Ethio Fast News-ኢትዮ ፈጣን መረጃ
3.24K subscribers
219 photos
25 videos
12 links
ከእየአቅጣጫው ሁሉም ዜናዎች በአንድ ቦታ የሚያገኙበት አዲስ ቻናል ነው
Download Telegram
ማይምሪ ከተማ

በሰሜን ጎንደር ዞን ምስራቅ ጠለምት ወረዳ ለአራት ተከታታይ ቀናት የቀጠለ ወታደራዊ ግጭት መኖሩንና ሁኔታውን ለመቃወም በሚጠምሪ ከተማ ዛሬ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል።

እንደ መረጃው ገለጻ፣ የትግራይ ኃይሎች በምስራቅ ጠለምት ወረዳ በኩል የከፈቱት ጥቃት ዛሬ አርብ ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም አራተኛ ቀኑን ይዟል።ግጭቱ በተለይም "ደጃች ሜዳ" የተባለችውን ከተማ ለመቆጣጠር ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።

የማጠምሪ ከተማ የከተማ አስተዳደር መዋቅር ያላትና የምዕራብ ጠለምት ወረዳ ዋና መቀመጫ በመሆን የምታገለግል የአካባቢው ቁልፍ የንግድና የአስተዳደር ማዕከል ናት።

ግጭቱ በሁለቱ ወገኖች መካከል የተደረሰውን የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን መረጃው ያመለክታል።


የትግራይ ኃይሎች በክልሎቹ መካከል ያለውን የተከዜ ወንዝ ወሰን አልፈው ጥቃት መፈጸማቸው "የስምምነቱ መፍረስ ማሳያ ነው" ሲል ሙሉነህ ዮሐንስ በጽሁፉ ገልጿል።

እስካሁን ድረስ ከፌደራል መንግሥትም ሆነ ከትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በኩል በጠለምት አካባቢ ስላለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።
4
ይህ ሆነ❗️

በባህርዳር ከተማ

በ24/05/2018 ከምሽቱ 1:30 አካባቢ አንድን የቀበሌ 15 ወጣት አጋቾች ተከታትለው መንገድ በመዝጋት ሊያግቱት ሲሞክሩ ልጁም መኪና ይዞ ስለነበር የዋዛ አይደለምና ቢከተሉትም አጋቾች መድረስ ባለመቻላቸው ከፍጥነት በላይ እያሽከረከረ ስለነበር ቀበሌ 15 አዲሱ ገቢያ ህንፃ አካባቢ ሲደርስ በወቅቱ ፓትሮል ሲያደርጉ የነበሩ ፓሊሶችና የፀጥታ አካላት መሳሪያቸውን ፊት ለፊት በመደገን የታጋች ሙከራ የሚደረግበትንና የአጋቾች የተጠቀሙበትን መኪኖች ያስቆሟቸው ሲሆን።

ከዛም የማገት ሙከራ ከሚያደርጉት መኪና ላይ 3 ሰዎች ወረዱ ፣ሊታገት የነበረውም ግለብም ከመኪናው ወረደና ሊያግቱኝ እያባረሩኝ ነበር በማለት ፓትሮል ሲያደረጉ ለነበሩት ለፓሊሶች አስረድቶ የአካባቢው ማህበረሰብም ጉዳዩን ሊመለከት ተሰበሰበ

ሆኖም የአጋች ቡድኖቹ በጣም ወከባ ፈጠሩና አንዴ የፀጥታ አካል ነን አንዴ የፌደራል ፓሊስነን አንዴ የደህንነት አካል ነን በማለት ለማጭበርበር ቢሞክሩም ነገር ግን ፓሊሶቹም የዋዛ አልነበሩምና ሁሎችንም ወደ ጣቢያ ወሰደው ያሰሯቸው ሲሆን በማግስቱ ጧት ላይ ሲታዩ የሆነው ጉድ አሳዛኝ ሆነ ማለትም አጋች ሆነው የተገኙት የፀጥታ አካል ሁነው ተገኙ ከዚያም በማጣራት ሰንሰለታቸው 7 ደረሰና ታሰሩ በሁለተኛው ሊታገት የነበረው ቃሉን ሰጦ ከእስር ቤት ወጥቷል።

