Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
25K subscribers
41K photos
338 videos
7 files
5.81K links
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
Download Telegram
እህትማማቾች በካቲካላ ሞቱ

ታህሳስ 21 ቀን 1965 ዓ.ም የታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ እህትማማቾች በቅርብ ያገኙትን አረቄ በመጠጣታቸው ህይወታቸውን ስላጡ ታዳጊዎች ተተከታዩን ዘገባ አስነብቦ ነበር።

ወይዘሪት ብዙነሽ ገብሬና ወይዘሪት እመቤት ገብሬ የተባሉ እህትማማቾች የእህል አረቄ ጠጥተው መሞታቸውን ከሸዋ ፖሊስ ማስታወቂያ ክፍል የተገኘው ዜና ገለጠ። ልጆቹ ለሞት የበቁት ወላጅ እናታቸው አረቄውን ካወጡ በኋላ አልጋ ስር አስቀምጠውት ወደ ገበያ ሲሄዱ ከተቀመጠበት ቦታ አንስተው በመጠጣታቸው ነው።

ሟቾቹ አረቄውን እንደጠጡ በያሉበት ተዘርረው ወድቀው ነበር። በኋላ ግን ሰው ደርሶ ለህክምና ፍቼ ጤና ጣቢያ ተወስደው ህክምና ቢደረግላቸውም ለመዳን ተስፋ በማጣታቸው በ 10 ሰዓት ልዩነት ሁለቱም ህይወታቸውን አጥተዋል።

በሁለቱ እህትማማቾች ላይ ይህ የሞት አደጋ የደረሰው ታህሳስ አራት ቀን 1965 ዓ.ም በሰላሌ አውራጃ በግራር ጃርሶ ወረዳ ግዛት ፍቼ ከተማ ውስጥ ነው። ወይዘሪት ብዙነሽ ገብሬ ዕድሜዋ ስምንት ዓመት ሲሆን ፣ የወይዘሪት እመቤት ደግሞ ስድስት ዓመት መሆኑን የማስታወቂያ ክፍሉ ባገኘው ሪፖርት መሰረት አስረድቷል።
ኮሮና ዛሬ በኢትዮጵያ
የ114 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ከሆስፒታል ወጡ

የ114 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ሆስፒታል መውጣታቸውን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ያሬድ አግደው በፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።

እኚህ የዕድሜ ባለፀጋ አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ለተጨማሪ ህክምና የካቲት 12 ሆስፒታል ናቸው ተብሏል ።
ሸገር ዳቦና የዳቦ ዱቄት ፋብሪካ እየተመረቀ ነው
*********************
(ኢ ፕ ድ)

በሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ አባል በሆነው ሆራይዘን ፕላንቴሽን ኩባንያ አማካኝነት የተገነባው ሸገር ዳቦና የዳቦ ዱቄት ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት እየተመረቀ ነው።

በመዲናዋ የሚስተዋለውን የዳቦና የዱቄት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በሰዓት 80 ሺህ ዳቦ የሚያመርተው ሸገር ዱቄት ፋብሪካ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በተገኙበት እየተመረቀ ይገኛል።

ፋብሪካው ምርቱን ዝቅተኛውን የማኅበረሰብ ክፍል ባገናዘበ ዋጋ የሚያከፋፍል ሲሆን፤ ይህም በከተማው የሚስተዋለውን የዳቦ አቅርቦት ማነስና የዋጋ ንረት ከመቅረፉ በላይ፥ ከዳቦ ማምረት እስከ ማከፋፈል ድረስ ባለው ሰንሰለት ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።፡፡

ፋብሪካው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በአራት ሄክታር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፤ በፕሮጀክቱ ሥራ ከ450 ሰዎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከ400 በላይ ያገለገሉ የአንበሳ የከተማ አውቶብሶች ለዳቦ ማከፋፈያነት እንደሚውሉም ታውቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “እንሥራ” የተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከልን ጎበኙ

*************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “እንሥራ” የተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

“እንሥራ በተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከል ለምትሠሩት እህቶቼና እናቶች እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እወዳለሁ፤ የድካማችሁን ፍሬ በማየቴ ደስ ብሎኛል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 141 ሰዎች ኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው
. በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥርም 81 ደርሷል
******************************
(ኢፕድ)
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4675 የላብራቶሪ ምርመራ 141 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5175 ደርሷል።

ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 18 (4 ከጤና ተቋም እና 14 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ የተገኝበት ናሙና የለም። ከዚህ ባለፈ ሶስት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 81 ደርሷል፡፡

በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት 58 ሰዎች (44 ከአዲስ አበባ፣ 8 ከኦሮሚያ ክልል፣ 3 ከሶማሊ ክልል፣ 2 ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል፣ እና 1 ከትግራይ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1544 ነው።
ኢትዮጵያ በቀሪዎቹ ሁለት ሳምንትታት የግድቡን ቀሪ ስራዎች በማጠናቀቅ ሙሌት ትጀምራለች ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ
*******************
(ኢ ፕ ድ)

