ETHIO-MEREJA®
Photo
በትግራይ ክልል እንዳትመሰክርብኝ በማለት የ14 ዓመት ታዳጊ በመድፈር በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሉ ሁለት ግለሰቦች በእድሜ ልክ እስራት ተቀጡ
ያይንሸት ገብረዋህድ አመሃ የተባው ግለሰብ ነዋሪነቱ በፅምብላ ወረዳ ሲሆን መስከረም 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከለሊቱ አምስት ሰዓት ላይ እንዳባጉና ከተማ ላይ ግሮሰሪ ከፍታ ራሷን የምታስተዳድርና የልጁ እናት የሆነቺውን ንግስቲ ገብረየውሃንስ የተባለች ሴት "አብረን እንደር ብየሽ እምቢ አልሺኝ" በሚል ቂም በመያዝና በቅናት በመነሳሳት ወደ መኖርያ ቤቷ በመግባት አልጋ ስር ተደብቆ በመቆየት የግል ተበዳይዋ በምትተኛበት ሰዓት ጭንቅላትዋ ላይ ሁለቴ በመምታት የግድያ ሙከራ መፈፀሙ የሰሜን ምእራብ ትግራይ ዞን አቃቢ ህግ አስታውቋል።
በዚህ ሳብያም ግለሰቡ በግድያ ሙከራ ወንጀል ተከሶ ጉዳዩ በፍርድ ሂደቴ ላይ ሳለ በዋስ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። ይሄኔ ታድያ የግል ተበዳይ ልጅ የሆነችን የ14 ዓመት ታዳጊ ሄዋን ጎይትኦም በቀረበበት ክስ ላይ ምስክር ሆና መገለፆ በመገንዘብ እንዳትመሰክርብኝ በማለት በአሰቃቂ ሁኔታ ለመግደል አቅዶ ይንቀሳቀሳል።
በዚህም ታዳጊዋ አያቷ ጋር እንዳለች በማረጋገጥ ፈልጌሽ ነው ነይ በማለት ከአያቷ ቤት ይዟት በመውጣት ዓዲ ሰዱ እየተባለ ወደሚታወቅ ገደላማ ስፍራ ይዟት ይሄዳል። በመቀጠልም በአንገቷ በማነቅ መሬት ላይ የጣላት ሲሆን በሰአቱ አብሮት ከነበረ ተባባሪው መዓሾ ሰለሙን ደስታ የተባለ ግለሰብ ጋር በመሆን በታዳጊዋ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ ግን በዛ ያበቃ አልነበረም። የፈፀሙት ወንጀል እንዳይጋለጥ በሚል መረጃ ለማጥፋት በተደረገ ጥረት የታዳጊዋን ሁለት አይኖች በቢላ በማውጣት ተሸክመው ወደ ገደል በመወርወር ህይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል።
በዚህም መሰረት ቸዞኑ አቃቢ ህግ የፌ/ዲ/ሪ/ኢ የወንጀል ህግ አንቀፅ 539(1)(ሐ) በመጥቀስ በሁለቱም ግለሰቦች ላይ ግፍ የተሞላበት ወንጀል በመፈፀም ክስ የመሰረተ ሲሆን በዚህም መሰረት የቀረበለትን የክስ መዝገብ ሲመለከት የቆየው የዞኑ ፍርድ ቤት ሁለቱም ግለሰቦች በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ብይን መስጠቱን ብስራት ሬድዮ ከትግራይ ክልል ሰሜን ምእራብ ዞን አቃቢ ህግ ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
ያይንሸት ገብረዋህድ አመሃ የተባው ግለሰብ ነዋሪነቱ በፅምብላ ወረዳ ሲሆን መስከረም 25 ቀን 2016 ዓ/ም ከለሊቱ አምስት ሰዓት ላይ እንዳባጉና ከተማ ላይ ግሮሰሪ ከፍታ ራሷን የምታስተዳድርና የልጁ እናት የሆነቺውን ንግስቲ ገብረየውሃንስ የተባለች ሴት "አብረን እንደር ብየሽ እምቢ አልሺኝ" በሚል ቂም በመያዝና በቅናት በመነሳሳት ወደ መኖርያ ቤቷ በመግባት አልጋ ስር ተደብቆ በመቆየት የግል ተበዳይዋ በምትተኛበት ሰዓት ጭንቅላትዋ ላይ ሁለቴ በመምታት የግድያ ሙከራ መፈፀሙ የሰሜን ምእራብ ትግራይ ዞን አቃቢ ህግ አስታውቋል።
በዚህ ሳብያም ግለሰቡ በግድያ ሙከራ ወንጀል ተከሶ ጉዳዩ በፍርድ ሂደቴ ላይ ሳለ በዋስ እንዲወጣ ይፈቀድለታል። ይሄኔ ታድያ የግል ተበዳይ ልጅ የሆነችን የ14 ዓመት ታዳጊ ሄዋን ጎይትኦም በቀረበበት ክስ ላይ ምስክር ሆና መገለፆ በመገንዘብ እንዳትመሰክርብኝ በማለት በአሰቃቂ ሁኔታ ለመግደል አቅዶ ይንቀሳቀሳል።
በዚህም ታዳጊዋ አያቷ ጋር እንዳለች በማረጋገጥ ፈልጌሽ ነው ነይ በማለት ከአያቷ ቤት ይዟት በመውጣት ዓዲ ሰዱ እየተባለ ወደሚታወቅ ገደላማ ስፍራ ይዟት ይሄዳል። በመቀጠልም በአንገቷ በማነቅ መሬት ላይ የጣላት ሲሆን በሰአቱ አብሮት ከነበረ ተባባሪው መዓሾ ሰለሙን ደስታ የተባለ ግለሰብ ጋር በመሆን በታዳጊዋ ላይ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመ ሲሆን የወንጀል ድርጊቱ ግን በዛ ያበቃ አልነበረም። የፈፀሙት ወንጀል እንዳይጋለጥ በሚል መረጃ ለማጥፋት በተደረገ ጥረት የታዳጊዋን ሁለት አይኖች በቢላ በማውጣት ተሸክመው ወደ ገደል በመወርወር ህይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል።
