Ethio Fm 107.8
20.4K subscribers
7.52K photos
16 videos
4 files
2.3K links
በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍ ኤም ሬዲዮ ነው!!!
Download Telegram
Audio
የዛሬው የኢትዮ ማለዳ ዜናዎቻችን 13-01-15

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።
በደቡብ ክልል አማሮ ልዩ ወረዳ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ አምስት ሰዎች ተገደሉ፡፡

በትላንትናዉ እለት የሸኔ የሽብር ቡድን በወረዳው ባደረሰው ጥቃት አምስት ሚሊሻዎች መሞታቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም ሰምቷል፡፡
የአማሮ ልዩ ወረዳ የፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንፔክተር አራርሶ ነጋሽ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት፣ በአካባቢው በተደጋጋሚ እየተከሰተ ያሉትን ግድያዎች በመፈጸም ላይ ያሉት ከምዕራብ ጉጂ ገላና ወረዳ የሚነሱ የሸኔ ታጣቂዎች ናቸው፡፡

ትላንት የተከሰተው የጸጥታ ችግርም ጠንሳሾቹ እነርሱ መሆናቸው የገለጹት አራርሶ ነጋሽ፣ በወረዳው አሁንም ከፍተኛ የጸጥታ ችግር መከሰቱን ተናግረዋል፡፡

በትላንትናው እለት ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተውጣጡ አካላት በወረዳው ከዚህ በፊት የተከሰተውን የጸጥታ ችግር በተመለከተ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ለመምከር እያቀኑ በነበረበት ጊዜ ነው ጥቃቱ የደረሰው፡፡
በአካባቢው ከፍተኛ “የታጣቂዎች ክምችት” እንዳለ ከነዋሪዎች መስማታቸውንና ይህንኑም ዛሬ ወደ አካባቢው የተንቀሳቀሰው የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል እና የፌደራል ፖሊስ አባላት ማረጋገጣቸውን ነግረዉናል።

በሔኖክ ወ/ገብርኤል
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
ሩሲያ ከዩክሬን በነጠቀቻቸዉ አራት ግዛቶች ህዝበ ዉሳኔ ማካሄድ ጀመረች፡፡

የሩሲያ ጦር ከዩክሬን በነጠቃቸዉ አራት ግዛቶች ህዝበ ዉሳኔ መጀመሩን የአገሪቱ መንግስት አስታዉቋል፡፡

ህዝበ ዉሳኔዉ የሚካሄደዉ በ ሉሃንስክ፤ ዶኔስክ፤ በኬርሶንና በዛፖርዢያ ግዛቶች ነዉ፡፡

ሂደቱ እስከ ቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ ድረስ እንደሚቀጥልም ሞስኮ አስታዉቃለች፡፡

ምዕራባዉያኑ ግን ህዝበ ዉሳኔዉን ለይስሙላ የሚደረግ ሲሉ አጣጥለዉታል፡፡

ሩሲያ ከስምንት አመት በፊት ከዩክሬ በወሰደችዉ ክረሚያ ግዛት ተመሳሳይ ህዝበ ዉሳኔ አድርጋ ማጠቃለሏ የሚታወስ ነዉ፡፡

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcast

Website https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።


በአባቱ መረቀ
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
ባህር ዳር ከተማ በጸሃይ ብርሃን የሚሰሩ የመንገድ ላይ መብራቶችን መገንባት ጀመረች፡፡


በከተማዋ በጸሃይ ብርሃን ወይም ሶላር ሲስተም የሚሰሩ እና 5 ኪሎ ሜትር የሚሸፍኑ የመንገድ ላይ መብራቶችን ግንባታ እንደተጀመረ የከተማዋ ኮሙኒካሽን አስታዉቋል፡፡

ከሃያ አራት ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን ወጪ የሚደረገበት በከተማው አምስት ቦታዎች ላይ የመንገድ ላይ መብራቶችን ግንባታ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ዶክተር ድረስ ሳህሉ አስጀምረዋል።

ይህም የባህርዳር መንገዶችን ምንጊዜም መብራታቸው የማይጠፋ ለማድረግ ያስችላል ተብሏል፡፡


ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
ቤተክርስቲያኗ ምዕመኑ የመስቀል ደመራ በዓልን መንፈሳዊ ይዘቱን በጠበቀ መንገድ እና በክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር እንዲያከብር ጥሪ አቀረበች::