ነገር ግን የማገት ሙከራ ያደረጉት 3ቱ ግለሰቦች ጥብቅ ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል።

አጋቾች በወቅቱ ይዘዋት የነበሩት ተሽከርካሪ ነጭ ሊፋን/ ያሪስ ታልጋ ቁጥር ኮድ 2-አአ C 05451 የሆነች ተሽከርካሪ ነበረች ጠዋት ታጋቹን ለመጠየቅ ታስራ ያገኘናት ታጋቾች ይዘዋት የነበረች መኪና ኮድ 4 አማ 05451 ሁኖ/ተቀይሮ ስናየው በጣም ገረመንና በምን ቅፅበት ቀየሩት ብለን ተገረምን ድንገት ተሳስተን ይሆን ብለን በወቅቱ ፎቶ አንስተው ከነበሩ ሰወች ጠይቀን ስናየው ደጋግመን ብናየውም ትክክል ነበርን።
በመሆኑም 1ኛ/እንዴትና የት ቦታ የመኪናዋ ታልጋው ተቀየረ ምን አልባት ፓሊስ ጣቢያ ከገቡ በኋላ በገንዘብ አስቀይረውት ሊሆን ይችላል ብለን ዝም አልን ምክንያቱም በወቅቱ የነበረና ወከባ ሲፈጥሩ በነበረበት ወቅት ለማስረጃ ብሎ ቪድዮ ሲቀርፅ ለምን ፎቶ አነሳህ ብለው አንድ ቀን አስረውት በስልኩ የነበረውን መረጃ አጥፍተው ሰደዱት ይህስ ለምን ተደረገ? ፖሊስ ለምን ማስረጃውን መጠቀም አልፈለገም? ምን አልባት ከላይ እንደገለፅኩት ሀለት/2 አይነት ታልጋ መኖራቸው እንዳይታወቅ ይሆን?

ስለሆነም የምርመራ ውጤቱን ወደፊት የምናየው ሁኖ ነገርግን ለባህር ዳር ከተማ ለ1ኛ ፓሊስ ጣቢያ እንድትጠይቁልን የምንፈልገው
የማገት ሙከራ ያደረጉት የፀጥታ አካላት በወቅቱ ሲጠቀሙበት የነበረው ታልጋ ቁጥር ማን ቀየረው? በምን ቅፅበት ተቀየረ? ለምንስ ወንጀሉ ከተፈፀመበት አካባቢ በመሄድ ለማጣራትና ተጨማሪ መረጃ ማግኘች አልተቻለም? በእገታ ሙከራ ላይ እንዴት ህዝብ ደህንነቴን ይጠብቃል ብሎ የሚተማመንበት የፀጥታ አካል ሊሳተፍ ቻለ? የሚሉ ጥያቄዎች በስፋት እየተነሱ መሆኑን ዘጋቢያችን ከባህርዳር የላከልን መረጃ ይገልፃል።
18👍5🤓3
የባንክ ሂሳብ እግድ