በዚህም መሰረት ቸዞኑ አቃቢ ህግ የፌ/ዲ/ሪ/ኢ የወንጀል ህግ አንቀፅ 539(1)(ሐ) በመጥቀስ በሁለቱም ግለሰቦች ላይ ግፍ የተሞላበት ወንጀል በመፈፀም ክስ የመሰረተ ሲሆን በዚህም መሰረት የቀረበለትን የክስ መዝገብ ሲመለከት የቆየው የዞኑ ፍርድ ቤት ሁለቱም ግለሰቦች በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ብይን መስጠቱን ብስራት ሬድዮ ከትግራይ ክልል ሰሜን ምእራብ ዞን አቃቢ ህግ ፅህፈት ቤት ያገኘው መረጃ ያሳያል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
👍75❤14😭9😱4👏3🤔2
ማንቼስተር ዩናይትድ 17ኛ ሽንፈቱን አስተናገደ
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ በ2024/25 የውድድር ዘመን 17ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል፡፡
በኦልድትራፎርድ ዌስትሃም ዩናይትድን ያስተናገደው ዩናይትድ ጃሮድ ቦውን እና ቶማስ ሱቼክ ባስቆጠሯቸው ግቦች 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡
በሌሎች የሊጉ 36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታዎች ክሪስታል ፓላስ ቶተንሃምን 2 ለ 0 ሲያሸነፍ ኖቲንግሃም ፎረስት ከሌስተር ሲቲ 2 አቻ ተለያተዋል፡፡
በሌሎች ጨዋታዎች ኒውካስትል ዩናይትድ ቼልሲን 2 ለ 0 ሲረታ፤ ቶተነሃም በሜዳው በክሪስታል ፓላስ 2 ለ 0 ተሸንፏል፡፡ ኖቲንግሃም ፎረስት እና ሌስተር ሲቲ ያደረጉት ጨዋታ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ዩናይትድ በ2024/25 የውድድር ዘመን 17ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል፡፡
በኦልድትራፎርድ ዌስትሃም ዩናይትድን ያስተናገደው ዩናይትድ ጃሮድ ቦውን እና ቶማስ ሱቼክ ባስቆጠሯቸው ግቦች 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡
በሌሎች የሊጉ 36ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታዎች ክሪስታል ፓላስ ቶተንሃምን 2 ለ 0 ሲያሸነፍ ኖቲንግሃም ፎረስት ከሌስተር ሲቲ 2 አቻ ተለያተዋል፡፡
በሌሎች ጨዋታዎች ኒውካስትል ዩናይትድ ቼልሲን 2 ለ 0 ሲረታ፤ ቶተነሃም በሜዳው በክሪስታል ፓላስ 2 ለ 0 ተሸንፏል፡፡ ኖቲንግሃም ፎረስት እና ሌስተር ሲቲ ያደረጉት ጨዋታ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቅቋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
👍61😁23❤3👎3😱3👏2
በወላይታ ዞን ሰርጉን አቋርጦ ቀዶ ህክምና የሰራው ሐኪም አድናቆት እየተቸረው ይገኛል
ዶ/ር ብሩክ ወይሻ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በወላይታ ዞን፣ በበሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ነው።
ወጣቱ ሐኪም ታዲያ የራሱን የሰርግ ዝግጅት አቋርጦ ወጥቶ ታካሚን ቀዶ ጥገና በማድረግ ሕይወት የማዳኑ ጉዳይ የአካባቢው ነዋሪዎች መነጋገሪያ ሆኗል።
የሰርጉ ዝግጅት ከነበረበት ከ40 በላይ ኪሎ ሜትር በላይ ወደ ሆስፒታሉ ተጉዞ ቀዶ ጥገና በማድረግ የሰው ሕይወት ማዳን መቻሉን ዶ/ር ብሩክ ለኢቢሲ ተናግሯል።
ወጣቱ ሐኪም የተሟላ የቀዶ ጥገና ሕክምና ገና በቅርቡ በጀመረው ሆስፒታል የመጀመሪያው ስፔሻሊስት ቅጥር ሲሆን፤ በሆስፒታሉ ሥራ ከጀመረም ገና ሶስት ሳምንቱ ነው።
በቀዶ ጥገና የታከመው በሽታ ከጨጓራ ሕመም ጋር ተያይዞ የሚከሰትና ሕይወትን አደጋ ላይ የሚጥል ሲሆን፤ ታካሚው በሰዓቱ ሕክምና ባይደረግለት ኖሮ ሕይወቱ ሊያልፍ ይችል እንደነበርም ነው የተገለፀው።
ቀዶ ጥገና የሕክምና ባለሙያዎች የቡድን ሥራ ነው ያለው ዶ/ር ብሩክ፤ በአጠቃላይ በቀዶ ጥገናው ለተሳተፈው የሕክምና ቡድን ምስጋና አቅርቧል ።
የቀዶ ጥገና ሕክምናው የተደረገለት የ40 ዓመት ታካሚ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለፀው ዶ/ር ብሩክ፤ ከዚህ የሚበልጥ ደስታ የለም ብሏል።
በሙያዬ የፈፀምኩትን ቃለ-መሃላ እና የገባሁትን ቃል-ኪዳን መቼም ቢሆን አላጥፍም፤ ለሙያው የሚገባውን ክብር እሰጣለሁ ብሏል ወጣቱ ሐኪም ብሩክ ወይሻ።(Via ETV)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
ዶ/ር ብሩክ ወይሻ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ በወላይታ ዞን፣ በበሌ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ነው።
ወጣቱ ሐኪም ታዲያ የራሱን የሰርግ ዝግጅት አቋርጦ ወጥቶ ታካሚን ቀዶ ጥገና በማድረግ ሕይወት የማዳኑ ጉዳይ የአካባቢው ነዋሪዎች መነጋገሪያ ሆኗል።
የሰርጉ ዝግጅት ከነበረበት ከ40 በላይ ኪሎ ሜትር በላይ ወደ ሆስፒታሉ ተጉዞ ቀዶ ጥገና በማድረግ የሰው ሕይወት ማዳን መቻሉን ዶ/ር ብሩክ ለኢቢሲ ተናግሯል።
ወጣቱ ሐኪም የተሟላ የቀዶ ጥገና ሕክምና ገና በቅርቡ በጀመረው ሆስፒታል የመጀመሪያው ስፔሻሊስት ቅጥር ሲሆን፤ በሆስፒታሉ ሥራ ከጀመረም ገና ሶስት ሳምንቱ ነው።
በቀዶ ጥገና የታከመው በሽታ ከጨጓራ ሕመም ጋር ተያይዞ የሚከሰትና ሕይወትን አደጋ ላይ የሚጥል ሲሆን፤ ታካሚው በሰዓቱ ሕክምና ባይደረግለት ኖሮ ሕይወቱ ሊያልፍ ይችል እንደነበርም ነው የተገለፀው።
ቀዶ ጥገና የሕክምና ባለሙያዎች የቡድን ሥራ ነው ያለው ዶ/ር ብሩክ፤ በአጠቃላይ በቀዶ ጥገናው ለተሳተፈው የሕክምና ቡድን ምስጋና አቅርቧል ።
የቀዶ ጥገና ሕክምናው የተደረገለት የ40 ዓመት ታካሚ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለፀው ዶ/ር ብሩክ፤ ከዚህ የሚበልጥ ደስታ የለም ብሏል።
በሙያዬ የፈፀምኩትን ቃለ-መሃላ እና የገባሁትን ቃል-ኪዳን መቼም ቢሆን አላጥፍም፤ ለሙያው የሚገባውን ክብር እሰጣለሁ ብሏል ወጣቱ ሐኪም ብሩክ ወይሻ።(Via ETV)
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
👍302👏34❤29🙏27🥰10🤔5
ጤና ባለሙያዎች!!
የደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄ በማንሳት ለመንግሥት የሰላሳ ቀናት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥተው የነበሩት የጤና ባለሙያዎች ምላሽ ባለማግኘታቸው ከፊል የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።
ባለሙያዎች ከጥቂት "የተመረጡ የሕክምና ክፍሎች" ውጪ ያሉ ክፍሎች ከዛሬ ግንቦት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ሥራ ማቆማቸውን ገልፀዋል።
ቢቢሲ ያነጋገራቸው አምስት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ባለሙያዎች ከድንገተኛ፣ ከማዋለጃ፣ ከፅኑ ሕሙማን እንዲሁም ከድንገተኛ ቀዶ ሕክምና ክፍሎች ውጪ ያሉ የሕክምና ተቋማት ክፍሎች አገልግሎቶች ማቋረጣቸውን ተናግረዋል።
በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በመላ ሀገሪቱ የተጀመረውን የከፊል የስራ ማቆም አድማ ለማካሄድ ሲሞክሩ ከመንግሥት አካላት ማስፈራሪያና ጫና እንደደረሰባቸውም አስታውቀዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በዛሬው ዕለት ተጠርቷል የተባለውን የህክምና ባለሙያዎች አድማ በዋና ዋና የመንግስት ሆስፒታሎች ማለትም በዳግማዊ #ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል፣ #በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል እና #በየካቲት12 ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል ጠዋት ላይ የከፊል የስራ ማቆም መካሄዱን ለመታዘብ ተችሏል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
የደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄ በማንሳት ለመንግሥት የሰላሳ ቀናት የቅድሚያ ማስጠንቀቂያ ጊዜ ሰጥተው የነበሩት የጤና ባለሙያዎች ምላሽ ባለማግኘታቸው ከፊል የሥራ ማቆም አድማ መምታታቸውን ለቢቢሲ ተናገሩ።