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ህዝበ ክርስቲያኑ የመስቀል ደመራ በዓልን መንፈሳዊ ይዘቱን በጠበቀ መንገድ እና በክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር እንዲያከብር መልዕክት አስተላለች።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የ2015 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓልን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸው የመስቀል ደመራ በዓል ያለምንም የጸጥታ ችግር በሰላም እንዲከበር ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል።

ለዚህም በቤተክርስቲያኗ በኩል የተለያዩ ኮሚቴዎች ተቋቁመው ከመንግስት የጸጥታ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነም አስረድተዋል።

ህዝበ ክርስቲያኑ የመስቀል ደመራ በዓልን መንፈሳዊ ይዘቱን በጠበቀ መንገድ እና ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባርን በተላበሰ ሁኔታ እንዲከበር መልዕክት አስተላልዋል።
ምዕመኑ የመስቀል ደመራ በዓልን ለማክበር ወደ መስቀል አደባባይ ሲመጣ የቤተክርስቲያኗን ስርዓት የሚገልፅ አለባበስ ለብሶ መምጣት እንዳለበት ማሳሰባቸዉን ኢዜአ ዘግቧል።

በበዓሉ ላይ ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት የሚያጋጩ መልዕክቶችንና ዓርማዎችን ይዞ መግባት የተከለከለ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ አብርሃም አክለውም ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በዓሉ የፍቅር የሰላምና የአንድት እንዲሆን እንዲሆን ተመኝተዋል፡፡

ህዝበ ክርስቲያኑ በዓሉን የተቸገሩትን በመርዳት፣የታመሙትን በመጠየቅ እንዲያከብርም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የድምፃዊት ሃሌሉያ ተክለፃዲቅ አዲስ አልበም ነገ ይለቀቃል

በቀድሞ ጃኖ ባንድ የምናዉቃት ተወዳጇ ድምፃዊት ሃሌሉያ ተክለፃዲቅ አዲስ የሰራችዉን "ተወዳጅ" የተሰኘ ሙሉ አልበም በነገው ዕለት ይለቀቃል።

የአልበሙን መለቀቅ በማስመልከት ዛሬ መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም ቦሌ በሚገኘዉ ቦስተን ዴይ ስፖ ሚድታወን ክለብ  ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል።

ድምፃዊት ሃሌሉያ እንዲሁም በአልበሙ ላይ የተሳተፉት ዳዊት ተስፋዬ እና ኤንዲ ቤተ -ዜማ በጋራ በሰጡት ማብራርያ አልበሙ 13 ሙዚቃዎች የያዘ ሲሆን ሰርቶ ለማጠናቀቅ ሶስት ዓመት ያህል ፈጅቷል።

ነገ መስከረም 14 ቀን 2015 ዓ.ም በኢንተርኔት የሚለቀቀዉ ይኸው አልበም  በቅርብ ደግሞ በሲዲ እንደሚለቀቅ ገልፀዋል። በተጨማሪም በቅርቡ በሀገር ዉስጥ እና በዉጭ ሀገራት ኮንሰርት ለማዘጋጀት ዕቅድ እንዳላት ድምፃዊት ሃሌሉያና ባልደረቦቿ ተናግረዋል ።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
በአዲስ አበባ ከተማ መስከረም 17 ቀን የሚከበረው የመስቀል በዓል በሰላም ተከብሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የሞተር ብስክሌት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ተወሰነ።


የትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ እሁድ ከቀኑ 7:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ማክሰኞ መስከረም 17 ቀን ማታ 12:00 ድረስ ምንም አይነት የሞተር እንቅስቃሴ በከተማዋ የተከለከለ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በዚህም ኤጀንሲው የሞተር ብስክሌት አሽከርካሪዎች ተገቢውን ጥንቃቄ አድርጉ ብሏል፡፡

ይሄንን ተላልፈው በሚገኙ ሞተረኞች ላይ ህጋዊ እርምጃ ይወሰዳል ማለቱን ከኤጀንሲው ያገኘነው መረጃ አመላክቷል።


ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን
መስከረም 14 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
በአቃቂ ቃሊቲ የእሳት አደጋ የሰው ህይወት አጠፋ::

ዛሬ ሌሊት 7 ሰዓት ከ44 ደቂቃ ላይ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ወረዳ 13 ቱሉዲምቱ አካባቢ የተለያዩ አነስተኛ የንግድ አገልግሎት የሚሰጡ 15 የሚሆኑ በላስቲክ፣ በሸራና አነስተኛ ቁሳቁስ ተሰሩ መጠለያዎች በእሳት አደጋ ወድመዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዕሳትና የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንዳስታወቁት፥ እሳቱ ወደሌላ ስፍራ ሳይዛመት በቀላሉ መቆጣጠር ተችሏል።


ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
ሳዑዲ አረቢያ ከፍተኛ የወርቅ ክምችት ማግኘቷን አስታወቀች፡፡

ሳዑዲ አረቢያ በመዲና ዉስጥ ከፍተኛ የወርቅ ክምችት ማግኘቷን አስታዉቃለች፡፡

የተገኘዉን ከፍተኛ የወርቅ ክምችት የተቀረዉ ዓለምም እንዲጠቀምበት ዕድሎችን እያመቻቸች መሆኗንም ገልጻለች፡፡
ሳዑዲ አረቢያ በእስልምና ቅዱሷ ከተማ ተብላ በምትጠራዉ መዲና ዉስጥ ከፍተኛ የሆነ የወርቅ እና መዳብ ክምችት ማግኘቷን የገለጸዉ የሀገሪቱ ጅኦሎጂካል ሰርቬይ ነዉ፡፡

የዚህ ክምችት መገኘት የሀገሪቱን በነዳጅ ላይ ጥገኛ የሆነ የኢኮኖሚ ዘርፍ ወደ ሌላ መስመር ያሸጋግርላታል ሲልም ያለዉን ተስፋ ገልጿል፡፡

እንደ አል አረቢያ ሪፖርት የሳዑዲ ባለስልጣናት የተገኘዉ ወርቅ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ የ5 መቶ 33 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት መሳብ ይችላል ፤ ለ4ሺህ ዜጎችም የስራ እድል ይፈጥራል ሲሉ ከአሁኑ ተስፋቸዉን ጥለዉበታል፡፡

የሀገሪቱ የአፈር እና የከበሩ ማዕድናት አጥኚዎች ቡድን እንዳለዉ ሳዑዲ አረቢያ ከ 5 ሺህ 3 መቶ በላይ የሆኑ የማዕድን ስፍራዎች አሏት፡፡
በነዚህ ስፍራዎችም ብረት፣ የህንጻ መሳሪያዎች፣ የማስጌጫ ድንጋዮች እና ዉድ የሆኑ የጌጣጌጥ ድንጋዮች ይገኙበታል ሲል የዘገበዉ ሚረር ነዉ፡፡

በእስከዳር ግርማ
መስከረም 14 ቀን 2015 ዓ.ም
ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከ5 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፈው በጀት ዓመት ከ5 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኩባንያ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው አስታውቀዋል።

አቶ መስፍን ለኢዜአ እንደገለጹት የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጭነት አገልግሎቱን በማሳደግና ተጽዕኖዎችን በመቋቋም ባለፈው በጀት ዓመት የተሻለ ገቢ ማግኘቱን አስታውቀዋል።

በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም አየር መንገዱ በሰጣቸው ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች 5 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ከ66 በላይ የበረራ መዳረሻዎች ላይ አገልገሎት እየሰጠ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቶጎው ስካይ፣የማላዊ፣ የዛምቢያ፣ የኮንጎ እና የናይጄሪያ አየር መንገዶች ስኬት እንዲያስመዘግቡ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

መስከረም 14 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos
የፀደይ ባንክ ስራ መጀመሩን በይፋ አበሰረ፡፡


የቀድሞው የአማራ ብድር እና ቁጠባ ተቋም (አብቁተ) የአሁኑ የፀደይ ባንክ በይፋ በዛሬው ዕለት የሥራ ማስጀመሪያ ሥነ ስርአት አካሂዷል፡፡

ባንኩ በ8 ቢሊየን ብር የተከፈለ ካፒታል በ148 ቅርንጫፎች በዛሬው ዕለት በመላ ሀገሪቱ ሥራ እንደሚጀምር ተገልጿል።

አብቁተ ወደ ፀደይ ባንክ የተቀየረው የነበሩትን 471 ቅርንጫፎችን ይዞ ነው።

46 ቢሊየን ብር የሚገመት ሀብት ያለው ፀደይ ባንክ ቁጠባ እና ኢንቨስትመንትን በማበረታታት እንዲሁም የሴቶችን እና የወጣቶችን ተሳትፎ በማሳደግ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ተገልጿል።

አሁን ላይ የፀደይ ባንክ የተፈረመ ካፒታል 7 ነጥብ 75 ቢሊየን ብር ሲሆን፥ የ10 ሺህ ብር ዋጋ ያላቸው 774 ሺህ 907 አክሲዮኖች አሉት፡፡


ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

መስከረም 14 ቀን 2015 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።
Telegram https://t.me/ethiofm107dot8
Twitter https://twitter.com/EthioFM
YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos