Ethio Fm 107.8
20.3K subscribers
7.4K photos
16 videos
4 files
2.3K links
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Download Telegram
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የጠቅላላ ጉባዔ እና የስራ አስፈጻሚ አባላትን መርጧል።

ጠቅላላ ጉባዔው ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋን በፕሬዝዳንትነት፣ ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲሁም ሸኽ ሀሚድ ሙሳን በዋና ፀሐፊነት ሰይሟል።

ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በኢትዮጵያ ሙስሊሞች የተቋማዊ ለውጥና አንድነት አገር አቀፍ ጉባዔ የተመረጠው ኮሚቴ በስድስት ወራት ውስጥ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጎ አመራሮችን እንዲያስመርጥ ኅላፊነት ቢሰጠውም ኅላፊነቱን ሳይወጣ ለሶስት ዓመት ከስድስት ወር ቆይቷል።

በወቅቱ የተመረጠው ኮሚቴ ኅላፊነቱን ባለመወጣቱ ወደ መደበኛው ጉባዔ እንዲመጣ ዛሬ ለሁለተኛ ዙር አገር አቀፍ ጉባኤ ከመላ ሀገሪቱ የተውጣጡ ተወካዮች በተገኙበት ተካሂዷል።

በጉባኤው ላይ በድምፅ ይሳተፋሉ ተብለው ከሚጠበቁት 300 ተሳታፊዎች መካከል 261ዱ ተገኝተዋል።

ሚያዚያ 23 ቀን 2011 ዓ.ም በተካሄደው ጉባኤ ከተሳተፉት መካከል 39ኙ በሞት፣ በህመም፣ ከሀጂ ጉዞ ባለመመለስና በልዩ ልዩ ምክንያቶች በዛሬው ጉባኤ አለመገኘታቸውም ታውቋል።

ጉባዔውን አስመልክቶ ንግግር ያደረጉት የኅይማኖት አባቶች ስለምርጫው ሂደቱ ማብራሪያና የመልካም ምኞት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በጉባዔው ምርጫ ከመካሄዱ ቀደም ብሎ የምርጫ መስፈርቶች ለጉባዔው በንባብ ቀርበዋል።

በዛሬው ጉባዔ መጂሊሱን ለሚቀጥሉት ሶስት ዓመታት የሚመሩ አመራሮች ምርጫ ተካሂዶ የሚከተሉት 14 ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ተመርጠዋል።

ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ
ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን
ሸኽ አልመርዲ ዐብዱላሂ
ሸኽ ሀሚድ ሙሳን
ሸኽ እድሪስ ዓሊይ ሁሴን
ሸኽ አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌ
ሸኽ መሀመድ አህመድ ያሲን
ሸኽ አሚን ኢብሮ
ኢንጂኔር አንዋር ሙስጠፋ
10. ሸኽ አብዱልሃሚድ አህመድ
11. ሀጂ ሙስጠፋ ናስር
12. ሸኽ ዛኪር ኢብራሂም
13. ሸኽ ሁሴን ሀሰን
14. ሸኽ መሀመድ አሚን ሰይድ
ከስራ አስፈጻሚ አባላቱ መካከልም ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋን በፕሬዝዳንትነት፣ ሸኽ አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን እና አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌን በምክትል ፕሬዝዳንትነት እንዲሁም ሸኽ ሀሚድ ሙሳን በዋና ፀሐፊነት ሰይሟል።

በምርጫው ተሳታፊ የጠቅላላ ጉባዔ አባላት ስም ዝርዝር

ሸኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ
ሸኽ አብዱልዐዚዝ አብዱልወሌ
ሸኽ አልመርዲ አብዱላሂ
ሸኽ ሐሚድ ሙሳ
ሸኽ እድሪስ ዓሊይ ሁሴን
ሸኽ መሀመድ አህመድ ያሲን
ሸኽ አሚን ኢብሮ
ኢንጂኔር አንዋር ሙስጠፋ
9. አብዱልከሪም ሸኽ በድረዲን
10. ሸኽ አብዱልሃሚድ አህመድ
11. ሐጂ ሙስጠፋ ናስር
12. ሸኽ ዛኪር ኢብራሂም
13. ሸኽ ሁሴን ሀሰን
14. ሸኽ መሃመድ አሚን ሰይድ ዐያሽ
15. ሸኽ ጣሃ መሃመድ ሐሩን
16. ዑስታዝ አብዱራህማን ሱልጣን
17. ሸክ መሃመድ ዑመር ፈታህ
18. ሸኽ ዐብዱልመናን ማህሙድ አደም
19. ሸክ መሃመድ ኢብራሂም ወርቁ
20. ሸክ ዐብዶልሃዲ አህመድ ቡርሃን
21. ዑስታዝ ሙሀመድ ሙስጠፋ ዑመር

