Book club
3.36K subscribers
234 photos
21 videos
1.68K files
1.58K links
በዚህ ቻናል ላይ ቆየት ያሉ አዳዲስ በገበያ ላይ የሌሉ መጽሐፍት በ pdf የሚለቀቅ ይሆናል
Download Telegram
03/11/2016
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 18:15-21


“ወንድምህም ቢበድልህ፥ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻችሁን ሆናችሁ ውቀሰው። ቢሰማህ፥ ወንድምህን ገንዘብ አደረግኸው፤ ባይሰማህ ግን፥ በሁለት ወይም በሦስት ምስክር አፍ ነገር ሁሉ እንዲጸና፥ ዳግመኛ አንድ ወይም ሁለት ከአንተ ጋር ውሰድ፤ እነርሱንም ባይሰማ፥ ለቤተ ክርስቲያን ንገራት፤ ደግሞም ቤተ ክርስቲያንን ባይሰማት፥ እንደ አረመኔና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ። እውነት እላችኋለሁ፥ በምድር የምታስሩት ሁሉ በሰማይ የታሰረ ይሆናል፥ በምድርም የምትፈቱት ሁሉ በሰማይ የተፈታ ይሆናል። ደግሞ እላችኋለሁ፥ ከእናንተ ሁለቱ በምድር በማናቸውም በሚለምኑት ነገር ሁሉ ቢስማሙ በሰማያት ካለው ከአባቴ ዘንድ ይደረግላቸዋል። ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት በዚያ በመካከላቸው እሆናለሁና።”

ቲቶ 3:8-ፍጻሜ
1 ጴጥሮስ 3:15-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 20:28-31


                           ምስባክ
                      መዝሙር 21:22-23


እነግሮሙ ስመከ ለአኃውየ

ወበማዕከለ ማኅበር እሴብሐከ

እለ ትፈርህዎ ለእግዚአብሔር ሰብሕዎ
04/11/2016
                       የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                        ማቴዎስ 21:33-ፍጻሜ


   የወይን አትክልት የተከለ ባለቤት ሰው ነበረ፤ ቅጥርም ቀጠረለት፥ መጥመቂያም ማሰለት፥ ግንብም ሠራና ለገበሬዎች አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። የሚያፈራበትም ጊዜ ሲቀርብ፥ ፍሬውን ሊቀበሉ ባሮቹን ወደ ገበሬዎች ላከ። ገበሬዎቹም ባሮቹን ይዘው አንዱን ደበደቡት አንዱንም ገደሉት ሌላውንም ወገሩት። ደግሞ ከፊተኞች የሚበዙ ሌሎች ባሮችን ላከ፥ እንዲሁም አደረጉባቸው። በኋላ ግን፦ ‘ልጄንስ ያፍሩታል፡’ ብሎ ልጁን ላከባቸው። “ገበሬዎቹ ግን ልጁን ባዩ ጊዜ እርስ በርሳቸው፦ ‘ወራሹ ይህ ነው፤ ኑ፥ እንግደለውና ርስቱን እናግኝ፡’ ተባባሉ። ይዘውም ከወይኑ አትክልት አወጡና ገደሉት።እንግዲህ የወይኑ አትክልት ጌታ በሚመጣ ጊዜ በእነዚህ ገበሬዎች ምን ያደርግባቸዋል?” እነርሱም፦ “ክፉዎችን በክፉ ያጠፋቸዋል፥ የወይኑንም አትክልት ፍሬውን በየጊዜው ለሚያስረክቡ ለሌሎች ገበሬዎች ይሰጠዋል፡” አሉት። ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ ‘ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤ ይህም ከጌታ ዘንድ ሆነ፥ ለዓይኖቻችንም ድንቅ ነው፡ የሚለውን ከቶ በመጽሐፍ አላነበባችሁምን ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት ከእናንተ ትወሰዳለች ፍሬዋንም ለሚያደርግ ሕዝብ ትሰጣለች። በዚህም ድንጋይ ላይ የሚወድቅ ይቀጠቀጣል፤ ድንጋዩ ግን የሚወድቅበትን ሁሉ ይፈጨዋል።” የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ምሳሌዎቹን ሰምተው ስለ እነርሱ እንደ ተናገረ አስተዋሉ፤ ሊይዙትም ሲፈልጉት ሳሉ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስላዩት ፈሩአቸው.....

