...እሺ በቃ እወድሻለሁ "አላት የሞት ሞቱን።ቃላቱ አልወጣ ብለው ተናንቀውት ነበር። "እወድሻለሁ ማለት መሸነፍ የሚመስላችሁ ለምንድን ነው?'' አለች ሰብለ።
ደስታ የሰማውን አላመነም ''አልሰማሽም እንዴ፤እወድሻለሁ ነው እኮ ያልኩት ''አለ። 'እሱንማ ሰምቼዋለሁ።
የጠየቁህ ግን ያንን ለማለት የፈጀብህን ጊዜ እና ሂደት ከግምት ውስጥ በማስገባት "እወድሻለሁ"ብሎ ደፍሮ ፊት ለፊት መናገር ለምን ይከብዳቸዋል ብዬ ነው አለች።''ትልቅ መሸነፍ ነው የሚሆንባችሁ"አለችው ከሱ መልስ ሳትጠብቅ። "መሸነፍማ ነው አላት። "ምን?ምን አልክ?"አለች እሷም በተራዋ የሰማችውን ባለማመን።
"አዎን መሸነፍ ነው ።ፍቅር መሸነፍ ነው።ፍቅር መያዝ ነው።ፍቅር ለስሜት ተገዢ መሆን ማለት ነው።ፍቅር ከምክንያት ውጪ ሆኖ መኖርን መቀበል ነው።ፍቅር ከራስ ቁጥጥር ውጪ መሆን ነው" ስለዚህ አዎ መሸነፍ ነው።ያስፈራል ፍቅር ፣የማይታከሙት ህመም፣የማይጠገን ቁስል፣የማያባራ እንባና ሰቆቃ :: ሊሆን ይችላል።
የሚያስፈራው ያፈቀርሽው ሰው ሳይሆን ፤ማፍቀር ራሱ ነው"ካፈቀርሽ በኋላ"እኔ የምትይው ሁሉ ይጠፋል።ለራስሽ ትርፍ ትሆኛለሽ።በፈቃደኝነት ከራስሽ የምታስቀድሚውና የምታስበልጪው ሌላ ሰው ይኖራል ማለት ነው።"
ፍቅር ያለ ውጊያ መማረክ ነው፣እጅ መስጠት፣ወዶ
መግባት ፣ከራስ መነጠል፣መጥፋት ፣በማያውቁት ሰው ዓለም ውስጥ ገብቶ መሰደድ ።አያስፈራም አትበይኝ ያስፈራል ::''
ወንድ ወይንም ሴት ስለሆንን ግን አይደለም ፍቅርን የምንፈራው።ሰው ስለሆንን ነው።
ማናችንም ብንሆን የህይወታችንን መንገድ መቆጣጠር ባንችል እንኳን ማቀድና መምራት እንፈልጋለን ።አንቺን ወደድኩሽ ስል ይህን ሁሉ መተው ማለት ነው።አንቺን በመውደዴ ከዚህ ቀደም የኖርኩት፣ ያቀድኩትና እያሰብኩት ሁሉ ተጠራርጎ ገደል ይገባል። ምን እንደሚሆን፣ምን እንደሚመጣ፣ምን እንደሚፈጠር አላውቅም፡፡ምክንያቱም ከኔ ቁጥጥር ውጪ ነው"
አለማወቅ ደግሞ ያስፈራል።
ራሴን እንኳን እየተቆጣጠርኩ ባለሁበት ሁኔታ፣ስለ ህይወቴ አካሄድ የማውቀው ጥቂት ነው።ግን የማውቅ ስለሚመስለኝ በሰላም እኖራለሁ "ፍቅር ግን መምሰልን ያጠፋል።ከፊት ለፊቴ የተቀመጠው ስራዬ፣ዕውቀቴ፣ ጓደኞቼ ወዘተ የምላቸው የኑሮ ማስመስያዎች በሙሉ ትርጉም ያጣሉ።ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ምን እንደሚያስፈራ ታውቂያለሽ ?አላት። ምን ? አለችው።
አፏን ከፍታ ስታዳምጠው ስለነበር ጥያቄውን ያነሳችው እሷ ራሷ መሆኗ ሁሉ ጠፍቶባት ነበር::
"ፍቅር መተወን አይችልም
በመሆኑም ከልቡ የወደደና ያፈቀረ ሰው ማፍቀሩን ማወጅ ቢያስፈራው አይደንቅም።በቀላሉ እወድሻለሁ የሚል ሰው መውደዱን ገና ያላወቀ ወይንም አስመሳይ ነው" አላት።
