ታሕሣሥ 26፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 3፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم
አዲስ አበባ |
ፕሬዚደንቱ ሕዝበ ሙስሊሙ ለትምህርት ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጥ አሳሰቡ
"ልጆቻችንን አላስተማርንም፤ አሁን ያገኘነውን ዕድል ተጠቅመን ጠንክረን በቁጭት ልንጠቀምበት ይገባል!" ሲሉ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ተናገሩ።
ፕሬዚደንቱ ይህን የተናገሩት፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትምህርት ተሳትፎ" በሚል ርዕስ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው።
የክብር ዶክተር ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር በኢትዮጵያ ከትምህርት አጀማመር ታሪክ አንስቶ ሙስሊሞች መዋቅራዊ በኾነ መልኩ ከትምህርቱ ዓለም የተገለሉ እንደነበረ አስታውሰዋል።
"ሴት ልጆቻችን ዲናቸውን እንደጠበቁ ይማራሉ፤ ሕግና ሕግን መሠረት አድርገን ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ሕጋዊ መፍትኄ እንዲያገኙ የሚመለከታቸውን አካላት በሮች እያንኳኳን ነው" ብለዋል።
ፕሬዚደንቱ አያይዘውም መስሊሞች የሁሉም ነገር መነሻ እውቀት መሆኑን ሳይዘነጉ፣ ያገኙትን ዕድል ተጠቅመው በቁጭት ልጆቻቸውን ሊያስተምሩ ይገባል" ብለዋል።
የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ኢንጂነር አንዋር ሙስጠፋ፣ ትምህርት ማኅበረሰባዊም ሆነ ሀገራዊ ፈይዳው የላቀ እንደኾነ ጠቅሰው፣ ዳይሬክቶሬቱ የትምህርት ዘርፍ መመሪያ አጸድቆ እየሠራ መሆኑን እና የዛሬው የምክክር መድረክ የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ ላይ ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል።
"የትምህርት ምንነት እና ትምህርት ለሀገር ዕድገት ያለው ፋይዳ" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረቡት አቶ ባህሩ ሽኩር፣ 'የትምህርት ምንነትን'፣ 'የትምህርት ታሪካዊ እድገት'ን፣ 'የትምህርት አይነቶች'ን እና 'ትምህርት ያለውን ፋይዳ' በጽሑፋቸው ዳስሰዋል።
በትምህርት ዙሪያ የረጅም ጊዜ ተሳትፎ ያላቸውና በእስላማዊ የምርምር ማዕከል የቦርድ አባል የሆኑት ኢንጅነር ቢንመሊክ አብዶ "ትምህርት በእስልምና ዕይታ" በሚል ርዕስ ትምህርትና ዕወቀት በእስልምና ያለውን ቦታ የተመለከተ ጽንሰ ሐሳባዊ ማብራሪያ አቅርበዋል።
የመድረኩ አወያይ ወይዘሮ ዘቢባ መልኪ የፓናል ውይይት ተሳታፊዎች በቡድን ተከፍለው በቀረቡላቸው ጥያቄዎች ላይ ተወያይተው ለቀጣዩ ቀን ሪፖርት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
መድረኩ ነገ እሑድ ሕዳር 27/2017 በሀገራችን የሕዝበ ሙስሊሙ የትምህርት ተሳትፎ በምን ደረጃ ላይ ነው? በሚለው እና መሰል የመወያያ ሪፖርቶችን በመስማት እንደሚቀጥል ተነግሯል።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيم
አዲስ አበባ |
ፕሬዚደንቱ ሕዝበ ሙስሊሙ ለትምህርት ከፍተኛ ትኩረት እንዲሰጥ አሳሰቡ
"ልጆቻችንን አላስተማርንም፤ አሁን ያገኘነውን ዕድል ተጠቅመን ጠንክረን በቁጭት ልንጠቀምበት ይገባል!" ሲሉ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት ተናገሩ።
ፕሬዚደንቱ ይህን የተናገሩት፣ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትምህርት ተሳትፎ" በሚል ርዕስ ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው።