ፍትህ ሚንስቴር የህውሃት ባለስልጣናት የባንክ ሂሳብ እንድታገድ ማዘዙ ተሰምቷል።በዝርዝሩ ውስጥ
📌ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል
📌 አቶ ጌታቸው አሰፋ
📌ዶ/ር አብርሃም ተከስተ
📌 ዶ/ር አዲስ አለም ባሌማ
📌ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር
📌 አቶ አማኑኤል አሰፋ
ከወታደራዊ አመራሮች፦
📌 ሜጀር ጀነራል ህንፃ ወልደጊዮርጊስ
📌 ሜጀር ጀነራል መአሾ በየነ
📌 ሜጀር ጀነራል ዮሐንስ ወልደጊዮርጊስ
📌 ብርጋዴር ጀነራል ምግበ ኃይለ
📌 ብርጋዴር ጀነራል አብርሃ ተስፋይ
📌 ብርጋዴር ጀነራል ጉዕሽ ገብሬ ይገኙበታል።
12
የአምባሳደር ዘውዴ ረታን "የኤርትራ ጉዳይ" መጽሐፍ በድጋሜ እያነበብኩት ነው። ከዋናው ጉዳይ በላይ ያስገረመኝ፣ በአማራ ላይ የተነዛው ጥላቻ በተባበሩት መንግሥታት 4ኛው ጉባኤ ላይ በጣሊያን ፕሮፓጋንዲስቶች መቅረቡ ነው። ኤርትራ ወደ እናት ሀገሯ ኢትዮጽያ እንዳትመለስ የሀሰት ትርክት መፈብረክ ነበረባቸው። እንዲህ ይላል: "ኢትዮጵያ በአማራ ዘር ተጨቁና የተያዘች ስለሆነ፣ የሰውን ልጅን መብትና እኩልነት ትቀበላላች ተብሎ አይጠበቅም..."። የጥላቻው መርዝ በፕሮጀክት መልክ በጣሊያን ተቀርጾ፣ በእነ ግብፅ ተኮትኩቶ፣ በአገር በቀል ነፃ አውጪ እንከፎች ስጋ ለብሶ፣ ከገማሽ ክፍለዘመን በኋላ ፍሬ አፍርቷል። በድንገት የተፈጠረ አንዳች ነገር የለም!

ገፅ: 222።
👍65
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት የኤርትራ ገዥው ሥርዓት በሦስት የተለያዩ ግንባሮች ላይ የተደራጁ የሜካናይዝድ ክፍሎችን አሰማርቷል። የአሰማራሩ ሂደት ታንኮችን፣ የመድፍ ሥርዓቶችን እና ሞርታሮችን ያካተተ ሲሆን፤ በዋና ዋና የድንበር ኮሪደሮች ላይ እንደሚከተለው ሰፍረዋል፦

ግንባር 1፡ በዛላንበሳ ዚባን ህፃ መስመር
ታንኮች፦ 22 (የተለያዩ ዓይነቶች)

122 ሚሜ መድፍ፦ 3 ባትሪ

130 ሚሜ መድፍ፦ 1 ባትሪ

155 ሚሜ መድፍ፦ 1 ባትሪ

80 ሚሜ ሞርታር፦ 10

120 ሚሜ ሞርታር፦ 6

ግንባር 2፡ በራማ ኮሪደር
ታንኮች፦ 20 (የተለያዩ ዓይነቶች)

122 ሚሜ መድፍ፦ 2 ባትሪ

130 ሚሜ መድፍ፦ 1 ባትሪ

155 ሚሜ መድፍ፦ 1 ባትሪ

80 ሚሜ ሞርታር፦ 8

120 ሚሜ ሞርታር፦ 4

ግንባር 3፡ በባድመ፣ ማይ ኩህሊ፣ ዓዲ ፀፀር፣ ዓዲ አሰር እና ሽመልባ ኮሪደር
ታንኮች፦ 30 (የተለያዩ ዓይነቶች)

122 ሚሜ መድፍ፦ 4 ባትሪ

ምንጭ 👉Conflict zone

130 ሚሜ መድፍ፦ 2 ባትሪ

155 ሚሜ መድፍ፦ 2 ባትሪ

80 ሚሜ ሞርታር፦ 20

120 ሚሜ ሞርታር፦ 12
6
ምን አይነት ግዜ ላይ ደረስን????😴

የምትመለከቱት ግለሰብ በአሰንዳቦ ከተማ በ20 kg ማር ዉስጥ 8.5 kg ትልቅ ድንጋይ ጋር አስመዝኖ ሲሸጥ ተያዘ።የገዛዉ ሰዉ ወደ እቃዉ ሊገለብጥ ሲል ተይዟል።
4😁4
የባንኮች የአገልግሎት ዋጋ ጭማሪ አደረጉ