ዕብራ 11:32-ፍጻሜ
2 ጴጥሮስ 1:19-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 10:37-ፍጻሜ


                                 ምስባክ   
                           መዝሙር 43:1-2


እግዚኦ ሰማዕነ በእዘኒነ

ወአበዊነሂ ዜነዉነ

ግብረ ዘገበርከ በመዋዕሊሆሙ በመዋዕለ ትካት
05/11/2016 /ጴጥሮስ ወጳውሎስ ብርሃናተ ዓለም 72 አርድእት ወይስሐቅ ሰማእት/
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ዮሐንስ 21:15-20


ምሳ ከበሉ በኋላም ኢየሱስ ስምዖን ጴጥሮስን፦ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን?” አለው። “አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ” አለው።“ግልገሎቼን አሰማራ፡” አለው። ደግሞ ሁለተኛ፦ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን?” አለው። “አዎን ጌታ ሆይ፥ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ፡” አለው። “ጠቦቶቼን ጠብቅ፡” አለው። ሦስተኛ ጊዜ፦ “የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን?” አለው። ሦስተኛ፦ “ትወደኛለህን?” ስላለው ጴጥሮስ አዘነና፦ “ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ፡” አለው። ኢየሱስም አለው፦ “በጎቼን አሰማራ። እውነት እውነት እልሃለሁ፥ አንተ ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን በገዛ ራስህ ታጥቀህ ወደምትወደው ትሄድ ነበር፤ ነገር ግን በሸመገልህ ጊዜ እጆችህን ትዘረጋለህ፥ ሌላውም ያስታጥቅሃል ወደማትወደውም ይወስድሃል።” በምን ዓይነት ሞት እግዚአብሔርን ያከብር ዘንድ እንዳለው ሲያመለክት ይህን አለ። ይህንም ብሎ፦ “ተከተለኝ፡” አለው።

የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት
1 ተሰሎንቄ 4:13-ፍጻሜ

   ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። ኢየሱስ እንደ ሞተና እንደ ተነሣ ካመንን፥ እንዲሁም በኢየሱስ ያንቀላፉቱን እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ያመጣቸዋልና። በጌታ ቃል የምንላችሁ ይህ ነውና፤ እኛ ሕያዋን ሆነን ጌታ እስኪመጣ ድረስ የምንቀር ያንቀላፉቱን አንቀድምም፤ ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ፤ ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን። ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ።

2 ጴጥሮስ 1:1-13
ሐዋ.ሥራ 23:10:16

ምስባክ
መዝሙር138:17-18


ወኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዚኦ

ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ

እኌልቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ
ዕርገቱ ለዕዝራ ነቢይ ወንስተሮኒን ወአልሞድያስ ወሥርቀተ ተሙዝ ወዮልዮህ ወተዝካረ በርተሎሜዎስ ወ፲፻ ሰማዕታት ወከላድያን ሊቀ ጳጳሳት
                     06/11/2016
                   የዕለቱ የወንጌል ክፍል


    “እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥ በዚያን ጊዜ በይሁዳ ያሉት ወደ ተራራዎች ይሽሹ፥ በሰገነትም ያለ በቤቱ ያለውን ሊወስድ አይውረድ፥ በእርሻም ያለ ልብሱን ይወስድ ዘንድ ወደ ኋላው አይመለስ። በዚያችም ወራት ለርጉዞችና ለሚያጠቡ ወዮላቸው። ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤ “በዚያን ጊዜ ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያልሆነ እንግዲህም ከቶ የማይሆን ታላቅ መከራ ይሆናልና። እነዚያ ቀኖችስ ባያጥሩ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ባልዳነም ነበር፤ ነገር ግን እነዚያ ቀኖች ስለ ተመረጡት ሰዎች ያጥራሉ። በዚያን ጊዜ ማንም፦ እነሆ፥ ክርስቶስ ከዚህ አለ፡ ወይም፦ ከዚያ አለ፡ ቢላችሁ አትመኑ፤ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ። እነሆ፥ አስቀድሜ ነገርኋችሁ። እንግዲህ፦ ‘እነሆ፥ በበረሀ ነው’ ቢሉአችሁ፥ አትውጡ፤ ‘እነሆ፥ በእልፍኝ ነው’ ቢሉአችሁ፥ አትመኑ፤ መብረቅ ከምሥራቅ ወጥቶ እስከ ምዕራብ እንደሚታይ፥ የሰው ልጅ መምጣት እንዲሁ ይሆናልና፤ በድን ወዳለበት በዚያ አሞራዎች ይሰበሰባሉ። ከዚያች ወራትም መከራ በኋላ ወዲያው ፀሐይ ይጨልማል፥ ጨረቃም ብርሃንዋን አትሰጥም፥ ከዋክብትም ከሰማይ ይወድቃሉ፥ የሰማያትም ኃይላት ይናወጣሉ። በዚያን ጊዜም የሰው ልጅ ምልክት በሰማይ ይታያል፥ በዚያን ጊዜም የምድር ወገኖች ሁሉ ዋይ ዋይ ይላሉ፥ የሰው ልጅንም በኃይልና በብዙ ክብር በሰማይ ደመና ሲመጣ ያዩታል፤ መላእክቱንም ከታላቅ መለከት ድምፅ ጋር ይልካቸዋል፥ ከሰማያትም ዳርቻ እስከ ዳርቻው ከአራቱ ነፋሳት ለእርሱ የተመረጡትን ይሰበስባሉ። ምሳሌውንም ከበለስ ተማሩ፤ ጫፍዋ ሲለሰልስ ቅጠልዋም ሲያቈጠቍጥ፥ ያን ጊዜ በጋ እንደ ቀረበ ታውቃላችሁ፤ እንዲሁ እናንተ ደግሞ ይህን ሁሉ ስታዩ በደጅ እንደ ቀረበ እወቁ። እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ሁሉ እስኪሆን ድረስ ይህ ትውልድ አያልፍም። ሰማይና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም።”

