በሕንድ በአንድ ቀን ከ15 ሺህ በላይ የኮሮናቫይረስ ህሙማን ተገኙ
----------------------------------------------------------------
ሕንድ በአንድ ቀን ውስጥ 15 ሺህ 413 በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎችን ማግኘቷን በምርመራ አረጋገጠች።
ይህም በአገሪቱ ወረርሽኙ መገኘቱ ከታወቀ ወዲህ በአንድ ቀን የተገኘው ከፍተኛው የህሙማን ቁጥር ነው።
በዛሬው ዕለት የተገኘው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ከፍተኛ ቁጥር እስካሁን በሕንድ ያለውን አጠቃላይ የህሙማን ብዛት ወደ 410 ሺህ 461 ያደረሰው ሲሆን ይህም ከአሜሪካ፣ ከብራዚልና ከሩሲያ ቀጥሎ ሕንድን በዓለም አራተኛ ደረጃ ላይ እንድትቀመጥ አድርጓታል።
ከዚህ በተጨማሪ በበሽታው ምክንያት 306 መሞታቸው በዛሬው ዕለት የተነገረ ሲሆን በአጠቃላይ በአገሪቱ የሞቱትን ሰዎች ብዛት ወደ 13 ሺህ 254 አድርሶታል። ቢ ቢ ሲ
----------------------------------------------------------------
ሕንድ በአንድ ቀን ውስጥ 15 ሺህ 413 በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎችን ማግኘቷን በምርመራ አረጋገጠች።
ይህም በአገሪቱ ወረርሽኙ መገኘቱ ከታወቀ ወዲህ በአንድ ቀን የተገኘው ከፍተኛው የህሙማን ቁጥር ነው።
በዛሬው ዕለት የተገኘው በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ከፍተኛ ቁጥር እስካሁን በሕንድ ያለውን አጠቃላይ የህሙማን ብዛት ወደ 410 ሺህ 461 ያደረሰው ሲሆን ይህም ከአሜሪካ፣ ከብራዚልና ከሩሲያ ቀጥሎ ሕንድን በዓለም አራተኛ ደረጃ ላይ እንድትቀመጥ አድርጓታል።
ከዚህ በተጨማሪ በበሽታው ምክንያት 306 መሞታቸው በዛሬው ዕለት የተነገረ ሲሆን በአጠቃላይ በአገሪቱ የሞቱትን ሰዎች ብዛት ወደ 13 ሺህ 254 አድርሶታል። ቢ ቢ ሲ
ግብጽ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ከጎኗ ለማሰለፍ የምታደርገው ጥረት ከእምነቱ አስተምህሮ ውጪ መሆኑ ተገለጸ
. ግብጾች፣ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን ስነልቦናም ሆነ አገራዊ አቋም አያውቁትም
አዲስ አበባ፡- ግብጽ በአባይ ጉዳይ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከጎኗ ለማሰለፍ የምታደርገው ጥረት የኢትዮጵያውያንን የአገር ፍቅር ስሜት ያላገናዘበና ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ውጪ በመሆኑ ከዚህ ድርጊቷ ልትቆጠብ እንደሚገባ የእምነቱ ከፍተኛ አባቶች ተናገሩ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የመስጊድ ኢማም ሼህ የሱፍ ቃሲም በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳሉት፤ ግብጽ አባይን የምትመለከትበትና የምታስተሳስርበት መቀነት አጥሯታል። አሁን አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከጎኔ ይቆማሉ የሚል አሉባልታ በመንዛት ላይ እንደሆነች መስማታቸውን ተናግረዋል። ይሁን እንጂ ጉዳዩ የኢትዮጵያን ሙስሊሞች ስነልቦናም ሆነ አገራዊ አቋም ፈጽሞ የማይወክልና ከእስልምና አስተምህሮት ውጪ ተራ ወሬ ተደርጎ የሚቆጠር እንደሆነም ገልጸዋል።
ግብጽ ከዚህ በፊት ስትከተላቸው የነበሩት የውዥንብር መንገዶች ረዥም ርቀት እንደማይወስዷት ተረድታለች። በዓለም የዲፕሎማሲና የፖለቲካ ሚዛን
ውሃ የማያነሱ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አቋም ጠንከር ባለ ቁጥር እንድትገነዘብ እያደረጋት ነው። በዚህ የተነሳም የኢትዮጵያውያንን ጠንከር ያለ አቋም ማላላት፣ሲቀጥልም ርስ በርስ እንዲከፋፈሉ በማድረግ የከረሩ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ማድረግን አልማ እየሰራች እንደሆነም ሼህ የሱፍ አስረድተዋል።
በየትኛውም ዓለም የሚገኙ ሙስሊሞች ወንድማማቾች ናቸው። ለዚህም የሚያስተሳስራቸው የእምነታቸው መሰረት የሆነው ‹‹ላኢላሃኢለሏህ ሙሐመድ ረሱለሏህ›› በአሏህ አንድነት እና በሙሐመድ (ሱ.ዐ.ወ) መላዕክተኛነት ማመን ነው። ነገር ግን ግብጽ የኢትዮጵያውያ ሙስሊሞችን ከግብጻውያን የእምነት ወንድሞቻቸው ጋር የሚያስተሳስራቸው የ ‹‹አባይ ወንዝ›› እንደሆነ አድርጋ ይዛ ብቅ ማለቷ በሙስሊሞች ዘንድ የተቀባይነት ቀቢጸ ተስፋን በማሳደሯ ከመሆን እንደማይዘል ሼህ የሱፍ አብራርተዋል።
በእስልምና ሃይማት ዙሪያ ጥናት በማድረግ የሚታወቁት ኡስታዝ ባህሩ ኡመር በበኩላቸው እንደገለፁት የእስልምና አስተምህሮ እኩልነትን፣ ፍትሃዊነትን ይሰብካል፣ ያስተምራል። ‹‹ወንድማማቾች
በአንድ ውሃ አጠቃቀም ላይ ቢጋጩ እንኳን›› ለውሃው ቅርበት ያለው ቀድሞ ይጠቀምና ወንድሙንም እንዲጠቀም ያድርግ›› የሚል ፍትሃዊ አስተምሮን እንደሚከተል በተለያዩ ‹‹ሐዲሶች›› ተጠቅሷል። ስለዚህ ፍትሃዊ ያልሆነና ሌሎችን የሚያስከፋ ተግባር መፈጸምን በእምነቱ አስተምህሮ በፍጹም የተከለከለ እንደሆነ አስረድተዋል።
ስለ እያንዳንዱ ነገር እምነቱ ፍትሃዊ የሆኑ አሰራሮችን ያስቀመጠ መሆኑ እየታወቀ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በአባይ ጉዳይ እኔን ይደግፋሉ፤ ይሄን ሐቅ በውስጥ ሰዎቼ አረጋግጫለሁ፤ የምትለው ግብጽ በፍጹም ከፕሮፓጋንዳነት ያለፈ እንደማይሆን ኡስታዝ ባህሩ ይናገራሉ።
‹‹ኢትዮጵያ አትጠቀም እኔ ልጠቀም›› የሚለው አስተሳሰብ ከሐይማኖት አንጻር ጭራሹን በሸሪዓ የተከለከለ እንደሆነ የተናገሩት ኡስታዝ ባህሩ ኡመር በእስልምና አስተምህሮ ፍትሃዊ ያልሆነ ጉዳይ ፈጽሞ የተከለከለ እንደሆነ ገልጸዋል።
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=34814
. ግብጾች፣ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን ስነልቦናም ሆነ አገራዊ አቋም አያውቁትም