​ባንኮች በዲጂታል ባንኪንግ እና በብድር አገልግሎቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጋቸውን ጀምረዋል። የዚህ እርምጃ ዋና ዋና ምክንያቶች እና ዝርዝሮች የሚከተሉት ናቸው፦

​1. የጭማሪው ምክንያት
የአደጋ ስጋት ፈንድ፦ መንግሥት በሀገሪቱ ለሚከሰቱ ሰው ሠራሽና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ገቢ ለመሰብሰብ ባወጣው አዋጅ መሠረት ነው።

የመንግሥት ትዕዛዝ፦ ባንኮች ከደንበኞቻቸው ላይ ክፍያ በመሰብሰብ ለ"ኢትዮጵያ አደጋ ስጋትና ምላሽ ፈንድ" ገቢ እንዲያደርጉ ታዝዘዋል።

​2. የታዩ የጭማሪ መጠኖች (ለምሳሌ በአዋሽ ባንክ)
በብድር ላይ፦ ከማንኛውም ዓይነት ብድር ላይ 1% ጭማሪ።

በዲጂታል ባንኪንግ፦ በአገልግሎት ክፍያ ላይ 5% ጭማሪ።

የተፈጻሚነት ጊዜ፦ ከየካቲት ወር ጀምሮ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል።

​3. ሌሎች ተያያዥ ክፍያዎች
ኢትዮ ቴሌኮም፦ ዘንድሮ ብቻ ሁለት ጊዜ የዋጋ ማሻሻያ በማድረግ እስከ 700 ብር የሚደርስ ጭማሪ አድርጓል።

የመንግሥት ሠራተኞች፦ በአዲስ አበባ የአስተዳደሩ ሠራተኞች ከደመወዛቸው 0.5% እየተቆረጠባቸው ይገኛል።

የከተማ ነዋሪዎች፦ ከወርኃዊ የውኃ ክፍያ ጋር 5 ብር ለዚሁ ፈንድ ገቢ ያደርጋሉ።
📌 ምንም እንኳን በሕግ ደረጃ ከሠራተኛ ደመወዝ ላይ ማስገደድ አይቻልም የሚሉ ድንጋጌዎች ቢኖሩም፣ በተግባር ግን ክፍያው እየተሰበሰበ መሆኑን ዘገባው ይጠቁማል።
3👏1
አልጀዚራ ይፋ ያወጣው የ20 ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞችና የእስራኤል የጋዛ ድርጊት ውዝግብ አስነሳ

አልጀዚራ "ሊስኒንግ ፖስት" በተሰኘው ፕሮግራሙ ባደረገው ምርመራ፤ እስራኤል በጋዛ እየፈጸመች ያለውን የዘር ፍጅት ገጽታ ለመቀየር 20 ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞችን ጨምሮ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ የሚዲያ ባለሙያዎችን ወጪ በመሸፈን አሳሳች ዘገባዎች እንዲሰሩ ማድረጓ ተጋልጧል።

📌 ከኢቢኤስ: ከአሚኮ፣ ኦቢኤን እና ኤንቢሲ ጨምሮ ከ10 የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን የተውጣጡ 20 ጋዜጠኞች በጉዞው ተካፍለዋል።

📌ጋዜጠኞቹ ባዘጋጇቸው ፕሮግራሞች የፍልስጤማውያንን ድምፅ ያላካተቱ፣ የጉዳቱን መጠን ያሳነሱ እና "ፍልስጤም የሚባል ሕዝብ እንደሌለ" የሚያስመስሉ ይዘቶችን ማሰራጨታቸው ተጠቅሷል።

