የእንስቶቹ ገፅ👩‍🦰👩‍🦱👩‍🦳🧕
172 subscribers
246 photos
27 videos
2 files
28 links
ይህ ሴቶች ብቻ የሚሰባሰቡበት ቻናል ነው ስለ ራሳችን የምናወራበት ከሌሎች ጋር የምናውጋበት ልዮ የእንስቶች መድረክ ነው እንስቶችን በተመለከተ ፅሁፍ,ፎቶ,ቪድዬ,ሊንክ ካገኛችሁ ማጋራታቹሁን እንዳትረሱ
እኛው ለእኛው እንሁን👩👧
Download Telegram
ክብርሽን ጠብቂ፡

ወንድ ልጅ በቀላሉ ያገኘውን ነገር በቀላሉ የመርሳት ዝንባሌ አለው

ዛሬ ስጦታ ፣ አበባና ቸኮሌት ሊኖር ይችላል። እነዚህ ሁሉ ያልፋሉ፤ አንቺ ግን ከራስሽ ጋር ለዘላለም ትኖሪያለሽ። ራስሽን ዝቅ አታድርጊ።

የካቲት 14 (Valentine's Day) እንደመሆኑ መጠን፣ ብዙ ሴቶች የፍቅር መግለጫ አድርገው "ክብራቸውን" (ድንግልናቸውን) ለወንዶች የመስጠት ዝንባሌ ሊኖራቸው ይችላል።


ይህ ውሳኔ ከስሜታዊነት በላይ የሆነና ነገ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ሊኖረው የሚችል በመሆኑ

🌹 ለራስሽ የምትሰጪው ስጦታ

ይህ ቀን የፍቅር ቀን ነው፤ ፍቅር ደግሞ ከራስ ይጀምራል። ለአንድ ሰው መስጠት የምትችዪው ትልቁ ስጦታ "አካልሽ" ሳይሆን "ክብርሽና ታማኝነትሽ" ነው።


ጊዜያዊ ስሜትና ዘላቂ ዋጋ፡

የአንድ ቀን የፍቅር ድባብና ስሜት እንዲያሸንፍሽ አትፍቀጂ። ስሜት እንደ ደመና ጠፊ ነው፤ ክብርሽ ግን የማንነትሽ መገለጫና አንዴ ከሄደ የማይመለስ ውድ ሀብትሽ ነው።



ፍቅር በስጦታ አይለካም፡

አንድ ወንድ በእውነት የሚያፈቅርሽ ከሆነ፣ ላንቺ ያለው ክብር አካልሽን ከመፈለግ በላይ መሆን አለበት። "ካላደረግሽው አታፈቅሪኝም" የሚል ግፊት ካለ፣ ያ ፍቅር ሳይሆን የፍላጎት መገበያያ ነው።


የነገዋ አንቺ፡ ዛሬ የምታደርጊው ነገር ነገ ስታስቢው ኩራት ወይስ ጸጸት እንደሚሰጥሽ ቆም ብለሽ አስቢ። ለትክክለኛው ሰው፣ በትክክለኛው ጊዜና ቦታ (በትዳር) የሚጠበቅ ስጦታ ሁልጊዜም የበለጠ ጣፋጭ ነው።


💡 ማስታወስ የሚገቡሽ ነጥቦች

"ሰውነታችሁ  የፈጣሪ ቤተ መቅደስ ነው" እንደሚባለው፣ ይሄ መቅደስ ለማንም በሩን የሚከፍት ሳይሆን ልዩ ጥበቃ የሚደረግለት መሆን አለበት።

የግፊት ሰለባ አትሁኚ፡

ጓደኞቼ አደረጉት ወይም አለም እያደረገው ነው በሚል ውሳኔ አትሳሳቢ። አንቺ ልዩ ነሽ፣ ዋጋሽም ውድ ነው።

ክብርሽን ጠብቂ፡

ወንድ ልጅ በቀላሉ ያገኘውን ነገር በቀላሉ የመርሳት ዝንባሌ አለው። በብዙ ትግልና በክብር ያገኘሽን ሴት ግን ዕድሜ ልኩን ሲያከብርሽ ይኖራል።

ራስሽን ውደጂ

ዛሬ ስጦታ፣ አበባና ቸኮሌት ሊኖር ይችላል። እነዚህ ሁሉ ያልፋሉ፤ አንቺ ግን ከራስሽ ጋር ለዘላለም ትኖሪያለሽ። ራስሽን ዝቅ አታድርጊ።


