Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
‹‹ለእውነተኛ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን ተገድለዋል›› ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ለእውነተኛ የህዝብ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን በበረሀ የትጥቅ ትግል ወቅት መገደላቸውን የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ህዝባችንን ከዚህ ማፍያ ቡድን እንታደገው ሲሉም ጥሪ አቀረቡ፡፡
አቶ ሊላይ ሃይለማርያም በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ የበረሀ ትግል ሲጀመር ትግሉን የተቀላቀሉ ኃይሎች ሁለት ባህሪ ነበራቸው፡፡ አንደኛው የህዝቡን እውነተኛ ጥያቄ ይዞ ለመታገል የገባ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከህዝብ ጥያቄ ይልቅ ስውር የሆነ ተልእኮ አንግቦ የተቀላቀለ ነው፡፡ ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=36166
‹‹ለእውነተኛ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን ተገድለዋል›› ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ለእውነተኛ የህዝብ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን በበረሀ የትጥቅ ትግል ወቅት መገደላቸውን የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ህዝባችንን ከዚህ ማፍያ ቡድን እንታደገው ሲሉም ጥሪ አቀረቡ፡፡
አቶ ሊላይ ሃይለማርያም በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ የበረሀ ትግል ሲጀመር ትግሉን የተቀላቀሉ ኃይሎች ሁለት ባህሪ ነበራቸው፡፡ አንደኛው የህዝቡን እውነተኛ ጥያቄ ይዞ ለመታገል የገባ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከህዝብ ጥያቄ ይልቅ ስውር የሆነ ተልእኮ አንግቦ የተቀላቀለ ነው፡፡
1968 ዓ.ም ጥቅምት ወር ሕወሃትን እንደተቀላቀሉ ያስታወሱት አቶ ሊላይ፣ ገሰሰ አየለ፣ ሙሴ ወደ በረሀ የገቡት ለእውነተኛ የህዝብ ትግል እንደነበር አመልክተዋል። እነዚህ የትግሉ መስራቾች ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ እንደነበራቸውም አስታውቀዋል።
ገሰሰ አየለ፣የትግራይ መገንጠል የሚባለውን እንደማይቀበልና ስህተት መሆኑንም ይናገር እንደነበር አመልክተው፤ የስብሓት ነጋ እና የአባይ ፀሃየ ቡድን ይህ ስላልጣመው የውጪ ግንኙነት እንዲሰራ በሚል በሱዳን በኩል እንዲወጣ ተደርጎ በመንገድ በነሱ አጃቢዎች ሆነ ተብሎ መገደሉን ጠቁመዋል፡፡
ገሰሰ፣ ደደቢት በረሀ ሲሄዱ የተሻለ ኢኮኖሚ፣ መሳሪያና የተሻለ ህዝባዊ ድጋፍ እንደነበረው ጠቅሰው፤ የገሰሰ ወደ በርሀ መግባት አብዛኞቹ የሽሬ ልጆች ለትግል እንዲነሳሱ የሞራል አቅም ፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል። በርካታ የሽሬ ልጆች ወደ ትግሉ መቀላቀላቸው ያስደነገጣቸው አቶ ስብሓት ነጋ፣ ‹‹ገሰሰ ፊውዳል ነው›› ብለው የስም ማጥፋት ዘመቻ እንደጀመረቡትም ተናግረዋል።
እየመጣ የአመራሩን ስፍራ በስፋት እንደተቆጣጠረው አመልክተው፤ ይህ ቡድን የሽሬ ልጆችን ‹‹ሰላይ ናችሁ›› በሚል ይገድል እንደነበር ተናግረዋል። በዚህ ሴራም ብዛት ያላቸው የሽሬ ልጆች መገደላቸውን አስታውቀዋል።
በወቅቱ ከኢዲዩ ጋር በተደረገው አስከፊ ጦርነት ብዙ ታጋዮች መሰዋታቸውን ጠቁመው፤ ከኢዲዩ ጋር ወደ ጦርነት ለመግባት ምንም ምክንያት አልነበረም ብለዋል። ችግሩን በውይይት መፈታት ይቻል እንደነበር የገለጹና ውጊያው አያስፈልግም ብለው ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች በወቅቱ እንዲገደሉ ተደርጓል ብለዋል።
ከ1967 እስከ 68 ዓ.ም የሽሬን ልጆች ካጸዱ በኋላ በ1969 ውጊያ የሚመሩ ሰዎች በአቶ ስብሓት ነጋ የቅርብ ዘመዶች መተካት መጀመራቸውን ገልጸዋል። ከዚያም ውጊያዎች መበላሸት መጀመራቸውን ያስተዋሉ ታጋዮች አቅም ያላቸው ሰዎች እያሉ ለምንድን ነው የማይመጥኑ ሰዎች እንዲመሩንና ውጊያ እንዲበላሽ የሚደረገው ሲሉ መጠየቅ መጀመራቸውንም ጠቅሰው፤ጉዳዩ በወቅቱ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ እንደነበርም አስታውሰዋል።
መደመር መጽሐፍ በኦሮምኛ ቋንቋ በድምፅ ተዘጋጅቶ ቀረበ.. https://medemer.et/
የጠፋው ቅርስ በ50 ዓመቱ ተገኘ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ከደብረ ሰላም ወርቻሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በ1962 ዓ.ም ጠፍቶ የነበረው የስንክሳር መጽሐፍ ተገኘ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ ነጋሽ እንዳሉት ከጠፋ ከ50 ዓመታት በኋላ የተገኘው ስንክሳር ከመጋቢት እስከ ነሐሴ የሚነበበውን የመንፈቅ ምንባብ የያዘ ነው፡፡ ስንክሳሩ ከ20 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያለው፡፡
ስንክሳር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የቅዱሳንን እና የጻድቃንን ታሪክ የያዘ ትልቅ ዓመቱን መገልገያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉ የሚዳሰሱ ቅርሶች መካከልም ትልቅ ሀገራዊ ገጽታ እና ሃይማኖታዊ ግልጋሎት ያለው ነው፡፡
