#ዓድዋ_127‼️
የዓድዋ ድል በዓል በዓድዋ ከተማ በሶሎዳ ተራራ ስር እየተከበረ ነው
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
127ኛው የዓድዋ ድል በዓል በዓድዋ ከተማ በሶሎዳ ተራራ ስር እየተከበረ ነው።
በበዓሉ ላይ ህፃናት ስለ ዓድዋ ድል የሚተርክ ህብረ ዝማሬ አቅርበዋል።
የከተማው ነዋሪዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በዓሉን ለመታደም ማልደው በሥፍራው ተገኝተዋል።
በጌትነት ምህረቴ (ዓድዋ)
የዓድዋ ድል በዓል በዓድዋ ከተማ በሶሎዳ ተራራ ስር እየተከበረ ነው
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
127ኛው የዓድዋ ድል በዓል በዓድዋ ከተማ በሶሎዳ ተራራ ስር እየተከበረ ነው።
በበዓሉ ላይ ህፃናት ስለ ዓድዋ ድል የሚተርክ ህብረ ዝማሬ አቅርበዋል።
የከተማው ነዋሪዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በዓሉን ለመታደም ማልደው በሥፍራው ተገኝተዋል።
በጌትነት ምህረቴ (ዓድዋ)
#ዓድዋ_127
127ኛው የዓድዋ ድል በዓል በመስቀል አደባባይ "አንድነት ጀግንነት እና ፅናት" በሚል መሪ ሃሳብ በከፍተኛ ድምቀት እየተከበረ ነው።
በበዓሉ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት፣ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት አመራሮች፣ አርበኞች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ተማሪዎች እንዲሁም ከተለያዩ አከባቢዎች የመጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ታድመዋል።
መርሃ ግብሩ በመከላከያ ሰራዊት የማርች ባንድ ታጅቦ እየተከናወነ ነው።
በመክሊት ወንደወሰን
127ኛው የዓድዋ ድል በዓል በመስቀል አደባባይ "አንድነት ጀግንነት እና ፅናት" በሚል መሪ ሃሳብ በከፍተኛ ድምቀት እየተከበረ ነው።
በበዓሉ ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት፣ የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት አመራሮች፣ አርበኞች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ተማሪዎች እንዲሁም ከተለያዩ አከባቢዎች የመጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ታድመዋል።
መርሃ ግብሩ በመከላከያ ሰራዊት የማርች ባንድ ታጅቦ እየተከናወነ ነው።
በመክሊት ወንደወሰን
#ዓድዋ_127‼️
የአድዋ ድል በዓል አከባበር በአድዋ ድልድይ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
127ኛው የአድዋ ድል በዓል በአድዋ ድልድይ በድመቀት እየተከበረ ነው።
በክብር በዓሉ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የትምህርትና ስልጠና መመሪያ ሀላፊ ብርጋዴር ጀነራል ሙልጌታ አምባቸው እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያውያን ባህር አቋርጦ የመጣውን የጠላት ጦር ተጋፍጦ ለማሸነፍ ተማምለው ቃል የተገባቡበት ስፍራ ነው ብለዋል። የ
አድዋ ታሪክ የተፀነሰበት ቦታ እንደሆነም አስታውሰዋል።
በስፍራውም ጀግናው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ወታደራዊ ሰልፍ ያሳየ ሲሆን፤ ከተለያዩ ክፍለ ከተሞች አድዋን የሚገልጹና ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት መሆኑዋን አመላካች መፈክሮችን በመያዝ ለበዓሉ ድምቀት ሰጥተዋል።
127ኛው የአድዋ ድል በዓል" አንድነት፣ ጀግንነት እና ጽናት" በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በመከበር ላይ ይገኛል።
በቃልኪዳን አሳዬ
የአድዋ ድል በዓል አከባበር በአድዋ ድልድይ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
127ኛው የአድዋ ድል በዓል በአድዋ ድልድይ በድመቀት እየተከበረ ነው።
በክብር በዓሉ ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የትምህርትና ስልጠና መመሪያ ሀላፊ ብርጋዴር ጀነራል ሙልጌታ አምባቸው እንደተናገሩት፤ ኢትዮጵያውያን ባህር አቋርጦ የመጣውን የጠላት ጦር ተጋፍጦ ለማሸነፍ ተማምለው ቃል የተገባቡበት ስፍራ ነው ብለዋል። የ
አድዋ ታሪክ የተፀነሰበት ቦታ እንደሆነም አስታውሰዋል።
በስፍራውም ጀግናው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ወታደራዊ ሰልፍ ያሳየ ሲሆን፤ ከተለያዩ ክፍለ ከተሞች አድዋን የሚገልጹና ኢትዮጵያ የአፍሪካ የነፃነት ተምሳሌት መሆኑዋን አመላካች መፈክሮችን በመያዝ ለበዓሉ ድምቀት ሰጥተዋል።
127ኛው የአድዋ ድል በዓል" አንድነት፣ ጀግንነት እና ጽናት" በሚል መሪ ቃል በመላው ኢትዮጵያ በመከበር ላይ ይገኛል።
በቃልኪዳን አሳዬ