አዲስ አበባ፡- ግብጽ በአባይ ጉዳይ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከጎኗ ለማሰለፍ የምታደርገው ጥረት የኢትዮጵያውያንን የአገር ፍቅር ስሜት ያላገናዘበና ከሃይማኖቱ አስተምህሮ ውጪ በመሆኑ ከዚህ ድርጊቷ ልትቆጠብ እንደሚገባ የእምነቱ ከፍተኛ አባቶች ተናገሩ።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን የመስጊድ ኢማም ሼህ የሱፍ ቃሲም በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳሉት፤ ግብጽ አባይን የምትመለከትበትና የምታስተሳስርበት መቀነት አጥሯታል። አሁን አሁን ደግሞ ይባስ ብሎ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን ከጎኔ ይቆማሉ የሚል አሉባልታ በመንዛት ላይ እንደሆነች መስማታቸውን ተናግረዋል። ይሁን እንጂ ጉዳዩ የኢትዮጵያን ሙስሊሞች ስነልቦናም ሆነ አገራዊ አቋም ፈጽሞ የማይወክልና ከእስልምና አስተምህሮት ውጪ ተራ ወሬ ተደርጎ የሚቆጠር እንደሆነም ገልጸዋል።
ግብጽ ከዚህ በፊት ስትከተላቸው የነበሩት የውዥንብር መንገዶች ረዥም ርቀት እንደማይወስዷት ተረድታለች። በዓለም የዲፕሎማሲና የፖለቲካ ሚዛን
ውሃ የማያነሱ መሆናቸውን የኢትዮጵያ አቋም ጠንከር ባለ ቁጥር እንድትገነዘብ እያደረጋት ነው። በዚህ የተነሳም የኢትዮጵያውያንን ጠንከር ያለ አቋም ማላላት፣ሲቀጥልም ርስ በርስ እንዲከፋፈሉ በማድረግ የከረሩ ግጭቶች እንዲፈጠሩ ማድረግን አልማ እየሰራች እንደሆነም ሼህ የሱፍ አስረድተዋል።
በየትኛውም ዓለም የሚገኙ ሙስሊሞች ወንድማማቾች ናቸው። ለዚህም የሚያስተሳስራቸው የእምነታቸው መሰረት የሆነው ‹‹ላኢላሃኢለሏህ ሙሐመድ ረሱለሏህ›› በአሏህ አንድነት እና በሙሐመድ (ሱ.ዐ.ወ) መላዕክተኛነት ማመን ነው። ነገር ግን ግብጽ የኢትዮጵያውያ ሙስሊሞችን ከግብጻውያን የእምነት ወንድሞቻቸው ጋር የሚያስተሳስራቸው የ ‹‹አባይ ወንዝ›› እንደሆነ አድርጋ ይዛ ብቅ ማለቷ በሙስሊሞች ዘንድ የተቀባይነት ቀቢጸ ተስፋን በማሳደሯ ከመሆን እንደማይዘል ሼህ የሱፍ አብራርተዋል።
በእስልምና ሃይማት ዙሪያ ጥናት በማድረግ የሚታወቁት ኡስታዝ ባህሩ ኡመር በበኩላቸው እንደገለፁት የእስልምና አስተምህሮ እኩልነትን፣ ፍትሃዊነትን ይሰብካል፣ ያስተምራል። ‹‹ወንድማማቾች
በአንድ ውሃ አጠቃቀም ላይ ቢጋጩ እንኳን›› ለውሃው ቅርበት ያለው ቀድሞ ይጠቀምና ወንድሙንም እንዲጠቀም ያድርግ›› የሚል ፍትሃዊ አስተምሮን እንደሚከተል በተለያዩ ‹‹ሐዲሶች›› ተጠቅሷል። ስለዚህ ፍትሃዊ ያልሆነና ሌሎችን የሚያስከፋ ተግባር መፈጸምን በእምነቱ አስተምህሮ በፍጹም የተከለከለ እንደሆነ አስረድተዋል።
ስለ እያንዳንዱ ነገር እምነቱ ፍትሃዊ የሆኑ አሰራሮችን ያስቀመጠ መሆኑ እየታወቀ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በአባይ ጉዳይ እኔን ይደግፋሉ፤ ይሄን ሐቅ በውስጥ ሰዎቼ አረጋግጫለሁ፤ የምትለው ግብጽ በፍጹም ከፕሮፓጋንዳነት ያለፈ እንደማይሆን ኡስታዝ ባህሩ ይናገራሉ።
‹‹ኢትዮጵያ አትጠቀም እኔ ልጠቀም›› የሚለው አስተሳሰብ ከሐይማኖት አንጻር ጭራሹን በሸሪዓ የተከለከለ እንደሆነ የተናገሩት ኡስታዝ ባህሩ ኡመር በእስልምና አስተምህሮ ፍትሃዊ ያልሆነ ጉዳይ ፈጽሞ የተከለከለ እንደሆነ ገልጸዋል።
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=34814
www.press.et
ግብጽ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞችን ከጎኗ ለማሰለፍ የምታደርገው ጥረት ከእምነቱ አስተምህሮ ውጪ መሆኑ ተገለጸ | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
ግብጽ የህዳሴ ግድብ ድርድር በሂደት ላይ እያለ ጉዳዩን ወደ መንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት መውሰዷን ሱዳን አወገዘች
*****************************************
(ኢ ፕ ድ)
ግብጽ የህዳሴ ግድብ ድርድር በሂደት ላይ እያለ ጉዳዩ ወደ መንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት መውሰዷን እንደማይቀበለው የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ኡመር ቀመርዲን ተናገሩ።
ሚኒስትር ዴኤታው ለቢቢሲ አረበኛው እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ውሃ ሙሌት ብትጀምር ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ወደ ግጭት አትገባም።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ችግሩ በድፕሎማሲ መንገድ ብቻ እንዲፈታ ሱዳን እንደምትሰራ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
*****************************************
(ኢ ፕ ድ)
ግብጽ የህዳሴ ግድብ ድርድር በሂደት ላይ እያለ ጉዳዩ ወደ መንግስታቱ ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት መውሰዷን እንደማይቀበለው የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ኡመር ቀመርዲን ተናገሩ።
ሚኒስትር ዴኤታው ለቢቢሲ አረበኛው እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ ውሃ ሙሌት ብትጀምር ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ወደ ግጭት አትገባም።
ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም ችግሩ በድፕሎማሲ መንገድ ብቻ እንዲፈታ ሱዳን እንደምትሰራ መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
ከጭምብል አጠቃቀማችን የሚታረሙ ስህተቶች
**************************
(ኢፕድ)
ዓለማችን ከምታስበው በላይ ጨካኝ፣ ከምታምነው በላይ ኃያልና ከምትገምተውም በላይ ጠንካራ በሆነባት የኖቭል ኮሮና ቫይረስ ምክንያት በከባድ የስቃይ ምዕራፍ ውስጥ ትገኛለች። ቫይረሱም በቴክኖሎጂ የመጠቁ፣በኢኮኖሚያ የበለፀጉና በህክምና አገልግሎት አቅርቦትም ሆነ ጥራት ከፊተኞቹ ተርታ ስማቸው የሚጠራላቸው አገራትን ሳይቀር አስጨንቃል። አሸብራል።