ኢትዮጵያ በቀሪዎቹ ሁለት ሳምንትታት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድቡን ቀሪ ስራዎች በማጠናቀቅ የውሃ ሙሌት ስራውን ትጀምራለች ሲል የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት አስታወቀ

ጽህፈት ቤቱ አሁን ባወጣው መግለጫ ላይ እነደገለጸው፤ ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን ትናንት በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት ትናንት ባደረጉት ስብሰባ በግድቡ ሙሌትና አስተዳደር ላይ የሚደረገው ድርድር በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት እንዲጠናቀቅ ተስማምተዋል።

"ኢትዮጵያ በቀሪዎቹ ሁለት ሳምንትታት የግድቡን ቀሪ ስራዎች በማጠናቀቅ ሙሌት ትጀምራለች። በእነዚህ ሁለት ሳምንትት አገራቱ ከስምምነት ላይ ለመድረስ ወስነዋል" ሲል ነው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በመግለጫው የጠቀሰው።

በተጨማሪም የአፍሪካ ህብረት ጉዳዩን መመልከት መጀመሩ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት እንዲገለጥ፣ የአፍሪካ ህብረት እና የመሪዎች ጉባኤ ቢሮ አባላት ድርድሩን እንዲደግፉ፣ ኢትዮጵያ ሱዳን እና ግብጽ ከቃላት ጦርነት መካረር እና አላስፈዐላጊ መግለጫዎች እንዲቆጠቡ አቅጣጫ ተቀምጦ ልዩ የመሪዎች ስብሰባ ተጠናቋል ሲል መግለጫው አስታውቋል።

