በገበያ ስርዓቱ ውስጥ እሴት የማይጨምሩ ተዋንያን ለዋጋ ግሽበቱ መንስኤ ሆነዋል
👉 የዋጋ ግሽበቱን ለማረጋጋት እስከ ፖሊሲ ማሻሻያ የዘለቀ መፍትሄ ይሻል
****************
(ኢ ፕ ድ)
በገበያ ስርዓቱ ውስጥ እሴት የማይጨምሩ በርካታ ተዋንያን መኖራቸውን፣ ዘርፉን በበላይነት የሚመሩና የሚከታተሉ ተቋማት በቂ የክትትልና የዕርምት ዕርምጃ አለመውሰዳቸው ለምግብ ዋጋ ግሽበቱ ምክንያት መሆናቸውን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የዋጋ ግሽበቱን ለማስተካከል እስከፖሊሲ ማሻሻያ የዘለቀ መፍትሄ እንደሚሻም ተጠቁሟል።
“የምግብ ዋጋ ግሽበት መንስኤዎችን እና የወደፊት መፍትኤ አቅጣጫዎችን” በተመለከተ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አምራቾችን፣ የምግብ እጥረት የሚያጠቃቸው አካባቢዎች እና ከተሞችን ማዕከል በማድረግ ያጠናውን ጥናት በትናንትናው እለት ይፋ አድርጓል።
ጥናቱን ያቀረቡት የኢንስቲትዩቱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ምርምር ማዕከል ኃላፊ ዶክተር ታደሰ ኩማ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። በአሁኑ ሰዓት በቂ ትኩረትና ፈጣን ዕርምጃ መውስድ ካልተቻለ ሀገራዊ ስጋት ሆኖ መቀጠሉ አይቀሬ ነው። ለዚህ ደግሞ እስከ ፖሊሲ ማሻሻያ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=90918
👉 የዋጋ ግሽበቱን ለማረጋጋት እስከ ፖሊሲ ማሻሻያ የዘለቀ መፍትሄ ይሻል
****************
(ኢ ፕ ድ)
በገበያ ስርዓቱ ውስጥ እሴት የማይጨምሩ በርካታ ተዋንያን መኖራቸውን፣ ዘርፉን በበላይነት የሚመሩና የሚከታተሉ ተቋማት በቂ የክትትልና የዕርምት ዕርምጃ አለመውሰዳቸው ለምግብ ዋጋ ግሽበቱ ምክንያት መሆናቸውን የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የዋጋ ግሽበቱን ለማስተካከል እስከፖሊሲ ማሻሻያ የዘለቀ መፍትሄ እንደሚሻም ተጠቁሟል።
“የምግብ ዋጋ ግሽበት መንስኤዎችን እና የወደፊት መፍትኤ አቅጣጫዎችን” በተመለከተ የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት አምራቾችን፣ የምግብ እጥረት የሚያጠቃቸው አካባቢዎች እና ከተሞችን ማዕከል በማድረግ ያጠናውን ጥናት በትናንትናው እለት ይፋ አድርጓል።
ጥናቱን ያቀረቡት የኢንስቲትዩቱ የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲ ምርምር ማዕከል ኃላፊ ዶክተር ታደሰ ኩማ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። በአሁኑ ሰዓት በቂ ትኩረትና ፈጣን ዕርምጃ መውስድ ካልተቻለ ሀገራዊ ስጋት ሆኖ መቀጠሉ አይቀሬ ነው። ለዚህ ደግሞ እስከ ፖሊሲ ማሻሻያ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=90918
ከኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት 40 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ ተገኝቷል
*************
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት 39 ነጥብ 83 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤት ሀገራት ማቅረብ መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገለፀ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ እንደሀገር 772 ሚሊዮን 393 ሺህ 74 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ለማድረግ ታቅዶ ሲሠራ ቆይቷል። በስድስት ወራት ውስጥ 706 ሚሊየን 90 ሺህ 38 ኪሎ ዋት ሰዓት ኃይል ኤክስፖርት ማድረግ ተችሏል።
ከገቢ አንፃር ሲታይ ደግሞ የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት በማድረግ ወደ 44 ነጥብ 57 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ዕቅድ ተይዞ እንደነበር እና ማሳካት የተቻለው ወደ 39 ነጥብ 83 ሚሊየን ዶላር መሆኑን ገልጸዋል። በኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ገቢ ለማግኘት ከታቀደው የ11 በመቶና በገንዘብ ሲሰላ ደግሞ የ4 ነጥብ 74 ሚሊየን የዶላር ቅናሽ አሳይቷል ሲሉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለተለያዩ ሀገራት ያደረገው የኤክስፖርት መጠን በተናጠል ሲታይም ወደ ጂቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገው ኪሎ ዋት ሰዓት ኃይል የ21 ነጥብ 47 ሚሊየን ዶላር ገቢ አስገኘቷል፤ ወደ ሱዳን ኤክስፖርት ከተደረገውም የ18 ነጥብ 37 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ ማግኘት መቻሉንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጂቡቲን የኃይል ሽያጭ አፈፃፀም...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=90901
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ‼️
https://twitter.com/PressEthio
*************
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ስድስት ወራት 39 ነጥብ 83 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤት ሀገራት ማቅረብ መቻሉን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ገለፀ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ እንደሀገር 772 ሚሊዮን 393 ሺህ 74 ኪሎ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ለማድረግ ታቅዶ ሲሠራ ቆይቷል። በስድስት ወራት ውስጥ 706 ሚሊየን 90 ሺህ 38 ኪሎ ዋት ሰዓት ኃይል ኤክስፖርት ማድረግ ተችሏል።
ከገቢ አንፃር ሲታይ ደግሞ የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት በማድረግ ወደ 44 ነጥብ 57 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ዕቅድ ተይዞ እንደነበር እና ማሳካት የተቻለው ወደ 39 ነጥብ 83 ሚሊየን ዶላር መሆኑን ገልጸዋል። በኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ገቢ ለማግኘት ከታቀደው የ11 በመቶና በገንዘብ ሲሰላ ደግሞ የ4 ነጥብ 74 ሚሊየን የዶላር ቅናሽ አሳይቷል ሲሉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለተለያዩ ሀገራት ያደረገው የኤክስፖርት መጠን በተናጠል ሲታይም ወደ ጂቡቲ ኤክስፖርት ከተደረገው ኪሎ ዋት ሰዓት ኃይል የ21 ነጥብ 47 ሚሊየን ዶላር ገቢ አስገኘቷል፤ ወደ ሱዳን ኤክስፖርት ከተደረገውም የ18 ነጥብ 37 ሚሊየን ዶላር ሽያጭ ማግኘት መቻሉንም ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።
ዳይሬክተሩ አክለውም፣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጂቡቲን የኃይል ሽያጭ አፈፃፀም...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=90901
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ‼️
https://twitter.com/PressEthio
ኮሚሽኑ ባለፉት ስድስት ወራት 1 ሺህ 544 የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን አስታወቀ
*************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ባለፉት ስድስት ወራት 1ሺህ 544 አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን አስታወቀ። ከተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎችም ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወይዘሮ መሠረት ወልደማርያም እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 2ሺህ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት አቅዶ ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፤ ከሀገርና ከአለም ነባራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ለ1ሺህ 544 ባለሀብቶች አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ አገልግሎት መስጠት ችሏል።
በተመሳሳይ መልኩ በግማሸ ዓመቱ ከኢንቨስትመንት ፈቃድና ፈቃድ ነክ አገልግሎቶች፣ከተለያዩ ድጋፍና ጨረታ 16 ሚሊዮን ለመሰብሰብ አቅዶ 13 ነጥብ 58 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
ኮሚሽኑ በግማሽ ዓመት ውስጥ 16 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቅዶ በተለያዩ ምክንያቶች 13 ነጥብ 58 ሚሊዮን ብር..
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=90909
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ‼️
https://twitter.com/PressEthio
*************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ባለፉት ስድስት ወራት 1ሺህ 544 አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፍቃድ መስጠቱን አስታወቀ። ከተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎችም ከ13 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን ጠቁሟል።
የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወይዘሮ መሠረት ወልደማርያም እንደገለጹት፤ ኮሚሽኑ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 2ሺህ አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ ለመስጠት አቅዶ ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፤ ከሀገርና ከአለም ነባራዊ ችግሮች ጋር ተያይዞ ለ1ሺህ 544 ባለሀብቶች አዳዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ አገልግሎት መስጠት ችሏል።
በተመሳሳይ መልኩ በግማሸ ዓመቱ ከኢንቨስትመንት ፈቃድና ፈቃድ ነክ አገልግሎቶች፣ከተለያዩ ድጋፍና ጨረታ 16 ሚሊዮን ለመሰብሰብ አቅዶ 13 ነጥብ 58 ሚሊዮን ብር ገቢ ማግኘት ተችሏል ብለዋል።
ኮሚሽኑ በግማሽ ዓመት ውስጥ 16 ሚሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት አቅዶ በተለያዩ ምክንያቶች 13 ነጥብ 58 ሚሊዮን ብር..
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=90909
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ‼️
https://twitter.com/PressEthio
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ለስራ ጉብኝት ሱዳን ካርቱም ገብተዋል
***************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ለአንድ ቀን የስራ ጉብኝት ሱዳን ካርቱም ገብተዋል::
የሱዳን ሪፐብሊክ የሽግግር ሉዓላዊነት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጄኔራል አብደል ፈታሕ አል ቡርሃን አቀባበል አድርገውላቸዋል::
***************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው ለአንድ ቀን የስራ ጉብኝት ሱዳን ካርቱም ገብተዋል::
የሱዳን ሪፐብሊክ የሽግግር ሉዓላዊነት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ጄኔራል አብደል ፈታሕ አል ቡርሃን አቀባበል አድርገውላቸዋል::
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በፖለቲካው ሂደት ላይ ከተሠማሩ ከሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያዩ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በፖለቲካው ሂደት ላይ ከተሠማሩ የተለያዩ የሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር እና ከሦስትዮሽ መፍትሔ አፈላላጊ ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ውይይት፣ የኢትዮጵያ ጣልቃ ገብ ያልሆነ መርሕ ለራሷ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ጭምር የሚሠራ መሆኑን በማረጋገጥ የሱዳን ሕዝብና ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገር በቀል መፍትሔዎችን እንዲፈልጉ አበረታቷል ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዘግቧል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ‼️
https://twitter.com/PressEthio
*******************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ በፖለቲካው ሂደት ላይ ከተሠማሩ የተለያዩ የሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር እና ከሦስትዮሽ መፍትሔ አፈላላጊ ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባደረጉት ውይይት፣ የኢትዮጵያ ጣልቃ ገብ ያልሆነ መርሕ ለራሷ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ጭምር የሚሠራ መሆኑን በማረጋገጥ የሱዳን ሕዝብና ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገር በቀል መፍትሔዎችን እንዲፈልጉ አበረታቷል ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዘግቧል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ‼️
https://twitter.com/PressEthio
"የሕዝብን ሕይወት ለማሻሻልና የአገርን እድገት ለማረጋገጥ የሚተጉ ሁሉ እውቅና ይገባቸዋል"
- ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
***************
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብን ሕይወት ለማሻሻልና የአገርን እድገት ለማረጋገጥ የሚተጉ ሁሉ እውቅና እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ።
ፕሬዚዳንቷ የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የዳያስፖራ አደረጃጀቶች በተዘጋጀ የእውቅና መርሃ ግብር ላይ እንደገለጹት፤ እውቅና ጤናማ ፉክክር በመፍጠር የበለጠ ሥራ እንዲሠራ የሚያበረታታ ነው።
በመሆኑም የሕዝብን ሕይወት ለማሻሻልና የአገርን እድገት ለማረጋገጥ የሚተጉ ሁሉ እውቅና ይገባቸዋል ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት በነበረው ችግር በጦር ሜዳ ከመሰለፍ ጀምሮ በየዘርፉ አገርን ለመደገፍ ብዙዎች መትጋታቸውን አስታውሰው፤ ዳያስፖራዎችም በዓለም ፊት ቆመው በመደገፍና በሌሎችም መስኮች ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
እንደ አገር አሁንም በርካታ የቤት ሥራዎች መኖራቸውን ያስታወሱት ፕሬዚዳንቷ፤ አስከፊውን ምዕራፍ በዘላቂነት ዘግተን ኢትዮጵያን የሚመጥናት ቦታ ላይ ለማስቀመጥ በጋራ መቆም ይገባናል ብለዋል።
ዳያስፖራዎች በመልሶ ማቋቋም ጨምሮ በሌሎችም መስኮች የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
በፋንታነሽ ከንዴ
- ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
***************
(ኢ ፕ ድ)
የሕዝብን ሕይወት ለማሻሻልና የአገርን እድገት ለማረጋገጥ የሚተጉ ሁሉ እውቅና እንደሚገባ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ።
ፕሬዚዳንቷ የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የዳያስፖራ አደረጃጀቶች በተዘጋጀ የእውቅና መርሃ ግብር ላይ እንደገለጹት፤ እውቅና ጤናማ ፉክክር በመፍጠር የበለጠ ሥራ እንዲሠራ የሚያበረታታ ነው።
በመሆኑም የሕዝብን ሕይወት ለማሻሻልና የአገርን እድገት ለማረጋገጥ የሚተጉ ሁሉ እውቅና ይገባቸዋል ብለዋል።
ባለፉት ዓመታት በነበረው ችግር በጦር ሜዳ ከመሰለፍ ጀምሮ በየዘርፉ አገርን ለመደገፍ ብዙዎች መትጋታቸውን አስታውሰው፤ ዳያስፖራዎችም በዓለም ፊት ቆመው በመደገፍና በሌሎችም መስኮች ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
እንደ አገር አሁንም በርካታ የቤት ሥራዎች መኖራቸውን ያስታወሱት ፕሬዚዳንቷ፤ አስከፊውን ምዕራፍ በዘላቂነት ዘግተን ኢትዮጵያን የሚመጥናት ቦታ ላይ ለማስቀመጥ በጋራ መቆም ይገባናል ብለዋል።
ዳያስፖራዎች በመልሶ ማቋቋም ጨምሮ በሌሎችም መስኮች የሚያበረክቱትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
በፋንታነሽ ከንዴ