📌 ጉዞው በእስራኤል መንግሥትና ለእስራኤል ቅርበት ባላቸው ተቋማት (እንደ ደቡብ አፍሪካው አይሁድ ቦርድ) የተመራና ወጪው የተሸፈነ ቢሆንም፣ አብዛኞቹ ጋዜጠኞች ግን የገንዘብ ምንጩን ሳይገልጹ ቀርተዋል።

📌 ጋዜጠኛ ዘካርያስ ዘላለም እና የዘርፉ ባለሙያዎች ድርጊቱን "የጋዜጠኝነት የሥነ-ምግባር ደንብ ጥሰት" እና እውነታን የማድበስበስ ሙከራ ሲሉ ነቅፈውታል።

📌 ከኢትዮጵያ በተጨማሪ ከኬንያ፣ ሩዋንዳ፣ ሴኔጋል እና ደቡብ አፍሪካ የሚዲያ ባለሙያዎችና የሶሻል ሚዲያ አንቂዎች በተመሳሳይ መልኩ ተመልምለው እንደነበር ተገልጿል።

📌በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው ፕሬስ ካውንስል ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ፣ የሚመለከታቸው ጋዜጦች ይቅርታ እንዲጠይቁና የገንዘብ ምንጫቸውን እንዲገልጹ የወሰነ ሲሆን፣ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ግን እስካሁን ለቀረበባቸው ክስ ምላሽ አልሰጡም።
6👍2
ሁለቱ የ4ኪሎ ሚንስትሮች የቃላት ጦርነት ውስጥ ገቡ!

ጌታቸው ረዳ እና በለጠ ሞላ የሚኒስትሮች ምክርቤት አባል ሲሆኑ፤ አገኘሁ ተሻገር የሚመሩት ቢሮ ወልቃይት እና ራያን በተመለከተ በወሰነው ውሳኔ የቃላት ምልልስ እያደረጉ ነው።

ሚኒስትሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔን ደግፈው ውሳኔው " የፕሪቶሪያ ስምምነትን ያከበረ ነው " ብለዋል።

የነ አቶ ጌታቸው ረዳን ፓርቲም " ከፕሪቶሪያ ስምምነት ያፈነገጠ " በሚል ወርፈዋል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ደብዳቤን ተከትሎ ምርጫ ቦርድ ያሳለፈው ውሳኔ ከፍተኛ ውዝግብ አስነስቷል።

የተለያዩ የትግራይ ፓርቲ አመራሮች እንዲሁም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ውሳኔው አደገኛ እንደሆነ አሳስበው ካልተቀለበሰ " መዘዝ አለው " ብለዋል።

የቦርዱን ውሳኔ ከተቃወሙት አንዱ አቶ ጌታቸው ረዳ የስምረት ፓርቲ ፕሬዜዳንት ናቸው። የፓርቲያቸውን አቋም በማያያዝ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ሃሳባቸውን ገልጸዋል።

ይህን ተከትሎ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) የአቶ ጌታቸውን መልዕክት ስክሪንሹት በማያያዝ ተቃውመዋቸዋል።

" የምርጫ ቀጠናዎችን በተመለከተ መንግስት የወሰነው ውሳኔ ህጋዊ እና የፕሪቶሪያ ስምምነትን ያከበረ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" ከፕሪቶሪያ ስምምነት ያፈነገጡ ህጋዊ የፖለቲካ ድርጅቶች ህግ እንዲያከብሩ እናሳስባለን " ሲሉም ገልጸዋል።

በዚሁ መልዕክታቸው የእነ አቶ ጌታቸውን ፓርቲ ከ " ፕሪቶሪያ ስምምነት ያፈነገጡ " ሲሉ ገልጸዋቸዋል።
14🔥2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
❝የጨፈ~ጨፍናቸው የጋዛ ህፃናት በአይነ ህሊናዬ እየመጡ መተናት አልቻልኩም እየተከተሉኝ ነው የፈፀምነው የግ¤ፍ ጥግ እረፍት ነስቶኛል። እንዲህ ሆኜ አልኖርም.....❞