ስብሰባው የተጠራው በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር በሆኑት የደቡብ አፍርካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ አማካኝነት መሆኑን የጠቀሰው መግለጫው፤ ከሶስቱ አገራት በተጨማሪ ኬኒያ፣ ማሊ እና የኮንጎ ዴሞክራቲክ መሪዎች መሳተፋቸው ተገልጿል።
በአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ የ13 ቀናት እና በአቶ በቀለ ገርባ ላይ የ11 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደ
**********************************
(ኢፕድ)
ከድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በኋላ ከተከሰተው አለመረጋጋት ጋር በተያያዘ ከሁለት ሳምንት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉት የአቶ ጃዋር መሐመድን ጉዳይ የተመለከተው ፍርድ ቤት ተጨማሪ የ 13 ቀናት የምርመራ ጊዜ ለፖሊስ ፈቀደ።
መርማሪ ፖሊስ በዋነኛነት ብሔርና ሃይማኖት መሰረት ያደረገ ግጭት እንዲቀሰቀስ ተጠርጣሪው የነበረውን አስተዋጽኦ ጠቅሶ፤ በተለይ የአርቲስት ሃጫሉን አስከሬን አቶ ጃዋር በሚመራው ቡድን ወደ ኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ ውስጥ በሃይል ለማስገባት መሞከራቸውን አስረድቷል። በዚህም አንድ የፖሊስ አባል ህይወት እንዲያልፍና ሶስት እንዲቆስሉ መሆኑን ገልጿል።
ይህ ሊሆን የቻለው ተጠርጣሪው በሰጠው ትዕዛዝ መሆኑን አመልክቷል። በተጨማሪም የስልክ ልውውጥ በማድረግ የአመጽ ቅስቀሳ ሲያደርግ እንደነበረ በመግለጽ ለነዚህ ሁሉ ጉዳዮች መርማሪ ፖሊስ ማስረጃ ማሰባሰቡን ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል። የምስክሮችን ቃል መቀበሉንም አስረድቷል።
በአዲስ አበባና በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢዎች የተጠርጣሪውን የአመጽ ጥሪ በመቀበል ወደ 181 ሰዎች ህይወት ማለፉን ያመለከተው መርማሪ ፖሊስ፤ ተጠርጣሪው በሚመራው ቡድን ስር በቁጥጥር ስር የዋሉ የጦር መሳሪያዎች በሙሉ ህገ ወጥ መሆናቸውን ገልጿል።
14 የምርመራ ቡድን ተዋቅሮ ተጨማሪ ማጣራት እያደረገ እንደሚገኝ ያመለከተው መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ ማስረጃ የማሰባሰብ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ አመልክቷል። ያልተያዙ ግብረ አበሮችን መኖራቸውን ያመለከተው መርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ 14 የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠውም ጠይቋል።
ተጠርጣሪው አቶ ጃዋር መሃመድ በበኩላቸው ወንጀሉን አለመፈጸማቸውን ገልጸው፤ ጉዳዩ ድራማ ነው ሲሉ ተናግረዋል። የተተኮሰ ጥይት አለመኖሩን ተናግረው፤ የተተኮሰ ጥይትም ሆነ የሞተ ሰው አለመኖሩን በመግለጽ የሚበጀው ቁጭ ብሎ መነጋገር ነው ሲሉ ለፍርድ ቤቱ ገልጸዋል።
የተጠርጣሪው ጠበቆች በእስር ቤት ያለው አያያዝና የቤተሰብ ጥየቃ ሁኔታ እንዲስተካከል ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።
ፍርድ ቤቱ ግራ ቀኙን አዳምጦ የተጠርጣሪው አያያዝ ሁኔታና የቤተሰብ ጥየቃ እንዲስተካከል ትዕዛዝ በመስጠት መርማሪ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ የፈቀደው ፍርድ ቤቱ 14ኛው ቀን በዓል በመሆኑ በ13ኛው ቀን ለሐምሌ 22 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በተያያዘ ሃምዛ አዳነ በተባለ ግለሰብ የምርመራ መዝገብ የሚጠሩ ዘጠኝ ተጠርጣሪዎች ‘’የአቶ ጃዋር ግብረ አበሮች’’ በሚል ፖሊስ ያቀረባቸው ናቸው። እነዚህ ተጠርጣሪዎች በዕለቱ በነበረው የአስከሬን ቅሚያ ጋር ተያይዞ ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ እነዚህ አካላት መኖራቸው፣ በማህበራዊ ሚዲያ መቀስቀሳቸውን፣ አመጽ እንዲቀጣጠል
ማድረጋቸውን እና ቡድኑ የተደራጀና መሳሪያ የታጠቀ መሆኑን መርማሪ ፖሊስ ገልጿል።
ይህ ቡድን ተኩስ መክፈቱንና ህይወት መጥፋቱን እንዲሁም ቡራዩ ላይ በነበረው ትንቅንቅ የጸጥታ ሃይሎች ላይ ተኩስ በመክፈት የሁለት ሰው ህይወት እንዲጠፋ ማድረጋቸውን በምርመራ ማረጋገጡን ገልጿል።
በመሆኑም ተጨማሪ ማጣራት የሚያደ ርግባቸው ጉዳዮች መኖራቸውንና ያልተያዙ ግብረ አበሮች እንዳሉ በመግለጽ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል። በዚሁ መሰረት ቀሪ ምርመራውን አጠናቆ ለሐምሌ 22 ቀን 2012 ዓ.ም እንዲቀርብ ተጨማሪ 13 ቀናት ጊዜ ፍርድ ቤቱ ሰጥቷል።