ማጠቃለያ

ውድ እህቴ፣ የዛሬው ደስታ የነገው ቁስል እንዳይሆን ተጠንቀቂ። እውነተኛ ፍቅር "ትዕግስት" አለው። የሚወድሽ ሰው ክብርሽን ይጠብቃል እንጂ አይቀማሽም። ዛሬን በንጽህና እና በክብር በማሳለፍ ለራስሽ ትልቅ ዋጋ ስጪ።

ይህ ቀን ያልፋል፤ ማንነትሽ ግን ይቀጥላል።

ቆም ብለሽ አስቢ!
3🔥1
Forwarded from እንማር
(ሁሌ ቫለንታይን ሲደርስ ትዝ የሚለኝ ታሪክ። ሶስት አመት ሞላው ይሄ ታሪክ ትንሽ ነው ኤዲት ያደረኳት እንጂ እውነት ናት... ዝለቁ በሉ..)

💠ካፈቀርኩት አመት ከሞላኝ ሰው ጋር በስልክ እያወራን ነው... በጣም ናፍቆኝ ረዥም ሰዓት አወራን። በመሃል ሳት ብሎኝ ያወራሁት ነገር ግን ህይወቴን እስከማጨለም አደረሰኝ። ከንግግራችን መሃል ይህን ሃሳብ አነሳሁለት

<ታውቃለህ ወጣትነቴን ቢያንስ በፎቶ ባስቀምጠው ደስ ይለኛል>

<ታድያ ብዙ ፎቶዎች አሉሽ እኮ>

💠<አይ እንደሱ አይነት ፎቶ ሳይሆን አለ አይደል ሰውነቴን... ይሄ መሸብሸብ ያልደረሰበት ... ሸንተረር ያላየው ሰውነቴን አንስቼ ባስቀምጥ ደስ ይለኛል። በኋላ ልጅ እና እርጅና ሲመጣ መልሼ የማላገኘውን ሰውነቴን...>

<ለሱ አታስቢ እኔ ጋር ... >

<አንተ ጋር ምን?... ንገረኝ... አንተ ጋር ምን?>

💠ከሳምንት በፊት የፍቅረኛሞች ቀን <ከቤት ወጥቼ ማደር አይፈቀድልኝም> ስለው <የታደሉ ፍቅረኛሞች ተቃቅፈው ይተኛሉ... እኔ ግን በምወዳት ልጅ ምክንያት እዚሁ አልጋዬ ላይ ተኮራምቼ...> ምናምን እያለ አለቃቀሰ። የምር አሳዝኖኛል። እወደዋለሁ። ይሄኔ ሌላ ሴት ቢያፈቅር እኮ አብራው ታድር ነበር እኔን በመምረጡ እና በማፍቀሩ ብቻ እየተቀጣ ነው... ብዬ አሰብኩ

<እሺ ምን ላድርግልህ?>

<በቃ እያሰብኩሽ ልተኛ ቢያንስ ፎቶሽን ላኪልኝ>

💠በጣም አሰብኩበት። አምነዋለው። እወደዋለው። አሳዘነኝ። በቃ ለዚህ እየቀጣሁት ላለሁት ሰው መካሻ ይሆነው ዘንድ እርቃን ፎቶዬን ልኬለት ነበር። አሁን እሱ ትዝ አለኝ። ግን ሲነጋ ወዲያው አጠፋዋለሁ ብሎኝ ስለነበር ያልጠበኩት የአፍ ወለምታ ስለሆነብኝ በጣም ደነገጥኩ

<አላጠፋኸውም እንዴ? >

<አጥፍቼዋለሁ በእውነት... ማለቴ... ሃሳቤ ውስጥ አንቺ አለሽ ለማለት ነው>

💠 ብዙም ሳንቆይ... የፍቅረኛሞች ቀን ላይ እሱ እንዳለው እና እኔ እንዳሰብኩት የላኩለትን ፎቶ አቅፎ በናፍቆት ተኮራምቶ ሳይሆን ... ከሌላኛዋ ሴት ጭን ስር ሲዋኝ እንዳደረ ሰማሁ። በጣም ተጣላን። በጣም አዘንኩ። በጣም ተከፋሁ። ራሴን እየረገምኩ ቆየሁ። ተለያየን።

በኋላ ላይ ግን ያ አሁን ሳይሆን ወደፊት... ካረጀሁ እና ከወለድኩ በኋላ ማየት የምፈልገው ገላዬ አሁን ላይ በየሶሻልሚዲያው ሲዘዋወር ተመለከትኩት። በእኔ እና በሱ መሃል ብቻ የነበረው የመሠለኝ ገላዬ የሁሉም ሆነ። ሁሉም አየው። በማመኔ ተፀፀትኩ። ስንቴ ነው የሚገለኝ? ስንቴ ነው የምሞተው? እስከመቼ ነው የሚያመኝ? የማመን ዋጋው እንዴት ነው? ምን ያስከፍለናል?