የክብር ዶክተር ሼይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር በኢትዮጵያ ከትምህርት አጀማመር ታሪክ አንስቶ ሙስሊሞች መዋቅራዊ በኾነ መልኩ ከትምህርቱ ዓለም የተገለሉ እንደነበረ አስታውሰዋል።
"ሴት ልጆቻችን ዲናቸውን እንደጠበቁ ይማራሉ፤ ሕግና ሕግን መሠረት አድርገን ሕገ-ወጥ ድርጊቶች ሕጋዊ መፍትኄ እንዲያገኙ የሚመለከታቸውን አካላት በሮች እያንኳኳን ነው" ብለዋል።
ፕሬዚደንቱ አያይዘውም መስሊሞች የሁሉም ነገር መነሻ እውቀት መሆኑን ሳይዘነጉ፣ ያገኙትን ዕድል ተጠቅመው በቁጭት ልጆቻቸውን ሊያስተምሩ ይገባል" ብለዋል።
የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል እና የትምህርትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ኢንጂነር አንዋር ሙስጠፋ፣ ትምህርት ማኅበረሰባዊም ሆነ ሀገራዊ ፈይዳው የላቀ እንደኾነ ጠቅሰው፣ ዳይሬክቶሬቱ የትምህርት ዘርፍ መመሪያ አጸድቆ እየሠራ መሆኑን እና የዛሬው የምክክር መድረክ የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።
ለሁለት ቀናት በሚቆየው በዚህ መድረክ ላይ ሁለት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት እየተደረገባቸው ይገኛል።
"የትምህርት ምንነት እና ትምህርት ለሀገር ዕድገት ያለው ፋይዳ" በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረቡት አቶ ባህሩ ሽኩር፣ 'የትምህርት ምንነትን'፣ 'የትምህርት ታሪካዊ እድገት'ን፣ 'የትምህርት አይነቶች'ን እና 'ትምህርት ያለውን ፋይዳ' በጽሑፋቸው ዳስሰዋል።
በትምህርት ዙሪያ የረጅም ጊዜ ተሳትፎ ያላቸውና በእስላማዊ የምርምር ማዕከል የቦርድ አባል የሆኑት ኢንጅነር ቢንመሊክ አብዶ "ትምህርት በእስልምና ዕይታ" በሚል ርዕስ ትምህርትና ዕወቀት በእስልምና ያለውን ቦታ የተመለከተ ጽንሰ ሐሳባዊ ማብራሪያ አቅርበዋል።
የመድረኩ አወያይ ወይዘሮ ዘቢባ መልኪ የፓናል ውይይት ተሳታፊዎች በቡድን ተከፍለው በቀረቡላቸው ጥያቄዎች ላይ ተወያይተው ለቀጣዩ ቀን ሪፖርት እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
መድረኩ ነገ እሑድ ሕዳር 27/2017 በሀገራችን የሕዝበ ሙስሊሙ የትምህርት ተሳትፎ በምን ደረጃ ላይ ነው? በሚለው እና መሰል የመወያያ ሪፖርቶችን በመስማት እንደሚቀጥል ተነግሯል።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Telegram
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
ታሕሣሥ 27፣ 2017 ዓ.ል | ረጀብ 5፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የሕዝበ ሙስሊሙ የዘመናዊ ትምህርት ተሳትፎ የሚገኝበት ደረጃ አሳሳቢ መኾኑ ተነገረ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የአገራችን ሕዝበ ሙስሊም የዘመናዊ ትምህርት ተሳትፎ የሚገኝበት ደረጃ አሳሳቢ መኾኑን አንድ የትምህርት ባለሙያ ተናገሩ።
የትምህርት ባለሙያው አብዱ አባ ጊቤ (ዶ/ር) ይህን የተናገሩት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትምህርት ተሳትፎ" በሚል ርዕስ ለሁለት ቀናት ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው።
በምክክር መድረኩ ላይ "የአገራችን ዘመናዊ ትምህርት ያለበት ደረጃ" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት
የትምህርትና የሥራ አመራር አማካሪው ዶ/ር አብዱ አባ ጊቤ