አለመኖር 📚
ደስታ የሰማውን አላመነም ''አልሰማሽም እንዴ፤እወድሻለሁ ነው እኮ ያልኩት ''አለ። 'እሱንማ ሰምቼዋለሁ።
የጠየቁህ ግን ያንን ለማለት የፈጀብህን ጊዜ እና ሂደት ከግምት ውስጥ በማስገባት "እወድሻለሁ"ብሎ ደፍሮ ፊት ለፊት መናገር ለምን ይከብዳቸዋል ብዬ ነው አለች።''ትልቅ መሸነፍ ነው የሚሆንባችሁ"አለችው ከሱ መልስ ሳትጠብቅ። "መሸነፍማ ነው አላት። "ምን?ምን አልክ?"አለች እሷም በተራዋ የሰማችውን ባለማመን።
"አዎን መሸነፍ ነው ።ፍቅር መሸነፍ ነው።ፍቅር መያዝ ነው።ፍቅር ለስሜት ተገዢ መሆን ማለት ነው።ፍቅር ከምክንያት ውጪ ሆኖ መኖርን መቀበል ነው።ፍቅር ከራስ ቁጥጥር ውጪ መሆን ነው" ስለዚህ አዎ መሸነፍ ነው።ያስፈራል ፍቅር ፣የማይታከሙት ህመም፣የማይጠገን ቁስል፣የማያባራ እንባና ሰቆቃ :: ሊሆን ይችላል።
የሚያስፈራው ያፈቀርሽው ሰው ሳይሆን ፤ማፍቀር ራሱ ነው"ካፈቀርሽ በኋላ"እኔ የምትይው ሁሉ ይጠፋል።ለራስሽ ትርፍ ትሆኛለሽ።በፈቃደኝነት ከራስሽ የምታስቀድሚውና የምታስበልጪው ሌላ ሰው ይኖራል ማለት ነው።"
ፍቅር ያለ ውጊያ መማረክ ነው፣እጅ መስጠት፣ወዶ
መግባት ፣ከራስ መነጠል፣መጥፋት ፣በማያውቁት ሰው ዓለም ውስጥ ገብቶ መሰደድ ።አያስፈራም አትበይኝ ያስፈራል ::''
ወንድ ወይንም ሴት ስለሆንን ግን አይደለም ፍቅርን የምንፈራው።ሰው ስለሆንን ነው።
ማናችንም ብንሆን የህይወታችንን መንገድ መቆጣጠር ባንችል እንኳን ማቀድና መምራት እንፈልጋለን ።አንቺን ወደድኩሽ ስል ይህን ሁሉ መተው ማለት ነው።አንቺን በመውደዴ ከዚህ ቀደም የኖርኩት፣ ያቀድኩትና እያሰብኩት ሁሉ ተጠራርጎ ገደል ይገባል። ምን እንደሚሆን፣ምን እንደሚመጣ፣ምን እንደሚፈጠር አላውቅም፡፡ምክንያቱም ከኔ ቁጥጥር ውጪ ነው"
አለማወቅ ደግሞ ያስፈራል።
ራሴን እንኳን እየተቆጣጠርኩ ባለሁበት ሁኔታ፣ስለ ህይወቴ አካሄድ የማውቀው ጥቂት ነው።ግን የማውቅ ስለሚመስለኝ በሰላም እኖራለሁ "ፍቅር ግን መምሰልን ያጠፋል።ከፊት ለፊቴ የተቀመጠው ስራዬ፣ዕውቀቴ፣ ጓደኞቼ ወዘተ የምላቸው የኑሮ ማስመስያዎች በሙሉ ትርጉም ያጣሉ።ከዚህ ሁሉ በላይ ግን ምን እንደሚያስፈራ ታውቂያለሽ ?አላት። ምን ? አለችው።
አፏን ከፍታ ስታዳምጠው ስለነበር ጥያቄውን ያነሳችው እሷ ራሷ መሆኗ ሁሉ ጠፍቶባት ነበር::
"ፍቅር መተወን አይችልም
በመሆኑም ከልቡ የወደደና ያፈቀረ ሰው ማፍቀሩን ማወጅ ቢያስፈራው አይደንቅም።በቀላሉ እወድሻለሁ የሚል ሰው መውደዱን ገና ያላወቀ ወይንም አስመሳይ ነው" አላት።
አለመኖር 📚
👍2❤🔥1🥰1
እሱ፤ አንድ ሚልዮን ብር ብሰጥሽ ከኔ ጋር ትተኛለሽ?
እሷ፤ አንድ ሚልዮን ብር? ዋው! ይመስለኛል አዎ፡፡
እሱ፤ በመቶ ብርስ?
እሷ ፤ ጥፋ ከዚህ፡፡ ምን መስዬህ ነው? ሴተኛ አዳሪ?
እሱ፤ ሴት አዳሪነትሽን መጀመሪያውኑ ተስማምተናል፡፡ አሁን በገንዘቡ ላይ እንደራደር።
ልክነት መቼ እና እንዴት ነው
የሚኖረው? መቼ ነው ይህቺን ሴት ሴተኛ አዳሪ የምንላት? መቼ ነው ይህቺን ሴት ክብሯን የጠበቀችው? መቶ ብር ወይስ መቶ ሺ ብር ላይ? ወይስ አንድ ሚሊዮን ላይ? መቼ ነው ክብሯን ያጣችው?
የገነባነው ክብር እና ፅድቅ በየትኛው የብር መጠን ላይ እንሽረዋለን? ከሻርነውስ የእውነት መልካም ሰው ነን ማለት እንችላለን?
ምናልባት ምግባራችን እንደ ሴቷ በገንዘብ ስላልተፈተነ ይሁን ጥሩ ሰው የመሰልነው ?
እሷ፤ አንድ ሚልዮን ብር? ዋው! ይመስለኛል አዎ፡፡
እሱ፤ በመቶ ብርስ?
እሷ ፤ ጥፋ ከዚህ፡፡ ምን መስዬህ ነው? ሴተኛ አዳሪ?
እሱ፤ ሴት አዳሪነትሽን መጀመሪያውኑ ተስማምተናል፡፡ አሁን በገንዘቡ ላይ እንደራደር።
ልክነት መቼ እና እንዴት ነው
የሚኖረው? መቼ ነው ይህቺን ሴት ሴተኛ አዳሪ የምንላት? መቼ ነው ይህቺን ሴት ክብሯን የጠበቀችው? መቶ ብር ወይስ መቶ ሺ ብር ላይ? ወይስ አንድ ሚሊዮን ላይ? መቼ ነው ክብሯን ያጣችው?
የገነባነው ክብር እና ፅድቅ በየትኛው የብር መጠን ላይ እንሽረዋለን? ከሻርነውስ የእውነት መልካም ሰው ነን ማለት እንችላለን?
ምናልባት ምግባራችን እንደ ሴቷ በገንዘብ ስላልተፈተነ ይሁን ጥሩ ሰው የመሰልነው ?
❤6
ፅጌረዳዋ ለአፍታ ዝም አለች፡፡ ከዛም በኩራትና በስኬት በተሞላ የተዳከመ ድምፅ፣«ለአንድ ሰአት እንደ ፅጌረዳ አበባ በኩራት ኖሬአለሁ፤ ለጥቂት ጊዜም እንደ ንግስት ኖሬአለሁ፤
በፅጌረዳ አበባ አይኖችም ዓለምን ተመልክቻለሁ፤ የሰማዩን ድምፅ በፅጌረዳ አበባ ጆሮዎች አድምጫለሁ ፤የብርሀን ልብስንም በፅጌረዳ (ቅጠሎች) ዳስሻለሁ፡፡ ከእናንተ መሀል ይህን ክብር ያገኘ አለ?»
✍ካህሊል ጂብራን
በፅጌረዳ አበባ አይኖችም ዓለምን ተመልክቻለሁ፤ የሰማዩን ድምፅ በፅጌረዳ አበባ ጆሮዎች አድምጫለሁ ፤የብርሀን ልብስንም በፅጌረዳ (ቅጠሎች) ዳስሻለሁ፡፡ ከእናንተ መሀል ይህን ክብር ያገኘ አለ?»
✍ካህሊል ጂብራን
🔥1
ከህይወት ጋር ፍቅር የያዛት ይመስላል...ከማግኘት፥ከማጣቱ ጋር ፣ ከውጣ ውረዱ ጋር ፤ ከመውጣት፥ከመውረዱ ጋር ፣ ከደስታም ከሐዘኑም ጋር ።
የምትል መርህ አላት።
አድር ባይ አይደለችም ሐቀኛ ናት ፤ የማይደረግ ነገር ሲደረግ ያስቆጣታል ማለፍ አትችልም ፥ በዚህም ሳቢያ ጋጠወጦች ፈፅመው አይወዷትም ። የዋህ ናት በጣም ለሰው ታስባለች ፤ ልወደድ ብላ ግን የማይሆን ነገር ይሁን ማለት አይቻላትም ።
...ትለፋለች ፣ ትደክማለች
የምትለው አባባል አላት ፤
ደግሞም ትላለች ።
እርሷ መሽቀርቀር አይደለም ውበቷ ፤ አፈር አይንካኝ በማለት አታምንም
ትላለች ።
ከህይወት ጋር ፍቅር የያዛት ትመስላለች ፤ እኔንም ልታሲዘኝ ነው።
ከ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ
ከፈጣሪ ውጪ ምንም ነገርን አጥብቀህ መያዝ የለብህም...ሁሉም የሚወድህ ከራሱ ወዲያ ነው ።
የምትል መርህ አላት።
አድር ባይ አይደለችም ሐቀኛ ናት ፤ የማይደረግ ነገር ሲደረግ ያስቆጣታል ማለፍ አትችልም ፥ በዚህም ሳቢያ ጋጠወጦች ፈፅመው አይወዷትም ። የዋህ ናት በጣም ለሰው ታስባለች ፤ ልወደድ ብላ ግን የማይሆን ነገር ይሁን ማለት አይቻላትም ።
...ትለፋለች ፣ ትደክማለች
የሚሰሩ እጆች የተባረኩ ናቸው
የምትለው አባባል አላት ፤
ስራዬ ነው ረፍቴ
ደግሞም ትላለች ።
እርሷ መሽቀርቀር አይደለም ውበቷ ፤ አፈር አይንካኝ በማለት አታምንም
የሰው ልጅ ውበቱ ስራው ነው
ትላለች ።
ከህይወት ጋር ፍቅር የያዛት ትመስላለች ፤ እኔንም ልታሲዘኝ ነው።
ከ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ
❤4
Educational Volunteers Needed!
Do you have just 2 hours per week to volunteer? You can join us in person or online!
What’s in it for you?
A certificate of participation.
An allowance to support your transport or internet needs.
What will you do?
Tutoring and Mentorship: Support students in public schools across Addis Ababa.
Educational Material Preparation: Create engaging and effective study materials online.
We’re looking for 2,000+ volunteers to make a real difference in education!
To apply fill out this form:https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScdxzxUL65oVGsuZUhnDVYkO44L49PmO7uZ1bu3HCvb6_-YAQ/viewform?usp=pp_url&entry.1131561500=kalkida _wegene
Deadline to apply: Tuesday, December 3, 2024.
የ በጎ አድራጎት ሥራ መስራት ለምትፈልጉ ሁሉ ነዉ apply በማድረግ መስራት ይምችሉትን ሞክሩ..... Certificate ም አለው ተጠቀሙበት
Join us and help shape the future of students!
Do you have just 2 hours per week to volunteer? You can join us in person or online!
What’s in it for you?
A certificate of participation.
An allowance to support your transport or internet needs.
What will you do?
Tutoring and Mentorship: Support students in public schools across Addis Ababa.
Educational Material Preparation: Create engaging and effective study materials online.
We’re looking for 2,000+ volunteers to make a real difference in education!
To apply fill out this form:https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScdxzxUL65oVGsuZUhnDVYkO44L49PmO7uZ1bu3HCvb6_-YAQ/viewform?usp=pp_url&entry.1131561500=kalkida _wegene
Deadline to apply: Tuesday, December 3, 2024.
የ በጎ አድራጎት ሥራ መስራት ለምትፈልጉ ሁሉ ነዉ apply በማድረግ መስራት ይምችሉትን ሞክሩ..... Certificate ም አለው ተጠቀሙበት
Join us and help shape the future of students!
Google Docs
Kelem Tutors Volunteer Program Application Form
Be Part of Our Volunteer Tutoring Program for over 2000 volunteers and Make a Difference!
Do you care about education and want to make a positive impact in your community? Join our one-month volunteer program and help us create a brighter future for students…
Do you care about education and want to make a positive impact in your community? Join our one-month volunteer program and help us create a brighter future for students…
እየዉልሽ ዓለሜ በዘመኔ ያስተዋልኩት ፍቅር ሁለት አይነት መልክ አለዉ፨አንዱ በግዴታም ይሁን በዉዴታ ሲገጥምሽ ራስሽ የምታበጃጅዉ ፍቅር ነዉ፨ሌላው ደግሞ ነፋስ የሚያመጣዉ ፍቅር ነዉ፨አሏት እማማ በምሽቱ መሃል እሳት ዳር ተቀምጠዉ እያወሩ..
ነፋስ..?
አዎ ንፋስ ..!
መነሻዉን መምጫዉን ሳታዉቂዉ ድንገት ከልብሽ ኖሮ ታገኝዋለሽ፨ያዉ ራሱ ያበጃጅሻል፨
ቆይ የትኛዉ ይበልጣል?
እኔ የማዉቀዉ ያበጀሁትን ነዉ፨ያዉ እስከዚ እድሜያችን ድረስ እንደተዋደድን እንደተፋቀርን አለን፨ሰዉ ያላየዉን እንዲህ ነዉ አይልም፨ብቻ ፍቅር ያዉ ፍቅር ነዉ፨ምን ለዉጥ አለዉ ብለሽ ነዉ ዓለሜ፨
እኔ እንጃ...ግን ወደ ልብ ከሚመጣ ይልቅ ልብ ዉስጥ ያለ የሚበልጥ ይመስለኛል፨እንጃ..🩵
#ዘመኔ
https://t.me/yeesua_queen
ነፋስ..?
አዎ ንፋስ ..!
መነሻዉን መምጫዉን ሳታዉቂዉ ድንገት ከልብሽ ኖሮ ታገኝዋለሽ፨ያዉ ራሱ ያበጃጅሻል፨
ቆይ የትኛዉ ይበልጣል?
እኔ የማዉቀዉ ያበጀሁትን ነዉ፨ያዉ እስከዚ እድሜያችን ድረስ እንደተዋደድን እንደተፋቀርን አለን፨ሰዉ ያላየዉን እንዲህ ነዉ አይልም፨ብቻ ፍቅር ያዉ ፍቅር ነዉ፨ምን ለዉጥ አለዉ ብለሽ ነዉ ዓለሜ፨
እኔ እንጃ...ግን ወደ ልብ ከሚመጣ ይልቅ ልብ ዉስጥ ያለ የሚበልጥ ይመስለኛል፨እንጃ..🩵
#ዘመኔ
https://t.me/yeesua_queen
❤4👍1
🔥4😭2
..."ለምን እንደሆነ ባላውቅም አለመፈለጋችን ላይ ትኩረት እንደምናበዛ" አለችኝ ራሷን እየታዘበች መሆኑ ነው። "ማለት እስኪ ግልፅ አድርጊልኝ" አልኳት።...
ሁላችንም ትኩረት ፈላጊዎች ነን ከሚወዱን ከሚፈልጉን ሠዎች ይልቅ ከተውን ከራቁን ጥቂት ሠዎች ላይ ትኩረት እንሰጣለን...እስከሞት ከወደደህ ፈጣሪ አብዝታ ከምትወድህ እናት በላይ በጣም ከሚወዱህ ቤተሰቦችህ ጓደኞችህ በላይ ለሆነ ሠሞን ያወከው አንድ ሠው ትንሽ ገሸሽ ሲያደርግህ ልብህ በሀዘን ይጎዳል" ።...
ሁላችንም ትኩረት ፈላጊዎች ነን ከሚወዱን ከሚፈልጉን ሠዎች ይልቅ ከተውን ከራቁን ጥቂት ሠዎች ላይ ትኩረት እንሰጣለን...እስከሞት ከወደደህ ፈጣሪ አብዝታ ከምትወድህ እናት በላይ በጣም ከሚወዱህ ቤተሰቦችህ ጓደኞችህ በላይ ለሆነ ሠሞን ያወከው አንድ ሠው ትንሽ ገሸሽ ሲያደርግህ ልብህ በሀዘን ይጎዳል" ።...
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
እህቴ ትክክለኛ የፍቅር ግንኙነት ውስጥ መሆንሽን ማረጋገጥ ከፈለግሽ እነዚህን ነገሮች ከፍቅረኛሽ ዘንድ መኖሩን አረጋግጪ👆👆👆
🔥3
✨ስንቱን አስታወስኩት ስንቱን አየሁት
ልቤን በትዝታ ወዲያ እየላኩት
የትናንቱ ፍቅር ጣዕሙ ቁም ነገሩ...
...ጣዕሙ ቁም ነገሩ...
ምነዉ ሙዚቃዉ ሃዘኔን አባባሰዉ፨
የናፈቅሽዉ ሰዉ አለ የኔ ልጅ?
አይ..እንደዉ ዉዚቃዉ ሆድ አስብሶኝ ነዉ፨
እሳት በሌለበት ጭስ አይጨስም፨ዉስጥ የሌለም አይብስም፨የምንወዳቸዉን ሰዎች ስንናፍቅ ዓለምን በሙሉ እንናፍቃለን፨ምክንያቱም የእኛ ዓለም በምንወደዉ ሰዉ ዉስጥ ነዉ ያለዉ፨
እንደርሱ አይደለም እናቴ....እንደዉ ትዝታ ዉስጥ ገብቼ ነዉ፨
አይይይ...ሰዎች በትዝታ መኖር ከጀመሩ ወይ እንደ እኔ አርጅተዋል አልያም ባሉበት ቆመዋል ማለት ነዉ፨አርጅተሻል እንዴ...?
መሰለኝ 😊
እየዉልሽ የኔ ልጅ በዚች ምድር ላይ ሁለት ነገሮች አይጣጣሙም፨ፍቅርና ሕግ!!አንዱ አንዱን ያፈርሰዋል፨ለማጣጣም አትሞክሪ ጥሰቱን ኑሪዉ🖤
#ስንብት
https://t.me/yeesua_queen
ልቤን በትዝታ ወዲያ እየላኩት
የትናንቱ ፍቅር ጣዕሙ ቁም ነገሩ...
...ጣዕሙ ቁም ነገሩ...
ምነዉ ሙዚቃዉ ሃዘኔን አባባሰዉ፨
የናፈቅሽዉ ሰዉ አለ የኔ ልጅ?
አይ..እንደዉ ዉዚቃዉ ሆድ አስብሶኝ ነዉ፨
እሳት በሌለበት ጭስ አይጨስም፨ዉስጥ የሌለም አይብስም፨የምንወዳቸዉን ሰዎች ስንናፍቅ ዓለምን በሙሉ እንናፍቃለን፨ምክንያቱም የእኛ ዓለም በምንወደዉ ሰዉ ዉስጥ ነዉ ያለዉ፨
እንደርሱ አይደለም እናቴ....እንደዉ ትዝታ ዉስጥ ገብቼ ነዉ፨
አይይይ...ሰዎች በትዝታ መኖር ከጀመሩ ወይ እንደ እኔ አርጅተዋል አልያም ባሉበት ቆመዋል ማለት ነዉ፨አርጅተሻል እንዴ...?
መሰለኝ 😊
እየዉልሽ የኔ ልጅ በዚች ምድር ላይ ሁለት ነገሮች አይጣጣሙም፨ፍቅርና ሕግ!!አንዱ አንዱን ያፈርሰዋል፨ለማጣጣም አትሞክሪ ጥሰቱን ኑሪዉ🖤
#ስንብት
https://t.me/yeesua_queen
Telegram
💙..ነጠብጣብ ✨🧩
✨ትዝታማ አለሽ
የለኝም ብትይኝ እኔም አላምንሽም
በህይወት መንገድ ላይ
ተራምደሽ ሳታልፊ ዛሬ ላይ አልቆምሽም፨
ህይወት ያለ ታሪክ
ቀን ያለ ጨለማ መች ቶሎ ይመሻል
ሰዉ ስለሆንሽ ብቻ
ለሰዉ ምታወጊዉ ቅፅበት ይኖርሻል፨
ትዝታ አለሽ?አዉጊኝ
ትዝታ አለኝ!ላዉጋሽ
..እንዲህ ብናወራስ...ቅፅበታት እናዉጋ.. የልብ ንግግሮችም አይታጡም..ግቡ💙
ለአስተያየታችሁ @AnchinayehuGebrie
የለኝም ብትይኝ እኔም አላምንሽም
በህይወት መንገድ ላይ
ተራምደሽ ሳታልፊ ዛሬ ላይ አልቆምሽም፨
ህይወት ያለ ታሪክ
ቀን ያለ ጨለማ መች ቶሎ ይመሻል
ሰዉ ስለሆንሽ ብቻ
ለሰዉ ምታወጊዉ ቅፅበት ይኖርሻል፨
ትዝታ አለሽ?አዉጊኝ
ትዝታ አለኝ!ላዉጋሽ
..እንዲህ ብናወራስ...ቅፅበታት እናዉጋ.. የልብ ንግግሮችም አይታጡም..ግቡ💙
ለአስተያየታችሁ @AnchinayehuGebrie
❤1🔥1
* የራስሽን ኮከብ ፈልጊ! *
አፍሪካውያን የሌላውን ሰው ኮከብ ተጠቅመህ አትነሳ የሚል አባላል አላቸው። ይህም ማለት አንድ ሰው አንድን ነገር ሲሰራ ስለተሳካለት አንቺም ተመሳሳይ ነገር በማድረግ ወይም በመስራት ስኬታማ ትሆኛለሽ ማለት አይደለም።
ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ ፍላጎት፣ አቅም እና ህልም አለው። ሰው ማሳካት ያለበት የራሱን ህልም እንጂ የሌለውን አይደለም።
እናም ወዳጄ ሆይ የራስሽን ህልም ፈልጊው፣ … እናም ኑሪው!
