የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት ተጠናቀቀ
**********************************
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የውሃ ሙሌቱ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ክረምቱ ገና ሳይገባደድ የመጀመሪያው ዙር ሙሌቱ በጥቂት ቀናት ሞልቶ መጠናቀቁና መፍሰስ መጀመሩ ለአገሪቱ ትልቅ የድል ምዕራፍ መክፈቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ ላደረገው የኢትዮጵያ ህዝብና በድርድር ሂደት ሙያዊና የዜግነት ህግዴታቸውን ለተወጡት ተደራዳሪዎችም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የአሁኑ ሙሊት በሁለት ተርባይን ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል ምዕራፍ መሆኑን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ የግድቡ ግንባታ ዳር እንዲደርስ በድፕሎማሲውም ሆነ በግንባታው ሂደት ገና ብዙ ሂደት ይቀረዋል ብለዋል።
በመሆኑም ህዝብና መንግስት በተባበረ ጥረት ለአገራዊ ለውጥና ተጠቃሚነት በጋራ መስራታቸውን እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
የግድቡን ህልውና በዘላቂነት ለማረጋገጥም በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
**********************************
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የውሃ ሙሌቱ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ክረምቱ ገና ሳይገባደድ የመጀመሪያው ዙር ሙሌቱ በጥቂት ቀናት ሞልቶ መጠናቀቁና መፍሰስ መጀመሩ ለአገሪቱ ትልቅ የድል ምዕራፍ መክፈቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ ላደረገው የኢትዮጵያ ህዝብና በድርድር ሂደት ሙያዊና የዜግነት ህግዴታቸውን ለተወጡት ተደራዳሪዎችም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የአሁኑ ሙሊት በሁለት ተርባይን ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል ምዕራፍ መሆኑን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ የግድቡ ግንባታ ዳር እንዲደርስ በድፕሎማሲውም ሆነ በግንባታው ሂደት ገና ብዙ ሂደት ይቀረዋል ብለዋል።
በመሆኑም ህዝብና መንግስት በተባበረ ጥረት ለአገራዊ ለውጥና ተጠቃሚነት በጋራ መስራታቸውን እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
የግድቡን ህልውና በዘላቂነት ለማረጋገጥም በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአፋር ሰመራ ችግኝ ተከሉ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን፣ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኝ አዲስ ፓርክ ችግኝ ተክለዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፤ የችግኝ የመትከያው ወቅት አጋማሽ ላይየተደረሰ ሲሆን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሊተከል ከታቀደው 5 ቢሊየን ችግኝ መካከል እስካሁን 2.9 ቢሊየን ችግኞች ተተክለዋል።
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን፣ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኝ አዲስ ፓርክ ችግኝ ተክለዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፤ የችግኝ የመትከያው ወቅት አጋማሽ ላይየተደረሰ ሲሆን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሊተከል ከታቀደው 5 ቢሊየን ችግኝ መካከል እስካሁን 2.9 ቢሊየን ችግኞች ተተክለዋል።
"ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ የላቸውም"- ጄኔራል አደም መሐመድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም
************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ እንደሌላቸው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድ አስታወቁ። የሰራዊቱ ወታደራዊ ቁመና የአገሪቱን ሉዓላዊነት እና የሕዝቡን ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል እንደሆነም አመለከቱ።
ጄኔራል አደም መሐመድ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ከህግ ውጪ ሆኖ፤ በተለይ በሕዝቦች መካከል ቁርሾ በመፍጠር፤ ግጭት በመፍጠር፤ በሃይማኖትና በተለያዩ ምክንያቶች ሰዎች እየተፈረጁ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ እንደማይኖራቸው አስታውቀዋል።
ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ፤ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ፤ ጎሳን ከጎሳ የሚያጋጩ ስራዎች ሆነ ተብለው የሚሰሩ ከሆነ፤ አድገው ወደ ዘር ማጥፋት፣ ወደ እልቂት የሚያመሩ በመሆኑ መንግስት እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቀዋል ። በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ መንግስት እርምጃ መውሰድ ካልቻለ የመንግስትነት ተልዕኮው ምን ሊሆን ይችላል? እንደዚህ አይነት ጥፋቶች አድገው እንደ ሩዋንዳና ሌሎች አገሮች እንደሆኑት የሚጠብቅ ከሆነ ሕገመንግስታዊነቱ በምን ይገለጻል ሲሉም ጠይቀዋል ፡፡
" ግልጽ መሆን ያለበት መንግስትና የመከላከያ ሰራዊት ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ እና አገርን የሚበትንና የሚያዳክም ማንኛውም ህገወጥ የሆኑ ተግባራትን እያየ ዝም አይልም ፡፡ ይህን ማስቆም በህገመንግስቱ የተሰጠው ኃላፊነት ነው ። የሰራዊቱም ተልዕኮ ይሄ ነው፡፡ መንግስትም ቢሆን የሀገርን ሉዓላዊነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ፤ ግዴታም አለበት" ብለዋል ፡፡
የመከላከያ ሰራዊቱ የኢትዮጵያውያን ሰራዊት ነው ፤ተልእኮውም የሚመነጨው ከህገ መንግስቱ እንደሆነ ያመለከቱት ጄኔራል አደም ፣ ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ይወጣል ለዚህም ዝግጁ ነው ብለዋል ። የሰራዊቱ ተልእኮ የሚመነጨው ከህገ መንግስቱ በመሆኑም ተልእኮውን ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ጋር አይይዞ ማየት እንደማያስፈልግ ገልጸዋል ። ህዝቡም እንደዚህ አይነት አስተሳሰቦችን ሊታገል እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የመከላከያ ሰራዊት ኢትዮጵያውያንን እኩል ሊያገለግል የሚችል ተቋም ሆኖ እየተገነባ መሆኑን አመልክተው፣ የጸጥታ ተቋማት የማንም ፓርቲ ዕሴት ወይም ሀብት ሳይሆኑ የኢትዮጵያ ሀብት ናቸው ሲሉም ተናግረዋል፡፡ በአንድ ፓርቲ ፕሮግራም ሊቀረጽና ሊገነባ የማይገባው እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን ዕሴቶች፣ በአገር ሉዓላዊነት፣ ደህንነትና ብሔራዊ ጥቅም ተመስርቶ መገንባት ያለበት ተቋም ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
በሰራዊቱ ውስጥ ለነበሩ በርካታ የሰራዊት የግንባታ ጥያቄዎች ብዙ ኪሳራዎች እንደነበሩ ጠቁመው፤ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ የተቋም ግንባታ ላይ የተቀመጡ አስተሳሰቦችን በግለሰብ ደረጃ አለመቀበል እንደ ኃጢያት ይቆጠር ነበር፡፡ በዚህም የከሰርናቸው ኪሳራዎች አልነበሩም ማለት አይቻልም ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም አንዱን ጠባብ ብለህ ታባርራለህ፤ ወይ ትከስሳለህ፡፡ ወይ አንዱን ትምክህተኛ ብለህ ትጠረጥራለህ፤ ታባርራለህ፤ ወይ ትከስሳለህ ነው ያሉት፡፡
የሰራዊቱም ጥንካሬ ከአንድ ፓርቲ የፖለቲካ ጥንካሬ የሚነሳ መሆን የለበትም፡፡ ከአንድ ፓርቲ የፖለቲካ ጥንካሬ የሚነሳ ከሆነ፤ ፓርቲው ሲጠነክር አብሮ የሚጠነክር ይሆናል፡፡ ሌላውን እያዳከመ የሚኖርም ይሆናል፡፡ ያ ፓርቲ ሲደክም፣ ነገ በሌላ መንገድ ወደ ስልጣን የሚመጣ ኃይል ደግሞ የሚንደውና የሚያፈርሰው መሆን የለበትም:: ይሄ ተቋም የአገር እና የሕዝብ ተቋም ሆኖ በትውልዶች መገንባት መቻል አለበት ብለዋል፡፡
ፓርቲዎች በራሳቸው በሚያደርጉት ጭቅጭቅና ንትርክ ይሄንን ተቋም መጠቀሚያ የሚያደርጉበት ሁኔታ ከተፈጠረ የሆነ ፓርቲ ወደስልጣን በመጣ ቁጥር እየወደቀና እየፈረሰ እንደገና የሚገነባ ይሆናል፡፡ እየፈረሰ እየተገነባ የሚሄድ ተቋም ደግሞ ይህችን ታላቅ አገር አይመጥንም ብለዋል ጄኔራል አደም፡፡