22. ሸክ አህመድ መሀመድ ዓሊይ

23. ሸክ ጁነይድ ሃምዛ የሱፍ

24. ዶክተር መሀመድ ሁሴን መሀመድ

25. ሸክ ሀቢብ ሙስጠፋ ሀሰን

26. ሸክ መሀመድ ዓሊይ ኸድር

27. ዑስታዝ ጋሊ አባቦር አባ ጎማን

28. ዑስታዝ ዚያድ አልይ ሁሴን

29. ሸክ አልኻድር አህመድ ዛይድ

30. ሸክ ኑረዲን ደሊል አወል

ተመራጩ ፕሬዝዳንት ሸኽ ኢብራሂም ቱፋ ባስተላለፉት መልዕክት ምርጫው ከየትኛውም አካል ጣልቃገብነት በጸዳ አግባብ በነጻነት ታሪካዊ ምርጫ እንደሆነ ተናግረዋል።

ምርጫው በሰላም እንዲጠናቀቅ የበኩላቸውን አስዋጽኦ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ታላቅ ኅላፊነት የተሰጣቸው መሆኑን የገለጹት ሸኽ ኢብራሂም ቱፋ፤ በተለይም የህዝብ ሙስሊምን አንድነት በማስጠበቅ ረገድ በትኩረት እንደሚሰሩ አረጋገጠዋል።

ህዝበ ሙስሊሙም ከጎናቸው እንዲቆም እና በጸሎት እንዲያግዛቸውም ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ሐምሌ 11 ቀን 2014 ዓ.ም
አትሌት ጎይቲቶም ገብረሥላሴ በ18ኛው አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች ማራቶን አሸነፈች


ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ጎይተቶም ገብረሥላሴ በ18ኛው አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች ማራቶን 1ኛ በመውጣት ለሀገሯ የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝታለች።
Audio
የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 12-11-14
የጌዶኦ ዞን ባለሁለት እግር ሞተሮኞች እንዳይንቀሳቀሱ ታገደ፡፡

የጌዲኦ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ በዞኑ ስምንት ወረዳዎች አምስት የከተማ አስተዳደሮች ውስጥ የባለሁለት አግር ሞተሮኞች ከትናንት ጀምሮ እንዳይንቀሳቀሱ አግዷል፡፡
መምሪያው እግዱን የጣለው የጌዲኦ ብሄር ራሱን በቻለ ክልል እንዲደራጅ የሚጠይቅ ህዝባዊ ሠልፍ እንዲሚካሄድ በበርካታ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች ጥሪ እየተላለፈ መሆኑን ተከትሎ ነዉ፡፡

በዞኑ አሁንም ሰላማዊ ሁኔታ መኖሩን ለዶቼ ቬለ DW በስልክ የገለጹት የጌዲኦ ዞን ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ሃላፊ አቶ አበባየሁ ኢሳያስ በሞተረኞች ላይ እግዱ የተጣለው ለጠላት ሴራ ያለውን ተጋላጭነት ለመቀነስ ነው ብለዋል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።


Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos


Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

ዌብሳይት https://ethiofm107.com/

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም
የሩሲያና የቱርክ መሪዎች ኢራን ገብተዋል፡፡

የሩሲያዉ ፕሬዝዳንት ቪላድሚር ፑቲንና የቱርኩ አቻቸዉ ረሲጵ ጣይጵ ኤርዶሃን ወደ ኢራን ገብተዋል፡፡

መሪዎቹ በቴህራን በሚኖራቸዉ ቆይታ ከፕሬዝዳንት ኢብራሂም ሬሲ ጋር በሶስትዮሽና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተለይም ፑቲንና ኤርዶሃን ዩክሬን በጥቁር ባህር በኩል ስንዴን ለአለም ገበያ እንድታቀርብ በሚቻልበት ሁኔት እንደሚመክሩ አልጄዚራ አስነብቧል፡፡

በተጨማሪም ሶስቱ መሪዎች በኢራን የኒኩለር ዉዝግብና በሶሪያ ጉዳይ እንደሚመክሩም ይጠበቃል፡፡

ኢራን በአሜሪካና አጋሮቿ የሚደርስባትን ተጽዕኖ ለመቋቋም ከሩሲያና አጋሮቿ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማጠናከር ጥረት እያደረገች ትገኛለች፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

ዌብሳይት https://ethiofm107.com/

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።


በአባቱ መረቀ
ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም
የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸዉን በቴሌ ብር መክፈል የሚችሉበት ስርዓት ተዘረጋ፡፡

ወደ 300 ሽህ የሚጠጉ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብራቸዉን በቴሌ ብር አማካኝነት መክፈል የሚያስችላቸዉን አሰራር ተግባራዊ ተደርጓል፡፡

አሰራሩን ተግባረዊ ያደረጉት ኢትዮ ቴሌኮምና የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ በመተባበር ነዉ፡፡

በዚህ የግብር ክፍያ ስርዓት፣የ 2014 በጀት ዓመት ግብራቸዉን የሚከፍሉ የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ያለ ምንም እነብግልትና ዉጣ ዉረድ ግብራቸዉን እንዲከፍሉ ያስችላቸዋልም ተብሏል፡፡

አገልግሎቱ ከሐምሌ 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ የዋለ ሲሆን እስካሁንም 679 ሰዎች በዚህ ስርዓት ግብራቸዉን ከፍለዋል፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

ዌብሳይት https://ethiofm107.com/

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

በሔኖክ ወ/ገብርኤል
ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም
በአዲስ አበባ የሆቴል ግብዓት አቅራቢዎች ኤክስፖ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በሀገር ውስጥ ያሉ የተለያዩ የሆቴል ግብአት አቅራቢዎች ከሆቴሎችጋር የሚገናኙበት ኤክስፖ በኤሊያና ሆቴል አዘጋጅነት ነዉ በመካሄድ ላይ የሚገኘዉ፡፡
አሁን በሀገራችን ባለው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ላይ ተዳምሮ በርካታ ነገሮች ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ በሚገቡበት በዚህ ሁኔታ፣ ከሀገር ውስጥ አቅራቢዎች ጋር በጋራ የሚሰራበት ሂደት መፈጠሩ የተሻለ ዉጤት ያመጣል የሚል ተስፋ እንዳላቸዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል፣ኪነ-ጥበብ እና ቱሪዝም ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሰው ገልጸዋል።
ለሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፉ የሚያገለግሉ ዕቃዎችን ከቀረጥ ነፃ በማስገባት ጭምር ለዘርፉ ድጋፍ ሲደረግ እንደነበርም ተናግረዋል።

በኮቪድ 19 ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት በደረሰባቸው የሆቴል እና ቱሪዝም ዘርፉ ላይ መነቃቃት እንዲኖር እና የተቀዛቀዘውን የሆቴል ኢንዱስትሪ ዘርፍ ላይ አዎንታዊ ተፅዕኖ እንደሚኖረውም ሃላፊዋ ገልጸዋል።
የሆቴል ማሰልጠኛ ተቋማት፣ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ድርጅቶች፣አየር መንገድ፣ ትራንስፖርት ፣የምግብ እና መጠጥ፣ የንፅህና መጠበቂያ አቅራቢዎች፣ደህንነት እና ጥበቃ፣የህክምና፣የመዝናኛ እንዲሁም የስዕል አቅራቢዎች የሚሳተፉበት ነው ተብሏል።
ዛሬ እና ነገ በሚካሄደው በዚህ ኤክስፖ ከ200 በላይ ተሳታፊዎች እና ከ10 ሺህ በላይ ጎብኚዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በእስከዳር ግርማ
ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም
ፈረንሳይ ሩሲያን በተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ልትተካ አስባለች::

ፈረንሳይና የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች በሃይል ዘርፍ በትብብር ለመስራት ተስማምተዋል፡፡
የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ፕሬዝዳንት ሙሃመድ ቢን ዛይድ ከፈረንሳይ አቻቸዉ ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በፓሪስ ተገናኝተዉ በነዳጅና በታዳሽ ሃይል ዘርፍ አብረዉ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡
ፓሪስ ከሞስኮ ጋር ያላት ግንኙነት እየተቀዛቀዘ መምጣቱን ተከትሎ በአቡዳቢ ለመተካት ስለማቀዷ ታዉቋል፡፡

የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ነዳጅና እና ሌሎች የሃይል ምርቶችን ለፈርንሳይ እንደምታቀርብም ተነግሯል፡፡
አቡዳቢ ለአለም የነዳጅ አቅርቦቷን እንደምታጠናክር የገለፁት ቢን ዛይድ፣ በዋናነት ደግሞ ለፈርንሳይ ድጋፍ ታደርጋለች ነዉ ያሉት፡፡
ፈረንሳይን ጨምሮ የአዉሮፓ አገራት ከሩሲያ የሚያገኙት ነዳጅ አስተማማኝ ባለመሆኑ የመካከለኛዉ ምስራቅ አገራትን በመማፀን ላይ ናቸዉ፡፡