ባለሙያዎች ከጥቂት "የተመረጡ የሕክምና ክፍሎች" ውጪ ያሉ ክፍሎች ከዛሬ ግንቦት 5/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ሥራ ማቆማቸውን ገልፀዋል።
ቢቢሲ ያነጋገራቸው አምስት በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገኙ ባለሙያዎች ከድንገተኛ፣ ከማዋለጃ፣ ከፅኑ ሕሙማን እንዲሁም ከድንገተኛ ቀዶ ሕክምና ክፍሎች ውጪ ያሉ የሕክምና ተቋማት ክፍሎች አገልግሎቶች ማቋረጣቸውን ተናግረዋል።
በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በመላ ሀገሪቱ የተጀመረውን የከፊል የስራ ማቆም አድማ ለማካሄድ ሲሞክሩ ከመንግሥት አካላት ማስፈራሪያና ጫና እንደደረሰባቸውም አስታውቀዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ በዛሬው ዕለት ተጠርቷል የተባለውን የህክምና ባለሙያዎች አድማ በዋና ዋና የመንግስት ሆስፒታሎች ማለትም በዳግማዊ #ምኒልክ ሪፈራል ሆስፒታል፣ #በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል እና #በየካቲት12 ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል ጠዋት ላይ የከፊል የስራ ማቆም መካሄዱን ለመታዘብ ተችሏል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
👍147❤11🤔6👎2
ሕወሓት ከፖለቲካ ፓርቲነት ተሠረዘ
ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡
ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ፡፡
ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከፖለቲካ ፓርቲነት መሠረዙን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያወጣው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
👍67👎16❤11😱3👏2🥰1
"ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ" - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተጀምሯል።
የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ መጀመሩን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም "ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ" ብለዋል።
"ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ" ያሉ ሲሆን፤ "በዚህ ኣማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ ኣድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ ኣድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው" ብለዋል።
ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
"የኢትዮጵያ ህዝብ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው" ያሉት ፓትርያርኩ፤ "እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ ኣሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት ኣካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን" ብለዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተጀምሯል።
የርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ መጀመሩን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም "ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ" ብለዋል።
"ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ" ያሉ ሲሆን፤ "በዚህ ኣማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ ኣድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ ኣድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው" ብለዋል።
ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
"የኢትዮጵያ ህዝብ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው" ያሉት ፓትርያርኩ፤ "እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ ኣሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት ኣካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን" ብለዋል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
👍154❤32🤯3👎2😱2🥰1
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ
የእግር ኳሱ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ2025 ከ275 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማግኘት የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ መሆን ችሏል።
ለሳዑዲዉ ክለብ አልናስር እየተጫወተ የሚገኘው ሮናልዶ ከስፖንሰር ሺፕ እና ከደሞዝ ጥቅማጥቅሞች ያገኘው ገቢ ከዓለም ቀዳሚው ስፖርተኛ አድርጎታል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ ሲሆን ይህ ለ3ኛ ተከታታይ ዓመታት መሆን ፎርብስ ዘግቧል።
የቅርጫት ኳሱ ኮከብ ስቴፈን ከሪ በ 156 ሚሊዮን ዶላር ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፤ ብሪታንያዊው ቦክሰኛ ታይሰን ፉሪ በ146 ሚሊዮን ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
ሌላኛው የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ 135 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 5ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡ እንዲሁም ሌላኛው የእግር ኳስ ተጫዋቾች ካሪም ቤንዜማ 104 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 8ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ተጫዋች ሆኗል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
የእግር ኳሱ ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ2025 ከ275 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማግኘት የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ መሆን ችሏል።
ለሳዑዲዉ ክለብ አልናስር እየተጫወተ የሚገኘው ሮናልዶ ከስፖንሰር ሺፕ እና ከደሞዝ ጥቅማጥቅሞች ያገኘው ገቢ ከዓለም ቀዳሚው ስፖርተኛ አድርጎታል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የዓለም ከፍተኛው ተከፋይ ስፖርተኛ ሲሆን ይህ ለ3ኛ ተከታታይ ዓመታት መሆን ፎርብስ ዘግቧል።
የቅርጫት ኳሱ ኮከብ ስቴፈን ከሪ በ 156 ሚሊዮን ዶላር ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ፤ ብሪታንያዊው ቦክሰኛ ታይሰን ፉሪ በ146 ሚሊዮን ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
ሌላኛው የእግር ኳስ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ 135 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 5ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል፡፡ እንዲሁም ሌላኛው የእግር ኳስ ተጫዋቾች ካሪም ቤንዜማ 104 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት 8ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠ ተጫዋች ሆኗል።
T.me/ethio_mereja
ኢትዮ-መረጃ
👍86❤27🤔5😢2👏1😁1🤯1