🔹ከሁሉም ያመመኝ ግን እንደኔ ሴት የሆኑት ሴቶች እንኳን በገላዬ ሲዘባበቱበት ሳይ ነው... ከሁሉም ነገር የከበደኝ እንደኔ በአንድ ወቅት አፍቅረው አምነው የነበሩ ሴቶች አሁን የኔን ሃጥያት ሲገልጡ እና ሲፈርዱብኝ ማየቴ ነው። ከሁሉም ህመሙ በራሳቸው ሲደርስ.. እንኳን ማየት ማሰብ የሚከብዳቸው ሴቶች ዛሬ የእኔን ነውር ሲቀባበሉት ሳይ ነው። ራሴን በራሴ ስቀጣው ቆይቻለሁ... በመላኬ ስሳቀቅም ስፀፀትም ቆይቻለሁ... አሁን ግን የመሰሎቼን ሳቅ እና ፌዝ መቋቋም አልቻልኩም።

💠ከደረሰብኝም በደል ካደረሰብኝም ሰው በላይ እኒህ መሰሎቼ ደጋግመው ገደሉኝ። እንዴት ብለው ፈረዱብኝ።

Fantu emu
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
1
Forwarded from እንማር
ዘማነቱ አይኑ ላይ ሲንቀለቀል ብዙ ቀን አይቼዋለሁ!! ከኔ ጋ ሆኖ የሌላ ሴት ዳሌ አንገቱን ጠምዝዞ ሲመለከት ተናግሬው አላቅም።እውነት ለመናገር ወድጄው ነበር... ከዚህ አመሉ ሌላ ሁሉ ነገሩ ሚወደድ ነው ።አለባበስ ያውቅበታል ፤ወሬ ያምርበታል፤ በተለይ ሲስቅ ቀልብ ይሰርቃል ፤ስራ ሲባል ልቡ ይሸፍታል ፤የስራ ሰው ነው።ለዚህ ነው ድክመቱን እያወቅኩ አንድ አመት ያፈቀርኩት.....

አንድ ቀን ላገባሽ እፈልጋለሁ ሲል እራት እየበላን ጠየቀኝ ...ለምን እንደሆን እንጃ ደስታ ቀደመኝ፤ሳቅ ሳቅ አለኝ፤ እዛው ትንሽዬ የቀለበት ፕሮግራም አድርገን ለመጋባት ቀን ቆርጠን ተለያየን።Chachaአእምሮዬ አልፈጠንሽም???ቆይ አስቢበት?? ተረጋጊ በደንብ አጥኚው...እያለ እየወተወተኝ ቆየሁ ብሰማውም አልተቀበልኩት።እያብሰለሰልኩ ሳምንታት ተቆጥረው የቀጠረኝ ሆቴል ልቤ እየፈራ ዘንጬ ተገኘሁ... ጓደኞቼን ጨምሮ ጥቂት ሰወች ሆቴል ውስጥ ተሰብስበዋል። ግማሹ ወይን ሌላው ቢራ በእጁ አንቆ የኔን መምጣት ከበር ይጠባበቃል። እኔም እግሬ እየሰነፈብኝ ቢሆንም የግዴን እየታሸው ወደ ሆቴሉ ገባው.

.. chachaሆቴሉ በጭብጨባ እና በሳቅ ተሞላ ከፊት ለፊቴ በቀይ በአበባ የተንቆጠቆጠው ልዩ ቦታ ላይ ነጭ የለበሰው ፍቅረኛዬ ቆሟል ልክ ወደሱ እንደተጠጋሁ ግን ተንበርክኮ የቀለበት ሳጥኑን እንደከፈተው ድንገት ከኋላ አንድ የሴት ድምፅ ተሰማ....

እሺ እንዳትዪው!!! የሚል ነበር ሁላችንም ደንግጠን ታዳሚ ወደተሰበሰበበት ጀርባ አየን።የቆመው ሰው ሁሉ እየከፈተ በዊልቸር የምትሄድ ..ፊቷ በማድያት ተጠብሶ ያደፈ ሺቲ የለበሰች ጥቁር ሻርብ የተከናነበች ሴት አጠገባችን ደርሳ ቆመች።chachaሁሉም በያለበት ረጭ ብሎ ክፍሉ ኦና የሆነ ያህል ሆኗል። ሁላችንም የምንጠብቀው የሷን አፍ ነው.....

የሰማንያ ባሌ ነው!!!chachaፊርማችን እንኳን አልተቀደደም።አንድ ሴት ልጅ ወልጄለታለሁ ...ወጣትነቴን ተጠቅሞ ተጫውቶብኝ መታመሜን ሲያውቅ ጥሎኝ ጠፋ!!ብከሰው እጁ ረጅም ነው...ዝም ብዬ ባየው ልጄን ማኖርበት እንኳ ሳንቲም አይሰጠኝም። chachaከኩላሊት ህመሜ ጋ እየታገልኩ ገፍትሮ ጥሎኝ በህመሜ ላይ ህመም የሰጠኝ እሱ ነው!!!ሰባራ አርጎ አጨልሞኝ ከድቶኝ የሄደው እሱ ነው!!!ሁሉንም ነገር እከታተላለሁ አንቺም እንዳትሸወጂ ይኸው ፍረዱኝ!! ፍረዱኝኝ በልጅ አምላክክክክ !!!እንባዋ መንታ ሆኖ እየወረደ ስታለቅስ አብረን አለቀስን አጅሬ አንገቱን ሰብሮ እንደተንበረከከ ነው

በጥፊ ልምታው?? ልርገጠው ???ልንከሰው??በኬኩ ቢላ ወጋግቼ ልግደለው??የቱ ቅጣት የዚህን ሰው ክፋት ይመልሳል??የቱ ፍርድ እቺን ምስኪን ቀና ያደርጋታል ??እንጃ!!

ለመሆኑ...."ታገቢኛለሽ ወይ?"ብሎ ፊትለፊትሽ የተንበረከከውን ወንድ ታቂዋለሽ ወይ??ሀላፊነት ሚሰማው ሚያከብርሽ እንደሴትነትሽ በወንድነቱ አክብሮሽ የሚያኖርሽ መሆኑን ታምኚበታለሽ ወይ??እሺ ብላለች ከመባሉ በፊት ጣትሽ ላይ ቀለበት ከመግባቱ በፊት አንቺ እና እሱ ተግባብታችኋል ወይ ታውቂዋለሽ ወይ????

እየውልሽ እህቴ..."አንዳንድ ክፋቶች ምድር ላይ ያሉ ቅጣቶች አይመጥኗቸውም!!ትዳር ከማያውቁት ጋ ትዳር ሳይሆን ረመጥ ነው
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
4🔥2
ሴት በወንድ ሕይወት ውስጥ ሦስት መልክ አላት፦ እናት፣ እህትና ሚስት። እናት መጀመሪያው ናት፣ እህት መንገዱ ናት፣ ሚስት ደግሞ መድረሻው ናት። ሴት ማለት የሕይወት መዝሙር፣ የወንድ ልጅ የልብ ትርታና የነፍሱ መስታወት ናት።

መራራው እውነት  የሰው ልጅ ሴትን እንደ "ዕቃ" ወይም እንደ "ንብረት" አድርጎ መመልከቱ ነው። ወንድ ሴትን ሊገዛትና ሊቆጣጠራት ይሞክራል፣ ነገር ግን ሴት ማለት እንደ ንፋስ ነጻ የሆነች ነፍስ ናት። ትልቁ ግጭት የሚፈጠረው ወንድ የሴትን "አካል" እንጂ "ነፍስ" መውደድ ሲያቅተው ነው። ሴት የአበባ ዘር ናት፤ በፍቅርና በክብር ካልተያዘች ትጠወልጋለች። ነገር ግን ስትፈካ ዓለምን በመዓዛዋ ትሞላለች። የሴት ስቃይ የዓለም ሁሉ ስቃይ ነው፤ ምክንያቱም ዓለም የምትኖረው በእሷ ትዕግስትና መስዋዕትነት ውስጥ ነውና።

📕 ርዕስ፦የጥበብ መንገድ
✍🏻 ደራሲ፦ካህሊል ጂብራን
🔥42
Forwarded from Bemnet Library
አንዲት ሴት ለማትወደው ሰው በወርቅና በሀብት ስትሸጥ አየሁ፤ ቤተሰቦቿም "ይህ ለደስታሽ ነው" አሏት። እሷ ግን በመጋረጃው ውስጥ ሆና በዝምታ ታለቅስ ነበር።በዚህ መካከል ትልቁ ሐዘን የሰውን ልጅ ልብ በገንዘብ መመዘናቸው ነው። ፍቅር ነጻ መሆን ሲገባው፣ በወርቅ ሰንሰለት ታስሮ ወደ መኝታ ክፍል ይወሰዳል። ያንን ሰው ስታቅፈው፣ የምታቅፈው ስጋውን እንጂ ነፍሱን አይደለም።

ይህ "ሕጋዊ ግልሙትና" ይባላል፤ ስሙ ግን "ጋብቻ" ተብሎ ይከበራል። ነፍስህ ከሌላ ጋር ሆና፣ ስጋህ ግን ከሌላ ጋር እንዲሆን መገደድ ከገሃነም በላይ የሚያም ስቃይ ነው።ሕብረተሰቡ "ክብር  ይለዋል፣ እኔ ግን "ሞት" እለዋለሁ። ስንት ንጹህ ልቦች በዚህ በወግና በልማድ ሰይፍ ተሰልበዋል? ስንት ህልሞችስ በሀብታሞች እግር ስር ተረግጠዋል? ይህ ግፍ በየቀኑ በቤቶቻችሁ ውስጥ ይፈጸማል፤ እናንተ ግን በዝምታ ትመለከታላችሁ። የሰው ልጅ ትልቁ ውድቀት፣ ፍቅርን ከመንፈስ አውጥቶ ወደ ንግድ የቀየረበት ዕለት ነው።

📕 ርዕስ፦የተሰበሩ ክንፎች
✍🏻 ደራሲ፦ካህሊል ጂብራን

📚 @Bemnet_Library
1🔥1
Forwarded from ካሊድ አቅሉ
ዐይን የሚሰማው ንግግር
(ካሊድ አቅሉ)

" ካላየነው በቀር የማንረዳው ብዙ ንግግር አለ ። "
----------------------------

ከአለቃዬ ጋር በመስሪያ ቤት Cafe ውስጥ ሻይ ቡና እያልን ነው በጫወታ መሀል ስላለፈው የአፍላ ወጣትነት ዘመንዋ በቁጭት አነሳች ፣ " እኔ እኮ ቃሊ ሚቆጨኝ ያኔ መንገድ ስስት ተመለሺ ብሎ ሚይዘኝ አንድ የቤተሰብ እንዴት አይኖርም ? ሁሉም እንደፈቀድሽ ብለው እሳት ውስጥ ስገባ ዳር ይዘው አዩኝ እናት ,አባት, ወንድም,እህት ጎረቤት .... አንድም አንቺ ልጅ ተመለሽ አይልም ? "

" እነሱን ወቀስሽ እንጂ ያኔ ቢመክሩሽስ ከጥፋት መንገድ እንደምትመለሺ እርግጠኛ አትሁኚ በወጣትነት ያውም ደሞ አፍላው ሰዓት ከምክር በላይ ዱላ ይቀለናል" አልኳት መብሰልሰልዋን ለመቀነስ በሚጥር ድምፅ . . . . " ልክ ነህ ደግሞም ካላየነው በቀር የማንረዳው ብዙ ንግግር አለ ፤ ወጣትነቴን ተጠቅሞ አንድ ልጅ አስታቅፎኝ ጥሎኝ ሄደ ፈጣሪዬን አመሰግነዋለው ጥርሴን ነክሼ ልጄን አሳደግኩ በማታ ፕሮግራም ማስተርሴን ተማርኩ ግን አሁንም ከሱ ጋር ያባከንኩት የመሸነጋገል ዘመን እንደ እግር እሳት ያንገበግበኛል !" ጥርስዋን አሁንም በቁጭት ስትነክስ "አይ አሁንም እኮ አረፈደም አንቺ እንደው ገና ነሽ " አልኳት ስላሳዎቹን ወደ መጨረስ ያለችዋን ሰብሊን በሙሉ አይኔ እያየው . . . . . . " እሱስ አዎ ግን ቀትር ላይ ያለው ፀሐይና አመሻሽ ላይ ምትጠልቀው ፀሐይ እኩል ብርሃን አይሰጡም " አለችኝ ለዘብ ብላ " ያንቺ ግዴታ በነቃሽ ሰዓት ያገኘሻትን ብርሃን በአግባብ መጠቀም ነው ። " ብዬ ከአፎችዋ መልስ ጠበኩ ሁለታችንም አቀርቅረን በትዝታ በየፈርጃችን ነጎድን . . . . .