1 ቆሮንጦስ  15:33-45
1 ዮሐንስ 2:20-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 16:14-18


                         ምስባክ
                     መዝሙር 55:13-14


እስመ አድኀንካ ለነፍስየ እሞት

ወለአዕይንትየኒ እምኣንብዕ

ወለእገርየኒ እምዳህፅ
አቤሮም ወኀተሞ በላኒ ወአባ ሚካኤል ወኤስድሮስ ወጴጥሮስ ወቢማ ወኪሮስ ወብሶይ
08/11/2016
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማርቆስ 4:1-24


ደግሞም በባሕር ዳር ሊያስተምር ጀመረ። እጅግ ብዙ ሰዎችም ወደ እርሱ ስለ ተሰበሰቡ እርሱ በታንኳ ገብቶ በባሕር ላይ ተቀመጠ፤ ሕዝቡም ሁሉ በባሕር ዳር በምድር ላይ ነበሩ። በምሳሌም ብዙ ያስተምራቸው ነበር፥ በትምህርቱም አላቸው፦ “ስሙ። እነሆ፥ ዘሪ ሊዘራ ወጣ። ሲዘራም አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀና ወፎች መጥተው በሉት። ሌላውም ብዙ መሬት በሌለበት በጭንጫ ላይ ወደቀና ጥልቅ መሬት ስላልነበረው ወዲያው በቀለ፤ ፀሐይም ሲወጣ ጠወለገ፥ ሥርም ስላልነበረው ደረቀ። “ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀ፥ እሾህም ወጣና አነቀው፥ ፍሬም አልሰጠም። ሌላውም በመልካም መሬት ላይ ወደቀና ወጥቶ አድጎ ፍሬ ሰጠ፥ አንዱም ሠላሳ አንዱም ስድሳ አንዱም መቶ አፈራ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ፡” አለ። ብቻውንም በሆነ ጊዜ፥ በዙሪያው የነበሩት ከአሥራ ሁለቱ ጋር ስለ ምሳሌው ጠየቁት። እንዲህም አላቸው፦ “ለእናንተ የእግዚአብሔርን መንግሥት ምሥጢር ማወቅ ተሰጥቶአችኋል፤ በውጭ ላሉት ግን፥ ‘አይተው እንዲያዩ እንዳይመለከቱም፥ ሰምተውም እንዲሰሙ እንዳያስተውሉም፥ እንዳይመለሱ ኃጢአታቸውም እንዳይሰረይላቸው’ ነገር ሁሉ በምሳሌ ይሆንባቸዋል።” አላቸውም፦ “ይህን ምሳሌ አታውቁምን? እንዴትስ ምሳሌዎቹን ሁሉ ታውቃላችሁ? ዘሪው ቃሉን ይዘራል። ቃልም በተዘራበት በመንገድ ዳር የሆኑት እነዚህ ናቸው፥ በሰሙት ጊዜም ሰይጣን ወዲያው መጥቶ በልባቸው የተዘራውን ቃል ይወስዳል። “እንዲሁም በጭንጫ ላይ የተዘሩት እነዚህ ናቸው፥ ቃሉንም ሰምተው ወዲያው በደስታ ይቀበሉታል፥ ለጊዜውም ነው እንጂ በእነርሱ ሥር የላቸውም፥ ኋላም በቃሉ ምክንያት መከራ ወይም ስደት በሆነ ጊዜ ወዲያው ይሰናከላሉ። “በእሾህም የተዘሩት ሌሎች ናቸው፥ ቃሉን የሰሙት እነዚህ ናቸው፥ የዚህም ዓለም አሳብና የባለጠግነት ማታለል የሌላውም ነገር ምኞት ገብተው ቃሉን ያንቃሉ፥ የማያፈራም ይሆናል። በመልካምም መሬት የተዘሩት ቃሉን ሰምተው የሚቀበሉት አንዱም ሠላሳ አንዱም ስድሳ አንዱም መቶ ፍሬ የሚያፈሩት እነዚህ ናቸው።” እንዲህም አላቸው፦ “መብራትን ከዕንቅብ ወይስ ከአልጋ በታች ሊያኖሩት ያመጡታልን? በመቅረዝ ላይ ሊያኖሩት አይደለምን? እንዲገለጥ ባይሆን የተሰወረ የለምና፤ ወደ ግልጥ እንዲመጣ እንጂ የተሸሸገ የለም። የሚሰማ ጆሮ ያለው ቢኖር ይስማ...

ኤፌሶን 6:10-19
1 ጴጥሮስ 3:10-15
ሐዋ.ሥራ 26:12-19



ምስባክ
መዝሙር 115:6-7

ክቡር ሞቱ ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር

እግዚኦ አነ ገብርከ

ገብርከ ወልደ ዓመትከ
09/11/2013
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ሉቃስ 13:18-23


እርሱም፦ “የእግዚአብሔር መንግሥት ምን ትመስላለች፥ በምንስ አስመስላታለሁ? ሰው ወስዶ በአትክልቱ የጣላትን የሰናፍጭ ቅንጣት ትመስላለች፤ አደገችም ታላቅ ዛፍም ሆነች፥ የሰማይ ወፎችም በቅርንጫፎችዋ ሰፈሩ፡” አለ። ደግሞም፦ “የእግዚአብሔርን መንግሥት በምን አስመስላታለሁ? ሴት ወስዳ ሁሉ እስኪቦካ ድረስ በሦስት መስፈሪያ ዱቄት የሸሸገችውን እርሾ ትመስላለች፡” አለ። ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ ከተማዎችንና መንደሮችን እያስተማረ ያልፍ ነበር....

1 ጢሞቴዎስ 3:1-11
1 ጴጥሮስ 5:1-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 20:28-31


ምስባክ
                    መዝሙር 83:6

እስመ መምህረ ህግ ይሁብ በረከተ

ወየኃውር እምኃይል ውስተ ኃይል

ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን

               ትርጉም

የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና

ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ

የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል
11/11/2016
                   የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                      ሉቃስ 6:20-27

   
    እርሱም ወደ ደቀ መዛሙርቱ ዓይኑን አነሣ፥ እንዲህም አላቸው፦  “እናንተ ድሆች ብፁዓን ናችሁ፥ የእግዚአብሔር መንግሥት የእናንተ ነውና። እናንተ አሁን የምትራቡ ብፁዓን ናችሁ፥ ትጠግባላችሁና። እናንተ አሁን የምታለቅሱ ብፁዓን ናችሁ፥ ትስቃላችሁና።ሰዎች ስለ ሰው ልጅ ሲጠሉአችሁ ሲለዩአችሁም ሲነቅፉአችሁም ስማችሁንም እንደ ክፉ ሲያወጡ፥ ብፁዓን ናችሁ። እነሆ፥ ዋጋችሁ በሰማይ ታላቅ ነውና በዚያን ቀን ደስ ይበላችሁ ዝለሉም፤ አባቶቻቸው ነቢያትን እንዲህ ያደርጉባቸው ነበርና። “ነገር ግን እናንተ ባለ ጠጎች ወዮላችሁ፥ መጽናናታችሁን ተቀብላችኋልና። እናንተ አሁን የጠገባችሁ ወዮላችሁ፥ ትራባላችሁና። እናንተ አሁን የምትስቁ ወዮላችሁ፥ ታዝናላችሁና ታለቅሱማላችሁ። ሰዎች ሁሉ መልካም ሲናገሩላችሁ፥ ወዮላችሁ፤ አባቶቻቸው ለሐሰተኞች ነቢያት እንዲሁ ያደርጉላቸው ነበርና.....