ቅርሱ ከጠፋ ጊዜ ጀምሮ የማፈላለግ ሥራ ሲከናወን ቆይቶ ሐምሌ 4/2012 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ደብረ-ገነት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በማዳበሪያ ተጠቅልሎ ጸሎት በሚያደርጉ እናቶች ተገኝቷል፡፡ ሕጋዊ ሂደቱን ተከትሎ ወደ ቦታው መመለሱንም ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ እንዳሉት ዞኑ የበርካታ ታሪካዊ እና ሃይማኖታዊ ቅርሶች መገኛ ቢሆንም ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ስለማይደረግላቸው ለጥፋት እየተዳረጉ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱም ከመንግሥት ጋር በመሆን በሰዎች እጅ የሚገኙ ቅርሶችን እያፈላለገ ነው፡፡ በዚህ ቅርሶች እየተገኙ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በቅርቡም ሁለት ግለሰቦች ቅርስ ተገኝቶባቸው በሕግ ተጠያቂ ተደርገው በእስር ላይ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ነገር ግን ቅርስ በሚዘርፉ እና በሚያጠፉት ላይ የሚወሰደው ርምጃ አስተማሪ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡
ቅርሶችን ለመንከባከብ በርካታ ሥራዎች ቢሠሩም ቅርሶች እየተዘረፉ መሆኑን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታውቋል፡፡ የሕዝቡ ተሳትፎ አናሳ መሆኑ፣ በአጥፊዎች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ጠንካራ አለመሆኑ እና በርካታ ቅርሶች በሰዎች እጅ መገኘታቸው በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡
የመምሪያ ኃላፊዋ ወይዘሮ ሰናይት አስራደው እንዳሉት መንግሥት በቅርሶች ላይ ቁጥጥርና ክትትል እንደሚያደርግ እና አዳዲስ ቅርሶችን እንደሚመዘግብ አስታውቋል፡፡ የተመዘገቡት በየዓመቱ ኦዲት ስለሚደረግባቸው የመጥፋት ዕድላቸው ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ማኅበረሰቡ ይሰረቅብናል በሚል በእጅ ያሉ ቅርሶችን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ አለመሆን ግን ፈተና ሆኖ ቆይቷል፡፡ በሚፈለገው ደረጃ ባይሆንም ግንዛቤ በመፍጠር ብዙ ቅርሶች ከማኅበረሰቡ ተመልሰው ምዝገባ ተደርጎላቸዋልም ብለዋል፡፡
ቀደም ብሎ የተዘረፉ ቅርሶችን የማፈላለግ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም መምሪያ ኃላፊዋ አስታውቀዋል፡፡ የታወቁ ጥንታዊ ቅርሶች ባሉባቸው ቦታዎችም የደብር ሙዚዬም በማሠራት ተገቢው እንክብካቤ ለቅርሶች እንደሚደረጉ ተመላክቷል፡፡
ሥራው በመንግሥት ብቻ ውጤታማ ስለማይሆን ሕዝቡ ቅርሱን ጠንክሮ ሊጠብቅ እንደሚገባም ወይዘሮ ሰናይት መክረዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች በእጃቸው ያሉ ቅርሶችን ለመንግሥት እንዲያሳውቁም ጥሪ አቅርበዋል ሲል የዘገበው አብመድ ነው።
የጠፋው ቅርስ በ50 ዓመቱ ተገኘ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ከደብረ ሰላም ወርቻሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በ1962 ዓ.ም ጠፍቶ የነበረው የስንክሳር መጽሐፍ ተገኘ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ ነጋሽ እንዳሉት ከጠፋ ከ50 ዓመታት በኋላ የተገኘው ስንክሳር ከመጋቢት እስከ ነሐሴ የሚነበበውን የመንፈቅ ምንባብ የያዘ ነው፡፡ ስንክሳሩ ከ20 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያለው፡፡
ስንክሳር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የቅዱሳንን እና የጻድቃንን ታሪክ የያዘ ትልቅ ዓመቱን መገልገያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉ የሚዳሰሱ ቅርሶች መካከልም ትልቅ ሀገራዊ ገጽታ እና ሃይማኖታዊ ግልጋሎት ያለው ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአፍሪካ 100 ስመ ጥር ግለሰቦች መካከል አንዱ ሆኑ
*****
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እ.አ.አ 2020 ላይ በአመራር ክህሎት ባበረከቱት አስተዋጽኦ ከአፍሪካ 100 ስመጥር ግለሰቦች መካከል በግንባር ቀደምትነት ተጠቃሽ ሆነዋል።
በዓለም የታዋቂ ሰዎችን ዝርዝር የሚያወጣው ተቋም /Reputation Poll International/ በተለያዩ ዘርፎች የ100 ስመ ጥር ግለሰቦችን ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በስም ዝርዝሩም 47 ሴቶች እና 53 ወንዶች አፍሪካውያን በአመራር፣ በመዝናኛ፣ በትምህርት፣ በንግድ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎች መመረጣቸው ተነግሯል።
ከእነዚህ መካከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በአመራር ክህሎታቸው በኢትዮጵያ ባመጡት ለውጥ 100 ስመ ጥር ግለሰቦች መካከል ተጠቃሽ ሆነው ተመርጠዋል።
ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያዊቷ ቤተልሔም ጥላሁንን ጨምሮ ሁለት የአፍሪካ ግለሰቦች በቢዝነስ ዘርፍ ከስመ ጥር አፍሪካውያን ዝርዝር ውስጥ መካተታቸውን ሪፑቴሽን ፖል የተሰኘው ድረ ገጽ አስነብቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም በ2012 በጀት አመት 47 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ
የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ ገቢው ከእቅዱ 105 ነጥ ብ 1 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል።
ይህም ከባለፈው አመትም ጋር ሲነጻጸር በ31 ነጥብ 4 በመቶ ብልጫ መኖሩን ጠቁመው ÷ ተቋሙ ከውጭ የስልክ ጥሪ 147 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘቱን ገልጸዋል። ከዚያም ባለፈ 10 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ብድር መመለስ ተችሏልም ነው ያሉት።
የዚምባብዌ ሚኒስትር በኮሮናቫይረስ ሕይወታቸው አለፈ
----------------------------------------------------
የዚምባብዌ የግብርና ሚኒስትር ፔሬንስ ሺሪ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ በኮሮናቫይረስ መሞታቸው የተረጋገጠው በምርመራ መሆኑንም የአገሪቱ መንግሥታዊ ጋዜጣ ሄራልድ ፕሬዚዳንቱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
ሚኒስትሩ የአለም አቀፉ ጤና ድርጅት በሚያዘው በኮሮናቫይረስ ለሞቱ ሰዎች የሚደረገው የቀብር ስነ ስርዓት መመሪያ መሰረት በነገው እለት እንደሚቀበሩም ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
የ65 አመቱ ሚኒስትር በመዲናዋ ሃራሬ በሚገኝ የግል ሆስፒታል ረቡዕ እለት ሕይወታቸው ማለፉ BBC
#አረንጓዴአሻራ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት በመገኘት ከትምህርት ቤቱ ተማሪዎች ጋር ችግኝ ተክለዋል፡፡
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሊት የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ደስታቸውን እየገለጹ ነው
*****************
(ኢ.ፕ.ድ)
በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሊት የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ደስታቸውን እየገለጹ ለግድቡ ያላቸውንም ድጋፍ እየገለጹ ነው።
በከተማዋ የተለያዩ መኖሪያ ሰፈሮች ህዝቡ በየቤቱ በራፍ በመሆን፤ በጋራ መኖሪያ ቤት ያሉ ደግሞ በየብሎኮቻቸው በረንዳ ላይ በመውጣት ድምጻቸውን ከፍ በማድረግ ደስታቸውን ገልጸዋል።
በተመሣሣይም ተሽከርካሪዎች ጡሩንባዎቻቸውን በማሰማት በግድቡ የመጀመሪያ ሙሊት የተሠማቸውን ደስታ እየገለጹ ነው።
በአፍሪካ ህብረት የሚመራውና ለጊዜው ተቋርጦ የነበረው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር ዛሬ ይቀጥላል
**************************
(ኢ ፕ ድ)
በአፍሪካ ህብረት መሪነት ለ11 ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ከሁለት ሳምንታት በፊት እ.አ.አ ሐምሌ 13/2020 የተቋረጠው የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር ዛሬ ከሰአት ይቀጥላል።
ድርድሩ ከሳምንት በፊት ሊቀጥል የነበረ ቢሆንም በሱዳን በኩል በቀረበው ለአንድ ሳምንት የይዘግይልኝ ጥያቄ መሠረት ለአንድ ሳምንት መዘግየቱን የውሃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የሶስትዮሽ ድርድሩ ከዛሬ ከሰዓት ጀምሮ ለቀጣዩ አንድ ሳምንት ይቀጥላል ተብሏል፡፡
የዚህ ሳምንቱ ድርድር ቀደም ሲል ከተካሄደው የ11 ቀናቱ ድርድር በኋላ ለመሪዎች በቀረበው ሰነድ መሠረት መሪዎቹ ባስቀመጠጡት አቅጣጫ የሚቀጥል ሲሆን፤ ኢትዮጵያ እንደ ከዚህ ቀደሙ ፍትሓዊና ምክንያታዊ ተጠቃሚነትን መሠረት ባደረገ ሁኔታ ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ ባደረገ መልኩ ድርድሩን ለመቋጨት ትሠራለች ሲል ሚኒስቴር መስሪያቤቱ አስታውቋል።
ከነሃሴ መጨረሻ ሳምንት በፊት ምንም አይነት የቀጣይ አመት የትምህርት ምዝገባ ማካሄድ የተከለከለ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ
********************************
(ኢ ፕ ድ)
ከነሃሴ መጨረሻ ሳምንት በፊት ምንም አይነት የቀጣይ አመት የትምህርት ምዝገባ ማካሄድ የተከለከለ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች ምዝገባ ለማድረግ ወላጆችን እያስገደዱ መሆኑ እና ምዝገባ በማካሄድ ላይ መሆናቸው ተሰምቷል።
ይህንን በተመለከተም የትምህርት ሚኒስቴር የኮምኒኬሽን ጉዳዬች ዳይሬክተር ወ/ሮ ሐረጓ ማሞ ማንኛውም ትምህርት ቤት ከነሀሴ መጨረሻ በፊት ምንም አይነት ምዝገባ ማካሄድ እንማይቻል እና ይህንን ወሳኔ አልፈው ምዝገባ በሚያካሂዱ ትምህርት ቤቶች ላይም አስፈላጊው የዕርምት እርምጃ እንደሚወሰድ ገልፀዋል።
የምዝገባው የግዜ ሰሌዳ እንዲራዘም የተፈለገው የኮሮና ቫይረስ ስርጭት መስፋፋትን ተከትሎ ወላጆች እና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት የሚያደርጉትን ጉዞ በመግታት የ ቫይረሱን ስርጭት ለመቀነስ መሆኑን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል።