@kalidakelu
Forwarded from She beyond
📢 Help Us Understand Girls’ Health Needs! 💜🌍
She Shapes Africa is conducting an independent research study on women’s health awareness among girls and young women.
Your voice matters! By taking part in this short survey, you’ll help us understand: What girls want to learn about in health education
How girls access health information
Challenges in getting reliable information
What kind of awareness activities are most helpful
🕒 Takes only 3–5 minutes
🔒 Anonymous responses
📊 Results will support a She Shapes Africa research report aimed at improving health education for girls.
🔗 Survey link: https://forms.gle/3dh9R4NUAZqLdeNv7⁠�
Please feel free to share it with friends, classmates, and others who may want to participate 💜
#SheShapesAfrica #GirlsHealth #WomenHealth #YouthResearch #EducationForGirls@sheshapesafrica
Forwarded from Strong girl's (Tsion Addisu)
* ቃቄ ውርድወት *


<ሴት ልጅ ተመርጣ ብቻ ሳይሆን መርጣም ማግባት አለባት>


'ከዘመኗ የቀደመች' ስለሚባልላትና፤ በ1840ዎቹ ከጉራጌ ማሕበረሰብ ስለተገኘችው ቃቄ ውርድወት(ቃቄ የአባቷ ስም ሲሆን ውርድወት የእርሷ ስም ነው። በሀገራችን ከልጅ በፊት የአባት ስም በቅድሚያ የሚጠራበት ባሕል እንዳለ ያውቋል?)ምን ያህል ታውቃላችሁ?

ይህች ሴት በዘመኗ በጉራጌ ማሕበረሰብ ዘንድ 'ኧጆካ' እስከሚባለው ከፍተኛው ሸንጎ ድረስ ለሴቶች መብት የተሟገተች ትንታግ ነበረች። ዛሬ ላይ ቀለም ቆጥረዋል ከምንላቸው ከብዙዎቹ እንስቶች በተሻለ ስለ ሴቶች ክብር የቆመች አብዮተኛ እንስት ነበረች።

ለማናቸውም ስለዚህች ጀግና ሴት ታሪክ አጠር ያለ ማብራሪያ ከፈለጋችሁ እነሆ ሊንኩ https://t.me/AdissAdmas/32080

በተጨማሪም ሰፋ ያለ ማብራሪያ ለሚሻ የእንዳለ ጌታ ከበደን 'እምቢታ' መፅሀፍን እጋብዛለሁ።
1
የchild wellbeing(CWB) አባል ያልሆናቹም ስለዚህ ስኮላርሽፕ ሂደት ማወቅ ከፈለጋቹ ሀሙስ ከምሽቱ 3:00 online meeting ይጠብቁን!
meet.google.com/rym-etmk-etv
🙏1
Forwarded from She beyond
📝 SHE BEYOND YOUTH WRITING COMPETITION 🌍💙

Theme: “Breaking Barriers: The Future I Want for African Girls”

Have an idea about the future of African girls? Share your voice, ideas, experiences, or solutions through writing!

📌 DETAILS
👥 Ages 14–18, across Africa
✍️ 300–500 words
🇬🇧 Written in English
📄 Original essay | PDF or DOCX
📝 One submission per participant
🗓️ August 21 – September 4, 2026

🎓 ALL PARTICIPANTS receive a Certificate of Participation.

🏆 PRIZES

🥇 1st Place — Gold Award Certificate
• Online Course
• Special Recognition from She Beyond

🥈 2nd Place — Silver Award Certificate
• Online Course
• Special Recognition from She Beyond

🥉 3rd Place — Bronze Award Certificate
• Online Course
• Special Recognition from She Beyond

📩 HOW TO ENTER

1. Write your 300–500 word essay.
2. Complete the submission form.
3. Upload your essay.
4. Submit before September 4, 2026.

🔗 Submit here:
Google Form

💙 Your voice can inspire change.

#SheBeyond@shebeyonds