የአድዋ ሙዚየም ፕሮጀክት አፈጻጸም 78 ነጥብ ሁለት በመቶ ደርሷል
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽህፈት ቤት በአድዋ ሙዚየም ፕሮጀክት አፈጻጸም ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል።
የፕሮጀክቶች ግንባታ ጽህፈት ቤት ኮንትራት አስተዳደር ዳሬክተር ዳዊት ጥበቡ (ኢንጅነር) በመግላጫው እንዳሉት፣ ፕሮጅክቱ የአድዋን ድል ታሪካዊ ዳራ መነሻ አድርጐ እየተገነባ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ፊዚካል አፈጻጸም 78 ነጥብ ሁለት በመቶ ደርሷል።
አድዋን በሰፊው የሚገልጽና የተለያዩ የአገሪቱ ካባቢዎችን መነሻ (ዜሮ ዜሮ ) ኪሎ ሜትርን እንደ ምልክት የሚጠቀመው ፕሮጀክቱ ከታሪካዊ መነሻው ባሻገር እንደ ሲኒማ፣ የትራንስፖርት ተርሚናል፣ ካፍቴሪያና አዳራሶችን እንዲሁም የተለያዩ መዝናኛዎችን ያቀፈ መሆኑን ኢንጂነር ዳዊት ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ለበርካታ ዜጐች የስራ እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
ግንባታው በሚቀጥለው አመት ጥቅምት ወር ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ አገልግሎት እንደሚጀመር ተጠቅሷል።
በአዲሱ ገረመው
******************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግዙፍ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽህፈት ቤት በአድዋ ሙዚየም ፕሮጀክት አፈጻጸም ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል።
የፕሮጀክቶች ግንባታ ጽህፈት ቤት ኮንትራት አስተዳደር ዳሬክተር ዳዊት ጥበቡ (ኢንጅነር) በመግላጫው እንዳሉት፣ ፕሮጅክቱ የአድዋን ድል ታሪካዊ ዳራ መነሻ አድርጐ እየተገነባ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ፊዚካል አፈጻጸም 78 ነጥብ ሁለት በመቶ ደርሷል።
አድዋን በሰፊው የሚገልጽና የተለያዩ የአገሪቱ ካባቢዎችን መነሻ (ዜሮ ዜሮ ) ኪሎ ሜትርን እንደ ምልክት የሚጠቀመው ፕሮጀክቱ ከታሪካዊ መነሻው ባሻገር እንደ ሲኒማ፣ የትራንስፖርት ተርሚናል፣ ካፍቴሪያና አዳራሶችን እንዲሁም የተለያዩ መዝናኛዎችን ያቀፈ መሆኑን ኢንጂነር ዳዊት ገልጸዋል።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ለበርካታ ዜጐች የስራ እድል መፍጠሩንም ተናግረዋል።
ግንባታው በሚቀጥለው አመት ጥቅምት ወር ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ አገልግሎት እንደሚጀመር ተጠቅሷል።
በአዲሱ ገረመው
የግብርና ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ከቻይና አምባሳደር ዛሆ ዚዩዋን ጋር ተወያዩ
********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ከሆኑት ዛሆ ዚዩዋን ጋር ቻይና የኢትዮጵያን የግብርና ዘርፍ ለማዘመን በምታደርገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ዙሪያ ውይይት አደረጉ፡፡
በኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን እና ምርታማነትን ለማሳደግ በዘርፉ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣ ዘመናዊ የግብርና መሳሪያዎች እና ቴክኖሎጂዎች ድጋፍ ቻይና እንደምታደርግ በውይይታቸው አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የቻይና ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የግብርናው ዘርፍ ላይ ተሰማርተው እንዲሰሩ የሚያችል ስራ እንደሚሰራም በውይይታቸው መገለጹን ከሚኒስቴሩ ያገኘነውመረጃ ያሳያል፡፡
********************
(ኢ.ፕ.ድ)
የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ከሆኑት ዛሆ ዚዩዋን ጋር ቻይና የኢትዮጵያን የግብርና ዘርፍ ለማዘመን በምታደርገው ሁለንተናዊ ድጋፍ ዙሪያ ውይይት አደረጉ፡፡
በኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን እና ምርታማነትን ለማሳደግ በዘርፉ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት፣ ዘመናዊ የግብርና መሳሪያዎች እና ቴክኖሎጂዎች ድጋፍ ቻይና እንደምታደርግ በውይይታቸው አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተፈጠረውን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም የቻይና ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የግብርናው ዘርፍ ላይ ተሰማርተው እንዲሰሩ የሚያችል ስራ እንደሚሰራም በውይይታቸው መገለጹን ከሚኒስቴሩ ያገኘነውመረጃ ያሳያል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቦረና ዞን የድርቅ ተጎጂዎች ያዘጋጀውን ድጋፍ ወደ ስፍራው ላከ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቦረና ዞን የድርቅ ተጎጂዎች ከተለያዩ ተቋማት እና የህብረተሰብ ክፍሎች ያሰባሰበውን ድጋፍ ዛሬ ማለዳ ወደ ስፍራው ላከ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመስቀል አደባባይ ተገኝተው ድጋፉን አስረክበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንዳሉት ድጋፉ ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት እና የህብረተሰብ ክፍሎች መሰባሰቡን ተናግረዋል።
