ኮርፖሬሽኑ የበዓል ስጦታ አበረከተ
ኮርፖሬሽኑ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ እና በክልል ቅርንጫፍ ለሚገኙ 574 የኮርፖሬሽኑ ሰራተኞች በዓይነትና በገንዘብ የተዘጋጀ የበዓል ስጦታ ሚያዚያ 03/ 2018 ዓ.ም አበረከተ፡፡
በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በተካሄደው ስጦታ የማበርከት ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉትና ሥጦታውን ያበረከቱት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ ስጦታው የተዘጋጀው ዝቅተኛ ክፍያ ያላቸውን ሰራተኞች ከነቤተሰቦቻቸው መልካም በዓል ለማለት እና ለእነርሱ ያለንን አክብሮትና ፍቅር ለመግለጽ ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም ኮርፖሬሽኑን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የእነርሱ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ተጋግዘን ለጋራ ዓላማ መስራት ይገባናል በማለት የሥራ ትጋታቸውን እንዳያቋርጡ አሳስበዋል፡፡
በዋናው መ/ቤት ከተለያዩ ዘርፎች ለተውጣጡና በቢሮ ውበትና በጽሕፈት ሥራ ረዳትነት እያገለገሉ ላሉ 50 ሰራተኞች ለእያንዳንዳቸው ሶስት ሊትር የምግብ ዘይት፣ አምስት ኪሎ የስንዴ ዱቄት እና ሁለት ሺህ ብር የተበረከተ ሲሆን በአዲስ አበባና በክልል ለሚገኙ 524 የቢሮ ደህንነት፣ የቢሮ ውበትና ጽሕፈት ሥራ ረዳት ሰራተኞች ደግሞ ለእያንዳንዳቸው የሶስት ሺህ ብር ስጦታ ተበርክቶላቸዋል፡፡
ኮርፖሬሽኑ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ እና በክልል ቅርንጫፍ ለሚገኙ 574 የኮርፖሬሽኑ ሰራተኞች በዓይነትና በገንዘብ የተዘጋጀ የበዓል ስጦታ ሚያዚያ 03/ 2018 ዓ.ም አበረከተ፡፡
በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በተካሄደው ስጦታ የማበርከት ሥነ ሥርዓት ላይ ተገኝተው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉትና ሥጦታውን ያበረከቱት የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በኃይሉ ንጉሴ ስጦታው የተዘጋጀው ዝቅተኛ ክፍያ ያላቸውን ሰራተኞች ከነቤተሰቦቻቸው መልካም በዓል ለማለት እና ለእነርሱ ያለንን አክብሮትና ፍቅር ለመግለጽ ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም ኮርፖሬሽኑን የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ የእነርሱ ሚና ከፍተኛ በመሆኑ ተጋግዘን ለጋራ ዓላማ መስራት ይገባናል በማለት የሥራ ትጋታቸውን እንዳያቋርጡ አሳስበዋል፡፡
በዋናው መ/ቤት ከተለያዩ ዘርፎች ለተውጣጡና በቢሮ ውበትና በጽሕፈት ሥራ ረዳትነት እያገለገሉ ላሉ 50 ሰራተኞች ለእያንዳንዳቸው ሶስት ሊትር የምግብ ዘይት፣ አምስት ኪሎ የስንዴ ዱቄት እና ሁለት ሺህ ብር የተበረከተ ሲሆን በአዲስ አበባና በክልል ለሚገኙ 524 የቢሮ ደህንነት፣ የቢሮ ውበትና ጽሕፈት ሥራ ረዳት ሰራተኞች ደግሞ ለእያንዳንዳቸው የሶስት ሺህ ብር ስጦታ ተበርክቶላቸዋል፡፡