ወላጆች ከተሳሳተ መረጃ እራሳቸውን በመጠበቅ እና የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን በመከላከልእና መንግስት ትምህርት እንዲጀመር ሲያሳውቅ ብቻ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን አውቀው ልጆቻቸውን በእጃቸው ላይ የሚገኙትን የመማሪያ ቁሳቁሶች እንዲያነቡና እንዲያጠኑ ድጋፍ እንዲያደርጉ የትምህርት ሚኒስቴር ጥሪ አቅርቧል።
የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዩም መስፍን "የፌደራል መንግስት፣ ኤርትራ እና አማራ ሊወረን ነው ታገሉ” በማለት የወጅራት ነዋሪዎችን ቢቀሰቅሱም ህዝቡ አሳፍሮ እንደመለሳቸው ተገለጸ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዩም መስፍን "የፌደራል መንግስት፣ ኤርትራ እና አማራ ሊወረን ነው ታገሉ” በማለት የወጅራት ነዋሪዎችን ቢቀሰቅሱም ህዝቡ አሳፍሮ እንደመለሳቸው ተገለጸ።
ትናንት በትግራይ ክልል የወጅራት ልዩ ስሙ ዓዲ ቀይሕ ነዋሪዎች የተካሄደውን ሰላማዊ ሰልፍ ያስተባበሩትና ስማቸው ሊገለጽ ያልፈለጉ ወጣቶች ለዝግጅት ክፍላችን እንደተናገሩት፤ በበቅርቡ የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ስዩም መስፍን የዋጅራት ህዝብን ህዝብ ሰብስበው፤ “ከድሮ ጀምሮ የወጅራት ህዝብ ጀግና ነው፤ አልገዛም ባይ ነው፤ ስለዚህ አሁንም የፌደራል መንግስት፣ ኤርትራ እና አማራ ሊወረን ነው ታገሉ” በማለት ቀስቅሰዋል።
የሰልፉ አስተባባሪዎች እንደገለጹትም፤ አቶ ስዩም የወረዳዋ ነዋሪዎች ያቀረበውን ጥያቄ ለማለባበስና ሌላ ውዥንብር ሊፈጥሩባቸው ቢሞክሩም
ህዝቡ ግን “እኛ የተሰበሰብነው ጥያቄያችን ልትመልሱልን መስሎን እንጂ ከማንም ጋር አንዋጋም በውጊያ ያተረፍነው ነገር የለም፤ ከሁሉም ጋር ተባብረን መልማት ነው የምንፈልገው” በማለት ለአቶ ስዩም መልስ እንደሰጧቸው የሰልፉ አስተባባሪዎች አስታውቀዋል።
ትናንት የተካሄደው ሰልፍም የህወሓት አመራሮች ጥያቄያችንን ከመመለስ ይልቅ የማፈንና ጥያቄውንም የማዳፈን አካሄዳቸው እየበዛ በመምጣቱ መሆኑንም ገልጸዋል።
በሰልፉ ከነበሩ መፈክሮች ውስጥ “ወረዳችን ይመለስልን፤ ለዛችን ባህላችን ይከበርልን፤ ወጣቱ እየተሰደደ ነውና ስራ ይፈጠርልን፤ ለውጥ እንፈልጋለን” የሚሉ እንደሚገኙበት አስተባባሪዎቹ ተናግረዋል።
ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ወረዳችን ይመለስልን የሚል ሰለማዊ ሰልፎች ቢደረጉም መንግስት ይሄን ከመመለስ ይልቅ ሌላ ስም በመለጠፍ እያሸማቃቸው እንደሆነ እነዚህ አስተያየት ሰጪዎቹ ገልጸዋል።
ጥያቄ ያቀረቡ ወጣቶችን እየመረጡ ማሰቃየት እስርና ድብደባም በህዝቡ እየተፈጸመባቸው እንደሆነ የሰልፉ አስተባባሪዎች ሳይገልጹ አላለፉም።
ተቋሙ ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ሀብት መዘረፉን አስታወቀ
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ:- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2012 በጀት ዓመት በአራት ክልሎች የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ በተፈጸመ ዘረፋ ከ35 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ እንደደረሰበት አስታወቀ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ መላኩ ታዬ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደተናገሩት፤ በበጀት ዓመቱ በመላ አገሪቱ በተቋሙ ልዩ ልዩ መሠረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ዝርፊያዎች ተባብሶ መቀጠሉን ጠቁመው፤ በበጀት ዓመቱ በአራት ክልሎች ልዩ ልዩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ በተፈጸመ ዘረፋ ብቻ ተቋሙ 35 ሚሊዮን 621 ሺ 688 ብር ኪሳራ ደርሶበታል።
ዳይሬክተሩ እንዳብራሩት፣ አንድ ትራንስፎርመር በአማካኝ 400 ሺ ብር የሚያወጣ ሲሆን፣ ከ20 እስከ 25 ዓመት አገልግሎት ይሰጣል። እንዲሁም አንዱ ትራንስፎርመር በትንሹ እስከ 200 አባወራዎችን የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ በመላ አገሪቱ በኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መሠረተ ልማቶች ላይ በሚደርሱ ስርቆቶች ተቋሙ አገልግሎቱን ለኅብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ፈታኝ ከማድረጉ ባሻገር በአገሪቱ ለሚታየው የኤሌክትሪክ አገልግሎት መቆራረጥ ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ይናገራሉ።
አቶ መላኩ በበጀት ዓመቱ በኦሮሚያ ክልል 14 ሚሊዮን 130ሺ 314 ብር፣ በአማራ ክልል ሦስት ሚሊዮን 977ሺ ሦስት ብር፣ በአፋር ክልል 514 ሺ 370 ብር በደቡብ 17 ሚሊዮን ብር በድምሩ በአራቱ ክልሎች ልዩ ልዩ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ በተፈጸመ ዘረፋ ብቻ ተቋሙ 35 ሚሊዮን 621 ሺ 688 ብር ኪሳራ እንደደረሰበት ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ተቋሙ በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ዘረፋ የፈጸሙና በኃይል ስርቆት ላይ በተሰማሩ 195 ግለሰቦች ላይ ክስ መመስረቱን ዳይሬክተሩ ጠቁመው፤ በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ላይ ዘረፋ የፈጸሙ 30 ግለሰቦች ከ3 እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት መቀጣታቸውን ተናግረዋል።
አዲስ ዘመን ሐምሌ 30/2012
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞች አነስተኛ ደመወዝ ላላቸው ባልደረቦቻቸው ድጋፍ አደረጉ
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፤ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞች እና አመራሮች በተቋሙ ውስጥ ለሚሰሩና የወር ደመወዛቸው አነስተኛ ለሆኑ የስራ ባልደረቦቻቸው የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ።
“እኛው ለእኛው” በሚል መርህ የተደረገው ይሄው ድጋፍ የተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮች ከወር ደሞዛቸው በመቀነስ ከለገሱት የተገኘ መሆኑን የድርጅቱ ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድም ተክሉ አስታውቀዋል።
እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ፤ ይህ ድጋፍ ትልቅ ስራ ነው ተብሎ የታሰበ አይደለም፤ ነገር ግን በአንድ ተቋም ውስጥ ሊኖር የሚገባውን የእርስ በእርስ መተሳሰብን ለማጠናከር ታስቦ የተደረገና ሌሎች መሰል ተቋማትም ይሄንኑ ተግባር እንዲያከናውኑ ለማነሳሳት ነው።
የዚህ አይነቱ እርስ በእርስ የመተሳሰብና የመረዳዳት ባህልን በተቋም ውስጥ መገንባት ከተቻለ ተቋሙ ሊያሳከው የሚፈልገውን ግብ ከዳር ለማድረስ እንደ አንድ ግብአት የሚረዳ ይሆናል ያሉት አቶ ወንድም፤ በሰራተኞች መካከልም መዋደድና መተሳሰብን የሚፈጥር ነው ብለዋል።
በቀጣይም በተቋሙ የሚታሰበው ትልቁ ስራ እነዚህ ሰራተኞች እራሳቸውን በኢኮኖሚ የሚጠቅሙበትን ሁኔታ ማመቻቸት መሆኑን የጠቆሙት አቶ ወንድም፤ የሰራተኛውን ችግር በቋሚነት ሊፈቱ የሚችሉ ስራዎች በተቋሙ እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
ለሰራተኞቹ የተደረገውን ድጋፍ ያስተባበሩት ወ/ሮ ብርሃኔ ደመቀ እንደተናጉት፤ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በኢትዮጵያ ከተከሰተ ወዲህ በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ አነስተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የኑሮ ጫናው በርትቶባቸዋል፤ ከዚህ አንጻር በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ውስጥ የሚገኙና የወር ገቢያቸው አነስተኛ የሆኑ ሰራተኞችን መደገፍ አስፈላጊ ሆኗል።
ይህንን የተቀደሰ ተግባር ከዳር ለማድረስም የድርጅቱ ሰራተኞችና አመራሮች ከወር ደመወዛቸው የሚቀነስ ገንዘብ በማዋጣት ለ43 የስራ ባልደረቦቻቸው ከጎናቸው መቆማቸውን በተግባር ማሳየት መቻላቸውን ወ/ሮ ብርሃኔ አብራርተዋል።
እንደ ወ/ሮ ብርሃኔ ገለፃ፤ እርስበርስ መረዳዳቱ በጣም አስፈላጊና ፈጣሪም የሚወደው ስራ ስለሆነ ድጋፍ የተደረገላቸውም ብቻ ሳይሆኑ ድጋፍ ያደረጉ ሰራተኞችም ደስተኛ ሆነዋል።
በእለቱ ድጋፍ ከተደረገላቸው ሰራተኞች መካከል የሆኑት ወ/ሮ ፀሀይ ደበሌ እና ወ/ሮ አበበች አስፋው እንደተናገሩት፤ የድርጅቱ ሰራተኞች ይህን መልካም ተግባር አስበው ድጋፍ በማድረጋቸው በእጅጉ ተደስተዋል። ይህ ክፉ ጊዜ እስኪያልፍ ድረስ እርስ በርስ እየተረዳዱ ማለፉን ፈጣሪ የሚወደው ተግባር ነው በሚል የስራ ባልደረቦቻቸው ያደረጉላቸው ድጋፍ ያልጠበቁት በመሆኑ ትልቅ ደስታን ፈጥሮላቸዋል። ለተደረገላቸው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሰራተኞችና አመራሮች ከዚህ በፊትም በተመሳሳይ የወር ደመወዛቸው አነስተኛ ለሆኑ ሰራተኞች ተመሳሳይ ድጋፎችን ማድረጉ ይታወሳል።
አዲስ ዘመን ሐምሌ 30/2012
« የወንጀለኞች ቡድን በአገር ጥቅም ከመደራደር ወደ ኋላ አይልም » - ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ
****************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የለውጡ አመራር ወደ ሥልጣን ከመጣ ማግስት ጀምሮ ወንጀል እየሰራ ያለው የወንጀለኞች ቡድን ወደ ሕግ የሚያቀርበው በመጥፋቱ ሥልጣን ይዞ እንደፈለገው ለመሆን ምንጊዜም በአገር ጥቅም ከመደራደር ወደ ኋላ እንደማይል ተገለጸ፡፡
ሌተናል ጀኔራል ባጫ ደበሌ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር በወቅታዊ አገራዊ ሁኔታ ላይ ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንደገለጹት፤ የለውጡ አመራር ወደ ሥልጣን ከመጣ ማግስት ጀምሮ ወንጀል እየሰራ ያለው የወንጀለኞች ቡድን ወደ ሕግ የሚያቀርበው በመጥፋቱ ሥልጣን ይዞ እንደፈልገው ለመሆን በአገር ጥቅም ከመደራደር ምንጊዜም ወደ ኋላ የሚል አይደለም።ሁሉም ወንጀለኞች የአገርን ጥቅም አሳልፈው አይሰጡም።የአገርን ጥቅም አሳልፈው የሚሸጡ ግን ሁሌም ወንጀለኞች ናቸው፡፡
መፈንቅለ መንግሥት የማድረግ ፍላጎት ያለው ይህ የወንጀለኞች ቡድን የለውጡ መንግሥት ሥልጣን ላይ እንዲቆይ እንደማይፈልግ አመልክተው፤ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው በሚል የደንቆሮዎች ፖሊሲ የአገርን ሉዓላዊነትና ነፃነት ለግብጽ አሳልፈው መስጠት የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያው የውሃ ሙሌት በሚጀመርበት ጊዜ ሀጫሉን በመግደል ለዜጎች ሞትና ለንብረት ውድመት እንዲከሰት ማድረጉን ተናግረዋል።
ይህ የወንጀለኞች ቡድን ኦሮሞና አማራን ማጋጨት በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ መቀልበስ ይቻላል ብሎ እንደሚያምን አመልክተው፤ ለዚህም ሲባል ሀጫሉ እንዲገደል ማድረጉ የቡድኑ የሴራ ፖለቲካ ውጤት መሆኑንም አስረድተዋል።
በሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች የተፈጠሩት የጸጥታ ችግሮች በጸረ ለውጡ ቡድን የተቀነባበሩ መሆናቸውን አውስተው፤ ከሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም በፊት መፈንቀለ መንግሥት ተሞከረ፣ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም ቦምብ ተወረወረ፣ ቡራዮ በተከሰተው ችግር መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ ኮማንዶ ቤተ መንግሥት መግባት፣በጥቅምትና ኅዳር ወራቶች 2011 ዓ.ም አካባቢ በኦሮሚያና በጌዲዮ፣ በኦሮሚያ እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በኦሮሚያና በደቡብ ክልል፣ በአማራ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በአማራና በቅማንት ግጭቶች ተከስተው በርካታ ሰዎች መፈናቀላቸው አመልክተዋል።
እንዲሁም የእስልምና እና የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮችን እንዲጋጩ መደረጉን፣ ቤተ ክርስቲያንና መስኪዶች መቃጠላቸውና ይህ መፈንቅለ መንግሥት መደረግ አለበት ብሎ ሲጎተጉት በነበረውና በተለያየ መንገድ ለውጡን እየመራ ያለ መንግሥት ደካማ ነው፤ ጸጥታ ማስከበር አይችልም የሚለውን ነገር ለማስረገጥ በማሰብም ሴት ልጆችን መጥለፉንና ጠለፍኩ ብሎ መናገር ያልቻለው በሕጋዊነት በአገር ላይ ስለሚኖር መሆኑንም ተናግረዋል።
ጸረ ለውጥ ቡድኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፖለቲካ ተቀባይነት እንዳያገኙ ብዙ ሴራዎች መፈጸሙን አመልክተው፤ ይህ ጸረ ለውጥ ቡድን ህዳሴ ግድብ ተሸጠ አለ፣ ሌላም ሌላም የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ነዛ ያቀደው ግን ሊሳካለት አለመቻሉና ወደፊትም እንደማይሳካት ገልጸዋል፡፡
መንግሥት የወንጀለኛውን ቡድን አባላት የትም ይሁን የትም የገቡበት ገብቶ ይዞ ፍርድ ቤት ማቅረብ አለበት የሚል እምነት እንዳላቸው አመልክተው፤ እስካሁንም መንግሥት በጣም ትዕግስት አድርጓል፤ ትዕግስት ማድረጉ ትክክል ቢሆንም ወንጀል በተለይም ልታልፈው በማይገባ ወንጀል ላይ ትዕግስት ማድረግ የለበትም፤ ምክንያቱም የኔት ወርክ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ማግስት ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ወንጀል የሚፈጸመው በተመሳሳይ ቡድን ነው ብለዋል፡፡
የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በመጥለፍ የተከሰሱ ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ
***************************
በእነ ከሊፋ አብዱረህማን የክስ መዝገብ የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ህዳር 24 እና 25/2012 ዓ.ም በመጥለፍ በሽብር ወንጀል ከተከሰሱት 17 ግለሰቦች መካከል ዘጠኙ በዛሬው ዕለት የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
በሦስት የሽብር ወንጀል የተከሰሱት ተከሳሾቹ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው የተከሰሱበት ወንጀል ተነቦላቸዋል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ተከሳሾቹ በበኩላቸው ለፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት መቃወሚያ በጽሁፍ አቅርበዋል።
ከሳሽ ዐቃቤ ህግ በመቃወሚያው ላይ ምላሽ እንዲሰጥና ትእዛዝ ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ለነሐሴ 25/2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል። EBC
“ቄሮ የለውጥ እንጂ የጥፋት ኃይል አይደለም” - ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ፣ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፡- የኦሮሚያ ክልል ወጣት(ቄሮ) የለውጥ እንጂ የጥፋት ኃይል እንዳልሆነ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ መርዳሳ አስታወቁ፡፡ ለዚህም የታገለለትንና ዋጋ የከፈለበትን ለውጥ ወደኋላ የሚመልሱ አክራሪ ጽንፈኞችን የሁከት ጥሪ በእምቢታ በማክሸፍ የለውጥ ኃይል መሆኑን በድጋሚ በግልጽ ማረጋገጡን አመልክተዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ቄሮ ለውጡን የሕይወት መስዋዕትነት ከፍሎ ያመጣው መሆኑን በማስታወስ ጽንፈኛ ኃይሎች ይህንን ኃይል የከንቱ ፍላጎታቸው ማስፈጸሚያ ለማድረግ የሁከትና የአመጽ ጥሪዎችን በተለያዩ ጊዜያት ቢያስተላልፉለትም ለጥሪያቸው እምቢተኝነቱን በመግለጽ የለውጥ ኃይልነቱን በአደባባይ በተጨባጭ አስመስክሯል ብለዋል፡፡
እንደ ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ ገለጻ፤ አሁን የሚደረጉ የሁከትና የአመጽ ጥሪዎች ባለፈው የተፈጠረውን ችግር ማስቀጠል የሚፈልጉ ኃይሎች ጥሪ ነው፤ ሰዎቹ የቀደመውን ሁከት ያቀነባበሩ ናቸው፡፡ በሕዝብ የተተፉ፣ ሌሎችም በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ የተደረጉ ናቸው፡፡
እነዚህ ኃይሎች አንድ እግራቸውን ኢትዮጵያ ውስጥ፤ አንድ እግራቸውን ደግሞ ውጪ አድርገው የሚጫወቱ መሆናቸውን የጠቆሙት ኮሚሽነሩ፣ ብሔርንና ሃይማኖትን መሰረት ያደረጉ ጥፋቶች እንዲቀጥሉ የሚፈልጉና ይሄንን ለማስፈጸም የሚንቀሳቀሱ እንደሆኑም አስታውቀዋል ።
ከዚህ በፊት ወጣቱ ለለውጥ ሲያደርግ የነበረው እንቅስቃሴ በእነሱ የተፈጠረ አጀንዳ እንደሆነ በማስመሰል እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጠቁመው፣ እነዚህ ሰዎች ዛሬ ላይ የሚያደርጉት ጥሪ እና እንቅስቃሴ፤ ትናንት ወጣቱ ሲያደርገው ከነበረው ትግልና እንቅስቃሴ ጋር በጣም የተለያየ ብቻ ሳይሆን ፈጽሞ የማይገናኝ ሆድና ጀርባ መሆኑን አመልክተዋል ።
ለዚህ እኩይ ተግባራቸው መሳካት እነሱ ቄሮ እያሉ የሚጣሩ ቢሆንም፤ ቄሮ የተፈጠረው ለእኩልነት ነው፣ ለፍትህ ነው የታገለው፤ ሕይወትም የከፈለው ለዚህ ነው ብለዋል ። ለሕዝቦች እኩልነትና ለፍትህ የታገለው ቄሮ ለእኩይ አላማቸው ጆሮውን በመንፈግ በኦሮሚያ ያለው ቄሮ የለውጥ ኃይል እንጂ የጥፋት ኃይል አለመሆኑን አሳይቷቸዋል ሲሉም ተናግረዋል።
ኮሚሽነር ጄኔራል አራርሳ እንደሚሉት፤ ቄሮ የታገለው የኦሮሞን ህዝብ ከሌላ ብሔር ጋር እኩል እንዲኖር፤ እኩል ተጠቃሚ እንዲሆን ነው። ሁሉም ሃይማኖት እኩል እንዲሆንና በእኩል እንዲከበር ነው። ከዚህ በተቃራኒው አንዱ የበላይ፣ ሌላው የበታች እንዲሆን፤ ጨቋኝና ተጨቋኝ እንዲኖር አይደለም።
ከውጪም ከውስጥም ሆነው ለእኩይ አላማ የሚንቀሳቀሱ እነዚህ ኃይሎች ትናንትና ቄሮ ጠይቆና ታግሎ ያመጣው ለውጥ በእነርሱ አጀንዳ እንደተፈጠረ አድርገው ለመሳል የሚያደርጉት ጥረት ከጅምሩም ትክክል አልነበረም፤ አሁን ደግሞ በተጨባጭ ትክክል እንዳልሆነ ከተግባራቸው ተረጋግጧል። ጉዞው ለየቅል መሆኑን ማየት ተችሏል፤ አሁንም መመልከት ይቻላል።
እነዚህ ኃይሎች እየተደረጉ ያሉት ቅስቀሳ ሆነ ጥሪ አገር የሚያጠፉ ነው ፤ ይሄን ለውጥ ወደኋላ እንዲመለስ የሚያደርግ ነው ፤ ይሄን የሚያደርጉ ቅጥረኞች ናቸው፤ ትናንትና እኛ ሞተን ያመጣነውን ለውጥ፣ ያመጣነውን እኩልነት ለመቀየር የሚደረጉ ጥረቶች ናቸው። ይሄን ጥረታቸውን ለማሳካትም በወጣቱ ስም የሚነግዱ መሆናቸውን አመልክተዋል።
“አሁንም የሚደረጉ ጥሪዎች እንዲከሽፉ፤ ሲቀሰቅሱ የነበሩት የጥፋት አጀንዳዎች ተግባራዊ እንዳይሆኑ ያደረገው ወጣቱ ራሱ ነው። በመሆኑም ይሄ ቅስቀሳና ጥሪ የወጣቱ አጀንዳ አይደለም። የጥቂት አክራሪዎች አጀንዳ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ደግሞ ወጣቱ የአክራሪነት ዝንባሌ የለውም። ጥያቄው ለሁሉም ሕዝቦች የእኩልነት፣ የፍትህና የማንነት ጥያቄ እንዲረጋገጥ ነው። ኦሮሚያ ውስጥ ቄሮ ትግል ሲጀምር ለኦሮሞ ብቻ አይደለም፤ ለሁሉም ነው የታገለው። ለሁሉም ነው የሞተው። አሁንም ይሄው አስተሳሰብ ነው ወጣቱ ውስጥ ያለው” ብለዋል ።
አሁን ያለው የብሔር አክራሪነትና የሃይማኖት አክራሪነት ኦሮሚያ ውስጥ ያለው ቄሮ አመለካከት አይደለም። ይሄንን የሚገልጽም አይደለም። አሁን የተደረገው ጥሪ የወደቀውም ከዚህ አንጻር ነው። አጀንዳቸውን የወጣቱ አጀንዳ ማድረግ ያልቻሉትም ከዚህ አንጻር ነው።
አሁን ወጣቱና የጸጥታ ኃይሉ አብሮ እየሰራ ነው። በዚህም በቅርቡ በተፈጠረው ግርግር ምንም ውስጥ የሌሉ ወጣቶች ችግሩን ለማስቀረት ሲሰሩ አካላቸውን ሕይወታቸውን ከፍለዋል። የብሔር ግጭት እንዳይፈጠር፤ የሃይማኖት ግጭት እንዳይፈጠር ከማድረግ አኳያ፤ አሁን እየሆነ ያለው ነገር ክፋት ነው በማለት ከፖሊስ ጎን ሆነው እንደ መንግስት ምንም ኃላፊነት ሳይኖራቸው ሕይወታቸውን የገበሩ ጥቂት እንዳልሆኑ አስታውቀዋል ።
ይሄ ደግሞ ትናንት የታገለለት የፍትህና ለእኩልነትና ዓላማ ወደኋላ እንዳይመለስ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። ሌሎች ጓደኞቻቸው ቀድመው የሞቱለት ዓላማ ወደኋላ እንዳይቀለበስ ለማድረግ እንደሆነ አስታውቀዋል። እዚም እዛም የሚታየውም ጥቂት ቅጥረኞች የሚያደርጉት እንጂ የወጣቱ አጀንዳና ተግባር አይደለም ብለዋል።
ለምሳሌ፣ ድንጋይ የሚያስቀምጡ ቅጥረኛ ኃይሎች አሉ፤ ወያኔም አሰልጥኖ የሚልካቸው ኃይሎች አሉ። እነዚህን ደግሞ ከጸጥታ ኃይሉ በተጓዳኝ ወጣቶች ናቸው ይዘው ለህግ እያቀረቧቸው ያሉት። በዚህም አሁን ኦሮሚያ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሰላም እንደሆነ አስታውቀዋል።
👍1
ከ8ኛና 12ኛ ክፍል ውጭ ላሉ ተማሪዎች የነፃ ዝውውር መደረጉ ትምህርት ጥራት ላይ የሚፈጥረው ችግር እንደማይኖር የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
*************************
የትምህርት ሚኒስቴር ከ8ኛ እና 12 ኛ ክፍል ውጭ ያሉ ተማሪዎች ወደ ቀጣዩ ክፍል ካለፈተና እንዲዛወሩ መወሰኑን ተከትሎ የትምህርት ጥራት ላይ ጥያቄዎች እየተነሱ ነው።
የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ዶ/ር ኢንጂ) የነፃ ዝውውር መደረጉ ተማሪዎች ላይ የሚፈጠረውን ጫና መንግስት እንዲሸከም በማድረግ ከትምህርት ውጭ የቆዩ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ለማድረግ ታስቦ ነው ብለዋል።
አሁን በምንከተለው ስርዓተ ትምህርት የትምህርት ጥራትን ማረጋገጥ አንችልም ያሉት ሚኒስትሩ 2014 ላይ ወደ ተግባር የሚገባ ስረዓተ ትምህርት የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል።
የትምህርት ጥራት ችግርን በዘላቂነት የሚፈታው ይህ ስርዓተ ትምህርት እንጂ ፈተና በመፈተንና ባለመፈተን የሚረጋገት የትምህርት ጥራት አይኖርም ነው ያሉት።
የትምህርት ሚኒስቴር የነፃ ዝውውር ውሳኔን ሲወስን የተለያዩ ሀገራትን ተሞክሮ በመውሰድና በተለያየ ምክንያት
የኮቪድ 19ኝ ወረርሽኝን ተከትሎ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ስለቆዩ በዚያው እንዳይቀሩ ለማድረግ ታስቦም ጭምር ነው።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ትምህርት ሚኒስቴር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተጠቁሟል።
ለ12ኛ ክፍል አይነ ስውራን ተማሪዎች እየተሰጠ ያለው የተስማሚ ቴክኖሎጂ ስልጠና በታሰበለት ደረጃ እየሄደ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
----------------------------------------------------
ሚኒስቴሩ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ሁሉም አይነሰውራን ተማሪዎች በኦንላይን እንዲፈተኑ ለማድረግ በሙሉ አቅም እየተሰራ መሆኑን አስታወቋል።
የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሁሪያ ዓሊ ተማሪዎቹ ፈተናውን በኦንላይን ለመፈተን የሚያስችላቸውን መሰረታዊ እውቀት እየያዙ መሆኑን ተናግረዋል።
ገና ስልጠናው ሳይጀመር ለፈተና ብቁ ሊሆኑ አይችሉም ብሎ መገመት ለተማሪዎቹ ዝቅ ያለ ግምት መስጠት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ በተቻለ መጠን ለፈተና ዝግጁ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል።
እንደ አስፈላጊነቱ አጋዥ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎችም ለመመደብ እቅድ መያዙን አብራርተዋል።
ተማሪዎቹ እንደየ አካባቢያቸው ሁኔታ ከዚህ ቀደም የኮምፒውተር እውቀት ያላቸውና የሌላቸው በመሆናቸው ተመሳሳይ አቀባበል የላቸውም ያሉት የተስማሚ ቴክኖሎጂ ለአይነስውራን በኢትዮጵያ ዳይሬክተርና አሰልጣኝ ታምሩ እውነቱ (ዶ/ር) ይህንን ታሳቢ በማድረግ ተማሪዎችን በመለየት ለፈተና ዝግጁ ለማድረግ ጥረት እያደረግን ነው ብለዋል።
ተማሪዎቹ በበኩላቸው አብዛኞቻችን ከዚህ ቀደም የኮምፒውተር እውቀት ስለሌለን የስልጠናው ጊዜ ቢራዘም የሚል ጥያቄ አንስተዋል።
ከመላ ሃገሪቱ የተውጣጡ 250 ዓይነስውራን ተማሪዎች በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተስማሚ ቴክኖሎጂ ስልጠና እየወሰዱ ነው።
ስልጠናው ለፈተና ዝግጁ ማድረግ ብቻ ሳይሆን በቀጣይ ለሚኖራቸው የስራ ጊዜ ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይታሰባል።
በየካ ክፍለ ከተማ የጎረቤቷን የኤቲኤም ካርድ በመስረቅ ከ5መቶ 80 ሺ ብር በላይ ወጪ አድርጋ ለግል ጥቅሟ ያዋለች ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ ገለፀ፡፡
***
የግልተበዳይ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ እና ወንጀሉን ፈፅማለች የተባለችው ግለሰብ የቅርብ ግንኙነት እና ጉርብትና አላቸው፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮተቤ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል መርማሪ ረዳት ሳጅን እስጢፋኖስ ገ/ታቲዎስ እንደገለፁት ተጠርጣሪዋ ከግል ተበዳይ ጋር ያላትን ቅርበት ተጠቅማ ወደ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ መኝታ ክፍል በመግባት ቁም ሳጥን ውስጥ ተቀምጦ የነበረ የዘመን ባንክ ኤቲኤም ካርድ ከነ ሚስጥር ቁጥሩ ሰርቃ በመውሰድ እና በተለያዩ ጊዜያት ከ5መቶ 80 ሺ ብር በላይ ከባንኩ ወጪ በማድረግ ለግል ጥቅሟ አውላች፡፡
የግል ተበዳይ ከሀገር ውጭ የሚኖሩ መሆናቸውን የገለፁት ተወካያቸው አቶ ወርቁ ለገሰ ወ/ሮ ሰናይ ቦጋለ የኤቲኤም ካርዱን ከባንኩ ከወሰዱበት ጊዜ ጀምሮ ተጠቅመውበት እንደማያውቁ እና ባላወቁት ሁኔታ ገንዘቡ ከባንክ ወጪ መደረጉን ባወቁ ጊዜ ለፖሊስ ማመልከታቸውን የተናገሩ ሲሆን ግለሰቧ የፈፀመችው ተግባር በመተማመን መካከል መልካም ግንኙነትን የሚያጠለሽ ክስተት ሊፈጠር እንደሚችል በመገንዘብ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ያየንበት ነው ብለዋል፡፡
ፖሊስ ከባንኩ ባገኘው መረጃ መሰረት በተጠርጣሪዋ ላይ ክትትል በማድረግ በየካ ክፍለ ከተማ ክልል ውስጥ በቁጥጥር ስር እንዳዋላት እና በአሁኑ ወቅትም ምርመራ እየተጣራባት እንደሚገኝ ያስረዱት ረዳት ሳጅን እስጢፋኖስ ገ/ታቲዎስ የኤቲኤም ካርድ የሚጠቀሙ ግለሰቦች የሚስጥር ቁጥራቸውን ከተቻለ በቃላቸው መዝግበው በመያዝ ወረቀቱን ማስወገድ ይህ ካልተቻለም ሚስጥራዊ ቦታ በማስቀመጥ ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