TIKVAH-ETHIO
684 subscribers
661 photos
27 videos
7 files
74 links
Download Telegram
#Egypt #Ethiopia #Sudan

በሕዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል የሚደረገው ድርድር በሚቀጥለው #እሁድ ታህሳስ 25 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚቀጥልም አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልፀዋል።

አምባሳደሩ ይህን የገለፁት በሰጡት ሳምንታዊ መግለጫ ላይ ነው።

ከታላቁ ህዳሴው ግድብ ድርድር ራሷን አግልላ የነበረችው #ሱዳን ወደ ድርድሩ እንደምትመለስ በቅርቡ ይፋ ማድረጓ ይታወቃል፡፡

አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በሰጡት መግለጫ ላይ ያነሷቸውን ሌሎች ጉዳዮች በዚህ ማግኘት ትችላላችሁ : telegra.ph/ALAIN-12-29 (መረጃውን አዘጋጅቶ ያሰራጨው አል ዓይን ኒውስ ነው)
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
ፎቶ ፦ ፌልትማን ኢትዮጵያ ገብተዋል።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የሆኑት ጄፍሪ ፌልትማን ዛሬ ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) ገብተዋል፤ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኃላም ከሙሳ ፋኪ ማሃመት ጋር ተገናኝተው መክረዋል።

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማሃማት ፌልትማንን በይፋዊ የትዊተር ገፃቸው ጄፍሪ ፌልትማንን በቢሯቸው ተቀብለው በ #ኢትዮጵያ እና #ሱዳን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን አሳውቀዋል።

Credit : Moussa Faki Mahamat (Twitter)

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA