነ የምጣኔ ሀብት ምሁር ገለጹ፡፡
በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ መምህርና በ‹‹ፍሮንቲየርአይ (Frontieri)›› ጥናትና አማካሪ ድርጅት ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር ሞላ አለማየሁ ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ አሁን...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93762
ክልሉ ለ215 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ ሰጠ
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት ለ215 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አስታወቀ፡፡
የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሐልጌዮ ጂሎ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፣ በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለጠየቁ 215 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጥቷል፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93761
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት ለ215 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል አስታወቀ፡፡
የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሐልጌዮ ጂሎ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፣ በክልሉ ባለፉት ስድስት ወራት የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለጠየቁ 215 ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ ተሰጥቷል፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93761
አዲስ አበባ በቀን 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ቢያስፈልጋትም እያመረተች ያለችው 725 ሺህ ብቻ ነው
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ በቀን ከሚያስፈልገው አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ አሁን ላይ እየተመረተ ያለው 725ሺህ ሜትር ኪዩብ ብቻ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ::
በ570 ሚሊዮን ብር በጀት ተጨማሪ 75ሺህ ሜትር ኪዩብ ውሃ እየለማ እንዳለ ተገልጿል::
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93752
*************
(ኢ.ፕ.ድ)
በአዲስ አበባ ከተማ በቀን ከሚያስፈልገው አንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ አሁን ላይ እየተመረተ ያለው 725ሺህ ሜትር ኪዩብ ብቻ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን አስታወቀ::
በ570 ሚሊዮን ብር በጀት ተጨማሪ 75ሺህ ሜትር ኪዩብ ውሃ እየለማ እንዳለ ተገልጿል::
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93752
ብሔራዊ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮች ላይ የሚመክር ጉባኤ እየተካሄደ ነው
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ብሔራዊ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮች ላይ የሚመክር ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
በፍትህ ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተካሄደ በሚገኘው የምክክር መድረክ ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሠብሳቢ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፣ ሚኒስትሮችና የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት ጊዜያት በነበሩ ግጭቶች የተፈጠሩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በሕግ ለመፍታት ተገቢው ትኩረት ባለመሰጠቱ የበዳይ ተበዳይ ትርክትና ቁርሾ ተበራክቷል ብለዋል።
በተለያዩ ጊዜያት የተፈጸሙ ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችንና ቁርሾዎችን አግባብነት ባለው መልኩ ለመፍታት ብሔራዊ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አስፈላጊ በመሆኑ ለውጤታማነቱ መስራት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
ግጭት ወቅት የተከሰቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተገቢው መንገድ ለመፍታት በሀገራችን ብሔራዊ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን ሲሉም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተናገሩት።
በጌትነት ተስፋማርያም
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
ብሔራዊ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አማራጮች ላይ የሚመክር ጉባኤ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ይገኛል።
በፍትህ ሚኒስቴር አስተባባሪነት እየተካሄደ በሚገኘው የምክክር መድረክ ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሠብሳቢ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ፣ ሚኒስትሮችና የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት ጊዜያት በነበሩ ግጭቶች የተፈጠሩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በሕግ ለመፍታት ተገቢው ትኩረት ባለመሰጠቱ የበዳይ ተበዳይ ትርክትና ቁርሾ ተበራክቷል ብለዋል።
በተለያዩ ጊዜያት የተፈጸሙ ጉልህ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችንና ቁርሾዎችን አግባብነት ባለው መልኩ ለመፍታት ብሔራዊ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ አስፈላጊ በመሆኑ ለውጤታማነቱ መስራት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
ግጭት ወቅት የተከሰቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በተገቢው መንገድ ለመፍታት በሀገራችን ብሔራዊ የሽግግር ፍትህ ፖሊሲ የሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ነን ሲሉም ነው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተናገሩት።
በጌትነት ተስፋማርያም