የአገራችን ትምህርት ሃይማኖታዊ፣ አገር በቀል እና ዘመናዊ ተብሎ እንደሚፈረጅ ጠቅሰው፣ "በአገራችን የሙስሊሙ ኅብረተሰብ የዘመናዊ ትምህርት ተሳትፎ በጥናት መታወቅ ይኖርበታል" ሲሉ ተናግረዋል።
የእስልምና እውቀት ሰፊ እና ሁለገብ እንደኾነ ያወሱት ጥናት አቅራቢው፣ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከስነ-ምግባራዊ ከፍታ ባሻገር የሳይንስ እውቀትና ቴክኖሎጂን በመማርና አቅሙን በማሳደግ ራሱን፣ ኅብረተሰቡን እና አገሩን መቀየር እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል።
በአገራችን በንጉሣዊው አገዛዝ ዘመን ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ዘመናዊ ትምህርት ተምሮ ለአገሩ በጎ አስተዋጽዖ እንዳያበረክት ስልታዊ ጫና ይደረግበት እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር አብዱ፣ በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የሃይማኖት እኩልነት በመረጋገጡ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ለትምህርት ዘርፉ ዕድገት የበኩሉን አስተዋጽዖ እንዲያበረክት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሮለታል ብለዋል።
ዶ/ር አብዱ ባቀረቡት ጥናት መነሻነት ከመድረኩ ተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲኾን፣ ጽሑፍ አቅራቢው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ሰጥተዋል።
የምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች "በአገራችን የሕዝበ ሙስሊሙ የትምህርት ተሳትፎ በምን ደረጃ ላይ ነው?" እና "ተሳትፎውን ከፍ ለማድረግ ቀጣዩ አቅጣጫ ምን ይሁን?" በሚሉ ርዕሶች ላይ በቡድኖች ተከፍለው ያደረጓቸውን ውይይቶች ውጤት በተወካዮቻቸው አማካይነት አቅርበዋል።
በምክክር መድረኩ መዝጊያ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ሥራ አሰኪያጅ ሐጂ ከማል ሀሩን ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር፣ ጠቅላይ ምክር ቤቱ እንደ ተቋም ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዐበይት ሥራዎች መስሊሙ ማኅበረሰብ በትምህርቱ ዘርፍ አገራዊ ሚናው ከፍ እንዲል የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ ጥረት ማድረግ መኾኑን ተናግረዋል።
"ባለፈው ሁነት ላይ ቁጭትና ለቅሶ አያስፈልግም። የግንዛቤ እጥረት፣ የክትትል ክፍተት እና የመደራጀት ማነስ ለትምህርት ትኩረት በመስጠት የሚለወጥ በመኾኑ፣ ክፍተቱን ለመሙላት ጠቅላይ ምክር ቤቱ ቀጣይና ተከታታይ ሥራዎችን ይሠራል" ብለዋል።
ዋና ሥራ አስኪያጁ አክለውም፣ የትምህርት ጉዳይ የጋራ ጉዳያችን በመኾኑ በዘርፉ ላይ ተጋግዘን የሙስሊሙን የትምህርት ተሳትፎ በማሳደግ ለፍሬ ለማብቃት መንገዱን ጀምረነዋል። ኑ አግዙን፤ በራችን ክፍት ነው" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የምክክር መድረኩ በመጨረሻም ባለ 12 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቅቋል።
የአቋም መግለጫውን ሙሉ ቃል ከዚህ በታች አያይዘናል።
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የሕዝበ ሙስሊሙ የዘመናዊ ትምህርት ተሳትፎ የሚገኝበት ደረጃ አሳሳቢ መኾኑ ተነገረ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የአገራችን ሕዝበ ሙስሊም የዘመናዊ ትምህርት ተሳትፎ የሚገኝበት ደረጃ አሳሳቢ መኾኑን አንድ የትምህርት ባለሙያ ተናገሩ።
