Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
11.4K subscribers
5.02K photos
76 videos
20 files
856 links
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
Download Telegram
ታሕሣሥ 28፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 6፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم

#የአፋር እስልምናን ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በአክሱም ሙስሊም ማኀበረሰብ ላይ የሚፈጸመውን የእምነትና የሰብአዊ ጥሰት በፅናት እናቃወማለን ሲል መግለጫ አወጣ የመግለጫው ሙሉ ቃል ከላይ ይመልከቱ።
ታሕሣሥ 30፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 10፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
በእቅድ ዝግጅት እና ሪፖርት አቀራረብ የተሰጠው ስልጠና ተጠናቀቀ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

አዲስ አበባ |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቋማዊ አሰራሩን ለማዘመን የሚያደርገው ጥረት እንዲሳካ የሰራተኛውን አቅም የሚያጎለብቱ የተለያዩ ሰልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል።

የዚሁ አካል የሆነውና ትኩረቱን በዕቅድ ዝግጅትና ሪፖርት አቀራረብ ዙሪያ አድርጎ ለሶስት ተከታታይ ቀናት
በኢትዬጵያ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት የስትራቴጅክ ማኔጅመንት የሰው ሀብት ስራ አስፈፃሚና የስልጠና ባለሙያ በሆኑት አቶ አብዱልኻሊቅ ረሺድ ሲሰጥ የቆየው ስልጠና በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።

ስልጠናውን በስኬት ላጠናቀቁ የተቋሙ የዘርፍ ሀላፊዎች፣ ዳይሬክቶሬቶችና የየክልሎች የመጅሊስ የስራ ሀላፊዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል።

የምስክር ወረቀቱን ለሰልጣኞች ያበረከቱት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ሥራ አሰኪያጅ ሀጂ ከማል ሀሩን በጠቅላይ ምክር ቤቱና በተዋረድ ባሉ አደረጃጀቶች ያለውን አሰራር ተቋማዊና ዘመናዊ ለማድረግ የአቅም ግንባታ ሥልጠና ትልቅ መሳሪያ ነው ብለዋል።

ዋና ስራ አስኪያጁ አክለውም ሰልጣኞች ከስልጠናው የቀሰሙትን እውቀትና ክህሎት በአግባቡ ተግባራዊ በማድረግና ሌሎችን በማሰልጠን ለተቋማዊ ግንባታው ስኬት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ሊወጡ ይገባልም ብለዋል።