በጋዛ ህፃናት ደም የአይምሮ ህመምተኛ የሆነችው የእስራኤል 🇮🇱 ወታደር

በመጨረሻ ጭንቅላቷን 🔫🔫 ዷዷዷዷዷ 🙊🙊🙊
17👎4
#Coffee

ዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ ከነበረበት 4 ዶላር ወደ 2.8 ዶላር ዝቅ አለ።

የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን በገለጸው መሰረት፣ ባለፉት ሁለት ወራት የዓለም አቀፍ የቡና ዋጋ ከነበረበት 4 ዶላር ወደ 2.8 ዶላር ዝቅ ብሏል፡፡

እንዲሁም በቀጣይ እስከ ወደ 2.5 ዶላር ሊወርድ እንደሚችል መተንበዩ በዘርፉ ላይ ከፍተኛ ስጋት ማሳረፉን የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አዱኛ ደበላ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

በመሆኑም፣ አቅራቢዎች እጃቸው ላይ ያላቸውን የቡና ምርት በፍጥነት ለገበያ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል።

ባለስልጣኑ ይህን ያለው፣ ዓለም አቀፉን የቡና ገበያ ሁኔታ እና የኢትዮጵያን ቡና ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ በሰጠው መግለጫ ነው። ለዋጋው መቀነስ ግን ምክንያቱ በዘገባው አልተጠቀሰም። #EPA
1
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
የእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣናት መደበቂያ “ባንከር” በኢራን ጥቃት ወደመ

በቴል አቪቭ የሚገኘውና እጅግ አስተማማኝ ደህንነት እንዳለው የሚነገርለት "የደህንነት ባንከር" በኢራን የሚሳኤል ጥቃት ሙሉ በሙሉ መውደሙ ተዘግቧል።

ይህ የምድር ውስጥ ዋሻ የእስራኤል ከፍተኛ ባለስልጣናት በከፋ የጥቃት ወቅት መደበቂያነት የሚጠቀሙበት ወሳኝ ስፍራ መሆኑ ጉዳዩን አነጋጋሪ አድርጎታል።
👏14👍62
በነዳጅ መዛባት ሳቢያ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ፤ በሚኒስትሩ ላይም ወቀሳ ቀረበ

ሰሞኑን በታየው የነዳጅ ግዥና ስርጭት መዛባት ሳቢያ የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ሶስት ከፍተኛ ኃላፊዎች እና 18 የንግድ ጽሕፈት ቤት አመራሮች በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።

በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ዲበራ ፉፋ፣ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ እስመለዓለም ምሕረቱ እና ምክትል ሥራ አስፈጻሚው ይገኙበታል።

ኃላፊዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲሆን፣ የባንክ ሂሳባቸውም ታግዶ ምርመራ እየተካሄደባቸው ይገኛል።
ሆኖም የውስጥ ምንጮች እንደሚሉት፣ እስሩ የችግሩን ዋና ምንጮች ያላካተተና "ፍትሐዊ ያልሆነ" ነው።

ምንጮቹ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ አቶ ካሳሁን ጎፌን በቀጥታ በመወቀስ፣ ሚኒስትሩ የነዳጅ ኩባንያዎችን የገበያ ድርሻ ለአንድ ልምድ ለሌለው ኩባንያ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዲሰጥ ማድረጋቸው ለስርጭት መዛባቱ ዋና መንስኤ መሆኑን ገልጸዋል።