የጤናው ዘርፍ ጠቢቢን ብሎም የምርምር ተቋማትም ዓለም ከቫይረሱ ጋር ከተዋወቀችበት ጊዜ አንስቶ መድኃኒትና ክትባት ፍለጋ ሌት ተቀን ደክመዋል። የወረርሽኙን ስርጭት ለመከላከልና ጉዳቱን ለመቀነስ መድኃኒት ከሚሆኑት አንዱ የአፍን አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል መጠቀም መሆኑን ከመጠቆም የተሻገረ መፍትሔን መስጠት ግን አልሆነላቸውም።
ኢትዮጵያም ይህን የመፍትሔ አቅጣጫ በመከተል ዜጎቻ ጭንብል መጠቀም ግዴታቸው መሆኑን ካሳወቁ አገራት መካከል አንዷ ናት። ይሁንና ህዝቦቿ ተገቢውን የጭንብል አጠቃቀም ሂደት መከተልና ጥንቃቄ ማድረግ ላይ በግልፅ የሚታይ ድክመት እንዳለባቸው ይነሳል።
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወይዘሪት ሜሮን ሙሉጌታም፣ ‹‹በመዲናዋ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብልን በአግባቡ ከሚጠቀሙት ይልቅ የማይጠቀሙት ይበልጣሉ፣ በተለይ የአንዳንዱ ተግባር በጋራ ዓለምና ሰማይ ስር የብቻውን ጤና የሚያጣጣም፡ የሌሎችን ሕይወት እያደፈረሰ የራሱን ለማጥራት የሚታትር ይመስላል›› ትላለች።
ጭንብል በሚደረግበት ጊዜ አፍና አፍንጫን እንዲሁም አገጭ ድረስ መሸፈን እንደሚገባ ቢገለፅም፤ በርካቶች ከአፍንጫቸው ዝቅ በማድረግ ለአፋቸው ብቻ ሲጠቀሙ›› ይስተዋላል የምትለው ሜሮን፣አንዳንዱ ደግሞ ጭንብል ለመግዛት ሞክሮ ሲያስቀምጥ መታዘቧን ታስታውሳለች።
ከመሰል የአጠቃቀም ድክመት ባሻገር በአሁን ወቅት በየመንገዱ የሚሸጡና ከጨርቅ የሚሠሩ ጭንብሎች ምን ያህል የመከላከል አቅም አላቸው? የሚለውን በቅጡ አለመታወቁ መሆኑን የምትገልጸው ሜሮን፣ጭንብሎቹ በማን እና በምን መሠራት እንዳለባቸው የሚገልጽ መረጃ አለማግኘቷን ትመሰክራለች።
ከደረጃው መለየት አንስቶ አጠቃቀምና አወጋገድን በሚመለከት ሁሉንም የሚያስማማና የሚስማማ ሃሳብ መፍጠር እንዳልተቻለ በመጠቆም እነዚህን የተራራቁ የግንዛቤ ክፍተቶችን ማገናኘትም ለነገ የማይቀመጥ የቤት ሥራ እንዳልሆነ ታስገነዝባለች።
በተለይ ለውጥ በአንድነት እንጂ በመለያየት እውን አይሆንምና ወይዘሪት ሜሮን መደረግ ስላለበት ስትገልጽም፣ቫይረሱ እጅ እንድንሰጥ የሚያደርጉ መሰል ስህተታችንን ሳይውል ሳያድር በመሞረድና በማስተካከል በተለይ በቸልተኝነት በማድረግ በሰውነታችን ለሰው ሁሉ ጤና ጥብቅና እንቁም›› ስትልም ነው ጥሪ ያቀረበችው።
የየካቲት 23 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህሩ አቶ ኡመር አብዱም.፣ህብረተሰቡ ‹‹ከጭንብሉ ጋር እንዴት ተዋውቆና ተግባብቶ መኖር እንደከበደው ለመረዳት የአንዳንዶቹን ምግባርና ተግባር ማየት በቂ ነው›› ይላል።
በከፍተኛ ጥንቃቄ ፋይዳውን ተገንዝቦ ጭንብሉን በአግባቡ የሚጠቀም ባይጠፋም የአንዳንዱ የጭንብል አጠቃቀም ራሱን አስደስቶ ሌላውን የሚያስኮርፍ መሆኑንም ያነሳሉ። ጭንብል የሚለብሱት የራሳቸውን ጤና ለመጠበቅ የማይመስላቸውና የፀጥታ አካላትን ሲመለከት ጭንብል የሚያጠልቁም ለዚህ እሳቤ ምስክር አድርጎ ያቀርባል።
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=34817
**************************
(ኢፕድ)
ዓለማችን ከምታስበው በላይ ጨካኝ፣ ከምታምነው በላይ ኃያልና ከምትገምተውም በላይ ጠንካራ በሆነባት የኖቭል ኮሮና ቫይረስ ምክንያት በከባድ የስቃይ ምዕራፍ ውስጥ ትገኛለች። ቫይረሱም በቴክኖሎጂ የመጠቁ፣በኢኮኖሚያ የበለፀጉና በህክምና አገልግሎት አቅርቦትም ሆነ ጥራት ከፊተኞቹ ተርታ ስማቸው የሚጠራላቸው አገራትን ሳይቀር አስጨንቃል። አሸብራል።
የጤናው ዘርፍ ጠቢቢን ብሎም የምርምር ተቋማትም ዓለም ከቫይረሱ ጋር ከተዋወቀችበት ጊዜ አንስቶ መድኃኒትና ክትባት ፍለጋ ሌት ተቀን ደክመዋል። የወረርሽኙን ስርጭት ለመከላከልና ጉዳቱን ለመቀነስ መድኃኒት ከሚሆኑት አንዱ የአፍን አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል መጠቀም መሆኑን ከመጠቆም የተሻገረ መፍትሔን መስጠት ግን አልሆነላቸውም።
ኢትዮጵያም ይህን የመፍትሔ አቅጣጫ በመከተል ዜጎቻ ጭንብል መጠቀም ግዴታቸው መሆኑን ካሳወቁ አገራት መካከል አንዷ ናት። ይሁንና ህዝቦቿ ተገቢውን የጭንብል አጠቃቀም ሂደት መከተልና ጥንቃቄ ማድረግ ላይ በግልፅ የሚታይ ድክመት እንዳለባቸው ይነሳል።
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ የሆነችው ወይዘሪት ሜሮን ሙሉጌታም፣ ‹‹በመዲናዋ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብልን በአግባቡ ከሚጠቀሙት ይልቅ የማይጠቀሙት ይበልጣሉ፣ በተለይ የአንዳንዱ ተግባር በጋራ ዓለምና ሰማይ ስር የብቻውን ጤና የሚያጣጣም፡ የሌሎችን ሕይወት እያደፈረሰ የራሱን ለማጥራት የሚታትር ይመስላል›› ትላለች።
ጭንብል በሚደረግበት ጊዜ አፍና አፍንጫን እንዲሁም አገጭ ድረስ መሸፈን እንደሚገባ ቢገለፅም፤ በርካቶች ከአፍንጫቸው ዝቅ በማድረግ ለአፋቸው ብቻ ሲጠቀሙ›› ይስተዋላል የምትለው ሜሮን፣አንዳንዱ ደግሞ ጭንብል ለመግዛት ሞክሮ ሲያስቀምጥ መታዘቧን ታስታውሳለች።
ከመሰል የአጠቃቀም ድክመት ባሻገር በአሁን ወቅት በየመንገዱ የሚሸጡና ከጨርቅ የሚሠሩ ጭንብሎች ምን ያህል የመከላከል አቅም አላቸው? የሚለውን በቅጡ አለመታወቁ መሆኑን የምትገልጸው ሜሮን፣ጭንብሎቹ በማን እና በምን መሠራት እንዳለባቸው የሚገልጽ መረጃ አለማግኘቷን ትመሰክራለች።
ከደረጃው መለየት አንስቶ አጠቃቀምና አወጋገድን በሚመለከት ሁሉንም የሚያስማማና የሚስማማ ሃሳብ መፍጠር እንዳልተቻለ በመጠቆም እነዚህን የተራራቁ የግንዛቤ ክፍተቶችን ማገናኘትም ለነገ የማይቀመጥ የቤት ሥራ እንዳልሆነ ታስገነዝባለች።
በተለይ ለውጥ በአንድነት እንጂ በመለያየት እውን አይሆንምና ወይዘሪት ሜሮን መደረግ ስላለበት ስትገልጽም፣ቫይረሱ እጅ እንድንሰጥ የሚያደርጉ መሰል ስህተታችንን ሳይውል ሳያድር በመሞረድና በማስተካከል በተለይ በቸልተኝነት በማድረግ በሰውነታችን ለሰው ሁሉ ጤና ጥብቅና እንቁም›› ስትልም ነው ጥሪ ያቀረበችው።
የየካቲት 23 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህሩ አቶ ኡመር አብዱም.፣ህብረተሰቡ ‹‹ከጭንብሉ ጋር እንዴት ተዋውቆና ተግባብቶ መኖር እንደከበደው ለመረዳት የአንዳንዶቹን ምግባርና ተግባር ማየት በቂ ነው›› ይላል።
በከፍተኛ ጥንቃቄ ፋይዳውን ተገንዝቦ ጭንብሉን በአግባቡ የሚጠቀም ባይጠፋም የአንዳንዱ የጭንብል አጠቃቀም ራሱን አስደስቶ ሌላውን የሚያስኮርፍ መሆኑንም ያነሳሉ። ጭንብል የሚለብሱት የራሳቸውን ጤና ለመጠበቅ የማይመስላቸውና የፀጥታ አካላትን ሲመለከት ጭንብል የሚያጠልቁም ለዚህ እሳቤ ምስክር አድርጎ ያቀርባል።
ለተጨማሪ https://www.press.et/Ama/?p=34817
www.press.et
ከጭምብል አጠቃቀማችን የሚታረሙ ስህተቶች | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
የኮቪድ-19 አንቲቦዲ (Antibody) የቅኝት ዳሰሳ አስመልክቶ የወጣ መግለጫ
በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ምርመራ ከጥር 29 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የተጀመረ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ላቦራቶሪዎች እስከ ሰኔ 14 ቀን 2012 ዓ.ም 216¸328 ምርመራ ተደርጓል። ይህ የምርመራ አይነት የኮቪደ-19 በሽታ ያለበት ሰው ላይ ቫይረሱን ለመለየት የሚረዳ የሞለኪዩላር ምርመራ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በማህበረሰብ ውስጥ ያለውን የበሽታ ስርጭት ለመረዳት (surveillance) እና በአንጻሩ ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም ይበልጥ ተጋላጭ በሆኑት የማህበረሰባችን ክፍሎች ላይ ያለውን የኮቪድ-19 በሽታ ስርጭት ለማወቅ የሚረዳ አንቲቦዲ ምርመራ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል፡፡ ይህ የአንቲቦዲ የቅኝትና ዳሰሳ ምርመራ አይነት በአገራችን ለምርምር ለመጠቀም እና ከላይ የተጠቀሱትን ዓላማዎች ለማሳካት ከሰኔ 15 እሰከ ሀምሌ 7 ቀን 2012 ድረስ በሀገራችን የሚካሄድ ይሆናል።
አንቲቦዲ ማለት ሰውነታችን ለበሽታ በሚጋለጠበት ወቅት ለበሽታው ከተጋለጠ ከአንድ እስከ ሶስት ሳምንት ድረስ በሽታውን ለመከላከል ሰውነታችን የሚያመርታቸው የበሽታ ተከላካዩች ናቸው። በሰውነታችን ውስጥ የአንቲቦዲ መመረት በእድሜ፣ የአመጋገብ ሁኔታ፣ የምንጠቀማቸው መድሁኒቶች፣ የበሽታው ከባድነት እና ተጓዳኝ በሽታዎች ላይ ይወሰናል። ምርመራው ከሰውነታችን ከ3-5 ሚሊ ሊትር ደም ናሙና በመውሰድ የሚደረግ ሲሆን የበሽታው ተከላካዮች (አንቲቦዲ) እንደየበሽታው ዓይነት የሚለያዩ ሲሆን ምርመራው ኮቪድ-19 ለመካላከል እና ለ መቆጣጠር ለሚደረገው የቅኝት ዳሰሳ ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ነገር ግን የአንቲቦዲ ምርመራ ውጤትን ብቻ ተጠቅሞ ህክምና መስጠት አይቻልም።
ይህ የቅኝት ዳሰሳ በሀገራችን ያለውን የኮሮና ቫይረስ በሽታ (ኮቪድ-19) ስርጭት ለማወቅ ከሰኔ 15 ቀን 2012 ጀምሮ በአዲስ አበባ፣ ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ይካሄዳል። በመሆኑም ህብረተሰቡ፣ የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለትግበራው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ እንጠይቃለን።
በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ምርመራ ከጥር 29 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ የተጀመረ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ላቦራቶሪዎች እስከ ሰኔ 14 ቀን 2012 ዓ.ም 216¸328 ምርመራ ተደርጓል። ይህ የምርመራ አይነት የኮቪደ-19 በሽታ ያለበት ሰው ላይ ቫይረሱን ለመለየት የሚረዳ የሞለኪዩላር ምርመራ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በማህበረሰብ ውስጥ ያለውን የበሽታ ስርጭት ለመረዳት (surveillance) እና በአንጻሩ ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም ይበልጥ ተጋላጭ በሆኑት የማህበረሰባችን ክፍሎች ላይ ያለውን የኮቪድ-19 በሽታ ስርጭት ለማወቅ የሚረዳ አንቲቦዲ ምርመራ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑ ይታመናል፡፡ ይህ የአንቲቦዲ የቅኝትና ዳሰሳ ምርመራ አይነት በአገራችን ለምርምር ለመጠቀም እና ከላይ የተጠቀሱትን ዓላማዎች ለማሳካት ከሰኔ 15 እሰከ ሀምሌ 7 ቀን 2012 ድረስ በሀገራችን የሚካሄድ ይሆናል።
አንቲቦዲ ማለት ሰውነታችን ለበሽታ በሚጋለጠበት ወቅት ለበሽታው ከተጋለጠ ከአንድ እስከ ሶስት ሳምንት ድረስ በሽታውን ለመከላከል ሰውነታችን የሚያመርታቸው የበሽታ ተከላካዩች ናቸው። በሰውነታችን ውስጥ የአንቲቦዲ መመረት በእድሜ፣ የአመጋገብ ሁኔታ፣ የምንጠቀማቸው መድሁኒቶች፣ የበሽታው ከባድነት እና ተጓዳኝ በሽታዎች ላይ ይወሰናል። ምርመራው ከሰውነታችን ከ3-5 ሚሊ ሊትር ደም ናሙና በመውሰድ የሚደረግ ሲሆን የበሽታው ተከላካዮች (አንቲቦዲ) እንደየበሽታው ዓይነት የሚለያዩ ሲሆን ምርመራው ኮቪድ-19 ለመካላከል እና ለ መቆጣጠር ለሚደረገው የቅኝት ዳሰሳ ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው። ነገር ግን የአንቲቦዲ ምርመራ ውጤትን ብቻ ተጠቅሞ ህክምና መስጠት አይቻልም።
ይህ የቅኝት ዳሰሳ በሀገራችን ያለውን የኮሮና ቫይረስ በሽታ (ኮቪድ-19) ስርጭት ለማወቅ ከሰኔ 15 ቀን 2012 ጀምሮ በአዲስ አበባ፣ ድሬደዋ ከተማ አስተዳደሮችን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ይካሄዳል። በመሆኑም ህብረተሰቡ፣ የጤና ባለሙያዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለትግበራው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ እንጠይቃለን።
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 131 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው
.በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1297 ደርሷል
*****************************
(ኢፕድ)
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3238 የላብራቶሪ ምርመራ 131 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 4663 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 26 (10 ከጤና ተቋም እና 16 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን አንድ ናሙና ከማህበረሰብ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ሰባ አምስት (75) ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት ሰማንያ አራት (84) ሰዎች (79 ሰዎች ከ አዲስ አበባ፣ 2ሰዎች ከኦሮሚያ፣ 2 ሰዎች ከትግራይ እና 1 ሰው ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1297 ነው።
.በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1297 ደርሷል
*****************************
(ኢፕድ)
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3238 የላብራቶሪ ምርመራ 131 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 4663 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 26 (10 ከጤና ተቋም እና 16 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን አንድ ናሙና ከማህበረሰብ የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶበታል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ሰባ አምስት (75) ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት ሰማንያ አራት (84) ሰዎች (79 ሰዎች ከ አዲስ አበባ፣ 2ሰዎች ከኦሮሚያ፣ 2 ሰዎች ከትግራይ እና 1 ሰው ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1297 ነው።
ከአንድ እናት በአንድ ጊዜ የተወለዱ ሦስት ጨቅላ ህጻናት ኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው
=============================
በሜክሲኮ ከአንዲት እናት በአንድ ጊዜ አዲስ የተወለዱ ሦስት ጨቅላ ህጻናት በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ።
ጨቅላ ህጻናቱ በቫይረሱ አንዴት ሊያዙ እንደቻሉ በጤና ባለሙያዎች ላይ ግርታን የፈጠረ ሲሆን፤ የጤና ባለሥልጣናትም ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ነገር ሰምተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ጨቅላ ህጻናቱ ምርመራ የተደረገላቸው ከተወለዱ በኋላ በሰዓታት ውስጥ ሲሆን ቫይረሱ እንዳለበት ከታወቀ ማንኛውም ሰው ጋር ምንም ዓይነት ንክኪ አልነበራቸውም ተብሏል። ቢ ቢ ሲ
=============================
በሜክሲኮ ከአንዲት እናት በአንድ ጊዜ አዲስ የተወለዱ ሦስት ጨቅላ ህጻናት በኮሮናቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ።
ጨቅላ ህጻናቱ በቫይረሱ አንዴት ሊያዙ እንደቻሉ በጤና ባለሙያዎች ላይ ግርታን የፈጠረ ሲሆን፤ የጤና ባለሥልጣናትም ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ነገር ሰምተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ጨቅላ ህጻናቱ ምርመራ የተደረገላቸው ከተወለዱ በኋላ በሰዓታት ውስጥ ሲሆን ቫይረሱ እንዳለበት ከታወቀ ማንኛውም ሰው ጋር ምንም ዓይነት ንክኪ አልነበራቸውም ተብሏል። ቢ ቢ ሲ
በአዲስ አበባ ከተማ እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ መረጃዎችን ማግኘትና ሀሳብ መስጠት የሚቻልበት የኪነ ህንጻ እና ከተማ ማእከል ተከፈተ።
ማእከሉ መስቀል አደባባይ ፊትለፊት ላይ የተዘጋጀ ሲሆን የካፌ አገልግሎትና ዋይፋይ የተዘጋጀለት ነው።
በማእከሉ የትኛውም ዜጋ ስለከተማዋ እቅዶችና ፕሮጀክቶች መመልከትና የራሱን ሀሳብ በፅሁፍና በድምፅ መስጠት ይችላል።
የተሰጡት አስተያየቶች በቦታው የሚገኙ ባለሙያዎች በማሰባሰብ ለከንቲባው በየጊዜው የሚያቀርቡ ይሆናል።
የማእከሉ መቋቋም የከተማዋ ነዋሪ በከተማዋ ላይ ያለው ተሳትፎ እንዲጨምርና ስለ ከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ላይ ግንዛቤ እንዲፈጠርና ግልፅነት ለመፍጠር ያለመ ነው።
ማእከሉ መስቀል አደባባይ ፊትለፊት ላይ የተዘጋጀ ሲሆን የካፌ አገልግሎትና ዋይፋይ የተዘጋጀለት ነው።
በማእከሉ የትኛውም ዜጋ ስለከተማዋ እቅዶችና ፕሮጀክቶች መመልከትና የራሱን ሀሳብ በፅሁፍና በድምፅ መስጠት ይችላል።
የተሰጡት አስተያየቶች በቦታው የሚገኙ ባለሙያዎች በማሰባሰብ ለከንቲባው በየጊዜው የሚያቀርቡ ይሆናል።
የማእከሉ መቋቋም የከተማዋ ነዋሪ በከተማዋ ላይ ያለው ተሳትፎ እንዲጨምርና ስለ ከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ ስራዎች ላይ ግንዛቤ እንዲፈጠርና ግልፅነት ለመፍጠር ያለመ ነው።
ባለፉት 24 ሰዓት ተጨማሪ 185 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3775 የላቦራቶሪ ምርመራ 185 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።
በአጠቃላይ በአገሪቱ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 4ሺህ 848 ደርሷል።
ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው 184 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ 1 ሰው የውጭ ዜጋ ነው ተብሏል።
ቫይረሱ የተገኘባቸው 47 ወንዶች እና 138 ሴቶች ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸውም ከ3 ወር ህጻን እስከ 80 ዓመት እንደሚገኙም ተገልጿል።
ቫይረሱ የተገኘባቸው 160 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 2 ሰዎች ከሱማሌ ክልል፣ 7 ሰዎች ከኦሮሚያ፣ 1 ሰው ከሀረሪ ክልል፣ 4 ሰዎች ከአፋር ክልል፣ 2 ሰዎች ከአማራ ክልል፣ 1 ሰው ከጋምቤላ ክልል፣ 7 ሰዎች ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል እና 1 ሰው ከትግራይ ክልል መሆናቸውን ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 115 ሰዎች (81 ከአዲስ አበባ፣ 23 ከአማራ፣ 6 ከኦሮሚያ፣ 2 ከሀረሪ፣ 2 ከቤንሻንጉል ጉምዝና 1 ሰው ከትግራይ) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥርን 1412 አድርሶታል።
በአጠቃላይ ቫይረሱ ተገኝቶባቸው በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ 3 ሺህ 359 ሰዎች ሲሆኑ ከነዚህ መካከል 38 በፀና የታመሙ መሆናቸው ተገልጿል።
በኢትዮጵያ እስካሁን 223 ሺህ 341 የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጓል
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3775 የላቦራቶሪ ምርመራ 185 ሰዎች የኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።
በአጠቃላይ በአገሪቱ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 4ሺህ 848 ደርሷል።
ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው 184 ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ 1 ሰው የውጭ ዜጋ ነው ተብሏል።
ቫይረሱ የተገኘባቸው 47 ወንዶች እና 138 ሴቶች ሲሆኑ የዕድሜ ክልላቸውም ከ3 ወር ህጻን እስከ 80 ዓመት እንደሚገኙም ተገልጿል።
ቫይረሱ የተገኘባቸው 160 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣ 2 ሰዎች ከሱማሌ ክልል፣ 7 ሰዎች ከኦሮሚያ፣ 1 ሰው ከሀረሪ ክልል፣ 4 ሰዎች ከአፋር ክልል፣ 2 ሰዎች ከአማራ ክልል፣ 1 ሰው ከጋምቤላ ክልል፣ 7 ሰዎች ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል እና 1 ሰው ከትግራይ ክልል መሆናቸውን ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በትናንትናው ዕለት 115 ሰዎች (81 ከአዲስ አበባ፣ 23 ከአማራ፣ 6 ከኦሮሚያ፣ 2 ከሀረሪ፣ 2 ከቤንሻንጉል ጉምዝና 1 ሰው ከትግራይ) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥርን 1412 አድርሶታል።
በአጠቃላይ ቫይረሱ ተገኝቶባቸው በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ 3 ሺህ 359 ሰዎች ሲሆኑ ከነዚህ መካከል 38 በፀና የታመሙ መሆናቸው ተገልጿል።
በኢትዮጵያ እስካሁን 223 ሺህ 341 የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጓል
አሜሪካ በኢትዮጵያ፣ በሱዳንና በግብጽ መካከል የተፈረመውን የመርህ ስምምነት እንድታከብር የአገሪቷ ጥቁር የኮንግረስ አባላት አሳሰቡ
***************************
(ኢ ፕ ድ)
አሜሪካም ሆነች ሌሎች አለም አቀፍ አካላት በኢትዮጵያ፣ በሱዳን እና በግብጽ መካከል እአአ በ2015 የተፈረመውን የመርሆች ስምምነት እንዲያከብሩ የአሜሪካ ጥቁር የኮንግረስ አባላት ስብስብ አሳሰበ።
የኮንግረስ አባላቱ ትናንት ባወጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ አሜሪካም ሆነች ሌሎች ዓለም አቀፍ ተዋንያን በሶስቱ አገራት መካከል እአአ በ2012 የተፈረመው የመርህ ስምምነት ማክበር አለባቸው ብለዋል።
ሶስቱ አገራት ወደ ስምምነት እንዲመጡ በአካባቢው ያሉ ዲፕሎማቶች በተለይም የአፍሪካ ህብረት ጉዳዩን እንዲፈታው አሜሪካም ሆነች ሌሎች አካለት ማገዝ አለባቸው ነው ያሉት።
ድርድሩ በጋራ ተጠቃሚነት፣ በመተማማንና በዓለም አቀፍ ህጎች መሰረት መጓዝ አለበት ያሉት አባላቱ፤ ይህ ታላቅ ግድብ ሲጠናቀቅ ለአፍሪካ ትልቁ የሃይል ምንጭ በመሆን ለኢትዮጵያም ብቻ ሳይሆን ለጎረቤቶቿ ጭምር የሚጠቅም ነው ብለዋል።
ግድቡ ከሶስቱ አገራት አንጻር ያለውን ፋይዳ በተናጠል በመግለጫቸው ያብራሩት የኮንግረስ አባላቱ፤ የግድቡ መጠናቀቅ ለግብጽ ግብርናም ሆነ ለሚዋዥቀው የወንዙ የውሃ ፍሰት አስተማማኝ በሆነ መልኩ የውሃ አቅርቦቷን ያሳድግላታል ብለዋል።
በተመሳሳይም ግድቡ ለሱዳን የውሃ አቅርቦት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑን በመጥቀስ፤ በተለይም የደለል መጠንን በመቀነስ፣ ግብርናን በማስፋፋት የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦትን በማሳደግና የጎርፍ አደጋን በመከላከል በኩል ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። ለኢትዮጵያን ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚህ አንጻር የግድቡ መጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ለግብጽ እና ለሱዳን የውሃ፣ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እና ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ብሎም ለቀጣናው የግብርና ስራ ያለው አስተዋጾ የላቀ መሆኑን አባላቱ ገልጸዋል።
በተዘረዘሩት ምክንያቶች ጥቁር የአሜሪካ የኮንግረስ አባላት የግድቡን መጠናቀቅ እንደሚደግፉና ለዚህም ሰላማዊ ውይይቶችን እንደሚያበረታቱ ጠቅሰው፤ የአፍሪካ ህብረት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለሚያደርጉት ሰላማዊና ሁሉንም ተጠቃሚ ለሚያደርግ ጥረት ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
***************************
(ኢ ፕ ድ)
አሜሪካም ሆነች ሌሎች አለም አቀፍ አካላት በኢትዮጵያ፣ በሱዳን እና በግብጽ መካከል እአአ በ2015 የተፈረመውን የመርሆች ስምምነት እንዲያከብሩ የአሜሪካ ጥቁር የኮንግረስ አባላት ስብስብ አሳሰበ።
የኮንግረስ አባላቱ ትናንት ባወጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፤ አሜሪካም ሆነች ሌሎች ዓለም አቀፍ ተዋንያን በሶስቱ አገራት መካከል እአአ በ2012 የተፈረመው የመርህ ስምምነት ማክበር አለባቸው ብለዋል።
ሶስቱ አገራት ወደ ስምምነት እንዲመጡ በአካባቢው ያሉ ዲፕሎማቶች በተለይም የአፍሪካ ህብረት ጉዳዩን እንዲፈታው አሜሪካም ሆነች ሌሎች አካለት ማገዝ አለባቸው ነው ያሉት።
ድርድሩ በጋራ ተጠቃሚነት፣ በመተማማንና በዓለም አቀፍ ህጎች መሰረት መጓዝ አለበት ያሉት አባላቱ፤ ይህ ታላቅ ግድብ ሲጠናቀቅ ለአፍሪካ ትልቁ የሃይል ምንጭ በመሆን ለኢትዮጵያም ብቻ ሳይሆን ለጎረቤቶቿ ጭምር የሚጠቅም ነው ብለዋል።
ግድቡ ከሶስቱ አገራት አንጻር ያለውን ፋይዳ በተናጠል በመግለጫቸው ያብራሩት የኮንግረስ አባላቱ፤ የግድቡ መጠናቀቅ ለግብጽ ግብርናም ሆነ ለሚዋዥቀው የወንዙ የውሃ ፍሰት አስተማማኝ በሆነ መልኩ የውሃ አቅርቦቷን ያሳድግላታል ብለዋል።
በተመሳሳይም ግድቡ ለሱዳን የውሃ አቅርቦት ያለው ፋይዳ የጎላ መሆኑን በመጥቀስ፤ በተለይም የደለል መጠንን በመቀነስ፣ ግብርናን በማስፋፋት የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦትን በማሳደግና የጎርፍ አደጋን በመከላከል በኩል ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል። ለኢትዮጵያን ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑን አብራርተዋል።
ከዚህ አንጻር የግድቡ መጠናቀቅ ለኢትዮጵያ ለግብጽ እና ለሱዳን የውሃ፣ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እና ለምግብ ዋስትና መረጋገጥ ብሎም ለቀጣናው የግብርና ስራ ያለው አስተዋጾ የላቀ መሆኑን አባላቱ ገልጸዋል።
በተዘረዘሩት ምክንያቶች ጥቁር የአሜሪካ የኮንግረስ አባላት የግድቡን መጠናቀቅ እንደሚደግፉና ለዚህም ሰላማዊ ውይይቶችን እንደሚያበረታቱ ጠቅሰው፤ የአፍሪካ ህብረት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለሚያደርጉት ሰላማዊና ሁሉንም ተጠቃሚ ለሚያደርግ ጥረት ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
እህትማማቾች በካቲካላ ሞቱ
ታህሳስ 21 ቀን 1965 ዓ.ም የታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ እህትማማቾች በቅርብ ያገኙትን አረቄ በመጠጣታቸው ህይወታቸውን ስላጡ ታዳጊዎች ተተከታዩን ዘገባ አስነብቦ ነበር።
ወይዘሪት ብዙነሽ ገብሬና ወይዘሪት እመቤት ገብሬ የተባሉ እህትማማቾች የእህል አረቄ ጠጥተው መሞታቸውን ከሸዋ ፖሊስ ማስታወቂያ ክፍል የተገኘው ዜና ገለጠ። ልጆቹ ለሞት የበቁት ወላጅ እናታቸው አረቄውን ካወጡ በኋላ አልጋ ስር አስቀምጠውት ወደ ገበያ ሲሄዱ ከተቀመጠበት ቦታ አንስተው በመጠጣታቸው ነው።
ሟቾቹ አረቄውን እንደጠጡ በያሉበት ተዘርረው ወድቀው ነበር። በኋላ ግን ሰው ደርሶ ለህክምና ፍቼ ጤና ጣቢያ ተወስደው ህክምና ቢደረግላቸውም ለመዳን ተስፋ በማጣታቸው በ 10 ሰዓት ልዩነት ሁለቱም ህይወታቸውን አጥተዋል።
በሁለቱ እህትማማቾች ላይ ይህ የሞት አደጋ የደረሰው ታህሳስ አራት ቀን 1965 ዓ.ም በሰላሌ አውራጃ በግራር ጃርሶ ወረዳ ግዛት ፍቼ ከተማ ውስጥ ነው። ወይዘሪት ብዙነሽ ገብሬ ዕድሜዋ ስምንት ዓመት ሲሆን ፣ የወይዘሪት እመቤት ደግሞ ስድስት ዓመት መሆኑን የማስታወቂያ ክፍሉ ባገኘው ሪፖርት መሰረት አስረድቷል።
ታህሳስ 21 ቀን 1965 ዓ.ም የታተመው አዲስ ዘመን ጋዜጣ እህትማማቾች በቅርብ ያገኙትን አረቄ በመጠጣታቸው ህይወታቸውን ስላጡ ታዳጊዎች ተተከታዩን ዘገባ አስነብቦ ነበር።
ወይዘሪት ብዙነሽ ገብሬና ወይዘሪት እመቤት ገብሬ የተባሉ እህትማማቾች የእህል አረቄ ጠጥተው መሞታቸውን ከሸዋ ፖሊስ ማስታወቂያ ክፍል የተገኘው ዜና ገለጠ። ልጆቹ ለሞት የበቁት ወላጅ እናታቸው አረቄውን ካወጡ በኋላ አልጋ ስር አስቀምጠውት ወደ ገበያ ሲሄዱ ከተቀመጠበት ቦታ አንስተው በመጠጣታቸው ነው።
ሟቾቹ አረቄውን እንደጠጡ በያሉበት ተዘርረው ወድቀው ነበር። በኋላ ግን ሰው ደርሶ ለህክምና ፍቼ ጤና ጣቢያ ተወስደው ህክምና ቢደረግላቸውም ለመዳን ተስፋ በማጣታቸው በ 10 ሰዓት ልዩነት ሁለቱም ህይወታቸውን አጥተዋል።
በሁለቱ እህትማማቾች ላይ ይህ የሞት አደጋ የደረሰው ታህሳስ አራት ቀን 1965 ዓ.ም በሰላሌ አውራጃ በግራር ጃርሶ ወረዳ ግዛት ፍቼ ከተማ ውስጥ ነው። ወይዘሪት ብዙነሽ ገብሬ ዕድሜዋ ስምንት ዓመት ሲሆን ፣ የወይዘሪት እመቤት ደግሞ ስድስት ዓመት መሆኑን የማስታወቂያ ክፍሉ ባገኘው ሪፖርት መሰረት አስረድቷል።
የ114 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ከሆስፒታል ወጡ
የ114 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ሆስፒታል መውጣታቸውን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ያሬድ አግደው በፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
እኚህ የዕድሜ ባለፀጋ አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ለተጨማሪ ህክምና የካቲት 12 ሆስፒታል ናቸው ተብሏል ።
የ114 ዓመት የዕድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ሆስፒታል መውጣታቸውን የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ያሬድ አግደው በፌስ ቡክ ገጻቸው ላይ አስፍረዋል።
እኚህ የዕድሜ ባለፀጋ አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ለተጨማሪ ህክምና የካቲት 12 ሆስፒታል ናቸው ተብሏል ።
ሸገር ዳቦና የዳቦ ዱቄት ፋብሪካ እየተመረቀ ነው
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ አባል በሆነው ሆራይዘን ፕላንቴሽን ኩባንያ አማካኝነት የተገነባው ሸገር ዳቦና የዳቦ ዱቄት ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት እየተመረቀ ነው።
በመዲናዋ የሚስተዋለውን የዳቦና የዱቄት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በሰዓት 80 ሺህ ዳቦ የሚያመርተው ሸገር ዱቄት ፋብሪካ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በተገኙበት እየተመረቀ ይገኛል።
ፋብሪካው ምርቱን ዝቅተኛውን የማኅበረሰብ ክፍል ባገናዘበ ዋጋ የሚያከፋፍል ሲሆን፤ ይህም በከተማው የሚስተዋለውን የዳቦ አቅርቦት ማነስና የዋጋ ንረት ከመቅረፉ በላይ፥ ከዳቦ ማምረት እስከ ማከፋፈል ድረስ ባለው ሰንሰለት ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።፡፡
ፋብሪካው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በአራት ሄክታር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፤ በፕሮጀክቱ ሥራ ከ450 ሰዎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከ400 በላይ ያገለገሉ የአንበሳ የከተማ አውቶብሶች ለዳቦ ማከፋፈያነት እንደሚውሉም ታውቋል፡፡
*********************
(ኢ ፕ ድ)
በሚድሮክ ኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ግሩፕ አባል በሆነው ሆራይዘን ፕላንቴሽን ኩባንያ አማካኝነት የተገነባው ሸገር ዳቦና የዳቦ ዱቄት ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት እየተመረቀ ነው።
በመዲናዋ የሚስተዋለውን የዳቦና የዱቄት አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ በሰዓት 80 ሺህ ዳቦ የሚያመርተው ሸገር ዱቄት ፋብሪካ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በተገኙበት እየተመረቀ ይገኛል።
ፋብሪካው ምርቱን ዝቅተኛውን የማኅበረሰብ ክፍል ባገናዘበ ዋጋ የሚያከፋፍል ሲሆን፤ ይህም በከተማው የሚስተዋለውን የዳቦ አቅርቦት ማነስና የዋጋ ንረት ከመቅረፉ በላይ፥ ከዳቦ ማምረት እስከ ማከፋፈል ድረስ ባለው ሰንሰለት ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ታውቋል።፡፡
ፋብሪካው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በአራት ሄክታር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፤ በፕሮጀክቱ ሥራ ከ450 ሰዎች የሥራ ዕድል እንደተፈጠረላቸው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ከ400 በላይ ያገለገሉ የአንበሳ የከተማ አውቶብሶች ለዳቦ ማከፋፈያነት እንደሚውሉም ታውቋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “እንሥራ” የተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከልን ጎበኙ
*************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “እንሥራ” የተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡
“እንሥራ በተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከል ለምትሠሩት እህቶቼና እናቶች እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እወዳለሁ፤ የድካማችሁን ፍሬ በማየቴ ደስ ብሎኛል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡
*************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “እንሥራ” የተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡
“እንሥራ በተሰኘው አዲስ የሸክላ ሥራ ማዕከል ለምትሠሩት እህቶቼና እናቶች እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እወዳለሁ፤ የድካማችሁን ፍሬ በማየቴ ደስ ብሎኛል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 141 ሰዎች ኮሮናቫይረስ ተገኘባቸው
. በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥርም 81 ደርሷል
******************************
(ኢፕድ)
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4675 የላብራቶሪ ምርመራ 141 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5175 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 18 (4 ከጤና ተቋም እና 14 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ የተገኝበት ናሙና የለም። ከዚህ ባለፈ ሶስት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 81 ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት 58 ሰዎች (44 ከአዲስ አበባ፣ 8 ከኦሮሚያ ክልል፣ 3 ከሶማሊ ክልል፣ 2 ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል፣ እና 1 ከትግራይ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1544 ነው።
. በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥርም 81 ደርሷል
******************************
(ኢፕድ)
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4675 የላብራቶሪ ምርመራ 141 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5175 ደርሷል።
ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 18 (4 ከጤና ተቋም እና 14 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ የተገኝበት ናሙና የለም። ከዚህ ባለፈ ሶስት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 81 ደርሷል፡፡
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት 58 ሰዎች (44 ከአዲስ አበባ፣ 8 ከኦሮሚያ ክልል፣ 3 ከሶማሊ ክልል፣ 2 ከደ/ብ/ብ/ሕ ክልል፣ እና 1 ከትግራይ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1544 ነው።