በተመሳሳይ ሐምሌ 6 ቀን 2012 ዓ.ም ቀርበው ትዕዛዝ ለመስጠት ለትናንት ተቀጥሮ የነበረው የአቶ በቀለ ገርባ መዝገብ ላይ የተጠየቀውን የመርማሪ ፖሊስ 14 ተጨማሪ ቀናት የመረመረው ፍርድ ቤቱ 11 ቀናት በቂ እንደሆነ በመግለጽ ለሐምሌ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
አቶ በቀለ ገርባ መኪናቸው በወንጀል ፍሬ ውስጥ የማትገኝ በመሆኑ በተወካያቸው በኩል መረከብ እንደሚችሉ መርማሪ ፖሊስ ለችሎቱ ገልጿል።
በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት የተጠረጠሩት እነ አራፋት አወቀ እና እነ አዲሱ ቶሎሳ ላይ ለመርማሪ ፖሊስ ተጨማሪ 11 ቀናት የምርመራ ጊዜ በመስጠት ለሐምሌ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።
በእነ አራፋት መዝገብ ስድስተኛ ተጠርጣሪ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸው በህክምና ላይ በመሆናቸው ጉዳያቸው ከህክምና በኋላ እንደሚታይ ፍርድ ቤቱ በመግለጽ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
አዲስ ዘመን ሐምሌ10/2012
የድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ በህዝቦች መካከል
እልቂት ለመፍጠር ያለመ ነበር
************************************
(ኢፕድ)
ከሰሞኑ የድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በአዲስ አበባ ከተማና በኦሮሚያ ክልሎች የተከሰተው ግርግር አሳዛኝና አሳፋሪ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ። ድርጊቱ ለዘመናት አብረው በኖሩ ህዝቦች መካከል ጥርጣሬና አለመግባባት በመፍጠር በአገሪቷ የመጣውን ለውጥ ለመቀልበስ የታሰበ እንደሆነም ይነገራል።
በርካታ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ድርጊቱን በማውገዝ በጉዳዩ ላይ ሃሳባቸውን በመገናኛ ብዙሃን ሲያንሸራሽሩ ተደምጠዋል።
አዲስ ዘመን ጋዜጣ ያነጋገራቸው በአማራ የህዝብ ንቅናቄ አብን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጣሂር መሐመድ እንደገለፁት፤ የድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ የነበሩት እንቅስቃሴዎች በህዝቦች መካከል ጥርጣሬና አለመግባባት እንዲሁም እልቂት እንዲፈጠር ታስቦ የተቀነባበረ ነው። ይህን እኩይ ተግባር ለመፈፀም ዝግጁ የነበሩ አካላት እንዳሉም ማሳያዎች ነበሩ ብለዋል።
ለዚህም መንግስት በአሁኑ ወቅት ለህዝብ እያደረሳቸው ያሉ መረጃዎች በተለይም ድምፃዊው ከ OMN የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ ሲታይ ታቅዶ የተደረገ ለመሆኑ አንዱ ማሳያ ነው። የሚሉት አቶ ጣሂር፤ አርቲስቱ ታዋቂና በህዝቡ ያለውን ተወዳጅነት ተጠቅመው ህዝባዊ ግጭቶችን ለመፍጠር ተጠንቶ የተደረገ ለመሆኑ ሂደቶቹ ምስክሮች ናቸው ይላሉ።
አቶ ጣሂር አያይዘውም የአማራ ንቅናቄ አብን በወቅቱ ለአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ባለቤት ሰጥተው ጉዳዩን ሲያንሸራሽሩ የነበሩ ሚዲያዎችን ታዝቧል። በመሆኑም ጉዳዩ ወዳልተፈለገ ቀውስ ይገባልና መንግስት ጥንቃቄ ያድርግ የሚል መልዕክት ያስተላለፈ መሆኑን አስታውሰዋል። ነገር ግን መንግስት ጥንቃቄ ባለማድረጉና ፈጥኖ እርምጃ ባለመውሰዱ እንደተፈራውም ክቡር በሆነው የሰዎች ህይወት እና ንብረት ላይ ከፍተኛ እልቂትና ውድመት የደረሰ መሆኑን ተናግረዋል።
ለብጥብጡ የተመረጠው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ መሆኑ ባይታወቅም እንዲህ አይነት የጥፋት አዝማሚያዎች ነበሩ። በተለይም በኦሮሚያና ደቡብ ክልል ያሉ ለጥፋት የተመረጡ ህዝቦች እንዳሉ ይታወቃል። የሚሉት አቶ ጣሂር፤ ለውጡ ከመጣበት ካለፉት ሁለት ዓመታት ወደዚህ በፅንፈኛው ኃይል “ይሄ የእኔ ክልል ነው፤ ከክልሌ ውጣልኝ” የሚል አይነት አዝማሚያዎችን እንደ ማስፈራሪያ ተይዘው ይንፀባረቁ እንደነበር አስታውሰዋል።
ስለዚህ አንድ ነገር በተከሰተ ቁጥር ሰለባ የሚሆኑ ህዝቦች እንዳሉ ይታወቃል። በተለይም የአማራ ህዝብ ተጎጂ የሚሆንበት አዝማሚያ በመኖሩ መንግስት ቅድመ ማስጠንቀቂያና ልዩ ጥበቃ ሊያደርግ እንደሚገባ ለብልፅግና ፓርቲና ለመንግስት የሥራ አመራሮች ይገልፁ እንደነበር አቶ ጣሂር ተናግረዋል።
ቢዘገይም አልቀርም እንደሚባለው ነውና አሁን ላይ መንግስት ቢዘገይም እየወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ያሉት አቶ ጣሂር፤ አሁን የደረሰው ጥፋት ከዚህ በፊት በተፈጠሩ ችግሮች ላይ ተጠያቂ መሆን የነበረባቸው ሰዎች ተጠያቂ ባለመሆናቸው የደረሰ ነው ይላሉ። ለአብነትም የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በተደጋጋሚ እንደ ሀገር መከላከያ ሠራዊት በብዙ መጠን ሲያስመርቃቸው የነበሩ የልዩ ሃይል አባላት ያሉበት ሊታወቅ ይገባል። ምናልባትም ለዚህ ጉዳይ ተባባሪ ሆነው ህዝባችንን ለከፍተኛ እልቂትና ውድመት ዳርገውት ከሆነም መጣራት እንዳለበት አመልክተዋል።
መንግስት ፈጥኖ እርምጃ መውሰድ እንደነበረበትና የዘገየ መሆኑን የገለፁት አቶ ጣሂር፤ በሰው ደም ላይ የሚደረግ ትዕግስትና ሆደ ሰፊነት የለም። መቀጠልም የለበትም ብለዋል። የሰዎች ሕይወት እየጠፋ ንብረት እየወደመ ሆደ ሰፊ እንሁን ማለት የማያዋጣ ነው።
እስካሁንም የተጓዝንበት መንገድ የስጋት እንደመሆኑ ለቀጣይም ይህ መንገድ አገር እንደ አገር እንዲቀጥል አያስያደርግምና መንግስት በተጠናከረ መንገድ አጥፊዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰድ አለበት ሲሉም አሳስበዋል።
እንደ አንድ ዜጋም ሆነ እንደ ፖለቲካ መሪ በአገሪቷ የተረጋጋ ሁኔታ እንዲኖር እፈለጋለሁ። የሚሉት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በበኩላቸው፤ በአገሪቷ ያሉ ህዝቦች ለበርካታ ዘመናት በጋራ ተከባብረው የኖሩ ህዝቦች መሆናቸውን አስታውሰው ነገር ግን እንደዚህ አይነት የደፈረሰና ፅንፍ የወጣ ጉዳይ እስከዛሬ አልገጠመንም ይላሉ። ጥፋቱ ከማሳዘንም አልፎ በጣም የሚያሳፍር ነው። ግለሰብን አጥፍቶ ድራማ ለመስራት የተደረገ አጀንዳ ከሆነም ኋላቀር አካሄድ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
ያለንበት ዘመን 21ኛው ከፍለ ዘመን እንደመሆኑ ኋላቀር የሆነ የፖለቲካ ጨዋታ የምንጫወትበት የአስተዳደር ዘመን አይደለም። ያሉት ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፤ በዚህ ወቅት መጫወት ያለብን ሰላማዊና ሰላማዊ ብቻ የሆኑ ሃሳቦችን በማንሸራሸር እንደሆነም ተናግረዋል። ነገር ግን ታዋቂ ግለሰብን ገድሎ በሚፈጠር ረብሻ መንግስት መገልበጥና ስልጣን ለመያዝ የሚያስቡ ካሉ እጅግ ኋላ የቀረ አስተሳሰብ ከመሆኑም በላይ አዋጭ አለመሆኑ አብራርተዋል።
ይሁንና ማንም ሆነ ማን በጥፋት ከተጠረጠረ መንግስት በተገቢው አካል መርምሮ ነፃ የሆነውን በነፃነቱ ማስተናገድ አለበት። ጥፋተኛውን ደግሞ ለፍትህ አካል ማቅረብ አንድ መንግስት ካለበት አገር የሚጠበቅ ነው። ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ከሞተ በኋላ መንግስት እያደረገ ባለው ክትትል የተያዙ ተጠርጣሪዎች አሉ። ይህ መሰረታዊና ተገቢ ተግባር ነው።
ይሁንና በመንጋ ወጥቶ የሀገር ሀብትና ንብረት እያጠፋ ያለው ወጣት ነገሮችን አዙሮ ማየት የሚችል አይመስልም። “ነገርን ከስሩ ውሃን ከጥሩ” እንደሚባለው መንግስት በሽታቸውን አውቆ ማከም እንዲችል ችግሩን ከሥሩ ማጥራት አለበት። በደቦ ወጥቶ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ወጣቶችን ማን ለምን ዓላማ እንደሚያሰማራቸው ከሥሩ ማጥራትና ተገቢውን እርምጃ መውሰድ ተገቢ ነው ሲሉም አሳስበዋል።
አዲስ ዘመን ሐምሌ 9/2012
ፍሬህይወት አወቀ
የታላቁ የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት ተጠናቀቀ
--------------------------------------------------
የኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
ባለፉት ሁለት ሳምንታት ከተገኘው ከፍተኛ የዝናብ መጠን የተነሣ፣ የግድቡ የመጀመሪያ ዓመት የውኃ ሙሌት ተጠናቋል ያለው የጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ውኃው በግንባታ ላይ ያለውን ግድብ አልፎ እየፈሰሰ እንደሚገኝ አስታውቋል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት ተጠናቀቀ
**********************************
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ሙሌት መጠናቀቁን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የውሃ ሙሌቱ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክተው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ክረምቱ ገና ሳይገባደድ የመጀመሪያው ዙር ሙሌቱ በጥቂት ቀናት ሞልቶ መጠናቀቁና መፍሰስ መጀመሩ ለአገሪቱ ትልቅ የድል ምዕራፍ መክፈቱን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
ለግድቡ ግንባታ ድጋፍ ላደረገው የኢትዮጵያ ህዝብና በድርድር ሂደት ሙያዊና የዜግነት ህግዴታቸውን ለተወጡት ተደራዳሪዎችም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የአሁኑ ሙሊት በሁለት ተርባይን ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል ምዕራፍ መሆኑን የገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፣ የግድቡ ግንባታ ዳር እንዲደርስ በድፕሎማሲውም ሆነ በግንባታው ሂደት ገና ብዙ ሂደት ይቀረዋል ብለዋል።
በመሆኑም ህዝብና መንግስት በተባበረ ጥረት ለአገራዊ ለውጥና ተጠቃሚነት በጋራ መስራታቸውን እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
የግድቡን ህልውና በዘላቂነት ለማረጋገጥም በተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአፋር ሰመራ ችግኝ ተከሉ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ጋር በመሆን፣ በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በሚገኝ አዲስ ፓርክ ችግኝ ተክለዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፤ የችግኝ የመትከያው ወቅት አጋማሽ ላይየተደረሰ ሲሆን፤ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሊተከል ከታቀደው 5 ቢሊየን ችግኝ መካከል እስካሁን 2.9 ቢሊየን ችግኞች ተተክለዋል።
"ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ የላቸውም"- ጄኔራል አደም መሐመድ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም
************************************
(ኢፕድ)
አዲስ አበባ፦ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ እንደሌላቸው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አደም መሐመድ አስታወቁ። የሰራዊቱ ወታደራዊ ቁመና የአገሪቱን ሉዓላዊነት እና የሕዝቡን ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ መጠበቅ የሚያስችል እንደሆነም አመለከቱ።
ጄኔራል አደም መሐመድ በተለይ ከአዲስ ዘመን ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ከህግ ውጪ ሆኖ፤ በተለይ በሕዝቦች መካከል ቁርሾ በመፍጠር፤ ግጭት በመፍጠር፤ በሃይማኖትና በተለያዩ ምክንያቶች ሰዎች እየተፈረጁ ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት የሚደረጉ ሴራዎች ካሁን በኋላ ቦታ እንደማይኖራቸው አስታውቀዋል።
ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ፤ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ፤ ጎሳን ከጎሳ የሚያጋጩ ስራዎች ሆነ ተብለው የሚሰሩ ከሆነ፤ አድገው ወደ ዘር ማጥፋት፣ ወደ እልቂት የሚያመሩ በመሆኑ መንግስት እርምጃ እንደሚወስድ አስታውቀዋል ። በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ መንግስት እርምጃ መውሰድ ካልቻለ የመንግስትነት ተልዕኮው ምን ሊሆን ይችላል? እንደዚህ አይነት ጥፋቶች አድገው እንደ ሩዋንዳና ሌሎች አገሮች እንደሆኑት የሚጠብቅ ከሆነ ሕገመንግስታዊነቱ በምን ይገለጻል ሲሉም ጠይቀዋል ፡፡
" ግልጽ መሆን ያለበት መንግስትና የመከላከያ ሰራዊት ሕዝብን ከሕዝብ የሚያጋጩ እና አገርን የሚበትንና የሚያዳክም ማንኛውም ህገወጥ የሆኑ ተግባራትን እያየ ዝም አይልም ፡፡ ይህን ማስቆም በህገመንግስቱ የተሰጠው ኃላፊነት ነው ። የሰራዊቱም ተልዕኮ ይሄ ነው፡፡ መንግስትም ቢሆን የሀገርን ሉዓላዊነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ፤ ግዴታም አለበት" ብለዋል ፡፡
የመከላከያ ሰራዊቱ የኢትዮጵያውያን ሰራዊት ነው ፤ተልእኮውም የሚመነጨው ከህገ መንግስቱ እንደሆነ ያመለከቱት ጄኔራል አደም ፣ ህገ መንግስቱ የሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ ይወጣል ለዚህም ዝግጁ ነው ብለዋል ። የሰራዊቱ ተልእኮ የሚመነጨው ከህገ መንግስቱ በመሆኑም ተልእኮውን ከየትኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ጋር አይይዞ ማየት እንደማያስፈልግ ገልጸዋል ። ህዝቡም እንደዚህ አይነት አስተሳሰቦችን ሊታገል እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
የመከላከያ ሰራዊት ኢትዮጵያውያንን እኩል ሊያገለግል የሚችል ተቋም ሆኖ እየተገነባ መሆኑን አመልክተው፣ የጸጥታ ተቋማት የማንም ፓርቲ ዕሴት ወይም ሀብት ሳይሆኑ የኢትዮጵያ ሀብት ናቸው ሲሉም ተናግረዋል፡፡ በአንድ ፓርቲ ፕሮግራም ሊቀረጽና ሊገነባ የማይገባው እንደሆነም ጠቁመዋል፡፡ በኢትዮጵያውያን ዕሴቶች፣ በአገር ሉዓላዊነት፣ ደህንነትና ብሔራዊ ጥቅም ተመስርቶ መገንባት ያለበት ተቋም ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡
በሰራዊቱ ውስጥ ለነበሩ በርካታ የሰራዊት የግንባታ ጥያቄዎች ብዙ ኪሳራዎች እንደነበሩ ጠቁመው፤ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ የተቋም ግንባታ ላይ የተቀመጡ አስተሳሰቦችን በግለሰብ ደረጃ አለመቀበል እንደ ኃጢያት ይቆጠር ነበር፡፡ በዚህም የከሰርናቸው ኪሳራዎች አልነበሩም ማለት አይቻልም ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም አንዱን ጠባብ ብለህ ታባርራለህ፤ ወይ ትከስሳለህ፡፡ ወይ አንዱን ትምክህተኛ ብለህ ትጠረጥራለህ፤ ታባርራለህ፤ ወይ ትከስሳለህ ነው ያሉት፡፡
የሰራዊቱም ጥንካሬ ከአንድ ፓርቲ የፖለቲካ ጥንካሬ የሚነሳ መሆን የለበትም፡፡ ከአንድ ፓርቲ የፖለቲካ ጥንካሬ የሚነሳ ከሆነ፤ ፓርቲው ሲጠነክር አብሮ የሚጠነክር ይሆናል፡፡ ሌላውን እያዳከመ የሚኖርም ይሆናል፡፡ ያ ፓርቲ ሲደክም፣ ነገ በሌላ መንገድ ወደ ስልጣን የሚመጣ ኃይል ደግሞ የሚንደውና የሚያፈርሰው መሆን የለበትም:: ይሄ ተቋም የአገር እና የሕዝብ ተቋም ሆኖ በትውልዶች መገንባት መቻል አለበት ብለዋል፡፡
ፓርቲዎች በራሳቸው በሚያደርጉት ጭቅጭቅና ንትርክ ይሄንን ተቋም መጠቀሚያ የሚያደርጉበት ሁኔታ ከተፈጠረ የሆነ ፓርቲ ወደስልጣን በመጣ ቁጥር እየወደቀና እየፈረሰ እንደገና የሚገነባ ይሆናል፡፡ እየፈረሰ እየተገነባ የሚሄድ ተቋም ደግሞ ይህችን ታላቅ አገር አይመጥንም ብለዋል ጄኔራል አደም፡፡
የመከላከያ ሰራዊቱ ከለውጡ በፊትም ሆነ በኋላ የልማት እና የሰላም ጀግና ሆኖ እየተንቀሳቀሰ እንደነበር ያመለከቱት ጄኔራል አደም፤ በዚህ በኩል ትልቅ ዝናና ስም ያለው ሰራዊት ነው፡፡ አሁንም በውስጥም ሆነ በውጪ ያሉ ማንኛውንም የሀገር እና የህዝብ ስጋቶችን በመከላከል ከፍተኛ ስራ እየሰራ ነው ብለዋል። በአገር ውስጥ ሰላምና መረጋጋትን በማረጋገጥና በማስከበር ሚናው ከፍተኛ እንደሆነም አስታውቀዋል ፡፡
ህገ መንግስቱ ሰራዊቱ ከፖለቲካ ገለልተኛ መሆን አለበት፤ በፖለቲካ ጉዳዮች እጁን አያስገባም ፣የፖለቲካ አዋላጅም መሆን እንደሌለበት በግልጽ ያስቀመጠ ቢሆንም ቀደም ባለው ጊዜ ሰራዊቱ የሚገነባበት የፖለቲካ ኢንዶክትሪኔሽን ህገ መንግስቱ ካስቀመጠው ከሰራዊቱ ዓላማና የግንባታ መርሆዎች አንጻር በተጻራሪው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ አስተሳሰብ ፤ በአንድ ፖለቲካ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ላይ የሚያተኩርና የሚያጠነጥን እንደነበር አመልክተዋል ።
የተለያዩ ርዕዮተ ዓለም እና አመለካከቶች ያላቸው ፓርቲዎች ህገ መንግስታዊ እውቅና አግኝተው እየተንቀሳቀሱ ባሉበት አገር፤ ሰራዊቱን በአንድ ፓርቲ ፕሮግራም ላይ፣ በአንድ ፓርቲ ርዕዮተ ዓለም ላይ መቅረጽና መገንባት ተገቢ እንዳልነበር ጠቁመዋል፡፡
በሪፎርሙ ከተከናወኑ ስራዎች አንዱ እና ትልቁ ሰራዊቱ የሰራዊት ግንባታ ዓላማ እና የሰራዊቱ ተልዕኮ ከየትኛውም የፓርቲ ፕሮግራም ወይም ርዕዮተ ዓለም በላይ እንዲሆን ማድረግ ነው ብለዋል ፡፡
በሪፎርሙ ሰራዊቱ በህገ መንግስቱ የተሰጠውን ተልእኮ በግልጽ አውቆ ለህገመንግስቱ ብቻ ታማኝ እንዲሆን በሚያስችል አስተሳሰብ እንዲገነባ ተደርጓል፤ ይሄ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ፣ የሰራዊቱ ህገ መንግስታዊ ተልዕኮ እጅጉን የገዘፈ ፤ከአንድ ፓርቲ ፕሮግራምና ዓላማ በላይ የሆነ ፣ የተከበረ፤ የአገርን ሉዓላዊነት፤ የሕዝብ ደህንነት ላይ መሰረት ያደረገ እንደሆነ ጠቁመዋል።
"ኢትዮጵያን እኔ ከሌለሁ ትፈርሳለች ወይም እኔ ካልተጠቀምኩ እናፍርሳት የሚለው አካል ሁል ጊዜ ቢናገርም፤ በእኔ በኩል ኢትዮጵያን የምትፈርሰው መጀመሪያ በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ላይ የሚያምኑት ሕዝቦቿ እና መሪዎቿ ከሌሉና ከሌሉ ብቻ ነው ፡፡ ከዛ በላይ ኢትዮጵያ የምትፈርሰው የመከላከያ ኃይላችን፣ የፀጥታ ኃይላችን፣ የደህንነት ኃይላችን ሲፈርስ፤ ወይም እሱ መስዋዕት ሆኖ ሲሸነፍ ብቻ ነው:: ስለዚህ አሁን ያለን የሪፎርም ስራዎች የአገራችንን ገናናነትና ሉዓላዊነት የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የሚያደርግ ስርዓት መፍጠር ላይ ያተኮረ ነው፤ የሰራዊት ግንባታውም እንዲሁ ፡፡ በአስተሳሰብም በተግባርም ኢትዮጵያን የበለጠ የሚያጠናክር ስራ ነው እየተሰራ ያለው" ብለዋል፡፡
አዲስ ዘመን ሐምሌ 18/2012
ወንድወሰን ሽመልስ
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 720 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው የ14 ሰዎች ሕይወትም አልፏል
*****************

በኢትዮጵያ 24 ሰዓታት በተደረገ 9 ሺህ 527 የላብራቶሪ ምርመራ 720 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ሲገኝባቸው የ14 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 13 ሺህ 968 መድረሱንም የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ባወጡት መረጃ አመላክተዋል።

በ24 ሰዓታት ዉስጥ ህይወታቸው ያለፈውን 14 ግለሰቦች ጨምሮ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 223 ደርሷል።

በዛሬው እለትም 250 ሰዎች ከበሽታው በማገገማቸው ባጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች 6 ሺህ 216 ደርሷል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል
**********************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል።
የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በዩኒቨርሲቲው 6 ኪሎ ግቢ ራስ መኮንን አዳራሽ እየተከናወነ ነው።
ስርጭቱም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቀጥታ እየተላለፈ ይገኛል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል
**********************
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በፊት ለፊት እና በኦንላይን ያስተማራቸውን ከ5600 በላይ ተማሪዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በvirtual እያስመረቀ ይገኛል።
የምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በዩኒቨርሲቲው 6 ኪሎ ግቢ ራስ መኮንን አዳራሽ እየተከናወነ ነው።
ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ዳግም ወደ ኢትዮጵያ በረራ ጀመሩ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ፡- የኮሮና በሽታ ከተከሰተ በኋላ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የመንገደኞች በረራ አገልግሎት መነቃቃት በማሳየቱ ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ወደ ኢትዮጵያ መብረር መጀመራቸውን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን የኤር ናቪጌሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሽመልስ ክብረአብ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ የኮሮና ቫይረስ በሽታ ከተከሰተ በኋላ በርካታ ሀገራት በረራቸውን አቋርጠው ቆይተዋል። በአሁኑ ወቅት ግን በአየር ትራንስፖርት የመንገደኞች በረራ አገልግሎት መነቃቃት በማሳየቱ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የውጭ ሀገራት አየር መንገዶች ሰባት ደርሰዋል። በአማካይ በቀን ሰባት የውጭ ሀገራት አየር መንገድ አውሮፕላኖች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ላይ ናቸው።
እንደ ኤር ናቪጌሽን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ሽመልስ ገለጻ፤ ኮሮና በሽታ በዓለም ላይ ከተስፋፋ በኋላ በድጋሚ ወደ ኢትዮጵያ መብረር ከጀመሩ አየር መንገዶች መካከል የዱባይ ፣ የቱርክ፣ የኳታር፣ የግብጽ፣ የሱዳን፣የኬንያ እና የጅቡቲ አየር መንገዶች ይገኙበታል። በአሁኑ ወቅትም በአማካይ ሁለት መደበኛ በረራ እና አምስት መደበኛ ያልሆኑ የመንገደኛ አገልግሎት የሚሰጡ አውሮፕላኖች ከውጭ ሀገራት ወደ ኢትዮጵያ እየበረሩ ይገኛሉ።
ጨፌ ኦሮሚያ 12ኛ መደበኛ፣ 5ኛ ዓመት 5ኛ የሥራ ዘመን ጉባዔውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ጉባኤው ዛሬ እና ነገ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ እንደሚመክር የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባዔ ወይዘሮ ሎሚ በዶ ተናግረዋል፡፡
በሁለት ቀን ውሎው የ2012 ዓ.ም የሥራ አፈፃፀም እንደሚገመግምም ነው የተናገሩት፡፡
በኮሮና ምክንያት ችግር የደረሰባቸው 30 ሺ 87 ዜጎች ከስደት ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል
*******************
(ኢ ፕ ድ)
አዲስ አበባ ፤ በተለያዩ ሀገራት በስደት ላይ የነበሩ እና በኮሮና በሽታ ምክንያት ችግር ውስጥ የወደቁ 30ሺህ 87 ኢትዮጵያውያን ወደሀገር ውስጥ መመለስ መቻሉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት፤ ዜጋ ተኮር የመንግስት ፖሊሲ ተግባራዊ በመደረጉ በኮሮና ምክንያት ለችግር የተጋለጡ እና በስደት የነበሩ 30ሺህ 87 ኢትዮጵያውያንን ወደሀገራቸው መመለስ ተችሏል።
በፍቃደኝነት ወደሃገራቸው የተመለሱ ዜጎች በአብዛኛው ከገልፍ እና ከጎረቤት ሀገራት የመጡ ናቸው።
አምባሳደር ዲና እንደገለጹት፤ በተለይ በአረብ ሀገራት እና በጎረቤት ሀገሮች በስደት የነበሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን በኮሮና በሽታ ወቅት ስራ በማጣት ጎዳና ላይ ሲወድቁ በየሀገራቱ የሚገኙ ቆንስላዎች ክትትል አድርገዋል። በተለይ በቤይሩት ከስራ ተባረው እና በመንገድ ላይ ተጥለው የነበሩ ኢትዮጵያውያንን በቆንስላው አማካኝነት ድጋፍ በማድረግ በፍቃደኝነት መመለስ ተችሏል።
በዚህ መሰረት ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ከተደረጉ 30ሺ በላይ ዜጎች መካከል ከቤይሩት 656 ዜጎች፤ ከአቡዳቢ 72፤ ከሳዑዲ አረቢያ 3ሺህ 539፣ ከኩዌት ደግሞ 1 ሺህ 23 ዜጎች እንዲሁም በድንበር በኩል ከተለያዩ ጎረቤት ሀገራት 4ሺህ 792 ዜጎች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።
https://www.press.et/Ama/?p=35961