Ministry of Education Ethiopia
120K subscribers
3.03K photos
32 videos
6 files
397 links
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
Download Telegram
የትምህርት ሚኒስቴር ከICDL Africa እና kepler ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
-------------------------- // ----------------------------
(ታህሳስ 04/2017 ዓ.ም) ስምምነቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ምሩቃንን የዲጂታልና ሶፍት ሰኪል በማጎልበት ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ድጋፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

በሂደትም የዩኒቨርሲቲ እና ኢንዱስትሪ ትብብርን በማሳደግ ምሩቃን የተሻለ ክህሎት እና የስራ እድል የሚያገኙበትን ሁኔታዎች ለማመቻቸት እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ምሩቃን ያለባቸውን የዲጂታልና ሶፍት ስኪል ክህሎት ክፍተቶች በመለየት ድጋፍ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።

ሚኒስተር ድኤታው አክለው እንደገለጹት የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከኢንዱስትሪ ዘርፉ ጋር ያላቸውን ትስስርና ትብብር በተለየ መልኩ ለመደገፍ እገዛ እንደሚኖረውም አብራርተዋል።

የአይሲዲኤል አፍሪካ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሶሎንዥ ኢሚዩሊሳ በበኩላቸው ድርጅታቸው አፍሪካውያን ተገቢውን የዲጂታል ክህሎት የተላበሱ እንዲሆኑ ለማድረግ የሚሰራ ደርጅት መሆኑን በመጥቀስ ባለው አቅም ድጋፍ ለማድረግና አብሮ ለመስራት ፍላጎት ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የኪፕለር ዳይሬክትር በበኩላቸው የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ምሩቃንን በመደገፍና በማሰልጠን ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ እንዲሆኑ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።
የት/ቤቶች ስፖርት ውድድር ለሀገራዊ ስፖርት ውጤታማነት የላቀ ሚና እንዳለው ተጠቆመ።
-------------------- // -------------------
(ታህሳስ 14/2017 ዓ.ም) የ2017 የት/ቤቶች የስፖርት ውድድር ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደርጓል።
በውይይቱ ወቅት በትምህርት ሚኒስቴር የትምህርት መሰረተ ልማትና አገልግሎት ዴስክ ሃላፊ አቶ ታየ ግርማ እንደገለጹት የት/ቤቶች ስፖርታዊ ውድድርን ማጠናከር ሳይቻል ሀገራዊ የስፖርት ውጤት መጠበቅ አይቻልም።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫሙ። https://www.facebook.com/share/p/19xVnQPMZj/
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ስራ በውጤታማነት ለመፈጸም የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ ነው።
…………………………………… // ……………………………..
በትምህርት ሚኒስቴርና በሁሉም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መካከል ነገ ታህሳስ 16/2017 ዓ.ም የሚፈረመው ስምምነት ተቋማት ብቃትና ችሎታ ያላቸው ምሩቃንን በማፍራት ሂደት ውስጥ ተጠያቂነትን ከማስፈን ባለፈ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል እንደሆነ ተጠቁሟል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። https://www.facebook.com/share/p/1DBLkMNhYa/
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአገሪቱን እድገትና የህዝቡን ህይወት ለማሻሻል ቅድሚያ ሰጥተው ሊሰሩ እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አስገነዘቡ።
--------------------- // -------------------------

ትምህርት ሚኒስቴር ከአርባ ሰባት (47) የመንግስተት ዩኒቨርስቲዎች ጋር በ2017 የሚተገበር ቁልፍ የአፈጻጸመም ውል ተፈራርሟል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስምምነቱ ወቅተት እንደገለጹት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው ምርምሮችና የሚያፈሯቸው ዜጎች አገር የሚለውጡና ከዓለም ጋር ተወዳድረው ማሸነፍ የሚችሉ ሊሆኑ ይገባል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ያግኙ። https://www.facebook.com/share/p/1EsCqztYFf/
የሙያና ተግባር ትምህርት ለሚያስተምሩ የ2ኛ ደረጃ መምህራን በሀገር አቀፍ ደረጃ ስልጠና እየተሠጠ ነው።
…………………………… // …………………………

(ታህሳስ 18/2017) የትምህርት ሚኒስቴር ከክልልና ከተማ መስተዳድር ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመተባበር በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል የሙያና ተግባር ትምህርት ለሚያስተምሩ መምህራን በአስራ ዘጠኝ የስልጠና ጣቢያዎች አራት ቀናት የሚቆይ ስልጠና እየሠጠ ነው። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። https://www.facebook.com/share/p/1AKexTYj6X/
የጎልማሶችና መደበኛ ያልሆነ ትምህርትን ማጠናከር ለመደበኛ ትምህርት መሻሻል ቁልፍ ሚና እንዳለው ተገለጸ።
……………………………… // …………………………….
ሀገር አቀፍ የመሰረተ ትምህርት ቀን “የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ለጋራ መግባባትና ሰላም “በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።

በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ እንደ ሀገር የጎልማሶች ትምህርት አፈጻጸም በሚፈለገው ደረጃ አለማደጉን ጠቅሰው ይህንን ዘርፍ ማጠናከር ለመደበኛ ትምህርት መሻሻል ሚናው የጎላ እንደሆነ ጠቁመዋል። ሙሉው መረጃውን ለማግኘት ይህንን ሊንክ ይጫኑ። https://www.facebook.com/share/p/18LhCBqLMs/