1 ጢሞቴዎስ 2:1-9
1 ጴጥሮስ 4:12-17
ሐዋ.ሥራ 14:20-ፍጻሜ
12/11/2016
                      የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                         ሉቃስ 18:1-9

      ሳይታክቱም ዘወትር ሊጸልዩ እንዲገባቸው የሚል ምሳሌን ነገራቸው፥ እንዲህ ሲል፦ “በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች፦ ‘ከባላጋራዬ ፍረድልኝ፡’ ትለው ነበር። አያሌ ቀንም አልወደደም፤ ከዚህ በኋላ ግን በልቡ፦ ‘ምንም እግዚአብሔርን ባልፈራ ሰውንም ባላፍር፥ ይህች መበለት ስለምታደክመኝ ሁልጊዜም እየመጣች እንዳታውከኝ እፈርድላታለሁ፡’ አለ።” ጌታም አለ፦ “ዓመፀኛው ዳኛ ያለውን ስሙ። እግዚአብሔር እንኪያስ ቀንና ሌሊት ወደ እርሱ ለሚጮኹ ለሚታገሣቸውም ምርጦቹ አይፈርድላቸውምን? እላችኋለሁ፥ ፈጥኖ ይፈርድላቸዋል። ነገር ግን የሰው ልጅ በመጣ ጊዜ በምድር እምነትን ያገኝ ይሆንን?”.............

ሮሜ 9:17-30
ይሁዳ 1:6-14
ሐዋ.ሥራ 10 3:9


                       ምስባክ
                 መዝሙር 32:16-17


ኢይድኅን ንጉሥ በብዝኀ ሠራዊቱ

ወያርብሕኒ ኢድኅነ በብዝኀ ኀይሉ

ወፈረስኒ ሐሰተ ኢያድኅን

                      ትርጉም

ንጉሥ በሠራዊቱ ብዛት አይድንም

ኃያልም በኃይሉ ብዛት አይድንም

ፈረስም ከንቱ ነው አያድንም
13/11/2016
                    የዕለቱ የወንጌል ክፍል
                     ማቴዎስ 10:32-ፍጻሜ


    ስለዚህ በሰው ፊት ለሚመሰክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ፤ በሰው ፊትም የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እክደዋለሁ። በምድር ላይ ሰላምን ለማምጣት የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ሰይፍን እንጂ ሰላምን ለማምጣት አልመጣሁም። ሰውን ከአባቱ፥ ሴት ልጅንም ከእናትዋ፥ ምራትንም ከአማትዋ እለያይ ዘንድ መጥቻለሁና፤ ለሰውም ቤተ ሰዎቹ ጠላቶች ይሆኑበታል። “ከእኔ ይልቅ አባቱን ወይም እናቱን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ ከእኔ ይልቅም ወንድ ልጁን ወይም ሴት ልጁን የሚወድ ለእኔ ሊሆን አይገባውም፤ መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም። ነፍሱን የሚያገኝ ያጠፋታል፥ ነፍሱንም ስለ እኔ የሚያጠፋ ያገኛታል። “እናንተን የሚቀበል እኔን ይቀበላል፥ እኔንም የሚቀበል የላከኝን ይቀበላል። ነቢይን በነቢይ ስም የሚቀበል የነቢይን ዋጋ ይወስዳል፥ ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል። ማንም ከእነዚህ ከታናናሾቹ ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ ብቻ በደቀ መዝሙር ስም የሚያጠጣ፥ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋው አይጠፋበትም......

ሮሜ 8:18-35
1 ጴጥሮስ 1:13-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 19:11-21


                                ምስባክ
                          መዝሙር 1:2-3


ወዘሕጎ ያነብብ መዓልተ ወሌሊተ

ወይከውን ከመ ዕፅ እንተ ትክልት ኀበ ሙኃዘ ማይ

እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ
14/11/2016
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 13:1-10

በዚያን ቀን ኢየሱስ ከቤት ወጥቶ በባሕር አጠገብ ተቀመጠ፤ እርሱም በታንኳ ገብቶ እስኪቀመጥ ድረስ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፥ ሕዝቡም ሁሉ በወደቡ ቆመው ነበር። በምሳሌም ብዙ ነገራቸው፥ እንዲህም አላቸው፦ “እነሆ፥ ዘሪ ሊዘራ ወጣ። እርሱም ሲዘራ አንዳንዱ በመንገድ ዳር ወደቀ፥ ወፎችም መጥተው በሉት። ሌላውም ብዙ መሬት በሌለበት በጭንጫ ላይ ወደቀ፤ ጥልቅ መሬትም ስላልነበረው ወዲያው በቀለ፥ “ፀሐይ በወጣ ጊዜ ግን ጠወለገ፥ ሥርም ስላልነበረው ደረቀ። ሌላውም በእሾህ መካከል ወደቀ፥ እሾህም ወጣና አነቀው። ሌላውም በመልካም መሬት ወደቀ፤ አንዱም መቶ፥ አንዱም ስድሳ፥ አንዱም ሠላሳ ፍሬ ሰጠ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ......

1 ተሰሎንቄ 4:1-13
1 ጴጥሮስ 5:6-ፍጻሜ
ሐዋ.ሥራ 14:19-ፍጻሜ


ምስባክ
መዝሙር 43:22-23


እስመ በእንቲአሁ ይቀትሉነ ኩሎ አሚረ

ወኮነ ከመ አባግዕ ዘይጠብሑ

ንቃዕ እግዚኦ ለምንት ትነውም
15/11/2016
የዕለቱ የወንጌል ክፍል
ማቴዎስ 4:17-21


ከዚያ ዘመን ጀምሮ ኢየሱስ፦ “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ፡” እያለ ይሰብክ ጀመር። በገሊላ ባሕር አጠገብ ሲመላለስም ሁለት ወንድማማች ጴጥሮስ የሚሉትን ስምዖንን ወንድሙንም እንድርያስን መረባቸውን ወደ ባሕር ሲጥሉ አየ፥ ዓሣ አጥማጆች ነበሩና። እርሱም፦ “በኋላዬ ኑና ሰዎችን አጥማጆች እንድትሆኑ አደርጋችኋለሁ፡” አላቸው። ወዲያውም መረባቸውን ትተው ተከተሉት።

ሮሜ 1:18-26
ዓዲ ኤፌሶን 5:7-21
ያዕቆብ 5:12-17
ሐዋ.ሥራ 9:22-30


ምስባክ
መዝሙር 88:6-7


መኑ ይትዔየሮ ለእግዚአብሔር በደመናት

ወመኑ ይመስሎ ለእግዚአብሔር እንደቂቀ አማልእክት

እግዚአብሔር ስቡሕ በምክረ ቅዱሳን
ነገ ሐምሌ 15 የጸጋህን ማእበል ግታልኝ ብሎ እስከመጸለይ የደረሰው ብዙ ድርሳናትን እና ተግሣጻትን የደረሰው በጉባኤ ኒቂያ ከ 318 ሊቃውንት ጋር የነበረው የውዳሴ ማርናም ደራሲ የቅዱስ ኤፍሬም የእረፍቱ በዓል ነው
ከቻላቹ ነገ የሰባቱን ቀን ውዳሴ ማርያም በማድረስ ታላቁን ቅዱስ ዘክረን ከበረከቱ እንካፈል

የቅዱሱ በረከት አይለየን
ይሄ ቻናል ከተከፈተ ከ 15/04/2015 እስካሁን ድረስ መጽሐፍትን እና የዕለቱን ግጻዌ ሲለቀቅ ቆይቷል በዚ ጊዜ ለነበረን ቆይታ ከልብ አመሰግናለሁ ከዚ በኋላ ይሄን ቻናል ማስተዳደር ስላልቻልኩ ( ማለትም የተከፈተበት የነበረው አካውንት ስለተደለተ ) ቻናሉን ለመደለት ተገድጃለው ከነገ ጀምሮ ቻናሉ የማይኖር ይሆናል የየዕለቱን ወንጌል ለማንበብ ከላይ ግጻዌ አለ ተጠቀሙ
https://t.me/onlyeotc_books


በዚ link ተቀላቀሉ
Book club
https://t.me/onlyeotc_books በዚ link ተቀላቀሉ
ይሄ ነገ ይደለታል ከላይ የላኩት link አዲስ የተከፈተው ነው ሰዎችን ጋብዙ እናንተም ተቀላቀሉ
ሁላቹም ከዚ ቻናል leave በማለት ተባበሩን በሌላ ሰው ቁጥጥር ስላለ መደለቱ ስላስቸገረኝ leave በማለት ተባበሩን
አዲሱ ቻናላችንን ተቀላቀሉ

https://t.me/ethiobookclub2