የትምህርት ባለሙያው አብዱ አባ ጊቤ (ዶ/ር) ይህን የተናገሩት በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የትምህርትና ማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት "የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የትምህርት ተሳትፎ" በሚል ርዕስ ለሁለት ቀናት ባዘጋጀው የምክክር መድረክ ላይ ነው።
በምክክር መድረኩ ላይ "የአገራችን ዘመናዊ ትምህርት ያለበት ደረጃ" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት
የትምህርትና የሥራ አመራር አማካሪው ዶ/ር አብዱ አባ ጊቤ
የአገራችን ትምህርት ሃይማኖታዊ፣ አገር በቀል እና ዘመናዊ ተብሎ እንደሚፈረጅ ጠቅሰው፣ "በአገራችን የሙስሊሙ ኅብረተሰብ የዘመናዊ ትምህርት ተሳትፎ በጥናት መታወቅ ይኖርበታል" ሲሉ ተናግረዋል።
የእስልምና እውቀት ሰፊ እና ሁለገብ እንደኾነ ያወሱት ጥናት አቅራቢው፣ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ከስነ-ምግባራዊ ከፍታ ባሻገር የሳይንስ እውቀትና ቴክኖሎጂን በመማርና አቅሙን በማሳደግ ራሱን፣ ኅብረተሰቡን እና አገሩን መቀየር እንደሚጠበቅበት ተናግረዋል።
በአገራችን በንጉሣዊው አገዛዝ ዘመን ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ዘመናዊ ትምህርት ተምሮ ለአገሩ በጎ አስተዋጽዖ እንዳያበረክት ስልታዊ ጫና ይደረግበት እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር አብዱ፣ በኢፌዲሪ ሕገ መንግሥት የሃይማኖት እኩልነት በመረጋገጡ ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ለትምህርት ዘርፉ ዕድገት የበኩሉን አስተዋጽዖ እንዲያበረክት ምቹ ሁኔታ ተፈጥሮለታል ብለዋል።
ዶ/ር አብዱ ባቀረቡት ጥናት መነሻነት ከመድረኩ ተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲኾን፣ ጽሑፍ አቅራቢው ለጥያቄዎቹ ምላሽ ሰጥተዋል።
የምክክር መድረኩ ተሳታፊዎች "በአገራችን የሕዝበ ሙስሊሙ የትምህርት ተሳትፎ በምን ደረጃ ላይ ነው?" እና "ተሳትፎውን ከፍ ለማድረግ ቀጣዩ አቅጣጫ ምን ይሁን?" በሚሉ ርዕሶች ላይ በቡድኖች ተከፍለው ያደረጓቸውን ውይይቶች ውጤት በተወካዮቻቸው አማካይነት አቅርበዋል።
በምክክር መድረኩ መዝጊያ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ዋና ሥራ አሰኪያጅ ሐጂ ከማል ሀሩን ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር፣ ጠቅላይ ምክር ቤቱ እንደ ተቋም ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ዐበይት ሥራዎች መስሊሙ ማኅበረሰብ በትምህርቱ ዘርፍ አገራዊ ሚናው ከፍ እንዲል የአመለካከት ለውጥ እንዲመጣ ጥረት ማድረግ መኾኑን ተናግረዋል።
"ባለፈው ሁነት ላይ ቁጭትና ለቅሶ አያስፈልግም። የግንዛቤ እጥረት፣ የክትትል ክፍተት እና የመደራጀት ማነስ ለትምህርት ትኩረት በመስጠት የሚለወጥ በመኾኑ፣ ክፍተቱን ለመሙላት ጠቅላይ ምክር ቤቱ ቀጣይና ተከታታይ ሥራዎችን ይሠራል" ብለዋል።
ዋና ሥራ አስኪያጁ አክለውም፣ የትምህርት ጉዳይ የጋራ ጉዳያችን በመኾኑ በዘርፉ ላይ ተጋግዘን የሙስሊሙን የትምህርት ተሳትፎ በማሳደግ ለፍሬ ለማብቃት መንገዱን ጀምረነዋል። ኑ አግዙን፤ በራችን ክፍት ነው" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የምክክር መድረኩ በመጨረሻም ባለ 12 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቅቋል።
የአቋም መግለጫውን ሙሉ ቃል ከዚህ በታች አያይዘናል።