TIKVAH-ETHIO
626 subscribers
661 photos
27 videos
7 files
74 links
Download Telegram
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከከተማው የፀጥታ አካላት ጋር አትክልት ተራ አካባቢ እየታየ ባለው መጨናነቅ ዙሪያ ተወያይተዋል።

ቦታው ከፍተኛ የአትክልት ምርት ማከፋፈያ ሲሆን ከፍተኛ የሰው ጭንቅንቅ በየእለቱ የሚታይበትና ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘም ለቁጥጥር አስቸጋሪ መሆኑ ተገምግሟል።

ስለሆነም ከመጪው ሰኞ ጀምሮ የአትክልት ግብይቱ በጊዜያዊነት ወደ ጃንሜዳ እንዲዘዋወር ተወስኗል። አትክልት ተራ ለጊዜው ለነጋዴዎቹ እንደ እቃ ማስቀመጫ (ስቶር) ብቻ እንዲያገለግል ተወስኗል።

ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከዛሬ ጥቅምት 30 ጀምሮ አዲስ የነዋሪዎች መታወቂያ መሰጠትና የመሸኛ አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ ተቋረጠ።

ይህን የገለፀው የአ/አ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ ነው።

የመታወቂያ እድሳት እና ምትክ መስጠት ግን አልተቋረጠም።

አዲስ መታወቂያ መስጠቱ የቆመው ወቅታዊው ሁኔታ ጋር በተያያዘ አዳዲስ መታወቂያ ተሰጥቶ ለተለያዩ እኩይ ዓላማ መጠቀሚያ እንዳይሆኑ ቁጥጥር ለማድረግ ነው ተብሏል።

Via Sheger FM 102.1
@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba

የሀገር መከላከያ ሰራዊት በቁጥጥር ስር እንዳዋሉ የገለፀው አቶ ስብሃት ነጋን ጨምሮ ዘጠኝ የህወሓት አመራሮች ዛሬ አዲስ አበባ መግባታቸው ተገጿል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
Media is too big
VIEW IN TELEGRAM
#AddisAbaba

ቀደም ሲል እንደተገለፀው አቶ ስብሃትን ጨምሮ ዘጠኝ (9) የህወሓት አመራሮች በመከላከያ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ማስረጃ ምሽቱን በኢዜአ በኩል ተሰራጭቷል።

የህወሓት አመራሮች በቁጥጥር ስር የዋሉት በማዕከላይ ትግራይ ውስጥ ኤዴር አዴት በሚባል አከባቢ ልዩ ስሙ "ጅራ" በሚባል ቦታ ሲሆን ዛሬ በጦር አውሮፕላን ተጭነው አዲስ አበባ ገብተዋል። [50 MB]

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba

የቀድሞ የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚዳንት አባይ ወልዱን ጨምሮ በቁጥጥር ስር የዋሉ የሕወሃት አመራሮች ዛሬ አዲስ አበባ መግባታቸው ተገልጿል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
አጭር መረጃ ስለ ዑራኤል-ወሎ ሰፈር የመንገድ ፕሮጀክት ፦

#AddisAbaba

- ይህ መንገድ ፕሮጀክት እየተሰራ የሚገኘው በአዲስ አበባ የመንገዶች ባለስልጣን ነው። ይህ ፕሮጀክት ባለስልጣኑ አቅዶ እያሰራቸው ካሉ ከ100 በላይ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው።

- የመንገድ ፕሮጀክቱ በአ/አ ከተማ አስተዳደሩ በጀት ተመድቦለት ነው እየተሰራ ያለው።

- ከዑራኤል-ወሎ ሰፈር ፕሮጀክት (አስፓልት የማንጠፍ ስራ) 1.1 ኪ.ሜ ርዝመት እና 35 ሜትር የጎን ስፋት አለው።

- ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ ከ111 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦለት ነው እየተሰራ የሚገኘው።

- 82 በመቶ ተጠናቋል።

- ቀንም ለሊትም ነው እየተሰራ ያለው። ይህም የምሽት የስራ ባህልን ያሳደገ እንደሆነ ተገልጿል።

- ከመገናኛ በኩል ከሚመጡ መንገዶች ጋር በቀጥታ የሚተሳሰር ሲሆን በአቅራቢያ ባሉ መንገዶች ላይ ያለውን መጨናነቅ ይቀንሳል ተብሎ ይጠበቃል።

- በሁለቱ መንገድ አካፋይ ፓርኪንግ ያለው ፣ በዳር በኩል የሳይክል መንገድ አለው፣ ሌላኛው የእግረኛ መንገድ ሲሆን ይህ የእግረኛ መንገድ የአካል ጉዳተኞችንም ታሳቢያ ያደረገ ነው።

- የመንገድ ስራው በፍጥነት እንዳይጠናቀቀ የወሰን ማስከበር ስራዎች አለመጠናቀቃቸው እንቅፋት ሆኗል። አሁንም ያተጠናቀቁ አሉ።

- ከወሰን ማስከበር ችግሮች ካሉባቸው ቦታዎች ውጪ እስከ ሰኔ ድረስ ለትራፊክ ክፍት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

[አዲስ ቴቪ ፣ የአ/አ መንገዶች ባለስልጣን ምክትል ዳይሬክተር አቶ እያሱ ሰለሞን፣ የሎት አንድ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት ፕሮጀክት ማናጀር ኢ/ር ብስራት ሙልጌታ]

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ላይ ዘጠኝ የምርጫ ጣቢያዎች ስልጠና የተሰጣቸው የምርጫ አስፈጻሚዎች በጣቢያው ሳይገኙ በመቅረታቸው ምርጫው በጣቢያዎቹ ዘግይቶ መጀመሩን ቦርዱ ገልጿል።

የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርትኳን ሚዴቅሳ እነዚህ ምርጫ ጣቢያዎች ላይ አሰልጣኝ የነበሩ ብቁ 27 አስፈጻሚዎች መተካታቸውንና ምርጫው መጀመሩን ገልፀዋል።

በተጨማሪም በአዲስ አበባ አንድ ምርጫ ጣቢያ የመራጮች መዝገብ መጥፋቱንም አሳውቀዋል።

ጉዳዩ እንደሚጣራ በመጥቀስ አሁን ላይ መዝገብ እና ምርጫ አስፈጻሚ ተልኮ በጣቢያው የተመዘገቡ ካርዳቸው ከጣቢያው መወሰዱ የተረጋገጠ መራጮች እየተመዘገቡ የምርጫ ሂደታቸውን እያከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል።

#ዘግይተው_የተከፈቱ የምርጫ ጣቢያዎችን አስመልክቶ ከጋዜጠኞች ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርትኳን ሂደቱን ተመልክቶ ቦርዱ በተለየ ሁኔታ ተጨማሪ ጊዜ ሊሰጥ እንደሚችል ገልጸዋል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba : የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በስኬት እንዲጠናቀቅ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን ለማስፈጸም በከተማ አስተዳደሩ ከተዋቀረው የኮማንድ ፖስት አባላት ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡

ከጥቅምት 29 - ህዳር 2 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በመሰራት ላይ መሆናቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

ብሄራዊ ፈተናው በከተማ ደረጃ በስኬት እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተከናውነዋል ያሉት የትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ አንዳንድ የግል ትምርት ቤቶች ግን እስከ አሁን አድሚሽን ካርድ ለተማሪዎች አለማድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ በ62 የፈተና ጣቢያዎች 36,415 ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ፈተና እንደሚወስዱ እና ይህንንም የሚመሩና የሚያስተባብሩ 2ሺ 600 የፈተና አስፈጻሚዎች ምልመላ መካሄዱን ቢራ ገልፆል፡፡

መረጃው የአ/አ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ነው።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba : የፍትህ ሚኒስቴር የህ/ተ/ም/ቤት አሸባሪ ብሎ ለፈረጀው ትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) ድጋፍ ያደርጋሉ፤ ግንኙነትም አላቸው ተብለው የታሸጉ ፋብሪካዎች ፣ የተለያዩ ድርጅቶች አስተዳዳሪ ተሹሞላቸው በቅርቡ ስራ ይጀምራሉ ሲል አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ ይህን ያሳወቀው ለሪፖርተር ጋዜጣ ነው።

ከጥቂት ወራት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ በርካታ የንግድ ድርጅቶች እና ሆቴሎች የንግድ ህጉን በመጣስ እና ለTPLF የሽብር ተግባር ድጋፍ ያደርጋሉ በሚል ጥርጣሬ ታሽገው ነበር።

ከተዘጉት የንግድ ድርጅቶች መካከል በርካቶቹ ተመልሰው እንደተከፈቱ ነገር ግን ቁጥራቸው በግልፅ የማይታወቅ ትልልቅ ሆቴሎች ጭምር አሁንም ድረስ ዝግ እንደሆኑ ናቸው።

ከሆቴሎቹ መካከል ፦
- ካሌብ ሆቴል
- ኔክሰስ ሆቴል
- አክሱም ሆቴል
- ንግስተ ሳባ ሆቴል
- ሀርመኒ ሆቴል እና ሌሎችም ይገኙበታል።

ቃላቸውን ለሪፖርተር ጋዜጣ የሰጡት የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍቃዱ ፀጋ ፥ " በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን የንግስ ድርጅቶች እና ሆቴሎች አስተዳዳሪ ተሹሞላቸው ስራቸውን እንደገና እንዲቀጥሉ ለማድረግ እየተሰራ ነው" ብለዋል። ነገር ግን በድርጅቶቹ ላይ የሚደረገር ምርመራ እንደሚቀጥል ለጋዜጣው አሳውቀዋል።

ፍትህ ሚኒስቴር በወንጀል የተጠረጠሩትን ተቋማትና ግለሰቦች ወደፍርድ እንደሚያቀርብ የጠቀሱት ሚኒስትር ዴኤታው የከተማ አሰተዳደሩ ድርጅቶቹን ለመክፈት ወይም ላለመክፈት አስተዳደራዊና የወንጀል ህጉን መሰረት በማድረግ ውሳኔ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።

አቶ ፍቃዱ ፥ በሆቴሎችም ሆነ በንግድ ድርጅቶች ውስጥ ይሰሩ የነበሩ ሰራተኞች ስራ አጥ መሆን የለባቸውም ያሉ ሲሆን ድርጅቶቹ በተቻለ መጠን ወደ ስራ እንዲመለሱ ለማድረግ እተሰራ ነው ብለዋል።

telegra.ph/ER-10-27

@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba : የጭነት፣ ማሽነሪዎች እና መሰል ተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ ክልከላ ወደ ነበረበት መመለሱ ተገለፀ፡፡

በመዲናዋ የጭነት፣ ማሽነሪዎች እና መሰል ተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት መመለሱን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

በአሁኑ ሰዓት ከትምህርት ቤቶች መከፈት ጋር ተያይዞ በስራ መግቢያና መውጫ ሰዓት በከተማው ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ አየተስተዋለ በመሆኑ የጭነት፣ ማሽነሪዎች እና መሰል ተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ወደ ነበረበት መመለስ እንዳስፈለገ ተገልጿል።

በመሆኑም ከጥቅምት 22 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ በመመሪያው መሰረት ማንኛውም የጭነት፣ የማሽነሪዎች እና መሰል ተሽከርካራች ከማለዳ 12፡30 እስከ 4፡00 ሰዓት እንዲሁም ከቀኑ 10፡00 እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት ወደ ከተማ ውስጥ መግባትም ሆነ በከተማ ውስጥ መንቀሳቀስ እንዲሁም ጭነት መጫንና ማራገፍ እንደማይችሉ የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ተጨማሪ አዳዲስ የደንብ ልብሶችን ስራ ላይ ማዋሉን ዛሬ አሳውቋል።

ነባሩን የደንብ ልብስ መጠቀም ማቆሙን ተቋሙ ገልጿል፡፡

ከዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ አዳዲሶቹ የደንብ አልባሳትን ብቻ መጠቀም እንደሚገባ እና ነባሩ የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ መቀየሩ ተገልጿል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ አሮጌውን የደንብ ልብስ ለብሶ የተገኘ አመራር እና አባል ላይ ጠንከር ያለ የዲስፕሊን እርምጃ ይወሰድበታል ተብሏል።

ህብረተሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አሮጌው የደንብ ልብስ ሙሉ በሙሉ በአዳዲሶቹ መቀየሩን ተገንዝበው አሮጌውን የደንብ ልብስ የለበሰ የፖሊስ አባል ሲያጋጥማቸው መረጃ በመስጠት እንዲተባበሩ ጥሪ ቀርቧል።

በተጨማሪም የአዲስ አበባ ፖሊስ ስራ ላይ ካዋላቸው አዳዲስ የደንብ አልባሳት ጋር ወይም ከሌሎች የፀጥታ አካላት የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ወይም ተቀራራቢ ዩኒፎርም መጠቀም ክልክል መሆኑ በህግ የተደገገ ስለሆነ ከአ/አ ፖሊስ የደንብ ልብስ ጋር ተመሳሳይ ዩኒፎርም የሚጠቀሙ አካላት ማስተካከያ እንዲያደርጉ ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።

#AddisAbabaPolice

#Share #ሼር

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA
#AddisAbaba

በእጃቹ ያለውን መሳሪያ እስከ ጥቅምት 27 / 2014 ደረስ ማስመዝገብ ትችላላችሁ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ በተለያዩ ምክንያቶች የጦር መሳሪያ ምዝገባው እስከ ጥቅምት 27 ቀን 2014 ዓ/ም በድጋሚ መራዘሙን አሳውቋል።

የጦር መሳሪያ በእጁ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብ በአስራ አንዱ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያዎችና በሁሉም ፖሊስ ጣቢያዎች በግንባር በመገኘት እንዲያስመዘግብ መልዕክት መተላለፉን ተከትሎ በርካታ ግለሰቦች በእጃቸው ላይ የሚገኝን የጦር መሳሪያ ለተከታታይ 3 ቀናት ማስመዝገባቸው ተገልጿል።

መሳሪያ በእጃቸው ላይ ያለ ሰዎች የማስመዝገብ ፍላጎቱ እያላቸው የምዝገባ ቀኑ በማጠሩ ፣ ያላቸውን የጦር መሳሪያ ሌላ ቦታ በማስቀመጣቸው እና ማስመዝገብ እንደሚቻል በቂ መረጃ ያልሰሙ ግለሰቦች በመኖራቸው ምክንያት ምዝገባው እስከ ጥቅምት 27 ቀን 2014 ዓ/ም መራዘሙ ተገልጿል።

በእጁ ላይ የሚገኝ የጦር መሳሪያ ያላስመዘገበ ማንኛውም ግለሰብ የተጨመረውን ቀን ተጠቅሞ እንዲያስመዘግብ የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳስቧል።

@ETHIO_TIKVHA
@ETHIO_TIKVHA