የመከላከያ ሰራዊቱ ከለውጡ በፊትም ሆነ በኋላ የልማት እና የሰላም ጀግና ሆኖ እየተንቀሳቀሰ እንደነበር ያመለከቱት ጄኔራል አደም፤ በዚህ በኩል ትልቅ ዝናና ስም ያለው ሰራዊት ነው፡፡ አሁንም በውስጥም ሆነ በውጪ ያሉ ማንኛውንም የሀገር እና የህዝብ ስጋቶችን በመከላከል ከፍተኛ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በአገር ውስጥ ሰላምና መረጋጋትን በማረጋገጥና በማስከበር ሚናው ከፍተኛ እንደሆነም አስታውቀዋል ፡፡
ህገ መንግስቱ ሰራዊቱ ከፖለቲካ ገለልተኛ መሆን አለበት፤ በፖለቲካ ጉዳዮች እጁን አያስገባም ፣የፖለቲካ አዋላጅም መሆን እንደሌለበት በግልጽ ያስቀመጠ ቢሆንም ቀደም ባለው ጊዜ ሰራዊቱ የሚገነባበት የፖለቲካ ኢንዶክትሪኔሽን ህገ መንግስቱ ካስቀመጠው ከሰራዊቱ ዓላማና የግንባታ መርሆዎች አንጻር በተጻራሪው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ አስተሳሰብ ፤ በአንድ ፖለቲካ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ላይ የሚያተኩርና የሚያጠነጥን እንደነበር አመልክተዋል ።
የተለያዩ ርዕዮተ ዓለም እና አመለካከቶች ያላቸው ፓርቲዎች ህገ መንግስታዊ እውቅና አግኝተው እየተንቀሳቀሱ ባሉበት አገር፤ ሰራዊቱን በአንድ ፓርቲ ፕሮግራም ላይ፣ በአንድ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ላይ መቅረጽና መገንባት ተገቢ እንዳልነበር ጠቁመዋል፡፡
በሪፎርሙ ከተከናወኑ ስራዎች አንዱ እና ትልቁ ሰራዊቱ የሰራዊት ግንባታ ዓላማ እና የሰራዊቱ ተልዕኮ ከየትኛውም የፓርቲ ፕሮግራም ወይም ርዕዮተ ዓለም በላይ እንዲሆን ማድረግ ነው ብለዋል ፡፡
በሪፎርሙ ሰራዊቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ተልእኮ በግልጽ አውቆ ለህገመንግስቱ ብቻ ታማኝ እንዲሆን በሚያስችል አስተሳሰብ እንዲገነባ ተደርጓል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ፣ የሰራዊቱ ህገ መንግስታዊ ተልዕኮ እጅጉን የገዘፈ ፤ከአንድ ፓርቲ ፕሮግራምና ዓላማ በላይ የሆነ ፣ የተከበረ፤ የአገርን ሉዓላዊነት፤ የሕዝብ ደህንነት ላይ መሰረት ያደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል።
"ኢትዮጵያን እኔ ከሌለሁ ትፈርሳለች ወይም እኔ ካልተጠቀምኩ እናፍርሳት የሚለው አካል ሁል ጊዜ ቢናገርም፤ በእኔ በኩል ኢትዮጵያን የምትፈርሰው መጀመሪያ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ላይ የሚያምኑት ሕዝቦቿ እና መሪዎቿ ከሌሉና ከሌሉ ብቻ ነው ፡፡ ከዛ በላይ ኢትዮጵያ የምትፈርሰው የመከላከያ ኃይላችን፣ የፀጥታ ኃይላችን፣ የደህንነት ኃይላችን ሲፈርስ፤ ወይም እሱ መስዋዕት ሆኖ ሲሸነፍ ብቻ ነው:: ስለዚህ አሁን ያለን የሪፎርም ስራዎች የአገራችንን ገናናነትና ሉዓላዊነት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያደርግ ስርዓት መፍጠር ላይ ያተኮረ ነው፤ የሰራዊት ግንባታውም እንዲሁ ፡፡ በአስተሳሰብም በተግባርም ኢትዮጵያን የበለጠ የሚያጠናክር ስራ ነው እየተሰራ ያለው" ብለዋል፡፡
አዲስ ዘመን ሐምሌ 18/2012
ወንድወሰን ሽመልስ
************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ እንደሌላቸው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድ አስታወቁ። የሰራዊቱ ወታደራዊ ቁመና የአገሪቱን ሉዓላዊነት እና የሕዝቡን ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል እንደሆነም አመለከቱ።
ጄኔራል አደም መሐመድ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ከህግ ውጪ ሆኖ፤ በተለይ በሕዝቦች መካከል ቁርሾ በመፍጠር፤ ግጭት በመፍጠር፤ በሃይማኖትና በተለያዩ ምክንያቶች ሰዎች እየተፈረጁ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ እንደማይኖራቸው አስታውቀዋል።
ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ፤ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ፤ ጎሳን ከጎሳ የሚያጋጩ ስራዎች ሆነ ተብለው የሚሰሩ ከሆነ፤ አድገው ወደ ዘር ማጥፋት፣ ወደ እልቂት የሚያመሩ በመሆኑ መንግስት እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቀዋል ። በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ መንግስት እርምጃ መውሰድ ካልቻለ የመንግስትነት ተልዕኮው ምን ሊሆን ይችላል? እንደዚህ አይነት ጥፋቶች አድገው እንደ ሩዋንዳና ሌሎች አገሮች እንደሆኑት የሚጠብቅ ከሆነ ሕገመንግስታዊነቱ በምን ይገለጻል ሲሉም ጠይቀዋል ፡፡
" ግልጽ መሆን ያለበት መንግስትና የመከላከያ ሰራዊት ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ እና አገርን የሚበትንና የሚያዳክም ማንኛውም ህገወጥ የሆኑ ተግባራትን እያየ ዝም አይልም ፡፡ ይህን ማስቆም በህገመንግስቱ የተሰጠው ኃላፊነት ነው ። የሰራዊቱም ተልዕኮ ይሄ ነው፡፡ መንግስትም ቢሆን የሀገርን ሉዓላዊነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ፤ ግዴታም አለበት" ብለዋል ፡፡
የመከላከያ ሰራዊቱ የኢትዮጵያውያን ሰራዊት ነው ፤ተልእኮውም የሚመነጨው ከህገ መንግስቱ እንደሆነ ያመለከቱት ጄኔራል አደም ፣ ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ይወጣል ለዚህም ዝግጁ ነው ብለዋል ። የሰራዊቱ ተልእኮ የሚመነጨው ከህገ መንግስቱ በመሆኑም ተልእኮውን ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ጋር አይይዞ ማየት እንደማያስፈልግ ገልጸዋል ። ህዝቡም እንደዚህ አይነት አስተሳሰቦችን ሊታገል እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የመከላከያ ሰራዊት ኢትዮጵያውያንን እኩል ሊያገለግል የሚችል ተቋም ሆኖ እየተገነባ መሆኑን አመልክተው፣ የጸጥታ ተቋማት የማንም ፓርቲ ዕሴት ወይም ሀብት ሳይሆኑ የኢትዮጵያ ሀብት ናቸው ሲሉም ተናግረዋል፡፡ በአንድ ፓርቲ ፕሮግራም ሊቀረጽና ሊገነባ የማይገባው እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን ዕሴቶች፣ በአገር ሉዓላዊነት፣ ደህንነትና ብሔራዊ ጥቅም ተመስርቶ መገንባት ያለበት ተቋም ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
በሰራዊቱ ውስጥ ለነበሩ በርካታ የሰራዊት የግንባታ ጥያቄዎች ብዙ ኪሳራዎች እንደነበሩ ጠቁመው፤ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ የተቋም ግንባታ ላይ የተቀመጡ አስተሳሰቦችን በግለሰብ ደረጃ አለመቀበል እንደ ኃጢያት ይቆጠር ነበር፡፡ በዚህም የከሰርናቸው ኪሳራዎች አልነበሩም ማለት አይቻልም ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም አንዱን ጠባብ ብለህ ታባርራለህ፤ ወይ ትከስሳለህ፡፡ ወይ አንዱን ትምክህተኛ ብለህ ትጠረጥራለህ፤ ታባርራለህ፤ ወይ ትከስሳለህ ነው ያሉት፡፡
የሰራዊቱም ጥንካሬ ከአንድ ፓርቲ የፖለቲካ ጥንካሬ የሚነሳ መሆን የለበትም፡፡ ከአንድ ፓርቲ የፖለቲካ ጥንካሬ የሚነሳ ከሆነ፤ ፓርቲው ሲጠነክር አብሮ የሚጠነክር ይሆናል፡፡ ሌላውን እያዳከመ የሚኖርም ይሆናል፡፡ ያ ፓርቲ ሲደክም፣ ነገ በሌላ መንገድ ወደ ስልጣን የሚመጣ ኃይል ደግሞ የሚንደውና የሚያፈርሰው መሆን የለበትም:: ይሄ ተቋም የአገር እና የሕዝብ ተቋም ሆኖ በትውልዶች መገንባት መቻል አለበት ብለዋል፡፡
ፓርቲዎች በራሳቸው በሚያደርጉት ጭቅጭቅና ንትርክ ይሄንን ተቋም መጠቀሚያ የሚያደርጉበት ሁኔታ ከተፈጠረ የሆነ ፓርቲ ወደስልጣን በመጣ ቁጥር እየወደቀና እየፈረሰ እንደገና የሚገነባ ይሆናል፡፡ እየፈረሰ እየተገነባ የሚሄድ ተቋም ደግሞ ይህችን ታላቅ አገር አይመጥንም ብለዋል ጄኔራል አደም፡፡
የመከላከያ ሰራዊቱ ከለውጡ በፊትም ሆነ በኋላ የልማት እና የሰላም ጀግና ሆኖ እየተንቀሳቀሰ እንደነበር ያመለከቱት ጄኔራል አደም፤ በዚህ በኩል ትልቅ ዝናና ስም ያለው ሰራዊት ነው፡፡ አሁንም በውስጥም ሆነ በውጪ ያሉ ማንኛውንም የሀገር እና የህዝብ ስጋቶችን በመከላከል ከፍተኛ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በአገር ውስጥ ሰላምና መረጋጋትን በማረጋገጥና በማስከበር ሚናው ከፍተኛ እንደሆነም አስታውቀዋል ፡፡
ህገ መንግስቱ ሰራዊቱ ከፖለቲካ ገለልተኛ መሆን አለበት፤ በፖለቲካ ጉዳዮች እጁን አያስገባም ፣የፖለቲካ አዋላጅም መሆን እንደሌለበት በግልጽ ያስቀመጠ ቢሆንም ቀደም ባለው ጊዜ ሰራዊቱ የሚገነባበት የፖለቲካ ኢንዶክትሪኔሽን ህገ መንግስቱ ካስቀመጠው ከሰራዊቱ ዓላማና የግንባታ መርሆዎች አንጻር በተጻራሪው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ አስተሳሰብ ፤ በአንድ ፖለቲካ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ላይ የሚያተኩርና የሚያጠነጥን እንደነበር አመልክተዋል ።
የተለያዩ ርዕዮተ ዓለም እና አመለካከቶች ያላቸው ፓርቲዎች ህገ መንግስታዊ እውቅና አግኝተው እየተንቀሳቀሱ ባሉበት አገር፤ ሰራዊቱን በአንድ ፓርቲ ፕሮግራም ላይ፣ በአንድ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ላይ መቅረጽና መገንባት ተገቢ እንዳልነበር ጠቁመዋል፡፡
በሪፎርሙ ከተከናወኑ ስራዎች አንዱ እና ትልቁ ሰራዊቱ የሰራዊት ግንባታ ዓላማ እና የሰራዊቱ ተልዕኮ ከየትኛውም የፓርቲ ፕሮግራም ወይም ርዕዮተ ዓለም በላይ እንዲሆን ማድረግ ነው ብለዋል ፡፡
በሪፎርሙ ሰራዊቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ተልእኮ በግልጽ አውቆ ለህገመንግስቱ ብቻ ታማኝ እንዲሆን በሚያስችል አስተሳሰብ እንዲገነባ ተደርጓል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ፣ የሰራዊቱ ህገ መንግስታዊ ተልዕኮ እጅጉን የገዘፈ ፤ከአንድ ፓርቲ ፕሮግራምና ዓላማ በላይ የሆነ ፣ የተከበረ፤ የአገርን ሉዓላዊነት፤ የሕዝብ ደህንነት ላይ መሰረት ያደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል።
"ኢትዮጵያን እኔ ከሌለሁ ትፈርሳለች ወይም እኔ ካልተጠቀምኩ እናፍርሳት የሚለው አካል ሁል ጊዜ ቢናገርም፤ በእኔ በኩል ኢትዮጵያን የምትፈርሰው መጀመሪያ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ላይ የሚያምኑት ሕዝቦቿ እና መሪዎቿ ከሌሉና ከሌሉ ብቻ ነው ፡፡ ከዛ በላይ ኢትዮጵያ የምትፈርሰው የመከላከያ ኃይላችን፣ የፀጥታ ኃይላችን፣ የደህንነት ኃይላችን ሲፈርስ፤ ወይም እሱ መስዋዕት ሆኖ ሲሸነፍ ብቻ ነው:: ስለዚህ አሁን ያለን የሪፎርም ስራዎች የአገራችንን ገናናነትና ሉዓላዊነት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያደርግ ስርዓት መፍጠር ላይ ያተኮረ ነው፤ የሰራዊት ግንባታውም እንዲሁ ፡፡ በአስተሳሰብም በተግባርም ኢትዮጵያን የበለጠ የሚያጠናክር ስራ ነው እየተሰራ ያለው" ብለዋል፡፡
አዲስ ዘመን ሐምሌ 18/2012
ወንድወሰን ሽመልስ
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 720 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው የ14 ሰዎች ሕይወትም አልፏል
*****************
በኢትዮጵያ 24 ሰዓታት በተደረገ 9 ሺህ 527 የላብራቶሪ ምርመራ 720 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው የ14 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 13 ሺህ 968 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።
በ24 ሰዓታት ዉስጥ ህይወታቸው ያለፈውን 14 ግለሰቦች ጨምሮ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 223 ደርሷል።
በዛሬው እለትም 250 ሰዎች ከበሽታው በማገገማቸው ባጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች 6 ሺህ 216 ደርሷል።
*****************
በኢትዮጵያ 24 ሰዓታት በተደረገ 9 ሺህ 527 የላብራቶሪ ምርመራ 720 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው የ14 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 13 ሺህ 968 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።
በ24 ሰዓታት ዉስጥ ህይወታቸው ያለፈውን 14 ግለሰቦች ጨምሮ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 223 ደርሷል።
በዛሬው እለትም 250 ሰዎች ከበሽታው በማገገማቸው ባጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች 6 ሺህ 216 ደርሷል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል
**********************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል።
የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በዩኒቨርሲቲው 6 ኪሎ ግቢ ራስ መኮንን አዳራሽ እየተከናወነ ነው።
ስርጭቱም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቀጥታ እየተላለፈ ይገኛል።
**********************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል።
የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በዩኒቨርሲቲው 6 ኪሎ ግቢ ራስ መኮንን አዳራሽ እየተከናወነ ነው።
ስርጭቱም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቀጥታ እየተላለፈ ይገኛል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል
**********************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል።
የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በዩኒቨርሲቲው 6 ኪሎ ግቢ ራስ መኮንን አዳራሽ እየተከናወነ ነው።
**********************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል።
የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በዩኒቨርሲቲው 6 ኪሎ ግቢ ራስ መኮንን አዳራሽ እየተከናወነ ነው።
ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ዳግም ወደ ኢትዮጵያ በረራ ጀመሩ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ፡- የኮሮና በሽታ ከተከሰተ በኋላ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የመንገደኞች በረራ አገልግሎት መነቃቃት በማሳየቱ ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ወደ ኢትዮጵያ መብረር መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኤር ናቪጌሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ክብረአብ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ የኮሮና ቫይረስ በሽታ ከተከሰተ በኋላ በርካታ ሀገራት በረራቸውን አቋርጠው ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት ግን በአየር ትራንስፖርት የመንገደኞች በረራ አገልግሎት መነቃቃት በማሳየቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ሰባት ደርሰዋል። በአማካይ በቀን ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገድ አውሮፕላኖች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ላይ ናቸው።
እንደ ኤር ናቪጌሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሽመልስ ገለጻ፤ ኮሮና በሽታ በዓለም ላይ ከተስፋፋ በኋላ በድጋሚ ወደ ኢትዮጵያ መብረር ከጀመሩ አየር መንገዶች መካከል የዱባይ ፣ የቱርክ፣ የኳታር፣ የግብጽ፣ የሱዳን፣የኬንያ እና የጅቡቲ አየር መንገዶች ይገኙበታል። በአሁኑ ወቅትም በአማካይ ሁለት መደበኛ በረራ እና አምስት መደበኛ ያልሆኑ የመንገደኛ አገልግሎት የሚሰጡ አውሮፕላኖች ከውጭ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ እየበረሩ ይገኛሉ።
**********************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ፡- የኮሮና በሽታ ከተከሰተ በኋላ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የመንገደኞች በረራ አገልግሎት መነቃቃት በማሳየቱ ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ወደ ኢትዮጵያ መብረር መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኤር ናቪጌሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ክብረአብ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ የኮሮና ቫይረስ በሽታ ከተከሰተ በኋላ በርካታ ሀገራት በረራቸውን አቋርጠው ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት ግን በአየር ትራንስፖርት የመንገደኞች በረራ አገልግሎት መነቃቃት በማሳየቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ሰባት ደርሰዋል። በአማካይ በቀን ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገድ አውሮፕላኖች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ላይ ናቸው።
እንደ ኤር ናቪጌሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሽመልስ ገለጻ፤ ኮሮና በሽታ በዓለም ላይ ከተስፋፋ በኋላ በድጋሚ ወደ ኢትዮጵያ መብረር ከጀመሩ አየር መንገዶች መካከል የዱባይ ፣ የቱርክ፣ የኳታር፣ የግብጽ፣ የሱዳን፣የኬንያ እና የጅቡቲ አየር መንገዶች ይገኙበታል። በአሁኑ ወቅትም በአማካይ ሁለት መደበኛ በረራ እና አምስት መደበኛ ያልሆኑ የመንገደኛ አገልግሎት የሚሰጡ አውሮፕላኖች ከውጭ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ እየበረሩ ይገኛሉ።