በአባቱ መረቀ
ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

ዌብሳይት https://ethiofm107.com/

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
በአዲስ አበባ 96 ቦታዎች የእሁድ ገበያ ተቋቁመዋል ተባለ፡፡

"በሸማቾች የህብረት ስራ ማህበራት፣ የሰብልና የአትክልት አቅራቢዎች፤ የጅምላ ነጋዴዎችና በምግብ ማቀነባበርያ የተሰማሩ ፋብሪካዎች እንዲሁም በኦሮምያ ልዩ ዞን የሚገኙ የህብረት ስራ ማህበራትን በማሳተፍ በየሳምንቱ የእሁድ ገበያ በከተማዋ በተመረጡ 96 ቦታዎች የፍጆታ እቃዎች እየቀረቡ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

የእሁድ ገበያው በአምራችና በሸማቹ መሀከል የነበረውን የገበያ ሰንሰለት በመበጣጠስ፤ተጠቃሚው በቀጥታ ከአምራቾች ምርትን በወቅቱና በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ በማድረግ የኑሮ ውድነት ጫናው ዝቅተኛ ገቢ ያለውን የማህበረሰብ ክፍል እንዳይጎዳ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከተ ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል፡፡

በእነዚህ በተመረጡ የእሁድ ገበያዎች የሚቀርቡ የፍጆታ እቃዎች የዋጋቸዉን ተመጣጣኝነትና አቅረቦትን በተመለከተ አድማጮች አስተያየቶቻችሁን ልትሰጡበት ትችላላችሁ፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ሐምሌ 12 ቀን 2014 ዓ.ም

Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

ዌብሳይት https://ethiofm107.com/

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
የኢትዮ ማለዳ የዜና ሰዓታችንን ይከታተሉ፦


በዛሬው የኢትዮ ማለዳ የዜና ሰዓታችን ( ከ12:30-2:30)


-ከቤት ሳንወጣና ስፖርታዊ ጉዳዮችን ትሰማላችሁ

- በመንገዳችን ላይ፦ከአዲስ አበባ ወደ ክፍለ ሀገር ሲጓዙም ሆነ ከክፍለ ሃገር ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ እርስዎም የሚታዘቡት በጉዞ ወቅት በአንዳንድ የትራፊክ ፖሊስ አባላት ላይ የተመለከትነውን ትዝብት እናጋራችኋለን።

- በፍተሻ ሰዓታችን መነጋገር ሊደፈር፣አለመነጋገር ሊፈራ ይገበዋል በሚል የመነጋገር ባህላችንን እንፈትሻለን፤ የባለሙያ ምክረ ሀሳብም ይዘንበታል!

-በኢትዮ ገበያችን ፦
በቱሪዝም ዘርፍ ላይ የተሰማራዉ የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች ዱባይ ቱሪዝም ለኢትዮጵያ አስጎብኚ ድርጅቶች አደርጋለሁ ስላላቸው የተለያዩ ድጋፎች እናነሳለን።

- ለጤናችን ዛሬ ትኩረቱን በዓለማችን እየተከሰተ ያለው ድርቅና ረሀብ በጤናችን ላይ የሚያደርሰው ተጽዕኖ ላይ አድርጓል

-በዓለም ጉዳይ፦ በዩክሬን ጉዳይ ትችት እየቀረበበት ስለሚገኘው የአውሮፓ ህብረት በትንታኔ አዘጋጅተንላችኋል።


- እንዲሁም ሌሎች አዳድስ የሀገር ውስጥና ዓለምዓቀፋዊ ጉዳዮችንም አሰናድተንላችኋል፤

እንድታደምጡ ተጋብዛችኋል።

ለአስተያየትዎ '6321' አጭር የጽሁፍ መልዕክት

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ንጋት ላይ በተካሄደ የ1 ሺህ 500 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ታደሰ ለሚ 8ኛ ሆኖ አጠናቀቀ።

የወንዶች 1 ሺህ 500 ሜትር የፍፃሜ ውድድር ንጋት 11፡30 ላይ ተካሂዷል።

ኢትዮጵያ በአትሌት ታደሰ ለሚ የተወከለች ሲሆን፥ አትሌቱ ስምንተኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቋል።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም
Audio
የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን
10 ሽህ ብር ጉቦ ስትቀበል እጅ ከፍንጅ ተያዘች፡፡

የመሬት አስተዳደር የንብረት ግምት ባለሙያ የሆነች አንዲት ግለሰብ 10 ሺ ብር ጉቦ ስትቀበል እጅ ከፍንጅ መያዟን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

የጉለሌ ክ/ከተማ የመሬት አስተዳደር የንብረት ግምት ባለሙያ የሆነችው ግለሰብ አንድን ባለ ጉዳይ ጉዳይህን እኔ እጨርስልሀለሁ በማለት 10ሺ ብር ጉቦ ስትቀበል ሀምሌ 6 ቀን 2014 ዓ/ም እጅ ከፍንጅ ተይዛ አስፈላጊው ምርመራ ተጣርቶ ክስ እንደተመሰረተባት የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የግል ተበዳይ በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከድንበር ጋር የተያያዘ ጉዳዩን ለማስጨረስ በሄደበት አጋጣሚ ግለሰቧ 30 ሺህ ብር ጉቦ የጠየቀችው ሲሆን 10ሺ ብር ቅድሚያ እንደሰጣት እና ቀሪውን 20 ሺህ ብር ደግሞ ጉዳዩ ሲያልቅ ለመወሰድ መጠየቋን የግል ተበዳይ ለክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ አሳዉቋል፡፡
በመሆኑም ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ/ም ጉቦውን ስትቀበል በፖሊስ እጅ ከፍንጅ ተይዛ አስፈላጊው ምርመራ ተጣርቶ ክስ እንደተመሰረተባት የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡
ማህበረሰቡ መሰል ወንጀል ፈፃሚዎችን ለህግ አካል አጋልጦ የመስጠት ልምዱ ይበል የሚያሰኝ ተግባር መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ተናግሯል፡፤
ወደፊትም ህዝብን እና መንግስትን የሰጣቸውን እምነት በማጉደል በማህበረሰቡ ላይ በደል የሚፈጽሙ አካላትን ወደ ህግ ለማቅረብ የሚደረገው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብሏል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም
የኢራኑ ናሽናል እና የሩሲያዉ ጋዝ ፕሮም ታሪካዊ ነዉ ያሉትን ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

የኢራን ናሽናል ነዳጅ ኩባንያ እና የሩሲያዉ ነዳጅ አምራች ጋዝ ፕሮም ወደ 40 ቢሊዮን የሚጠጋ የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸዉን የኢራን የነዳጅ ሚኒስቴር ዜና ወኪል ሻና ዘግቧል፡፡
የኢራን ባለስልጣናት እንደገለጹት 20 ሚሊዮኑ ለኪሽ እና ለሰሜናዊ ፓርስ የጋዝ ማምረቻ የሚከፋፈል ሲሆን፤በቀን የ100 ሚሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ተጨማሪ ጋዝ እንዲያመርቱም ይረዳል ነዉ የተባለዉ፡፡

የሩሲያዉ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ከኢራኑ አቻቸዉ ጋር ለመምከር ወደ ቴህራን ባቀኑበት ወቅት የሁለቱም ኩባንያ ሃላፊዎች በኦንላይን ባደረጉት ዝግጅት ነዉ ስምምነቱ የተፈረመዉ፡፡
ጋዝ ፕሮም የኢራን ናሽናል ነዳጅ ኩባንያን የኪሽ እና ሰሜናዊ ፓርስ የጋዝ ማምረቻ ቦታዎችን በማልማት ረገድ እንደሚደግፋት እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ ስድስት የጋዝ ማምረቻ ቦታዎችን በማልማትም ትብብር እንደሚያደርግ ነዉ የተገለጸዉ፡፡

ጋዝ ፕሮም ከዚህ በተጨማሪም የተፈጥሮ ጋዝ አምራች ፕሮጀክትን እና የጋዝ ማስተላለፊያ ቱቦዎችን በመገንባት ኢራንን እንደሚረዳ ተገልጿል፡፡

ኢራን ከሩሲያ በመቀጠል በዓለም ሁለተኛዋ ከፍተኛ የጋዝ ክምችት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ የአሜሪካ ማዕቀብ ከቴክኖሎጂ ጋር ግንኙነት እንዳይኖራት ያቀባት በመሆኑ ወደ ዉጭ የሚላከዉ የጋዝ ዕድገት አዝጋሚ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
የሩሲያ-ዩክሬንን መዉረር በዓለም ነዳጅ እና የነዳጅ ገበያዉ ላይ ባሳደረዉ ተጽዕኖ ምክንያት የፑቲን የቴህራን ጉብኝት በከፍተኛ ሁኔታ የዓለምን ትኩረት የሳበ እንደሆነ አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

በእስከዳር ግርማ
ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም