መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ 5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደርስ (5 million Ethiopian Coders) የተሰኘ ስልጠና አመቻችቷል።
መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ “5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ” የተሰኘ አዲስ የስልጠና እድል አመቻችቷል። ይህ ኢኒሼቲቭ ከአይሲቲ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኮርሶች ጥራቱና በጥልቅ ይዘቶች በሚታወቀው በኦዳሲቲ ፕላትፎርም (Udacity Platform) የፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ሌሎችም ከአይሲቲ ጋር የተገናኙ ኮርሶችን ከክፍያ ነፃ ማግኘት የሚያስችል ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን ያለምንም ወጪ በእነዚህ ኮርሶች በመመዝገብ ይህንን ልዩ የስልጠና እድል መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍና ችሎታቸውን በማጎልበት በአለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ተወዳዳሪ መሆን ይችላሉ።
በዚህ ስልጠና ተመዝግበውና የትምህርት ይዘቶቹን ተምረው ያጠናቀቁ ተሳታፊዎች በአለም አቀፍ ድርጅቶች እውቅና ያለው እና የስራ እድልን በእጅጉ ሊያሳድግ ከሚችለው Udacity የምስክር ወረቀት ያገኛሉ።
ትምህርት ሚኒስቴር በስልጠናው እንዴት መመዝገብና መሳተፍ እንደሚቻል የሚያሳዩ መመሪያዎችን በጽሁፍና በቪዲዮ አዘጋጅቷል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎችና መምህራን ይሄንን በበዙ ክፍያ ይሰጥ የነበረን ስልጠና መመሪያውን ተከትሎ ብቻ በመመዝገብ በነጻ መሰልጠን ትችላላችሁ።
የመመሪያውን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/-zSmhhD5qE4 ላይ በመግባት መመልከት የምትችሉ ሲሆን በምስል የተደገፈውን መመሪያም ከዚህ ፖስት ጋር አጋርተናል።
ይሄንን ጠቃሚና ነጻ የስልጠና እድል ፍላጎቱ ላላቸውና የትምህርት ዝግጅታቸው ከዚህ ስልጠና ጋር ለሚገናኝ ጓደኞቻችሁ፣ ወዳጅ ፣ ቤተሰባችሁ እንዲሁም ተማሪዎችና መምህራን በማጋራት ተጨቃሚ እንዲሆኑ አድርጉ።
መንግስት በአጋር አካላት ድጋፍ “5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደርስ” የተሰኘ አዲስ የስልጠና እድል አመቻችቷል። ይህ ኢኒሼቲቭ ከአይሲቲ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ኮርሶች ጥራቱና በጥልቅ ይዘቶች በሚታወቀው በኦዳሲቲ ፕላትፎርም (Udacity Platform) የፕሮግራሚንግ፣ ዳታ ሳይንስ፣ አርተፊሻል ኢንተለጀንስና ሌሎችም ከአይሲቲ ጋር የተገናኙ ኮርሶችን ከክፍያ ነፃ ማግኘት የሚያስችል ነው።
ተማሪዎች እና መምህራን ያለምንም ወጪ በእነዚህ ኮርሶች በመመዝገብ ይህንን ልዩ የስልጠና እድል መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህ ፕሮግራም ውስጥ በመሳተፍና ችሎታቸውን በማጎልበት በአለም አቀፍ ገበያ ከፍተኛ ተወዳዳሪ መሆን ይችላሉ።
በዚህ ስልጠና ተመዝግበውና የትምህርት ይዘቶቹን ተምረው ያጠናቀቁ ተሳታፊዎች በአለም አቀፍ ድርጅቶች እውቅና ያለው እና የስራ እድልን በእጅጉ ሊያሳድግ ከሚችለው Udacity የምስክር ወረቀት ያገኛሉ።
ትምህርት ሚኒስቴር በስልጠናው እንዴት መመዝገብና መሳተፍ እንደሚቻል የሚያሳዩ መመሪያዎችን በጽሁፍና በቪዲዮ አዘጋጅቷል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎችና መምህራን ይሄንን በበዙ ክፍያ ይሰጥ የነበረን ስልጠና መመሪያውን ተከትሎ ብቻ በመመዝገብ በነጻ መሰልጠን ትችላላችሁ።
የመመሪያውን የቪዲዮ ሊንክ https://youtu.be/-zSmhhD5qE4 ላይ በመግባት መመልከት የምትችሉ ሲሆን በምስል የተደገፈውን መመሪያም ከዚህ ፖስት ጋር አጋርተናል።
ይሄንን ጠቃሚና ነጻ የስልጠና እድል ፍላጎቱ ላላቸውና የትምህርት ዝግጅታቸው ከዚህ ስልጠና ጋር ለሚገናኝ ጓደኞቻችሁ፣ ወዳጅ ፣ ቤተሰባችሁ እንዲሁም ተማሪዎችና መምህራን በማጋራት ተጨቃሚ እንዲሆኑ አድርጉ።
YouTube
5 million Ethiopian coders Initiative - Step By Step Guide to Register on Udacity
ማስታወቂያ
የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ የሚካሄደው ከሐምሌ 24 - ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት በ https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ የሚካሄደው ከሐምሌ 24 - ነሐሴ 05/2016 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ የመመዝገቢያው ቅጽ ላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች በሟሟላት በ https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ngat.ethernet.edu.et
Ministry of Education
Ministry of Education | National GAT
ስርዓተ ትምህርቱ የአገሪቱን ተጨባጭ ሁኔታና ቀጣይ ጊዜያትን መሠረት ያደረገ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስታወቁ።
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አድርገዋል
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ሥርዓተ ትምህርቱ የአገሪቱን የአሁንና የመጪውን ጊዜ ፍላጎት ዝንዲሁም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማዕከል የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።
የአንድ አገር ስርዓተ ትምህርት የአገርን የረጅም ጊዜ ጥቅም ማስጠበቅ የሚችሉ ዜጎች ማፍራት መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ሲቪል ሰርቫንቱም ከማንኛውም የፓለቲካ ፓርቲ ተጽእኖ ነጻ ሆኖ በችሎታውና በብቃቱ ብቻ ህዝብና አገረ መንግስትን ማገልገል እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ሠራተኞችም የአገርና የህዝብን ጥቅም በማስጠበቅ ለተጀመሩ የለውጥና ዓበይት ስራዎች ውጤታማነት ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በውይይቱ ወቅት የአጠቃላይ ትምህርት፣ የከፍተኛ ትምህርት፣ የኢትዮጵያ ትምህርት ባለስልጣንና የአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዕቅድ ከፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና የየተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች በዓመታዊ ዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አድርገዋል
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በውይይቱ ወቅት እንደገለጹት ሥርዓተ ትምህርቱ የአገሪቱን የአሁንና የመጪውን ጊዜ ፍላጎት ዝንዲሁም ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን ማዕከል የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል።
የአንድ አገር ስርዓተ ትምህርት የአገርን የረጅም ጊዜ ጥቅም ማስጠበቅ የሚችሉ ዜጎች ማፍራት መሆኑንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ሲቪል ሰርቫንቱም ከማንኛውም የፓለቲካ ፓርቲ ተጽእኖ ነጻ ሆኖ በችሎታውና በብቃቱ ብቻ ህዝብና አገረ መንግስትን ማገልገል እንደሚጠበቅበትም አስገንዝበዋል።
የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ሠራተኞችም የአገርና የህዝብን ጥቅም በማስጠበቅ ለተጀመሩ የለውጥና ዓበይት ስራዎች ውጤታማነት ሃላፊነታቸውን እንደሚወጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በውይይቱ ወቅት የአጠቃላይ ትምህርት፣ የከፍተኛ ትምህርት፣ የኢትዮጵያ ትምህርት ባለስልጣንና የአገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዕቅድ ከፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
በውይይቱ ላይ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱና የየተቋማቱ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል።
የከፍተኛ ትምህርት፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ የምርምር ተቋማትና የኢንዱስትሪ ትስስር አዋጅን ለማስጀመርና የማስፈጸሚያ የህግ ማዕቀፎችን ለማጽደቅ የሚያግዝ መርሃ-ግብር ተካሄዷል። ዝርዝር መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይቻላል። https://www.facebook.com/share/7rkmK3ZiaLhY5Lxz/?mibextid=oFDknk
በአገር አቀፍ ደረጃ ለ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረው የዘንድሮው የክረምት የኮምፒውተር ፕሮግራሚንግና አልጎሪዚም ሥልጠና መርሃ-ግብር ተጠናቀቀ
====================
በስልጠናው ማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ ቁልፍ መልዕከት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል ዕወቀት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት አለሙ ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በርካታ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ኮምፒውተር ችሎታ ያላቸው ዜጎችን ማፍራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው መርሃ-ግብሩ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በቅርቡ ካስተዋወቁት የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢንሼቲቭ ፕሮግራም ጋር የሚጣጣም መሆኑን አንስተዋል፡፡
ወ/ሮ ሰላማዊት አክለውም በቀጣይ ጊዜያት የሥልጠናውን ቀጣይነት ከማረጋገጥ በተጨማሪ ተደራሸነቱና ጥራቱም እንዲጨምር ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ ኮደር ጋር በትብብር የሚሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአዲስ ኮደር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ፕሮፌሠር ጂላኒ ኒልሰን በበኩላቸው ሥልጠናው በመስኩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸውን ከ9-11ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎቸን በመመልመል እውቀታቸውንና ከህሎታቸውን በማሳደግ በቀጣይ ሀገራቸውን የሚጠቅሙ ብቁ ዜጎችን ማፍራት አላማ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በመስኩ ልምድ ያላቸው 26 የአገር ውስጥና የውጪ ሀገራት በጎ ፍቃደኛ አሰልጣኞች እና 99 ተማሪዎች የስልጠናው ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ለ7ኛ ጊዜ የተሰጠውን ስልጠና የትምህርት ሚኒስቴር አዲሰ ኮደር ከተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑ ታውቋል፡፡
====================
በስልጠናው ማጠናቀቂያ መርሃ ግብር ላይ ቁልፍ መልዕከት ያስተላለፉት የትምህርት ሚኒስቴር የማህበረሰብ ጉድኝትና ሀገር በቀል ዕወቀት ዴስክ ኃላፊ ወ/ሮ ሰላማዊት አለሙ ዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ በርካታ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂና ኮምፒውተር ችሎታ ያላቸው ዜጎችን ማፍራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰው መርሃ-ግብሩ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በቅርቡ ካስተዋወቁት የ5 ሚሊዮን ኮደርስ ኢንሼቲቭ ፕሮግራም ጋር የሚጣጣም መሆኑን አንስተዋል፡፡
ወ/ሮ ሰላማዊት አክለውም በቀጣይ ጊዜያት የሥልጠናውን ቀጣይነት ከማረጋገጥ በተጨማሪ ተደራሸነቱና ጥራቱም እንዲጨምር ትምህርት ሚኒስቴር ከአዲስ ኮደር ጋር በትብብር የሚሠራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የአዲስ ኮደር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ፕሮፌሠር ጂላኒ ኒልሰን በበኩላቸው ሥልጠናው በመስኩ ተሰጥኦ እና ፍላጎት ያላቸውን ከ9-11ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎቸን በመመልመል እውቀታቸውንና ከህሎታቸውን በማሳደግ በቀጣይ ሀገራቸውን የሚጠቅሙ ብቁ ዜጎችን ማፍራት አላማ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በመስኩ ልምድ ያላቸው 26 የአገር ውስጥና የውጪ ሀገራት በጎ ፍቃደኛ አሰልጣኞች እና 99 ተማሪዎች የስልጠናው ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ለ7ኛ ጊዜ የተሰጠውን ስልጠና የትምህርት ሚኒስቴር አዲሰ ኮደር ከተሰኘ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው መሆኑ ታውቋል፡፡
ማ ስ ታ ወ ቂ ያ
የምዝገባ ጊዜን መራዘሙን ስለማሳወቅ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ እስከ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም መራዘሙን እያሳወቅን እስከ ተጠቀሰው ጊዜ ድረስ በ https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴ
የምዝገባ ጊዜን መራዘሙን ስለማሳወቅ
ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ላላቸው አመልካቾች የሚሰጠው የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ እስከ ነሐሴ 10/2016 ዓ.ም መራዘሙን እያሳወቅን እስከ ተጠቀሰው ጊዜ ድረስ በ https://NGAT.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴ
ngat.ethernet.edu.et
Ministry of Education
Ministry of Education | National GAT
የመምህራንን ክብርና አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ እንደሆነ ተገለጸ
--------------------------------------
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሀሮምያ ዩኒቨርስቲ በክረምት መርሃ-ግብር የሚሰለጥኑ መምህራንን ጎብኝተዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ወቅት ከሰልጣኞች ጋር ባደረጉት ውይይት መምህርነት ሙያ የተከበረ እና የአንድ ሀገር የእድገት መሰረት በመሆኑ ይህን ታለቅ ሙያ ወደነበረበት ክብር ለመመለስና የመምህራንን አቅም መገንባት ፤ኑሮውን ማሻሻል የግድ በመሆኑ መንግስት ከፍተኛ ትከረት ሰጥቶ አየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ከደመወዝ ጭማሪ ጀምሮ የመምህራን ባንክ እስከመክፈት የሚደርሱ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በመምህራኑ የሚከፈተው ባንክ ሙያውንና ኑሮአቸውን ለመቀየር ትልቅ ሚና እንደሚኖረውም ጨምረው ተናግረዋል።
ሰልጣኝ መምህራንም በበኩላቸው በክቡር ሚኒስትሩ መጎብኘታቸው ደስ እንዳሰኛቸው ገልጸው ስልጠናውም ለሙያቸው ትልቅ አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል። መምህራኑ ጨምረውም በስልጠናው አዳዲስ እውቀቶችን እንደቀሰሙና ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንዴት ማስተማር እንሚቻል ጭምር አውቀት ያጉኙበትና ከዘመኑ ጋር የሚሄድ መምህር ለመሆን እንዳነሳሳቸው ገልጸዋል፡
--------------------------------------
የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሀሮምያ ዩኒቨርስቲ በክረምት መርሃ-ግብር የሚሰለጥኑ መምህራንን ጎብኝተዋል።
ክቡር ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ወቅት ከሰልጣኞች ጋር ባደረጉት ውይይት መምህርነት ሙያ የተከበረ እና የአንድ ሀገር የእድገት መሰረት በመሆኑ ይህን ታለቅ ሙያ ወደነበረበት ክብር ለመመለስና የመምህራንን አቅም መገንባት ፤ኑሮውን ማሻሻል የግድ በመሆኑ መንግስት ከፍተኛ ትከረት ሰጥቶ አየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንንም ተግባራዊ ለማድረግ የአጭርና የረጅም ጊዜ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ከደመወዝ ጭማሪ ጀምሮ የመምህራን ባንክ እስከመክፈት የሚደርሱ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል። በመምህራኑ የሚከፈተው ባንክ ሙያውንና ኑሮአቸውን ለመቀየር ትልቅ ሚና እንደሚኖረውም ጨምረው ተናግረዋል።
ሰልጣኝ መምህራንም በበኩላቸው በክቡር ሚኒስትሩ መጎብኘታቸው ደስ እንዳሰኛቸው ገልጸው ስልጠናውም ለሙያቸው ትልቅ አቅም እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል። መምህራኑ ጨምረውም በስልጠናው አዳዲስ እውቀቶችን እንደቀሰሙና ቴክኖሎጂን በመጠቀም እንዴት ማስተማር እንሚቻል ጭምር አውቀት ያጉኙበትና ከዘመኑ ጋር የሚሄድ መምህር ለመሆን እንዳነሳሳቸው ገልጸዋል፡
የትምህርት ሚኒስቴርና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አኖሩ
----------------------------------------
በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጠዋል።
በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ ወረዳ ዋሬርሶ ማሌማ ቀበሌ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አሻራቸውን ያኖሩት የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አረንጓዴ አሻራችንን በማኖር አርአያነታችንንና ቁርጠኝነታችንን ለትውልድ በተግባር ማሳየት ይገባናል ብለዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በጉጉት ስንጠብቀው ለነበረው ለዚህ ቀን ደርሰው አረንጓዴ አሻራቸውን በማስቀመጣቸው ደስ ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሀገራችን ለዓለም አስተዋጽኦ ያደረገችበት መርሃ-ግብር መሆኑን ተናግረዋል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ችግኞቹን የተከሉት በተራቆተ ቦታ በመሆኑ ከአቻ መስሪያ ቤቶች ጋር በመተባበርም የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ እና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የግድ መሆኑን ተናግረዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች አገር ለትውልድ ለማውረስ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ኃላፊነታችንን ልንወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ አካባቢ በተካሄደው አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሀ ግብር የትምህርት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
----------------------------------------
በአንድ ጀምበር 600 ሚሊዮን ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች አረንጓዴ አሻራቸውን አስቀምጠዋል።
በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ ወረዳ ዋሬርሶ ማሌማ ቀበሌ በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አሻራቸውን ያኖሩት የትምህርት ሚኒስትሩ ክቡር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አረንጓዴ አሻራችንን በማኖር አርአያነታችንንና ቁርጠኝነታችንን ለትውልድ በተግባር ማሳየት ይገባናል ብለዋል፡፡
በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒሰትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ አየለች እሸቴ በበኩላቸው በጉጉት ስንጠብቀው ለነበረው ለዚህ ቀን ደርሰው አረንጓዴ አሻራቸውን በማስቀመጣቸው ደስ ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሀገራችን ለዓለም አስተዋጽኦ ያደረገችበት መርሃ-ግብር መሆኑን ተናግረዋል።
የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና የተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ችግኞቹን የተከሉት በተራቆተ ቦታ በመሆኑ ከአቻ መስሪያ ቤቶች ጋር በመተባበርም የመንከባከብ ስራ እንደሚሰራ እና ለቀጣዩ ትውልድ ማስተላለፍ የግድ መሆኑን ተናግረዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሹኔ በበኩላቸው በሁለንተናዊ መልኩ የበለጸገች አገር ለትውልድ ለማውረስ ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ ኃላፊነታችንን ልንወጣ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል በሱሉልታ አካባቢ በተካሄደው አረንጓዴ አሻራ የማኖር መርሀ ግብር የትምህርት ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
ማስታወቂያ
የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እና የፈተና ቀንን ስለማሳወቅ
በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸሁ እና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑንን እየገለጽን በየተመደባችሁበት የፈተና ማዕከላት እና የመፈተኛ ፕሮግራም መሰረት ከ ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናው የሚሰጥ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ
በፈተና ወቅት የተሰጣችሁን User Name and Password፣ እና ማንነታችሁን የሚገልጽ መታዋቂያ ይዛችሁ መቅረብ ይጠበቃባችኋል።
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር
የድህረምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እና የፈተና ቀንን ስለማሳወቅ
በ2017 የትምህርት ዘመን የድህረምረቃ ፕሮግራሞች ለመማር ፍላጎት ያላቸሁ እና በተለያዩ ምክንያቶች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ ያመለጣችሁ አመልካቾች እስከ ነሐሴ 26/2016 ዓ.ም ድረሰ በ https://ngat.ethernet.edu.et በኩል መመዝገብ የምትችሉ መሆኑንን እየገለጽን በየተመደባችሁበት የፈተና ማዕከላት እና የመፈተኛ ፕሮግራም መሰረት ከ ነሐሴ 30 እስከ ጳጉሜን 1/2016 ዓ.ም ድረስ ፈተናው የሚሰጥ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ
በፈተና ወቅት የተሰጣችሁን User Name and Password፣ እና ማንነታችሁን የሚገልጽ መታዋቂያ ይዛችሁ መቅረብ ይጠበቃባችኋል።
የኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር
ngat.ethernet.edu.et
Ministry of Education
Ministry of Education | National GAT
የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በትምህርት ተቋማት ስፖርት ልማት ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡
======================
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የመግባቢያ ስምምነቱን በተፈራረሙበት ወቅት ስፖርት አእምሮአዊና አካላዊ ብቃት የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ብቃት ያላቸው ዜጎችን የማፍራት ተግባር የትምህርት ዘርፉ ሪፎርም አካል አድርጎ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በዚህም መሠረት በቀጣዩ የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድርን ለማካሄድ እና መርሃ ግብሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው በሁሉም ዘርፍ አሸናፊ አገር ለመፍጠር ብቁና ንቁ ዜጎች ማፍራት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው በማህበረሰብ አቀፍ እና በባህላዊ ስፖርቶች ላይ የትምህርት ማህበረሰቡን በማሳተፍ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ ተቋማት በዕለቱ የተፈረረሙት የመግባቢያ ሰነድ መሰረት በቀጣይ በየደረጃው ባሉ ቴክኒካል ባለሙያዎች በየጊዜው እየታቀደ እና እየዳበረ ለተሻለ ስኬት እንደሚውል ጠቁመዋል፡፡
የትብብር ስምምንቱ ዓላማ በሁለቱ ተቋማት መካከል ወጥ እና ተከታታይነት ያለው ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠር የትምህርት ቤት ስፖርት ልማትን በማስፋፋት የስፖርት ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
ሰፖርታዊ ልማትን ባህል ያደረገ በመማር ውጤቱ የተሻለ የሆነ ንቁና ሁለንተናዊ ሰብዕናው የተሟላ ተተኪ ትውልድ ለማፍራት ምቹ ሁኔታን መፍጠር የስምምነት ሰነዱ ሌለው ዓላማ መሆኑን ተመላክቷል፡፡
===////====
======================
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የመግባቢያ ስምምነቱን በተፈራረሙበት ወቅት ስፖርት አእምሮአዊና አካላዊ ብቃት የተላበሱ ዜጎችን ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በመሆኑም የትምህርት ሚኒስቴር ብቃት ያላቸው ዜጎችን የማፍራት ተግባር የትምህርት ዘርፉ ሪፎርም አካል አድርጎ እየሰራ መሆኑን አመልክተዋል፡፡ በዚህም መሠረት በቀጣዩ የትምህርት ዘመን የትምህርት ቤቶች ስፖርት ውድድርን ለማካሄድ እና መርሃ ግብሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የባህልና ስፖርት ሚኒስትሯ ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በበኩላቸው በሁሉም ዘርፍ አሸናፊ አገር ለመፍጠር ብቁና ንቁ ዜጎች ማፍራት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው በማህበረሰብ አቀፍ እና በባህላዊ ስፖርቶች ላይ የትምህርት ማህበረሰቡን በማሳተፍ በጋራ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ሁለቱ ተቋማት በዕለቱ የተፈረረሙት የመግባቢያ ሰነድ መሰረት በቀጣይ በየደረጃው ባሉ ቴክኒካል ባለሙያዎች በየጊዜው እየታቀደ እና እየዳበረ ለተሻለ ስኬት እንደሚውል ጠቁመዋል፡፡
የትብብር ስምምንቱ ዓላማ በሁለቱ ተቋማት መካከል ወጥ እና ተከታታይነት ያለው ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠር የትምህርት ቤት ስፖርት ልማትን በማስፋፋት የስፖርት ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል መሆኑ ተጠቅሷል፡፡
ሰፖርታዊ ልማትን ባህል ያደረገ በመማር ውጤቱ የተሻለ የሆነ ንቁና ሁለንተናዊ ሰብዕናው የተሟላ ተተኪ ትውልድ ለማፍራት ምቹ ሁኔታን መፍጠር የስምምነት ሰነዱ ሌለው ዓላማ መሆኑን ተመላክቷል፡፡
===////====