ጨፌ ኦሮሚያ 12ኛ መደበኛ፣ 5ኛ ዓመት 5ኛ የሥራ ዘመን ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ጉባኤው ዛሬ እና ነገ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክር የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ሎሚ በዶ ተናግረዋል፡፡
በሁለት ቀን ውሎው የ2012 ዓ.ም የሥራ አፈፃፀም እንደሚገመግምም ነው የተናገሩት፡፡
በሁለት ቀን ውሎው የ2012 ዓ.ም የሥራ አፈፃፀም እንደሚገመግምም ነው የተናገሩት፡፡
በኮሮና ምክንያት ችግር የደረሰባቸው 30 ሺ 87 ዜጎች ከስደት ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ ፤ በተለያዩ ሀገራት በስደት ላይ የነበሩ እና በኮሮና በሽታ ምክንያት ችግር ውስጥ የወደቁ 30ሺህ 87 ኢትዮጵያውያን ወደሀገር ውስጥ መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ዜጋ ተኮር የመንግስት ፖሊሲ ተግባራዊ በመደረጉ በኮሮና ምክንያት ለችግር የተጋለጡ እና በስደት የነበሩ 30ሺህ 87 ኢትዮጵያውያንን ወደሀገራቸው መመለስ ተችሏል።
በፍቃደኝነት ወደሃገራቸው የተመለሱ ዜጎች በአብዛኛው ከገልፍ እና ከጎረቤት ሀገራት የመጡ ናቸው።
አምባሳደር ዲና እንደገለጹት፤ በተለይ በአረብ ሀገራት እና በጎረቤት ሀገሮች በስደት የነበሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በኮሮና በሽታ ወቅት ስራ በማጣት ጎዳና ላይ ሲወድቁ በየሀገራቱ የሚገኙ ቆንስላዎች ክትትል አድርገዋል። በተለይ በቤይሩት ከስራ ተባረው እና በመንገድ ላይ ተጥለው የነበሩ ኢትዮጵያውያንን በቆንስላው አማካኝነት ድጋፍ በማድረግ በፍቃደኝነት መመለስ ተችሏል።
በዚህ መሰረት ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ከተደረጉ 30ሺ በላይ ዜጎች መካከል ከቤይሩት 656 ዜጎች፤ ከአቡዳቢ 72፤ ከሳዑዲ አረቢያ 3ሺህ 539፣ ከኩዌት ደግሞ 1 ሺህ 23 ዜጎች እንዲሁም በድንበር በኩል ከተለያዩ ጎረቤት ሀገራት 4ሺህ 792 ዜጎች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።
https://www.press.et/Ama/?p=35961
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ ፤ በተለያዩ ሀገራት በስደት ላይ የነበሩ እና በኮሮና በሽታ ምክንያት ችግር ውስጥ የወደቁ 30ሺህ 87 ኢትዮጵያውያን ወደሀገር ውስጥ መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ዜጋ ተኮር የመንግስት ፖሊሲ ተግባራዊ በመደረጉ በኮሮና ምክንያት ለችግር የተጋለጡ እና በስደት የነበሩ 30ሺህ 87 ኢትዮጵያውያንን ወደሀገራቸው መመለስ ተችሏል።
በፍቃደኝነት ወደሃገራቸው የተመለሱ ዜጎች በአብዛኛው ከገልፍ እና ከጎረቤት ሀገራት የመጡ ናቸው።
አምባሳደር ዲና እንደገለጹት፤ በተለይ በአረብ ሀገራት እና በጎረቤት ሀገሮች በስደት የነበሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በኮሮና በሽታ ወቅት ስራ በማጣት ጎዳና ላይ ሲወድቁ በየሀገራቱ የሚገኙ ቆንስላዎች ክትትል አድርገዋል። በተለይ በቤይሩት ከስራ ተባረው እና በመንገድ ላይ ተጥለው የነበሩ ኢትዮጵያውያንን በቆንስላው አማካኝነት ድጋፍ በማድረግ በፍቃደኝነት መመለስ ተችሏል።
በዚህ መሰረት ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ከተደረጉ 30ሺ በላይ ዜጎች መካከል ከቤይሩት 656 ዜጎች፤ ከአቡዳቢ 72፤ ከሳዑዲ አረቢያ 3ሺህ 539፣ ከኩዌት ደግሞ 1 ሺህ 23 ዜጎች እንዲሁም በድንበር በኩል ከተለያዩ ጎረቤት ሀገራት 4ሺህ 792 ዜጎች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።
https://www.press.et/Ama/?p=35961
‹‹ትህነግ የተለያዩ ማንነቶችን ጨፍልቆ አንድ ማንነት ለመገንባት እየጣረ ነው›› አቶ አገዘው ህዳሩ የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት
*****************************
(ኢፕድ)
ህውሃት በትግራይ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ማንነቶችን በመጨፍለቅ አንድ ማንነት ለመገንባት ጥረት እያደረገ መሆኑን የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አገዘው ህዳሩ አስታወቁ፡፡ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ህልፈተ ህይወት በኋላ የህወሃት አፈና መጠናከሩንም ገልጸዋል፡፡
የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አገዘው ህዳሩ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ እንደገለጹት በትግራይ ውስጥ የተለያዩ ማንነቶች ያላቸው የራያ ፤የኩናማ ፤የሳሆ ፤የአገው እና የኢሮብ ሕዝቦች ቢኖሩም ሕውሓት እንደእርሳቸው አባባል ትህነግ ሁሉንም በአንድ ቅርጫት ውስጥ በመጨፍለቅ አንድ ማንነት ለመፍጠር ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የራያ ህዝብ ከታሪክ አንጻር ትስስሩ ሰፊ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ ራያ ከኦሮሞ ማህበረሰብ ፤ከአማራ፤ከአገው ጋር ውህድ ማንነት ያለው ሲሆን በታሪክ ሂደትም የራሱን ማንነትን የፈጠረ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ሆኖም ግን የራያንም ሆነ በትግራይ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ማንነቶችን ባለመቀበል ትህነግ በህዝቦች ላይ የተለያዩ በደሎችን በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡
የራያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የራያ ማህበረሰብ የሚገኝበት አካባቢ በሙሉ እና በራያ ወረዳዎች የህዝቡን ማንነት እንዲገነባ ከምርጫ ቦርድ ፍቃድ የተሰጠው ቢሆንም ፓርቲው በራያ ውስጥ እንዳይንቀሳቀስ በትህነግ በርካታ ማስፈራሪያዎችና ጥቃቶች እየደረሱበት መሆኑን አቶ አገዘው ያስረዳሉ፡፡
የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲንና ሌሎች ትህነግን የሚቃወሙ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ባንዳ የሚል ተቀጽላ በማውጣት የማሸማቀቅ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን የገለጹት አቶ አገዘው በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ 12 ከሚደርሱ ፓርቲዎች ውስጥም የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በግንባር ቀደምትነት ባንዳ ተብሎ መፈረጁንም ጠቁመዋል ፡፡
የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በግንባር ቀደምትነት ባንዳ ተብሎ በህወሃት የተፈረጀበትንም ዋነኛ ምክንያትን አቶ አገዘው ሲስረዱ ‹‹ የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ጠንክሮ ከወጣ ተመሳሳይ የማንነት ጥያቄ ያላቸው የአገው፤የኩናማ፤የሳሆ፤የውጅራትና የኢሮብ ማህበረሰቦች ትግላቸውን ማፋፋማቸው አይቀርም፡፡ስለዚህም የራያን የማንነት ጥያቄ ማፈን እና ጥያቄውንም የሚያነሱትንም እያሳደዱ ማጥፋት በዋነኝነት ትህነግ የሚከተለው ስልት ነው፡፡›› ሲሉ አብራርተዋል፡፡
በራያና አላማጣ ወረዳዎች የሚገኙ ነዋሪዎችን የራያራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ደጋፊዎች ናችሁ በማለት የማንገላታትና በልዩ ልዩ የማሰቃያ መንገዶች ተማረው አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት የፓርቲው ፕሬዚዳንት የራያ ማንነትን የሚያቀነቅኑ ግለሰቦችን አድኖ ከመግደል አንስቶ የማህበረሰቡን ሽማግሌዎችና ታዋቂ ግለሰቦችን ስልታዊ በሆነ መንገድ የመግደልና የማጥፋት ስራዎችን ሀገሪቱን ማስተዳደር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ሲከወን መቆየቱንም አብራርተዋል፡፡
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=35937
*****************************
(ኢፕድ)
ህውሃት በትግራይ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ማንነቶችን በመጨፍለቅ አንድ ማንነት ለመገንባት ጥረት እያደረገ መሆኑን የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አገዘው ህዳሩ አስታወቁ፡፡ከአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ህልፈተ ህይወት በኋላ የህወሃት አፈና መጠናከሩንም ገልጸዋል፡፡
የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት አቶ አገዘው ህዳሩ ከአዲስ ዘመን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ እንደገለጹት በትግራይ ውስጥ የተለያዩ ማንነቶች ያላቸው የራያ ፤የኩናማ ፤የሳሆ ፤የአገው እና የኢሮብ ሕዝቦች ቢኖሩም ሕውሓት እንደእርሳቸው አባባል ትህነግ ሁሉንም በአንድ ቅርጫት ውስጥ በመጨፍለቅ አንድ ማንነት ለመፍጠር ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የራያ ህዝብ ከታሪክ አንጻር ትስስሩ ሰፊ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ ራያ ከኦሮሞ ማህበረሰብ ፤ከአማራ፤ከአገው ጋር ውህድ ማንነት ያለው ሲሆን በታሪክ ሂደትም የራሱን ማንነትን የፈጠረ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ሆኖም ግን የራያንም ሆነ በትግራይ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ማንነቶችን ባለመቀበል ትህነግ በህዝቦች ላይ የተለያዩ በደሎችን በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡
የራያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ የራያ ማህበረሰብ የሚገኝበት አካባቢ በሙሉ እና በራያ ወረዳዎች የህዝቡን ማንነት እንዲገነባ ከምርጫ ቦርድ ፍቃድ የተሰጠው ቢሆንም ፓርቲው በራያ ውስጥ እንዳይንቀሳቀስ በትህነግ በርካታ ማስፈራሪያዎችና ጥቃቶች እየደረሱበት መሆኑን አቶ አገዘው ያስረዳሉ፡፡
የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲንና ሌሎች ትህነግን የሚቃወሙ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ባንዳ የሚል ተቀጽላ በማውጣት የማሸማቀቅ ስራ በመስራት ላይ መሆኑን የገለጹት አቶ አገዘው በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ 12 ከሚደርሱ ፓርቲዎች ውስጥም የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በግንባር ቀደምትነት ባንዳ ተብሎ መፈረጁንም ጠቁመዋል ፡፡
የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በግንባር ቀደምትነት ባንዳ ተብሎ በህወሃት የተፈረጀበትንም ዋነኛ ምክንያትን አቶ አገዘው ሲስረዱ ‹‹ የራያ ራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ጠንክሮ ከወጣ ተመሳሳይ የማንነት ጥያቄ ያላቸው የአገው፤የኩናማ፤የሳሆ፤የውጅራትና የኢሮብ ማህበረሰቦች ትግላቸውን ማፋፋማቸው አይቀርም፡፡ስለዚህም የራያን የማንነት ጥያቄ ማፈን እና ጥያቄውንም የሚያነሱትንም እያሳደዱ ማጥፋት በዋነኝነት ትህነግ የሚከተለው ስልት ነው፡፡›› ሲሉ አብራርተዋል፡፡
በራያና አላማጣ ወረዳዎች የሚገኙ ነዋሪዎችን የራያራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ደጋፊዎች ናችሁ በማለት የማንገላታትና በልዩ ልዩ የማሰቃያ መንገዶች ተማረው አካባቢውን ለቀው እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን የተናገሩት የፓርቲው ፕሬዚዳንት የራያ ማንነትን የሚያቀነቅኑ ግለሰቦችን አድኖ ከመግደል አንስቶ የማህበረሰቡን ሽማግሌዎችና ታዋቂ ግለሰቦችን ስልታዊ በሆነ መንገድ የመግደልና የማጥፋት ስራዎችን ሀገሪቱን ማስተዳደር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ሲከወን መቆየቱንም አብራርተዋል፡፡
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=35937
www.press.et
‹‹ትህነግ የተለያዩ ማንነቶችን ጨፍልቆ አንድ ማንነት ለመገንባት እየጣረ ነው››አቶ አገዘው ህዳሩ የራያራዩማ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ፕሬዚዳንት | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
“የበላይነትን የለመደ እኩል ሁን ስትለው የተዋረደ ይመስለዋል”
አቶ ታዬ ደንደኣ
**********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ ፦አንድ ጊዜ የበላይነትን የለመደ አካል እኩል ሁን ሲባል የተዋረደ ይመስለዋል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ አመለከቱ። የህወሓት ጥገኛ ቡድን በሴራ ፖለቲካ የተካነ ስለመሆኑም የቀደሙ ታሪኮቹ ህያው ምስክሮች እንደሆኑ አስታወቁ ።
አቶ ታዬ ደንደኣ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደገለጹት፤አሁንም ድረስ ምናልባትም በሚዲያዎች እንደሚሰማው ህወሃቶች እኛ በታሪክ ካለን አስተዋጽዖ አንጻር የተለየና የበለጠ ቦታ፤ስልጣንና ኢኮኖሚ ይገባናል ብለው በግልጽም ያነሳሉ። ከዚህ ባለፈም በዚህ አገር ውስጥ በአንድ በኩል የተዘረፉና የተሰረቁ በርካታ ነገሮች አሉ፤ እናም ይሄ ለውጥ መሰረቱን ይዞ በትክክለኛው አቅጣጫ የሚዘልቅ ከሆነ ምናልባትም ነገ ተጠያቂነት ይመጣል የሚል ስጋትም አለባቸው።
እነዚህ ሃይሎች ያለፈውን ትተን እሱ ስለማይጠቅመን መልካም ነገሮችን አጎልብተን የተበላሹትን ለማስተካከል ከዚህ ጀምረን እንስራ፤ የይቅርታ መንገድ እንከተል የሚለውንም ለማመን አልፈለጉም የሚሉት አቶ ታዬ፣ለማመን ያልፈለጉት ደግሞ እነርሱ ስለማይታመኑ ሁሉም እንደዛው ስለሚመስላቸው ነው ብለዋል። እነርሱ በአፋቸው የሚሉት ሌላ፤ በልባቸው የያዙት ሌላ ስለሆነ ሰው በቅንነት በዚህ ደረጃ ነው ለኢትዮጵያ የሚያዋጣው ብሎ ቢነገር ከራሳቸው አንጻር ስለሚመነዝሩት ይሄንንም ሊያምኑ አልቻሉም። እየተጠራጠሩ ነው የመጡት ሲሉ ያብራራሉ።
እንደ አቶ ታዬ ገለጻ፤ሁለተኛው ደግሞ እነርሱ ለዛ ክልልም ሆነ ማህበረሰብ በስሙ ነገዱበት እንጂ ለ27 ዓመታትም ሆነ ዛሬም ድረስ ያ ማህበረሰብ ችግር ውስጥ ነው። እነርሱ የሚሰሩት ለራሳቸው ስለሆነ ይህች ኢትዮጵያ እኛ ካልገዛናት፤ እኛ እንደፈለግን የማናደርጋት ከሆነች “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” አይነት የአህያ ብሂል ኢትዮጵያን ወይ እኛ እንግዛት ካልሆነ ደግሞ ትጥፋ በሚል እየተንቀሳቀሱ ናቸው።
ከዚህ አንጻር መልሶ ስልጣን ለመቆጣጠር ፍላጎት አለ፤ ያ የማይሳካ ከሆነ ደግሞ ኢትዮጵያ እንደ አገር መቀጠል የለባትም፤ እኛ የዛን ክልል ማህበረሰብ ለይተን እንገዛዋለን (እናስተዳድረዋለን ሳይሆን እንገዛዋለን ነው)፤ ሌላው ደግሞ ሀገር ሲቃጠል ዳር ሆነን እናያለን የሚል ስሜት አላቸው።
ይህ ሁሉ የሚሆነውም ለዚሁ ነው። ‹‹የሴራ ፖለቲካ የህወሓት የተካነበት ነው። የሚያውቁት የሚናገሩትም ይሄንኑ ነው። ››ያሉት አቶ ታዬ፣ይህንንም በምሳሌ ሲያብራሩ ደርግ የመሬት ላራሹ ጥያቄን ሲመልስ ሁሉም የኢትዮጵያ አርሶአደሮች በአዎንታ ነው የተቀበሉት መሆኑን ጠቅሰዋል። ‹‹ያንንም ትግራይ ላይም ጭሰኛ የነበሩ ዜጎች መሬት ሲያገኙ ደርግን ተቀብለውታል። ህወሓት መጀመሪያ መጥቶ ሲሰብካቸውም “እኛ መሬት አግኝተናል፤ ከዚህ በኋላ ሌላ አንፈልግም” ሲሏቸው፤ ሲያደርጉ የነበረው የደርግ ልብስ በመልበስ ደርግን መስለው ማታ ማታ እየገረፉና እየገደሉም ጭምር፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ እየመጡ ደርግ ገዳይ ነው፤ ደርግ እንደዚህ ነው፤ ይደፍራል፣ ይገድላል፣ ይገርፋል ብለው ይሰብኳቸው እንደነበር የሚያውቋቸው ይናገራሉ ሲሉ ያብራራሉ።
ከኢህአፓ ጋር የነበረውም ይሄው እንደሆነ ጠቅሰው፣አሲምባ ላይ በሴራ ነው በርካታ ሺዎች የኢህአፓ አባላት እንዲያልቁ የተደረገው ብለዋል።
እንደ አቶ ታዩ ገለጻ፤የሀውዜንም ሁኔታ ሰዎች የሚመለከቱት ያኔ ደርግ ከትግራይ ጥሎ ስለወጣ ከዚህ በኋላ የሰበካችሁን ትግራይን ነጻ እንድናውጣ ነበረ፤ ትግራይ ውስጥ ደርግ የለም፤ ስለዚህ ከዚህ በኋላ አንዘምትም በሚል ወታደሮቻቸው ጥያቄ ሲያነሱ በደርግም ውስጥ ከነበሯቸው ሰዎች ጋር በመቀናጀት በሴራ ያ እልቂት እንዲፈጠር አደረጉ። ከዛም ደርግ ከምንጩ ካልጠፋ በስተቀር እዚህ ሰላም ልናገኝ አንችልም የሚል ሰበካ አመጡ። እናም ከመጀመሪያው አንስቶ በሴራ ነው እዚህ የደረሱት። አሁንም በሴራ እንጂ በትክክለኛ መንገድ በያዝነው አስተሳሰብ ልናሸንፍ እንችላለን ብለው አምነውም አያውቁም።
ይሄ ሴራ ባለፉት 27 ዓመታትም በኦሮሞና በአማራ መካከል በኢህአዴግ ውስጥም በነበሩት ብአዴንና ኦህዴድ ውስጥም፤ ከዛ ውጪም በልሂቃን መካከል መቃቃር እንዲኖር ሆን ተብሎ የተሰራና የተሰላ ስሌት ነበር ያሉት አቶ ታዬ፣ ያ ስሌት ደግሞ አማራና ኦሮሞ ሊታረቅ የማይችል ቅራኔ አላቸው የሚል መሆኑን ገልጸዋል። ይሄንንም በመጽሐፍ ጭምር መጻፋቸውን ፣በሚዲያዎችና በጋዜጣም ብዙ መሰበኩን አቶ ታዬ ጠቅሰዋል።
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=36169
አቶ ታዬ ደንደኣ
**********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ ፦አንድ ጊዜ የበላይነትን የለመደ አካል እኩል ሁን ሲባል የተዋረደ ይመስለዋል ሲሉ የኦሮሚያ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታዬ ደንደኣ አመለከቱ። የህወሓት ጥገኛ ቡድን በሴራ ፖለቲካ የተካነ ስለመሆኑም የቀደሙ ታሪኮቹ ህያው ምስክሮች እንደሆኑ አስታወቁ ።
አቶ ታዬ ደንደኣ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ እንደገለጹት፤አሁንም ድረስ ምናልባትም በሚዲያዎች እንደሚሰማው ህወሃቶች እኛ በታሪክ ካለን አስተዋጽዖ አንጻር የተለየና የበለጠ ቦታ፤ስልጣንና ኢኮኖሚ ይገባናል ብለው በግልጽም ያነሳሉ። ከዚህ ባለፈም በዚህ አገር ውስጥ በአንድ በኩል የተዘረፉና የተሰረቁ በርካታ ነገሮች አሉ፤ እናም ይሄ ለውጥ መሰረቱን ይዞ በትክክለኛው አቅጣጫ የሚዘልቅ ከሆነ ምናልባትም ነገ ተጠያቂነት ይመጣል የሚል ስጋትም አለባቸው።
እነዚህ ሃይሎች ያለፈውን ትተን እሱ ስለማይጠቅመን መልካም ነገሮችን አጎልብተን የተበላሹትን ለማስተካከል ከዚህ ጀምረን እንስራ፤ የይቅርታ መንገድ እንከተል የሚለውንም ለማመን አልፈለጉም የሚሉት አቶ ታዬ፣ለማመን ያልፈለጉት ደግሞ እነርሱ ስለማይታመኑ ሁሉም እንደዛው ስለሚመስላቸው ነው ብለዋል። እነርሱ በአፋቸው የሚሉት ሌላ፤ በልባቸው የያዙት ሌላ ስለሆነ ሰው በቅንነት በዚህ ደረጃ ነው ለኢትዮጵያ የሚያዋጣው ብሎ ቢነገር ከራሳቸው አንጻር ስለሚመነዝሩት ይሄንንም ሊያምኑ አልቻሉም። እየተጠራጠሩ ነው የመጡት ሲሉ ያብራራሉ።
እንደ አቶ ታዬ ገለጻ፤ሁለተኛው ደግሞ እነርሱ ለዛ ክልልም ሆነ ማህበረሰብ በስሙ ነገዱበት እንጂ ለ27 ዓመታትም ሆነ ዛሬም ድረስ ያ ማህበረሰብ ችግር ውስጥ ነው። እነርሱ የሚሰሩት ለራሳቸው ስለሆነ ይህች ኢትዮጵያ እኛ ካልገዛናት፤ እኛ እንደፈለግን የማናደርጋት ከሆነች “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” አይነት የአህያ ብሂል ኢትዮጵያን ወይ እኛ እንግዛት ካልሆነ ደግሞ ትጥፋ በሚል እየተንቀሳቀሱ ናቸው።
ከዚህ አንጻር መልሶ ስልጣን ለመቆጣጠር ፍላጎት አለ፤ ያ የማይሳካ ከሆነ ደግሞ ኢትዮጵያ እንደ አገር መቀጠል የለባትም፤ እኛ የዛን ክልል ማህበረሰብ ለይተን እንገዛዋለን (እናስተዳድረዋለን ሳይሆን እንገዛዋለን ነው)፤ ሌላው ደግሞ ሀገር ሲቃጠል ዳር ሆነን እናያለን የሚል ስሜት አላቸው።
ይህ ሁሉ የሚሆነውም ለዚሁ ነው። ‹‹የሴራ ፖለቲካ የህወሓት የተካነበት ነው። የሚያውቁት የሚናገሩትም ይሄንኑ ነው። ››ያሉት አቶ ታዬ፣ይህንንም በምሳሌ ሲያብራሩ ደርግ የመሬት ላራሹ ጥያቄን ሲመልስ ሁሉም የኢትዮጵያ አርሶአደሮች በአዎንታ ነው የተቀበሉት መሆኑን ጠቅሰዋል። ‹‹ያንንም ትግራይ ላይም ጭሰኛ የነበሩ ዜጎች መሬት ሲያገኙ ደርግን ተቀብለውታል። ህወሓት መጀመሪያ መጥቶ ሲሰብካቸውም “እኛ መሬት አግኝተናል፤ ከዚህ በኋላ ሌላ አንፈልግም” ሲሏቸው፤ ሲያደርጉ የነበረው የደርግ ልብስ በመልበስ ደርግን መስለው ማታ ማታ እየገረፉና እየገደሉም ጭምር፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ እየመጡ ደርግ ገዳይ ነው፤ ደርግ እንደዚህ ነው፤ ይደፍራል፣ ይገድላል፣ ይገርፋል ብለው ይሰብኳቸው እንደነበር የሚያውቋቸው ይናገራሉ ሲሉ ያብራራሉ።
ከኢህአፓ ጋር የነበረውም ይሄው እንደሆነ ጠቅሰው፣አሲምባ ላይ በሴራ ነው በርካታ ሺዎች የኢህአፓ አባላት እንዲያልቁ የተደረገው ብለዋል።
እንደ አቶ ታዩ ገለጻ፤የሀውዜንም ሁኔታ ሰዎች የሚመለከቱት ያኔ ደርግ ከትግራይ ጥሎ ስለወጣ ከዚህ በኋላ የሰበካችሁን ትግራይን ነጻ እንድናውጣ ነበረ፤ ትግራይ ውስጥ ደርግ የለም፤ ስለዚህ ከዚህ በኋላ አንዘምትም በሚል ወታደሮቻቸው ጥያቄ ሲያነሱ በደርግም ውስጥ ከነበሯቸው ሰዎች ጋር በመቀናጀት በሴራ ያ እልቂት እንዲፈጠር አደረጉ። ከዛም ደርግ ከምንጩ ካልጠፋ በስተቀር እዚህ ሰላም ልናገኝ አንችልም የሚል ሰበካ አመጡ። እናም ከመጀመሪያው አንስቶ በሴራ ነው እዚህ የደረሱት። አሁንም በሴራ እንጂ በትክክለኛ መንገድ በያዝነው አስተሳሰብ ልናሸንፍ እንችላለን ብለው አምነውም አያውቁም።
ይሄ ሴራ ባለፉት 27 ዓመታትም በኦሮሞና በአማራ መካከል በኢህአዴግ ውስጥም በነበሩት ብአዴንና ኦህዴድ ውስጥም፤ ከዛ ውጪም በልሂቃን መካከል መቃቃር እንዲኖር ሆን ተብሎ የተሰራና የተሰላ ስሌት ነበር ያሉት አቶ ታዬ፣ ያ ስሌት ደግሞ አማራና ኦሮሞ ሊታረቅ የማይችል ቅራኔ አላቸው የሚል መሆኑን ገልጸዋል። ይሄንንም በመጽሐፍ ጭምር መጻፋቸውን ፣በሚዲያዎችና በጋዜጣም ብዙ መሰበኩን አቶ ታዬ ጠቅሰዋል።
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=36169
‹‹ለእውነተኛ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን ተገድለዋል›› ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ለእውነተኛ የህዝብ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን በበረሀ የትጥቅ ትግል ወቅት መገደላቸውን የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ህዝባችንን ከዚህ ማፍያ ቡድን እንታደገው ሲሉም ጥሪ አቀረቡ፡፡
አቶ ሊላይ ሃይለማርያም በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ የበረሀ ትግል ሲጀመር ትግሉን የተቀላቀሉ ኃይሎች ሁለት ባህሪ ነበራቸው፡፡ አንደኛው የህዝቡን እውነተኛ ጥያቄ ይዞ ለመታገል የገባ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከህዝብ ጥያቄ ይልቅ ስውር የሆነ ተልእኮ አንግቦ የተቀላቀለ ነው፡፡ ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=36166
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ለእውነተኛ የህዝብ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን በበረሀ የትጥቅ ትግል ወቅት መገደላቸውን የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ህዝባችንን ከዚህ ማፍያ ቡድን እንታደገው ሲሉም ጥሪ አቀረቡ፡፡
አቶ ሊላይ ሃይለማርያም በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ የበረሀ ትግል ሲጀመር ትግሉን የተቀላቀሉ ኃይሎች ሁለት ባህሪ ነበራቸው፡፡ አንደኛው የህዝቡን እውነተኛ ጥያቄ ይዞ ለመታገል የገባ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከህዝብ ጥያቄ ይልቅ ስውር የሆነ ተልእኮ አንግቦ የተቀላቀለ ነው፡፡ ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=36166
‹‹ለእውነተኛ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን ተገድለዋል›› ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ለእውነተኛ የህዝብ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን በበረሀ የትጥቅ ትግል ወቅት መገደላቸውን የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ህዝባችንን ከዚህ ማፍያ ቡድን እንታደገው ሲሉም ጥሪ አቀረቡ፡፡
አቶ ሊላይ ሃይለማርያም በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ የበረሀ ትግል ሲጀመር ትግሉን የተቀላቀሉ ኃይሎች ሁለት ባህሪ ነበራቸው፡፡ አንደኛው የህዝቡን እውነተኛ ጥያቄ ይዞ ለመታገል የገባ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከህዝብ ጥያቄ ይልቅ ስውር የሆነ ተልእኮ አንግቦ የተቀላቀለ ነው፡፡
1968 ዓ.ም ጥቅምት ወር ሕወሃትን እንደተቀላቀሉ ያስታወሱት አቶ ሊላይ፣ ገሰሰ አየለ፣ ሙሴ ወደ በረሀ የገቡት ለእውነተኛ የህዝብ ትግል እንደነበር አመልክተዋል። እነዚህ የትግሉ መስራቾች ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ እንደነበራቸውም አስታውቀዋል።
ገሰሰ አየለ፣የትግራይ መገንጠል የሚባለውን እንደማይቀበልና ስህተት መሆኑንም ይናገር እንደነበር አመልክተው፤ የስብሓት ነጋ እና የአባይ ፀሃየ ቡድን ይህ ስላልጣመው የውጪ ግንኙነት እንዲሰራ በሚል በሱዳን በኩል እንዲወጣ ተደርጎ በመንገድ በነሱ አጃቢዎች ሆነ ተብሎ መገደሉን ጠቁመዋል፡፡
ገሰሰ፣ ደደቢት በረሀ ሲሄዱ የተሻለ ኢኮኖሚ፣ መሳሪያና የተሻለ ህዝባዊ ድጋፍ እንደነበረው ጠቅሰው፤ የገሰሰ ወደ በርሀ መግባት አብዛኞቹ የሽሬ ልጆች ለትግል እንዲነሳሱ የሞራል አቅም ፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል። በርካታ የሽሬ ልጆች ወደ ትግሉ መቀላቀላቸው ያስደነገጣቸው አቶ ስብሓት ነጋ፣ ‹‹ገሰሰ ፊውዳል ነው›› ብለው የስም ማጥፋት ዘመቻ እንደጀመረቡትም ተናግረዋል።
እየመጣ የአመራሩን ስፍራ በስፋት እንደተቆጣጠረው አመልክተው፤ ይህ ቡድን የሽሬ ልጆችን ‹‹ሰላይ ናችሁ›› በሚል ይገድል እንደነበር ተናግረዋል። በዚህ ሴራም ብዛት ያላቸው የሽሬ ልጆች መገደላቸውን አስታውቀዋል።
በወቅቱ ከኢዲዩ ጋር በተደረገው አስከፊ ጦርነት ብዙ ታጋዮች መሰዋታቸውን ጠቁመው፤ ከኢዲዩ ጋር ወደ ጦርነት ለመግባት ምንም ምክንያት አልነበረም ብለዋል። ችግሩን በውይይት መፈታት ይቻል እንደነበር የገለጹና ውጊያው አያስፈልግም ብለው ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች በወቅቱ እንዲገደሉ ተደርጓል ብለዋል።
ከ1967 እስከ 68 ዓ.ም የሽሬን ልጆች ካጸዱ በኋላ በ1969 ውጊያ የሚመሩ ሰዎች በአቶ ስብሓት ነጋ የቅርብ ዘመዶች መተካት መጀመራቸውን ገልጸዋል። ከዚያም ውጊያዎች መበላሸት መጀመራቸውን ያስተዋሉ ታጋዮች አቅም ያላቸው ሰዎች እያሉ ለምንድን ነው የማይመጥኑ ሰዎች እንዲመሩንና ውጊያ እንዲበላሽ የሚደረገው ሲሉ መጠየቅ መጀመራቸውንም ጠቅሰው፤ጉዳዩ በወቅቱ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ እንደነበርም አስታውሰዋል።
********************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ለእውነተኛ የህዝብ ትግል በረሀ የገቡ ብዙ የትግራይ ልጆች በህወሃት ሴረኛ ቡድን በበረሀ የትጥቅ ትግል ወቅት መገደላቸውን የቀዳማይ ወያነ መስራች የብላታ ሃይለማርያም ልጅ ሊላይ ሃይለማርያም ረዳ አስታወቁ። ህዝባችንን ከዚህ ማፍያ ቡድን እንታደገው ሲሉም ጥሪ አቀረቡ፡፡
አቶ ሊላይ ሃይለማርያም በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት፤ የበረሀ ትግል ሲጀመር ትግሉን የተቀላቀሉ ኃይሎች ሁለት ባህሪ ነበራቸው፡፡ አንደኛው የህዝቡን እውነተኛ ጥያቄ ይዞ ለመታገል የገባ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከህዝብ ጥያቄ ይልቅ ስውር የሆነ ተልእኮ አንግቦ የተቀላቀለ ነው፡፡
1968 ዓ.ም ጥቅምት ወር ሕወሃትን እንደተቀላቀሉ ያስታወሱት አቶ ሊላይ፣ ገሰሰ አየለ፣ ሙሴ ወደ በረሀ የገቡት ለእውነተኛ የህዝብ ትግል እንደነበር አመልክተዋል። እነዚህ የትግሉ መስራቾች ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ እንደነበራቸውም አስታውቀዋል።
ገሰሰ አየለ፣የትግራይ መገንጠል የሚባለውን እንደማይቀበልና ስህተት መሆኑንም ይናገር እንደነበር አመልክተው፤ የስብሓት ነጋ እና የአባይ ፀሃየ ቡድን ይህ ስላልጣመው የውጪ ግንኙነት እንዲሰራ በሚል በሱዳን በኩል እንዲወጣ ተደርጎ በመንገድ በነሱ አጃቢዎች ሆነ ተብሎ መገደሉን ጠቁመዋል፡፡
ገሰሰ፣ ደደቢት በረሀ ሲሄዱ የተሻለ ኢኮኖሚ፣ መሳሪያና የተሻለ ህዝባዊ ድጋፍ እንደነበረው ጠቅሰው፤ የገሰሰ ወደ በርሀ መግባት አብዛኞቹ የሽሬ ልጆች ለትግል እንዲነሳሱ የሞራል አቅም ፈጥሮ እንደነበር አስታውሰዋል። በርካታ የሽሬ ልጆች ወደ ትግሉ መቀላቀላቸው ያስደነገጣቸው አቶ ስብሓት ነጋ፣ ‹‹ገሰሰ ፊውዳል ነው›› ብለው የስም ማጥፋት ዘመቻ እንደጀመረቡትም ተናግረዋል።
እየመጣ የአመራሩን ስፍራ በስፋት እንደተቆጣጠረው አመልክተው፤ ይህ ቡድን የሽሬ ልጆችን ‹‹ሰላይ ናችሁ›› በሚል ይገድል እንደነበር ተናግረዋል። በዚህ ሴራም ብዛት ያላቸው የሽሬ ልጆች መገደላቸውን አስታውቀዋል።
በወቅቱ ከኢዲዩ ጋር በተደረገው አስከፊ ጦርነት ብዙ ታጋዮች መሰዋታቸውን ጠቁመው፤ ከኢዲዩ ጋር ወደ ጦርነት ለመግባት ምንም ምክንያት አልነበረም ብለዋል። ችግሩን በውይይት መፈታት ይቻል እንደነበር የገለጹና ውጊያው አያስፈልግም ብለው ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች በወቅቱ እንዲገደሉ ተደርጓል ብለዋል።
ከ1967 እስከ 68 ዓ.ም የሽሬን ልጆች ካጸዱ በኋላ በ1969 ውጊያ የሚመሩ ሰዎች በአቶ ስብሓት ነጋ የቅርብ ዘመዶች መተካት መጀመራቸውን ገልጸዋል። ከዚያም ውጊያዎች መበላሸት መጀመራቸውን ያስተዋሉ ታጋዮች አቅም ያላቸው ሰዎች እያሉ ለምንድን ነው የማይመጥኑ ሰዎች እንዲመሩንና ውጊያ እንዲበላሽ የሚደረገው ሲሉ መጠየቅ መጀመራቸውንም ጠቅሰው፤ጉዳዩ በወቅቱ የመወያያ አጀንዳ ሆኖ እንደነበርም አስታውሰዋል።
የጠፋው ቅርስ በ50 ዓመቱ ተገኘ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ከደብረ ሰላም ወርቻሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በ1962 ዓ.ም ጠፍቶ የነበረው የስንክሳር መጽሐፍ ተገኘ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ ነጋሽ እንዳሉት ከጠፋ ከ50 ዓመታት በኋላ የተገኘው ስንክሳር ከመጋቢት እስከ ነሐሴ የሚነበበውን የመንፈቅ ምንባብ የያዘ ነው፡፡ ስንክሳሩ ከ20 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያለው፡፡
ስንክሳር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የቅዱሳንን እና የጻድቃንን ታሪክ የያዘ ትልቅ ዓመቱን መገልገያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉ የሚዳሰሱ ቅርሶች መካከልም ትልቅ ሀገራዊ ገጽታ እና ሃይማኖታዊ ግልጋሎት ያለው ነው፡፡
ቅርሱ ከጠፋ ጊዜ ጀምሮ የማፈላለግ ሥራ ሲከናወን ቆይቶ ሐምሌ 4/2012 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ደብረ-ገነት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በማዳበሪያ ተጠቅልሎ ጸሎት በሚያደርጉ እናቶች ተገኝቷል፡፡ ሕጋዊ ሂደቱን ተከትሎ ወደ ቦታው መመለሱንም ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ እንዳሉት ዞኑ የበርካታ ታሪካዊ እና ሃይማኖታዊ ቅርሶች መገኛ ቢሆንም ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ስለማይደረግላቸው ለጥፋት እየተዳረጉ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱም ከመንግሥት ጋር በመሆን በሰዎች እጅ የሚገኙ ቅርሶችን እያፈላለገ ነው፡፡ በዚህ ቅርሶች እየተገኙ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በቅርቡም ሁለት ግለሰቦች ቅርስ ተገኝቶባቸው በሕግ ተጠያቂ ተደርገው በእስር ላይ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ነገር ግን ቅርስ በሚዘርፉ እና በሚያጠፉት ላይ የሚወሰደው ርምጃ አስተማሪ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡
ቅርሶችን ለመንከባከብ በርካታ ሥራዎች ቢሠሩም ቅርሶች እየተዘረፉ መሆኑን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታውቋል፡፡ የሕዝቡ ተሳትፎ አናሳ መሆኑ፣ በአጥፊዎች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ጠንካራ አለመሆኑ እና በርካታ ቅርሶች በሰዎች እጅ መገኘታቸው በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡
የመምሪያ ኃላፊዋ ወይዘሮ ሰናይት አስራደው እንዳሉት መንግሥት በቅርሶች ላይ ቁጥጥርና ክትትል እንደሚያደርግ እና አዳዲስ ቅርሶችን እንደሚመዘግብ አስታውቋል፡፡ የተመዘገቡት በየዓመቱ ኦዲት ስለሚደረግባቸው የመጥፋት ዕድላቸው ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ማኅበረሰቡ ይሰረቅብናል በሚል በእጅ ያሉ ቅርሶችን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ አለመሆን ግን ፈተና ሆኖ ቆይቷል፡፡ በሚፈለገው ደረጃ ባይሆንም ግንዛቤ በመፍጠር ብዙ ቅርሶች ከማኅበረሰቡ ተመልሰው ምዝገባ ተደርጎላቸዋልም ብለዋል፡፡
ቀደም ብሎ የተዘረፉ ቅርሶችን የማፈላለግ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም መምሪያ ኃላፊዋ አስታውቀዋል፡፡ የታወቁ ጥንታዊ ቅርሶች ባሉባቸው ቦታዎችም የደብር ሙዚዬም በማሠራት ተገቢው እንክብካቤ ለቅርሶች እንደሚደረጉ ተመላክቷል፡፡
ሥራው በመንግሥት ብቻ ውጤታማ ስለማይሆን ሕዝቡ ቅርሱን ጠንክሮ ሊጠብቅ እንደሚገባም ወይዘሮ ሰናይት መክረዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች በእጃቸው ያሉ ቅርሶችን ለመንግሥት እንዲያሳውቁም ጥሪ አቅርበዋል ሲል የዘገበው አብመድ ነው።
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ከደብረ ሰላም ወርቻሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በ1962 ዓ.ም ጠፍቶ የነበረው የስንክሳር መጽሐፍ ተገኘ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ ነጋሽ እንዳሉት ከጠፋ ከ50 ዓመታት በኋላ የተገኘው ስንክሳር ከመጋቢት እስከ ነሐሴ የሚነበበውን የመንፈቅ ምንባብ የያዘ ነው፡፡ ስንክሳሩ ከ20 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያለው፡፡
ስንክሳር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የቅዱሳንን እና የጻድቃንን ታሪክ የያዘ ትልቅ ዓመቱን መገልገያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉ የሚዳሰሱ ቅርሶች መካከልም ትልቅ ሀገራዊ ገጽታ እና ሃይማኖታዊ ግልጋሎት ያለው ነው፡፡
ቅርሱ ከጠፋ ጊዜ ጀምሮ የማፈላለግ ሥራ ሲከናወን ቆይቶ ሐምሌ 4/2012 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ደብረ-ገነት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በማዳበሪያ ተጠቅልሎ ጸሎት በሚያደርጉ እናቶች ተገኝቷል፡፡ ሕጋዊ ሂደቱን ተከትሎ ወደ ቦታው መመለሱንም ዋና ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ እንዳሉት ዞኑ የበርካታ ታሪካዊ እና ሃይማኖታዊ ቅርሶች መገኛ ቢሆንም ተገቢ ጥበቃና እንክብካቤ ስለማይደረግላቸው ለጥፋት እየተዳረጉ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱም ከመንግሥት ጋር በመሆን በሰዎች እጅ የሚገኙ ቅርሶችን እያፈላለገ ነው፡፡ በዚህ ቅርሶች እየተገኙ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ በቅርቡም ሁለት ግለሰቦች ቅርስ ተገኝቶባቸው በሕግ ተጠያቂ ተደርገው በእስር ላይ መሆናቸውን አንስተዋል፡፡ ነገር ግን ቅርስ በሚዘርፉ እና በሚያጠፉት ላይ የሚወሰደው ርምጃ አስተማሪ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡
ቅርሶችን ለመንከባከብ በርካታ ሥራዎች ቢሠሩም ቅርሶች እየተዘረፉ መሆኑን የዞኑ ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታውቋል፡፡ የሕዝቡ ተሳትፎ አናሳ መሆኑ፣ በአጥፊዎች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ጠንካራ አለመሆኑ እና በርካታ ቅርሶች በሰዎች እጅ መገኘታቸው በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡
የመምሪያ ኃላፊዋ ወይዘሮ ሰናይት አስራደው እንዳሉት መንግሥት በቅርሶች ላይ ቁጥጥርና ክትትል እንደሚያደርግ እና አዳዲስ ቅርሶችን እንደሚመዘግብ አስታውቋል፡፡ የተመዘገቡት በየዓመቱ ኦዲት ስለሚደረግባቸው የመጥፋት ዕድላቸው ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ማኅበረሰቡ ይሰረቅብናል በሚል በእጅ ያሉ ቅርሶችን ለማስመዝገብ ፈቃደኛ አለመሆን ግን ፈተና ሆኖ ቆይቷል፡፡ በሚፈለገው ደረጃ ባይሆንም ግንዛቤ በመፍጠር ብዙ ቅርሶች ከማኅበረሰቡ ተመልሰው ምዝገባ ተደርጎላቸዋልም ብለዋል፡፡
ቀደም ብሎ የተዘረፉ ቅርሶችን የማፈላለግ ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም መምሪያ ኃላፊዋ አስታውቀዋል፡፡ የታወቁ ጥንታዊ ቅርሶች ባሉባቸው ቦታዎችም የደብር ሙዚዬም በማሠራት ተገቢው እንክብካቤ ለቅርሶች እንደሚደረጉ ተመላክቷል፡፡
ሥራው በመንግሥት ብቻ ውጤታማ ስለማይሆን ሕዝቡ ቅርሱን ጠንክሮ ሊጠብቅ እንደሚገባም ወይዘሮ ሰናይት መክረዋል፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች በእጃቸው ያሉ ቅርሶችን ለመንግሥት እንዲያሳውቁም ጥሪ አቅርበዋል ሲል የዘገበው አብመድ ነው።
የጠፋው ቅርስ በ50 ዓመቱ ተገኘ
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ከደብረ ሰላም ወርቻሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በ1962 ዓ.ም ጠፍቶ የነበረው የስንክሳር መጽሐፍ ተገኘ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ ነጋሽ እንዳሉት ከጠፋ ከ50 ዓመታት በኋላ የተገኘው ስንክሳር ከመጋቢት እስከ ነሐሴ የሚነበበውን የመንፈቅ ምንባብ የያዘ ነው፡፡ ስንክሳሩ ከ20 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያለው፡፡
ስንክሳር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የቅዱሳንን እና የጻድቃንን ታሪክ የያዘ ትልቅ ዓመቱን መገልገያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉ የሚዳሰሱ ቅርሶች መካከልም ትልቅ ሀገራዊ ገጽታ እና ሃይማኖታዊ ግልጋሎት ያለው ነው፡፡
*************************
(ኢ ፕ ድ)
በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ከደብረ ሰላም ወርቻሜ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በ1962 ዓ.ም ጠፍቶ የነበረው የስንክሳር መጽሐፍ ተገኘ፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ፀሐይ ጸዳሉ ነጋሽ እንዳሉት ከጠፋ ከ50 ዓመታት በኋላ የተገኘው ስንክሳር ከመጋቢት እስከ ነሐሴ የሚነበበውን የመንፈቅ ምንባብ የያዘ ነው፡፡ ስንክሳሩ ከ20 ኪሎ ግራም በላይ ክብደት ያለው፡፡
ስንክሳር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የቅዱሳንን እና የጻድቃንን ታሪክ የያዘ ትልቅ ዓመቱን መገልገያ ነው፡፡ በኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉ የሚዳሰሱ ቅርሶች መካከልም ትልቅ ሀገራዊ ገጽታ እና ሃይማኖታዊ ግልጋሎት ያለው ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአፍሪካ 100 ስመ ጥር ግለሰቦች መካከል አንዱ ሆኑ
*****
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እ.አ.አ 2020 ላይ በአመራር ክህሎት ባበረከቱት አስተዋጽኦ ከአፍሪካ 100 ስመጥር ግለሰቦች መካከል በግንባር ቀደምትነት ተጠቃሽ ሆነዋል።
በዓለም የታዋቂ ሰዎችን ዝርዝር የሚያወጣው ተቋም /Reputation Poll International/ በተለያዩ ዘርፎች የ100 ስመ ጥር ግለሰቦችን ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በስም ዝርዝሩም 47 ሴቶች እና 53 ወንዶች አፍሪካውያን በአመራር፣ በመዝናኛ፣ በትምህርት፣ በንግድ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎች መመረጣቸው ተነግሯል።
ከእነዚህ መካከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በአመራር ክህሎታቸው በኢትዮጵያ ባመጡት ለውጥ 100 ስመ ጥር ግለሰቦች መካከል ተጠቃሽ ሆነው ተመርጠዋል።
ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያዊቷ ቤተልሔም ጥላሁንን ጨምሮ ሁለት የአፍሪካ ግለሰቦች በቢዝነስ ዘርፍ ከስመ ጥር አፍሪካውያን ዝርዝር ውስጥ መካተታቸውን ሪፑቴሽን ፖል የተሰኘው ድረ ገጽ አስነብቧል።
*****
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እ.አ.አ 2020 ላይ በአመራር ክህሎት ባበረከቱት አስተዋጽኦ ከአፍሪካ 100 ስመጥር ግለሰቦች መካከል በግንባር ቀደምትነት ተጠቃሽ ሆነዋል።
በዓለም የታዋቂ ሰዎችን ዝርዝር የሚያወጣው ተቋም /Reputation Poll International/ በተለያዩ ዘርፎች የ100 ስመ ጥር ግለሰቦችን ስም ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በስም ዝርዝሩም 47 ሴቶች እና 53 ወንዶች አፍሪካውያን በአመራር፣ በመዝናኛ፣ በትምህርት፣ በንግድ እና በበጎ አድራጎት ሥራዎች መመረጣቸው ተነግሯል።
ከእነዚህ መካከል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ በአመራር ክህሎታቸው በኢትዮጵያ ባመጡት ለውጥ 100 ስመ ጥር ግለሰቦች መካከል ተጠቃሽ ሆነው ተመርጠዋል።
ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያዊቷ ቤተልሔም ጥላሁንን ጨምሮ ሁለት የአፍሪካ ግለሰቦች በቢዝነስ ዘርፍ ከስመ ጥር አፍሪካውያን ዝርዝር ውስጥ መካተታቸውን ሪፑቴሽን ፖል የተሰኘው ድረ ገጽ አስነብቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም በ2012 በጀት አመት 47 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ገቢ አገኘ
የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ ገቢው ከእቅዱ 105 ነጥ ብ 1 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል።
ይህም ከባለፈው አመትም ጋር ሲነጻጸር በ31 ነጥብ 4 በመቶ ብልጫ መኖሩን ጠቁመው ÷ ተቋሙ ከውጭ የስልክ ጥሪ 147 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘቱን ገልጸዋል። ከዚያም ባለፈ 10 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ብድር መመለስ ተችሏልም ነው ያሉት።
የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዛሬው እለት በሰጡት መግለጫ ገቢው ከእቅዱ 105 ነጥ ብ 1 በመቶ ብልጫ አለው ብለዋል።
ይህም ከባለፈው አመትም ጋር ሲነጻጸር በ31 ነጥብ 4 በመቶ ብልጫ መኖሩን ጠቁመው ÷ ተቋሙ ከውጭ የስልክ ጥሪ 147 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማግኘቱን ገልጸዋል። ከዚያም ባለፈ 10 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ብድር መመለስ ተችሏልም ነው ያሉት።
የዚምባብዌ ሚኒስትር በኮሮናቫይረስ ሕይወታቸው አለፈ
----------------------------------------------------
የዚምባብዌ የግብርና ሚኒስትር ፔሬንስ ሺሪ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ በኮሮናቫይረስ መሞታቸው የተረጋገጠው በምርመራ መሆኑንም የአገሪቱ መንግሥታዊ ጋዜጣ ሄራልድ ፕሬዚዳንቱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
ሚኒስትሩ የአለም አቀፉ ጤና ድርጅት በሚያዘው በኮሮናቫይረስ ለሞቱ ሰዎች የሚደረገው የቀብር ስነ ስርዓት መመሪያ መሰረት በነገው እለት እንደሚቀበሩም ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
የ65 አመቱ ሚኒስትር በመዲናዋ ሃራሬ በሚገኝ የግል ሆስፒታል ረቡዕ እለት ሕይወታቸው ማለፉ BBC
----------------------------------------------------
የዚምባብዌ የግብርና ሚኒስትር ፔሬንስ ሺሪ በኮሮናቫይረስ ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኤመርሰን ምናንጋግዋ ገልፀዋል።
ሚኒስትሩ በኮሮናቫይረስ መሞታቸው የተረጋገጠው በምርመራ መሆኑንም የአገሪቱ መንግሥታዊ ጋዜጣ ሄራልድ ፕሬዚዳንቱን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
ሚኒስትሩ የአለም አቀፉ ጤና ድርጅት በሚያዘው በኮሮናቫይረስ ለሞቱ ሰዎች የሚደረገው የቀብር ስነ ስርዓት መመሪያ መሰረት በነገው እለት እንደሚቀበሩም ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
የ65 አመቱ ሚኒስትር በመዲናዋ ሃራሬ በሚገኝ የግል ሆስፒታል ረቡዕ እለት ሕይወታቸው ማለፉ BBC