ያሬድ ነኝ ከዱባይ
ስኬታማ እና የተባረከ ቀን ይሁንልሽ😘🥇!
አፍሪካውያን የሌላውን ሰው ኮከብ ተጠቅመህ አትነሳ የሚል አባላል አላቸው። ይህም ማለት አንድ ሰው አንድን ነገር ሲሰራ ስለተሳካለት አንቺም ተመሳሳይ ነገር በማድረግ ወይም በመስራት ስኬታማ ትሆኛለሽ ማለት አይደለም።
ሁሉም ሰው የራሱ የሆነ ፍላጎት፣ አቅም እና ህልም አለው። ሰው ማሳካት ያለበት የራሱን ህልም እንጂ የሌለውን አይደለም።
እናም ወዳጄ ሆይ የራስሽን ህልም ፈልጊው፣ … እናም ኑሪው!
ያሬድ ነኝ ከዱባይ
ስኬታማ እና የተባረከ ቀን ይሁንልሽ😘🥇!
❤3
የ እኔ ፡ ውብ
ከሁሉም ፡ ይልቅ ፡ ልብሽን ፡ ማውጋትሽን ፡ ስሜትሽን ፡ ሃሳብሽን ፡ መሰተርሽን ፡ አስቀድሜ ……
አትሞኚ ፡ አትቸኩዬ ፡ እንዲች ፡ ብለሽ ፡ በጥድፍያ ፡ ውስጥ ፡ ህይወትሽን ፡ እንዳትግዬ ……
ይልቅ ፡ መለስ ፡ በይ ፡ ይልቅ ፡ አረፍ ፡ ብይ ፡ ይልቅ ፡ መስኮትሽን ፡ ክፈቺ ፡ ብዕርሽን ፡ አንሺ ፡ ልብሽን ፡ ነብስሽን ፡ ደግፊ ፡ ከጥድፍያሽ ፡ ሩጠሽ ፡ አምልጪ ………
ረጋ ፡ በይ ፡ ሁሉን ፡ በአቅሙ ፡ ለኪ ፡ መጥኒ ፡ ስፈሪ ፡ የልብሽን ፡ ሸክም ፡ አቅልዬ ………🧚♂
ከሁሉም ፡ ይልቅ ፡ ልብሽን ፡ ማውጋትሽን ፡ ስሜትሽን ፡ ሃሳብሽን ፡ መሰተርሽን ፡ አስቀድሜ ……
አትሞኚ ፡ አትቸኩዬ ፡ እንዲች ፡ ብለሽ ፡ በጥድፍያ ፡ ውስጥ ፡ ህይወትሽን ፡ እንዳትግዬ ……
ይልቅ ፡ መለስ ፡ በይ ፡ ይልቅ ፡ አረፍ ፡ ብይ ፡ ይልቅ ፡ መስኮትሽን ፡ ክፈቺ ፡ ብዕርሽን ፡ አንሺ ፡ ልብሽን ፡ ነብስሽን ፡ ደግፊ ፡ ከጥድፍያሽ ፡ ሩጠሽ ፡ አምልጪ ………
ረጋ ፡ በይ ፡ ሁሉን ፡ በአቅሙ ፡ ለኪ ፡ መጥኒ ፡ ስፈሪ ፡ የልብሽን ፡ ሸክም ፡ አቅልዬ ………🧚♂
🔥3❤1
ከንቱ ኩራትን ምን አመጣው?
ሟች መሆንሽ ተረሳ?
ምክንያትሽ ምንድን ነው?
ሰው ነሽና ሰው የማይረዳው ምክንያት አታጪም::
የምድር ህይወት መሰቃየት ነው::
የልጅነት የዋነት ተሰርቀሻል::
የአምላክ ፍቅርን ክደሽ በቁስ ፍቅር ተጠምቀሻል::
ባርነት ነው::ነፍስን አጥቶ አለምን ማግኘት ታላቅ ክስረት ነው::
ፊትሽ ይስቃል::አለባበስሽ ያንፀባርቃል::
ሰው ሁሉ አንቺን መሆን ሲመኝ ያአንቺ ውስጥ ግን ሞትን ይመኛል::
ምንድን ነው ግን ህይወት?
ምንድን ነው ግን የመኖር መጨረሻው?
ሞት?
ሞት አለ::
ሁሉን በዜሮ ያበዛል::
ከአፈር ጋር ይደምራል::
ታዲያ በምድር ቁስ መሰብሰቡ ሞትን ካላሸነፈ ምን ይሰራል?
ሞትን የሚያሸንፍ አንድ ነገር የነፍስሽ መንቃት ነው::
ነፍስ ስጋዊ ምኞትን ጥሳ መንፈሳዊ ውበቷን ስታገኝ የህይወት ብርሃን ወደ ህይወትሽ ይፈሳል::
ማንም የማያውቃቸው ልባዊ ህመሞች : በር ዘግተሽ ያፈሰስሻቸው እንባዎች ትክክለኛ መድህኒት ያገኛሉ::
ለምን እኖራለው? የሚለው አሰልቺ ጥያቄ አምላክን ስታገኚ ይቆማል::
ከንቱ የሆነው ህይወትሽ በአምላክሽ ብርሃን ትርጉም ያገኛል::
የፈጠረሽ አምላክ ባንቺ በኩል ወደ አለም ይመጣል::
ለሀሳብሽ ብርሃን ..ለስራሽ መንፈሳዊ ሐይል ..እና ..ለስኬትሽ በረከት ይችራል::
አላማሽ አላማውሲሆን
በትንሿ ልጁ ትልቁ አምላክ ይከብራል::
የመዳኛሽ ሰዓቱ አሁን ነው::
አንቺ ሺ ጊዜ ብታጠፊ እሱ ቢሊዬን ጊዜ ይረዳሻል::
ቢሊዬን ጊዜ ብትሳሳቺ ደግሞ ለዓለመ ዓለም ይጠብቅሻል::
ለከንቱ አለም ብለሽ ህያው አምላክሽን አታስጠብቂው::
አሁን ልብሽን ወደ አምላክሽ አድርጊ::
አሁን ወስኚ.........
አለም ይሻልሻል ወይስ አምላክ?
ሟች መሆንሽ ተረሳ?
ምክንያትሽ ምንድን ነው?
ሰው ነሽና ሰው የማይረዳው ምክንያት አታጪም::
የምድር ህይወት መሰቃየት ነው::
የልጅነት የዋነት ተሰርቀሻል::
የአምላክ ፍቅርን ክደሽ በቁስ ፍቅር ተጠምቀሻል::
ባርነት ነው::ነፍስን አጥቶ አለምን ማግኘት ታላቅ ክስረት ነው::
ፊትሽ ይስቃል::አለባበስሽ ያንፀባርቃል::
ሰው ሁሉ አንቺን መሆን ሲመኝ ያአንቺ ውስጥ ግን ሞትን ይመኛል::
ምንድን ነው ግን ህይወት?
ምንድን ነው ግን የመኖር መጨረሻው?
ሞት?
ሞት አለ::
ሁሉን በዜሮ ያበዛል::
ከአፈር ጋር ይደምራል::
ታዲያ በምድር ቁስ መሰብሰቡ ሞትን ካላሸነፈ ምን ይሰራል?
ሞትን የሚያሸንፍ አንድ ነገር የነፍስሽ መንቃት ነው::
ነፍስ ስጋዊ ምኞትን ጥሳ መንፈሳዊ ውበቷን ስታገኝ የህይወት ብርሃን ወደ ህይወትሽ ይፈሳል::
ማንም የማያውቃቸው ልባዊ ህመሞች : በር ዘግተሽ ያፈሰስሻቸው እንባዎች ትክክለኛ መድህኒት ያገኛሉ::
ለምን እኖራለው? የሚለው አሰልቺ ጥያቄ አምላክን ስታገኚ ይቆማል::
ከንቱ የሆነው ህይወትሽ በአምላክሽ ብርሃን ትርጉም ያገኛል::
የፈጠረሽ አምላክ ባንቺ በኩል ወደ አለም ይመጣል::
ለሀሳብሽ ብርሃን ..ለስራሽ መንፈሳዊ ሐይል ..እና ..ለስኬትሽ በረከት ይችራል::
አላማሽ አላማውሲሆን
በትንሿ ልጁ ትልቁ አምላክ ይከብራል::
የመዳኛሽ ሰዓቱ አሁን ነው::
አንቺ ሺ ጊዜ ብታጠፊ እሱ ቢሊዬን ጊዜ ይረዳሻል::
ቢሊዬን ጊዜ ብትሳሳቺ ደግሞ ለዓለመ ዓለም ይጠብቅሻል::
ለከንቱ አለም ብለሽ ህያው አምላክሽን አታስጠብቂው::
አሁን ልብሽን ወደ አምላክሽ አድርጊ::
አሁን ወስኚ.........
አለም ይሻልሻል ወይስ አምላክ?
❤2❤🔥2👍1