ድጋፉ 250 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መሆኑን ጠቅሰው ድጋፉም በቀጣይ ሁተኛ ዙር እንደሚደረግም አመላክተዋል።
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝዳንት አወሉ አብዲ በዞኑ የተከሰተው ድርቅ በተከታታይ በክልሉ 10 ዞኖች ዝናብ አለመዝነቡን ተከትሎ መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላደረገው ድጋፍም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ምስጋና አቅርበዋል።
በዛሬው እለት በተደረገው ድጋፍ የምግብ፣ የእንስሳት መኖ፣የውሃ ቦቴዎች ይገኙበታል።
በኦሮሚያ ክልል በተከሰተው ድርቅ 4 ነጥብ 3 ሚልዮን ዜጎች ድጋፍ እንደሚሹ ክልሉ ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
**************
(ኢ.ፕ.ድ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለቦረና ዞን የድርቅ ተጎጂዎች ከተለያዩ ተቋማት እና የህብረተሰብ ክፍሎች ያሰባሰበውን ድጋፍ ዛሬ ማለዳ ወደ ስፍራው ላከ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመስቀል አደባባይ ተገኝተው ድጋፉን አስረክበዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንዳሉት ድጋፉ ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት እና የህብረተሰብ ክፍሎች መሰባሰቡን ተናግረዋል።
ድጋፉ 250 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መሆኑን ጠቅሰው ድጋፉም በቀጣይ ሁተኛ ዙር እንደሚደረግም አመላክተዋል።
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ፕሬዝዳንት አወሉ አብዲ በዞኑ የተከሰተው ድርቅ በተከታታይ በክልሉ 10 ዞኖች ዝናብ አለመዝነቡን ተከትሎ መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ ኢዜአ ዘገባ፤ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ላደረገው ድጋፍም ምክትል ፕሬዝዳንቱ ምስጋና አቅርበዋል።
በዛሬው እለት በተደረገው ድጋፍ የምግብ፣ የእንስሳት መኖ፣የውሃ ቦቴዎች ይገኙበታል።
በኦሮሚያ ክልል በተከሰተው ድርቅ 4 ነጥብ 3 ሚልዮን ዜጎች ድጋፍ እንደሚሹ ክልሉ ማስታወቁ የሚታወስ ነው።
“በትግራይ ሽግግር መንግስት የአንድ ፓርቲ የበላይነት እንዳይፈጠርና እንደገና ወደ ችግር እንዳይገባ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል” አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ የቀድሞ የመቀሌ ከተማ ከንቲባ
********************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ በሚመሰረተው የትግራይ ሽግግር መንግስት የአንድ ፓርቲ የበላይነት እንዳይፈጠርና እንደገና ወደ ችግር እንዳይገባ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ የቀድሞ የመቀሌ ከተማ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ ተናገሩ።
በሀገራቸው ጉዳይ ይመለከተናል የሚሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ሲቪክ ማህበራትን እንዲሁም ዲያስፖራውን ሊያካትት እንደሚገባም ገልጸዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93303
********************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ በሚመሰረተው የትግራይ ሽግግር መንግስት የአንድ ፓርቲ የበላይነት እንዳይፈጠርና እንደገና ወደ ችግር እንዳይገባ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ የቀድሞ የመቀሌ ከተማ ከንቲባ አቶ አታኽልቲ ኃይለስላሴ ተናገሩ።
በሀገራቸው ጉዳይ ይመለከተናል የሚሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ ሲቪክ ማህበራትን እንዲሁም ዲያስፖራውን ሊያካትት እንደሚገባም ገልጸዋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93303
ክልሉ በሌማት ቱሩፋት አንድ ሺህ የንብ ቀፎዎችን ለማሠራጨት እየሠራ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
በሌማት ቱሩፋት መርሃ ግብር አንድ ሺህ የንብ ቀፎዎችን ለማሰራጨት እየሠራ መሆኑን የቤኒሻንጉል ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቤኒሻንጉል ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ኸሊፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በክልሉ በተለይ የሌማት ቱሩፋት ከተጀመረ ጀምሮ ከፍተኛ የንብ ማነብ ስራ ለማካሄድ ስራዎች ተጀምረዋል፡፡ የሌማት ቱርፋት ፕሮጀክት ከተጀመረ አንስቶ ከአንድ ሺህ በላይ የንብ ቀፎዎችን ለ10 መንደሮች ለማሰራጨት እቅድ ተይዞ ስራ ተጀምሯል፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93300
****************
(ኢ ፕ ድ)
በሌማት ቱሩፋት መርሃ ግብር አንድ ሺህ የንብ ቀፎዎችን ለማሰራጨት እየሠራ መሆኑን የቤኒሻንጉል ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቤኒሻንጉል ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ባበክር ኸሊፋ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደተናገሩት፤ በክልሉ በተለይ የሌማት ቱሩፋት ከተጀመረ ጀምሮ ከፍተኛ የንብ ማነብ ስራ ለማካሄድ ስራዎች ተጀምረዋል፡፡ የሌማት ቱርፋት ፕሮጀክት ከተጀመረ አንስቶ ከአንድ ሺህ በላይ የንብ ቀፎዎችን ለ10 መንደሮች ለማሰራጨት እቅድ ተይዞ ስራ ተጀምሯል፡፡
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93300
ባንኮቹ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ የማህበረሰቡን እኩል ተሳታፊነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ናቸው
************
(ኢ ፕ ድ)
ከወለድ ነጻ ባንኮች ማህበረሰቡ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ እኩል ተሳታፊ እንዲሆን ያላቸው ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ተገለጸ።
የሂጅራ ባንክ የሸሪያ ቦርድ አማካሪና ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ከወለድ ነጻ ባንኮች ከወለድ ነጻ የሆነ አገልግሎት የሚፈልጉ የማህበረሰብ ክፍሎች በፋይናንስ ዘርፉ እኩል ተሳታፊ እንዲሆኑ ያደርጋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93309
************
(ኢ ፕ ድ)
ከወለድ ነጻ ባንኮች ማህበረሰቡ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ እኩል ተሳታፊ እንዲሆን ያላቸው ሚና ከፍተኛ እንደሆነ ተገለጸ።
የሂጅራ ባንክ የሸሪያ ቦርድ አማካሪና ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ከወለድ ነጻ ባንኮች ከወለድ ነጻ የሆነ አገልግሎት የሚፈልጉ የማህበረሰብ ክፍሎች በፋይናንስ ዘርፉ እኩል ተሳታፊ እንዲሆኑ ያደርጋል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93309
ለ30 ሺህ ዜጎች ነጻ የዓይን ህክምና አገልግሎት ሊሰጥ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
በወራቤ፣ በጅማ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ 30 ሺህ ዜጎች ከፓኪስታን የሚመጡ ዜጎች ነጻ የዓይን ሕክምና ሊሰጡ መሆኑ ተገለጸ።
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና ያሲን ፋውንዴሽን በትናንትናው ዕለት በሰጡት የጋራ መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በወራቤ፣ በጅማ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ 30 ሺህ ዜጎች ነፃ የዓይን ሕክምና ከፓኪስታን በሚመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ይሰጣል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93308
****************
(ኢ ፕ ድ)
በወራቤ፣ በጅማ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ 30 ሺህ ዜጎች ከፓኪስታን የሚመጡ ዜጎች ነጻ የዓይን ሕክምና ሊሰጡ መሆኑ ተገለጸ።
የአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና ያሲን ፋውንዴሽን በትናንትናው ዕለት በሰጡት የጋራ መግለጫ እንዳስታወቁት፤ በወራቤ፣ በጅማ እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ 30 ሺህ ዜጎች ነፃ የዓይን ሕክምና ከፓኪስታን በሚመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ይሰጣል።
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=93308