ባለፈው ሳምንት በአማካሪ ሚኒስትር አቶ ግርማ ብሩ በተመራ ስብሰባ ላይ በሚኒስትሩና በኩባንያዎች መካከል "እልህ አስጨራሽ" ክርክር መደረጉ የተጠቀሰ ሲሆን፣ የታሰሩት ኃላፊዎች የሚኒስትሩን ትዕዛዝ አስፈጻሚዎች እንጂ ዋና ተዋናይ እንዳልሆኑ ተመልክቷል። ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ላይ እስካሁን የተወሰደ እርምጃ አለመኖሩም ቅሬታ አስነስቷል።
መረጃው የመሠረት ሚዲያ ነው።
11👎2
በለገጣፎ በለሊት የተሞከረው አስገራሚ የፖሊስ ድራማ እና የዳያስፖራው ብልህ ዘዴ
ከአንድ ወር በፊት በለገጣፎ አካባቢ በእኩለ ሌሊት የተከሰተው ድርጊት ለሁላችንም ትልቅ ማስጠንቀቂያ የሚሆን ነው።

ከውጭ ሀገር የመጡ አንድ ዳያስፖራ በመኖሪያ ቤታቸው ተኝተው ሳለ፣ በሃይል በሚንኳኳ የግቢ በር ድንገት ይባንናሉ።

በሩን የሚደበድቡት አካላት ከፌዴራል ፖሊስ ነን፤ የፍርድ ቤት መያዣ ማዘዣ ይዘናል፤ በአስቸኳይ በሩን ይክፈቱ! በማለት ትዕዛዝ ያስተላልፋሉ።

ግለሰቡ ማንነታቸውን ሲጠይቁም፣ ወንጀለኞቹ ማዘዣ የተባለውን ወረቀት በበር ስር ይወረውራሉ።

ሆኖም ግለሰቡ በድንጋጤ በሩን ከመክፈት ይልቅ ብልህ ዘዴን ተጠቀሙ፤ ቆዩኝ፣ ውሻው ተፈቷል ልሰረው፤ ልብስም ልደርብ በማለት ጊዜ ከመግዛታቸውም በላይ፣ ለጎረቤታቸው ስልክ በመደወል ና ውጣና እይልኝ ሲሉ እርዳታ ይጠይቃሉ።

ይሄኔ ነው ፖሊስ ነን ያሉቱ ግለሰቦች ድራማቸው መክሸፉን አውቀው በጨለማው ውስጥ ድምጻቸውን አጥፍተው የተሰወሩት።

በኋላ ላይ ለለገጣፎ ፖሊስ የቀረበው ያው "የመያዣ ማዘዣ" ወረቀት፣ ትክክለኛ የፍርድ ቤት ሰነድ ተመስሎ በረቀቀ ሁኔታ የተዘጋጀ መሆኑ ተረጋግጧል።

አፍነው ሊወስዱኝ ነበር፤ እግዚአብሔር ነው ያተረፈኝ የሚሉት እኚህ ግለሰብ፣ ሌሎች የኢትዮጵያ ቤተሰቦች መሰል የሌሊት ጥቃት እንዳይሰነዘርባቸውና በሩን ከመክፈታቸው በፊት በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲመረምሩ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
9👍2
ባለ ብሬሱ መነኩሴ ተያዘ‼️

ለረዥም ጊዜ ቆሞስ ነኝ በማለት በTikTok ''አባ'' የሚል አካውንት ከፍቶ አስተምራለሁ በሚል ሲንቀሳቀስ የነበረ፣ ባለ ብሬሱ መነኩሴ እየተባለ የሚጠራው ወጣት በትግራይ ክልል በሚገኙ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ወጣቶች እጅ ከፍንጅ ተይዟል።

ግለሰቡ ከሚኖርበት ከተማ ርቆ በሌላ ከተማ ከሚገኝ መስጊድ የምንኩስና ልብሱን እና ቆቡን አውልቆ ገብቶ ሲወጣና የሐሰት የክህነት ማስረጃውን በመያዝ ዳግም የምንኩስና ልብሱን ሲለብስ በቁጥጥር ስር አውለውታል።

ግለሰቡ ሚዲያ ላይ መሰረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት አስተምራለሁ በሚል በ Telegram እና Tiktok ላይ ሰዎችን በመመዝገብ ላይ መቆየቱም ተነግሯል።
9👍5🔥3😁1🤯1