Ethio-Terit SACCOS Official Channel
446 subscribers
681 photos
39 videos
183 links
አልመው ይቆጥቡ አቅደው ይበደሩ!
Kaayyoon qusadhaa, karooraan liqeeffadhaa!

Save purposely, borrow strategically!
Download Telegram
Forwarded from Aboma Ejara
አራተኛ ቀን

ኢትዮ ጥሪት ቁጠባና ብድር ኀ/የተ/መ/ህ/ስ/ማህበር ለአዳዲስ ሰራተኞች እየሰጠ የሚገኘውን ስልጠና ዛሬም በአራተኛ ቀን ውሎ ቀጥሏል ።

ስልጠናውን የሰጡትም የማህበሩ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሙላቱ በዕደ እና የማህበሩ የማርኬቲንግ እና ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር አታክልት ኃይሉ ሲሆኑ ስልጠናውም በአቶ ሙላቱ በዕደ ስለ ድርጅታዊ ባህል እና የስራ ላይ ስነምግባር (work ethics) በተጨማሪም በዶ/ር አትክልት ደግሞ ስለ አዎንታዊ ማረጋገጫ (positive affirmation) ነበረ።

አዳዲስ ሰራተኞቹም በስልጠናው በጣም ተጠቃሚ እንደሆኑ ወደ ስራ ሲቀላቀሉም እንደሚቀላቸው እና ቤተሰባዊነት  እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።


የቤት ፣ የመኪና ፣ የንግድ መጀመሪያ እና ማስፋፊያ፣ የዱንያ (ከወለድነፃ) እና በደመወዝ ዋስትና የብድር አገልግሎት ማግኘት የምትፈልጉ ማንኛውም ሰው ከታች በተቀመጡት ስልክ ቁጥሮች እና ማህበራዊ ሚዲያዎች እኛን ማግኘት ይችላሉ :

Face book :-  https://www.facebook.com/profile.php?id=100070815460611
Telegram :- https://t.me/ethioterit21
Instagrma :- https://www.instagram.com/ethioteritsaccos?igsh=
Linkedin:- https://www.linkedin.com/in/terit-saccos
Youtube:-  https://youtube.com/@teritsaccos-wd9hm?si
Phone number:- 0957073701/0957076716
3👍1
Forwarded from Aboma Ejara
የኢትዮ ጥሪት ቁጠባና ብድር ኀ/የተ/ህ/ስ/ማ በየሳምንቱ ለአባላቶቹ የሚሰጠውን ስልጠና ለ14ተኛ ዙር ዛሬም ሰጥቷል ።

አዲስአበባ 3/12/2017



በዋናነት የቁጠባ የብድር ና የማማከር አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው የኢትዮ ጥሪት ቁጠባና ብድር ኀ/የተ/የህ/ስ/ማ በየሳምንቱ ለአባላቶቹ የሚሰጠውን ስልጠና ለ14ተኛ ዙር ገላን ኮንደሚኒየም በሚገኘው በማህበሩ ዋና ቢሮ ዛሬም ሰጥቷል ።

  ስልጠናውንም የሰጡት የማህበሩ የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል ኀላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ በቀለ ሲሆኑ ስልጠናው ለአባላቶች ጠቃሚ ይዘት እንዳለው ስልጠናውን ያልወሰዱ አባላትም በቀጣይ እንደሚዳረሱ ተናግረዋል።

   የስልጠናው ይዘቶችም ስለ ሕብረት ስራ ማህበራት ጥቅሞች እና መርሆዎች ፣ የኢትዮ ጥሪት አባላት መብት ና ግዴታዎች ፣ የብድር መስፈርቶች ፣ እና ከሌሎች መሰል ማህበራት የሚለይባቸውን እና መሰል ጉዳዮችን ይዟል።

በስልጠናው ላይም የማህበሩ የፋይናንስ ክፍል ኀላፊ የሆኑት አቶ አበበ ጋዲሳ  በበኩላቸው  የማህበሩ አባላቶች በዚህ ስልጠና በተገቢው መንገድ እየተሳተፉ ማህበሩንም ሆነ ራሳቸውን እንዲጠቅሙ ጥሪ አቅርበዋል ።

  በስልጠናው ከተሳተፉት አባላቶችም ይህ አይነቱ ስልጠና ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።  ሌላው በስልጠናው የተሳተፉት አባላቶች በበኩላቸው ከዚህ ስልጠና ብዙ ትምህርት እንዳገኙ እና በተግባር እንደሚያውሉ ተናግረዋል ።

   ስልጠናውም ከዚህ በፊት ከነበሩት ሳምንታት የበለጠ የተሳታፊ ብዛትም ሆነ ድምቀትም ታይቶበታል ።
👏1