ታሕሣሥ 17፣ 2017 ዓ.ል | ጁማዱል ሳኒ 25፣1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የነጃሺ እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክት የሾሪንግ ቁፋሮና ግንባታን ለማስጀመር የውል ስምምነት ተፈራረሙ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአዲስ አበባ፣ አፍሪካ ሕብረት አቅራቢያ የሚያስገነባው የነጃሺ እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክትን ለማስጀመር የሾሪንግ ቁፋሮና ግንባታ ከሚያካሂደው ኩባንያ ጋር ዛሬ የውል ስምምነት ፈጸመ።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ የውል ስምምነት የፈፀመው ከአንከር ፋውንዴሽን ስፔሻላይዝድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ጋር ነው።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በኩል ዋና ሥራ አስኪያጁ ሐጂ ከማል ሐሩን፣ በአንከር ፋውንዴሽን ስፔሻላይዝድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በኩል ደግሞ የድርጅቱ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ተሾመ ፈርመዋል።
በዚህ የፕሮጀክቱ ምዕራፍ የሚካሄደው የሾሪንግ ቁፋሮና ግንባታ ሥራ የአፈር መናድንና በድንበር ላይ የሚገኙ ሕንጻዎችን መሠረት ከመናድ ለመከላከል ያለመ መኾኑን ከባለሙያዎች ገለጻ ለማወቅ ተችሏል።
የጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በተገኙበት በተካሄደው የፊርማ ስነ ሥርዓት ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልሃዲ ሙሐመድ ሥራውን የሚያካሂደውን ኩባንያ ለመምረጥ ስለተካሄደው ጨረታ ሂደት ገለጻ አድርገዋል።
የነጃሺ መስጂድና እስላማዊ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ዐብይ ኮሚቴ የወከላቸው የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት በመረጣ ሂደቱ ላይ የአሸናፊው ኩባንያ የሥራ አፈጸጸም ብቃትና አቅም እንደተመዘነ እና ኩባንያው ውሉ በተፈረመ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን በመጀመር በአፋጣኝ ሊያጠናቅቅ ከመግባባት ላይ መደረሱን ለፕሬዚደንቱ አስረድተዋል።
በዚህ ሥራ ዘርፍ ቀደምትና የረጅም ጊዜ የካበተ ልምድ ያለው የአንከር ፋውንዴሽን ስፔሻላይዝድ ኃላ/የተ/የግል ኩባንያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ተሾመ ኩባንያው የሕዝብ ሀብት የኾነውን የነጃሺ መስጂድና እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክትን የሾሪንግ ሥራ ለማካሄድ ዕድል በማግኘቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
ኩባንያቸው በውሉ መሠረት ሥራውን በታማኝነት እና በጥራት
ሠርቶ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እንደሚያስረክብም አቶ ኤርሚያስ ተናግረዋል።
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በዚሁ ጊዜ የንጉሥ ነጃሺ መስጂድ እና እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክት እንደ ሀገርም እንደ ሙስሊም ማኀበረሰብም ትልቅ ታሪክ በመኾኑ፣ "ኩባንያችሁ በዚህ ታሪካዊ ሥራ ላይ አሻራውን ለማሳረፍ በመብቃቱ እንኳን ደስ ያላችሁ" ብለዋል።
የዚህን ፕሮጀክት ስኬትና አገልግሎት ሕዝበ-ሙስሊሙ በጉጉት እንደሚጠብቀው የጠቀሱት ክቡር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ ኩባንያው ሥራውን በአጭር ጊዜና በጥራት ሠርቶ እንዲያጠናቅቅ ከእኛ የሚጠበቀውን ሁሉ እናደርጋለን ብለዋል።
•••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የነጃሺ እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክት የሾሪንግ ቁፋሮና ግንባታን ለማስጀመር የውል ስምምነት ተፈራረሙ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በአዲስ አበባ፣ አፍሪካ ሕብረት አቅራቢያ የሚያስገነባው የነጃሺ እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክትን ለማስጀመር የሾሪንግ ቁፋሮና ግንባታ ከሚያካሂደው ኩባንያ ጋር ዛሬ የውል ስምምነት ፈጸመ።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ የውል ስምምነት የፈፀመው ከአንከር ፋውንዴሽን ስፔሻላይዝድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት ጋር ነው።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በኩል ዋና ሥራ አስኪያጁ ሐጂ ከማል ሐሩን፣ በአንከር ፋውንዴሽን ስፔሻላይዝድ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ በኩል ደግሞ የድርጅቱ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ተሾመ ፈርመዋል።
በዚህ የፕሮጀክቱ ምዕራፍ የሚካሄደው የሾሪንግ ቁፋሮና ግንባታ ሥራ የአፈር መናድንና በድንበር ላይ የሚገኙ ሕንጻዎችን መሠረት ከመናድ ለመከላከል ያለመ መኾኑን ከባለሙያዎች ገለጻ ለማወቅ ተችሏል።
የጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በተገኙበት በተካሄደው የፊርማ ስነ ሥርዓት ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዱልሃዲ ሙሐመድ ሥራውን የሚያካሂደውን ኩባንያ ለመምረጥ ስለተካሄደው ጨረታ ሂደት ገለጻ አድርገዋል።
የነጃሺ መስጂድና እስላማዊ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ዐብይ ኮሚቴ የወከላቸው የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት በመረጣ ሂደቱ ላይ የአሸናፊው ኩባንያ የሥራ አፈጸጸም ብቃትና አቅም እንደተመዘነ እና ኩባንያው ውሉ በተፈረመ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሥራውን በመጀመር በአፋጣኝ ሊያጠናቅቅ ከመግባባት ላይ መደረሱን ለፕሬዚደንቱ አስረድተዋል።
በዚህ ሥራ ዘርፍ ቀደምትና የረጅም ጊዜ የካበተ ልምድ ያለው የአንከር ፋውንዴሽን ስፔሻላይዝድ ኃላ/የተ/የግል ኩባንያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤርሚያስ ተሾመ ኩባንያው የሕዝብ ሀብት የኾነውን የነጃሺ መስጂድና እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክትን የሾሪንግ ሥራ ለማካሄድ ዕድል በማግኘቱ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
ኩባንያቸው በውሉ መሠረት ሥራውን በታማኝነት እና በጥራት
ሠርቶ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እንደሚያስረክብም አቶ ኤርሚያስ ተናግረዋል።
የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዚደንት የክብር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በዚሁ ጊዜ የንጉሥ ነጃሺ መስጂድ እና እስላማዊ ማዕከል ፕሮጀክት እንደ ሀገርም እንደ ሙስሊም ማኀበረሰብም ትልቅ ታሪክ በመኾኑ፣ "ኩባንያችሁ በዚህ ታሪካዊ ሥራ ላይ አሻራውን ለማሳረፍ በመብቃቱ እንኳን ደስ ያላችሁ" ብለዋል።
የዚህን ፕሮጀክት ስኬትና አገልግሎት ሕዝበ-ሙስሊሙ በጉጉት እንደሚጠብቀው የጠቀሱት ክቡር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ ኩባንያው ሥራውን በአጭር ጊዜና በጥራት ሠርቶ እንዲያጠናቅቅ ከእኛ የሚጠበቀውን ሁሉ እናደርጋለን ብለዋል።
•••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1
Telegram
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
ታሕሣሥ 19፣ 2017 ዓ.ል | ጁማዱል ሳኒ 27፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ኸይራት የአካል ጉዳተኞች እስላማዊ ማኅበር ጉባዔውን አካሄደ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
ኸይራት የአካል ጉዳተኞች እስላማዊ ማኅበር 2ኛ መደበኛ ጉባዔውን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር አካሄደ።
በጠቅላይ ምክር ቤቱ አዳራሽ በተካሄደው ጉባዔ መክፈቻ ላይ የተገኙት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ የአካል ጉዳተኛ ኾነው በእስልምና ታሪክ ውስጥ ትልልቅ ቦታ የተሰጣቸው ሙስሊሞችን ታሪክ አውግተዋል።
ኸይራት የሙስሊም የአካል ጉዳተኞ ማኅበር ከተመሠረተ ጀምሮ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር ተቀራርቦ እየሠራ መሆኑን ሸይኽ ሐሚድ ተናግረዋል።
ሸይኽ ሐሚድ አክለውም ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለሁሉም ተደራሽ እና "ከፊሎቻችሁ ለከፊሉ ረዳቶች ናችሁ" የሚለው ቁርኣናዊ እሴት መገለጫም በመኾኑ፣ ተቋሙ በሚችለው አቅም ማኅበሩን ያግዛል ብለዋል።
በጉባዔው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አልዩ ሰዒድ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ወደ ሪፎሮም ከገባ ጀምሮ ሕዝበ-ሙስሊሙን አሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ መኾኑን ተናግረዋል።
በሀገራችን በሚሊዮን የሚቆጠሩ አካል ጉዳተኛ ሙስሊሞች መንፈሣዊ ሕይወታቸውና እስላማዊ አኗኗራቸው ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ ኸይራት የሙስሊም የአካል ጉዳተኞች ማኅበርን የመሰሉ ተቋማትን መደገፍና ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አቶ አልዩ ሰዒድ የሙስሊም አካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ችግር ለመቅረፍ የሁላችንም ድጋፍ እና የግንዛቤ ለውጥ ያስፈልጋል ሲሉ ጥሪ አድርገዋል።
የኸይራት የሙስሊም አካል ጉዳተኞች ማኀበር ፕሬዚደንት አቶ ሡልጣን ኢሰሙ፣ የማኅበሩን የሥራ አንቅስቃሴ ሪፖርት እና የ2017 እቅድ ለጉባዔተኛውና ለባለድርሻ አካላት አቅርበዋል።
አቶ ሡልጣን በሪፖርታቸው ማኀበሩ ሁሉንአቀፍ የአካል ጉዳተኞች ማኅበር እንደመሆኑ፣ የተለያዩ የአካል ጉዳተኞችን የሚወክል መሆኑን አስታውሰዋል።
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ስር የተቋቋመው ማኀበሩ 3 ሺህ 500 አባላት አሉት።
በኸይራት የአካል ጉዳተኞች እስላማዊ ማኀበር መደበኛ ጉባዔ ላይ የተሳተፉ የማኅበሩ አባላት በቀረበው ሪፖርትና እቅድ ዙርያ አስተያየትና ጥያቄዎች አቅርበዋል።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ በመዋቅሩ ውስጥ የአካል ጉዳተኛ ሙስሊሞችን ጉዳይ የሚከታተል ራሱን የቻለ ዳይሬክቶሬት ሊኖረው ይገባል የሚል ሐሳብም ከተሳታፊዎቹ በአጽንዖት ተነስቷል።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ኸይራት የአካል ጉዳተኞች እስላማዊ ማኅበር ጉባዔውን አካሄደ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
ኸይራት የአካል ጉዳተኞች እስላማዊ ማኅበር 2ኛ መደበኛ ጉባዔውን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር አካሄደ።
በጠቅላይ ምክር ቤቱ አዳራሽ በተካሄደው ጉባዔ መክፈቻ ላይ የተገኙት የጠቅላይ ምክር ቤቱ ዋና ፀሐፊ ሸይኽ ሐሚድ ሙሳ የአካል ጉዳተኛ ኾነው በእስልምና ታሪክ ውስጥ ትልልቅ ቦታ የተሰጣቸው ሙስሊሞችን ታሪክ አውግተዋል።
ኸይራት የሙስሊም የአካል ጉዳተኞ ማኅበር ከተመሠረተ ጀምሮ ከጠቅላይ ምክር ቤቱ ጋር ተቀራርቦ እየሠራ መሆኑን ሸይኽ ሐሚድ ተናግረዋል።
ሸይኽ ሐሚድ አክለውም ጠቅላይ ምክር ቤቱ ለሁሉም ተደራሽ እና "ከፊሎቻችሁ ለከፊሉ ረዳቶች ናችሁ" የሚለው ቁርኣናዊ እሴት መገለጫም በመኾኑ፣ ተቋሙ በሚችለው አቅም ማኅበሩን ያግዛል ብለዋል።
በጉባዔው ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የማኀበራዊ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አልዩ ሰዒድ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ወደ ሪፎሮም ከገባ ጀምሮ ሕዝበ-ሙስሊሙን አሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ ዘርፈ ብዙ ተግባራት እያከናወነ መኾኑን ተናግረዋል።
በሀገራችን በሚሊዮን የሚቆጠሩ አካል ጉዳተኛ ሙስሊሞች መንፈሣዊ ሕይወታቸውና እስላማዊ አኗኗራቸው ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ ኸይራት የሙስሊም የአካል ጉዳተኞች ማኅበርን የመሰሉ ተቋማትን መደገፍና ማጠናከር እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
አቶ አልዩ ሰዒድ የሙስሊም አካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ ችግር ለመቅረፍ የሁላችንም ድጋፍ እና የግንዛቤ ለውጥ ያስፈልጋል ሲሉ ጥሪ አድርገዋል።
የኸይራት የሙስሊም አካል ጉዳተኞች ማኀበር ፕሬዚደንት አቶ ሡልጣን ኢሰሙ፣ የማኅበሩን የሥራ አንቅስቃሴ ሪፖርት እና የ2017 እቅድ ለጉባዔተኛውና ለባለድርሻ አካላት አቅርበዋል።
አቶ ሡልጣን በሪፖርታቸው ማኀበሩ ሁሉንአቀፍ የአካል ጉዳተኞች ማኅበር እንደመሆኑ፣ የተለያዩ የአካል ጉዳተኞችን የሚወክል መሆኑን አስታውሰዋል።
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ስር የተቋቋመው ማኀበሩ 3 ሺህ 500 አባላት አሉት።
በኸይራት የአካል ጉዳተኞች እስላማዊ ማኀበር መደበኛ ጉባዔ ላይ የተሳተፉ የማኅበሩ አባላት በቀረበው ሪፖርትና እቅድ ዙርያ አስተያየትና ጥያቄዎች አቅርበዋል።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ በመዋቅሩ ውስጥ የአካል ጉዳተኛ ሙስሊሞችን ጉዳይ የሚከታተል ራሱን የቻለ ዳይሬክቶሬት ሊኖረው ይገባል የሚል ሐሳብም ከተሳታፊዎቹ በአጽንዖት ተነስቷል።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Telegram
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት
ታሕሣሥ 20፣ 2017 ዓ.ል | ጁማዱል ሳኒ 28፣ 1446 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ለሙስሊም ወጣት አመራሮች እና ሴቶች የስነ-ምግባር ሥልጠና ተሰጠ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
በወጣት አደረጃጀት ኃላፊነት ላይ ላሉ ወጣቶች፣ ሴቶች እና መምህራን በእስልምና ስነ-ምግባር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ።
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የወጣቶች ሊግ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ የአንድ ቀን ሥልጠና ላይ ሁለት የጥናት 'ማኑዋሎች' ቀርበዋል።
በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊዋ ዑስታዛ ፋጡማ ሑሴን ወጣቶችና ሴቶች በማኅበረሰብ ግንባታ ውስጥ ሰፊ ቁጥር ያላቸው እና ትልቅ ተስፋ የሚጣልባቸው መኾናቸውን ተናግረዋል።
ኃላፊዋ አክለውም በስነ-ምግር የታነፀ፣ ከሱስ የፀዳ እና ራዕይ ያለው ትውልድ ለማፍራት የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ከባለድርሻ አካት ጋር ሀሉ አብሮ ይሠራል ብለዋል።
ሥልጠናውን በንግግር የከፈቱት የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ አሰፈጻሚ አባል እና የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ አብዱልሐሚድ አሕመድ የወጣትነት ተልዕኮን ብርቱነት አስመልክተው ቁርኣንና ሐዲስን ዋቢ ያደረገ ምክራቸውን ለግሰዋል።
"ወጣትነታችሁን አላህን በማላቅ፣ የራሳችሁንና የወላጆችን ሐቅ በመወጣት፣ በታታሪነት እና በስነ-ምግባር ለመወጣት ጥረት ማድረግ ይጠበቅባችኋል ሲሉ አደራ ብለዋል።
በሥልጠናው መርኃግብር ላይ በእንግድነት የተገኙት የአገር አቀፉ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዚደንት ዑስታዝ ሐይደር ከድር አብዱልቃድር ወጣትነትን አስመልክቶ ከእስልምና አኳያ ሰፋ ያለ ትምህርታዊ ንግግር አቅርበዋል።
ሙስሊም ወጣቶች እንደ ማኅበረሰብም ሆነ እንደ አገር ሚናችን የጎላ እንዲሆን ኃላፊነትን ለመሸከም ራሳችንን ማዘጋጀት ይገባናል ብለዋል።
ወጣቶች በችግር ጊዜ በግንባር ቀደምነት ተሰልፈን ዋጋ እንደምንከፍለው ሁሉ በመዋቅሮችም ውስጥ በንቃትና በብቃት ኃላፊነት የመሸከም ሚናችንን የማላቅ፣ ተቋማችንን ከፍ የማድረግ እና የለውጥ ሠራዊት መሆን ይገባናል ሲሉ የሥልጠና ተሳታፊውን አነቃቅተዋል።
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ሙሐመድ አሕመድ በበኩሉ ሊጉ ከተመሠረተ ጀምሮ የከተማውን ወጣቶች በማደራጀትና በማንቃት ሰፊ ሥራ መሥራቱን ተናግሯል።
ወጣትነት ለትልቅ ኃላፊነት የሚታጩበት መሠረት በመሆኑ የከተማውን የወጣት ሊግ አመራር አቅም ለማሳደግ ይህን መሰል የስነ-ምግባር ሥልጠና ትልቅ ግብዓት የሚገኝበት መሆኑን ተናግረዋል።
በሥልጠናው ላይ በዶክተር ዱረቲ ቃሲም "የዘመኑ የወጣቶች ፈተና" በሚል ርዕስ ጽሑፍ የቀረበ ሲኾን፣ ወጣቶች ለሱስ ተጋላጭ የሚሆኑበት ገፊ ምክንያት፣ የባህሪ ለውጥ፣ የዕድገት ሂደት፣ ማኅበራዊና ስነ ልቦናዊ ጫና መሠረት ያደረጉ ሳይንሳዊ የግንዛቤ ማብራሪያዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በዑስታዝ አሕመድ ሙስጠፋ "ስነ-ምግባር በሁለቱ ዓለም፣ ለማኅበረሰባዊ ግንባታ - እስላማዊ ዕይታ" በሚል ርዕስ ስነ-ምግባር ለማኅበረሰብ ግንባታ ያለውን እሴት ከግለሰባዊ፣ ቤተሰባዊ እና ከሀገራዊ ኃላፊነት አኳያ አሳታፊ የሆነ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ከሱስ የፀዳ ትውልድ እና ጤናማ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ለወጣቶችና ለሴቶች ትኩረት በማድረግ መሰል ሥልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተነግሯል።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ለሙስሊም ወጣት አመራሮች እና ሴቶች የስነ-ምግባር ሥልጠና ተሰጠ።
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ |
በወጣት አደረጃጀት ኃላፊነት ላይ ላሉ ወጣቶች፣ ሴቶች እና መምህራን በእስልምና ስነ-ምግባር ላይ ያተኮረ ሥልጠና ተሰጠ።
በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ከአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የወጣቶች ሊግ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት በዚህ የአንድ ቀን ሥልጠና ላይ ሁለት የጥናት 'ማኑዋሎች' ቀርበዋል።
በሥልጠናው መክፈቻ ላይ የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ኃላፊዋ ዑስታዛ ፋጡማ ሑሴን ወጣቶችና ሴቶች በማኅበረሰብ ግንባታ ውስጥ ሰፊ ቁጥር ያላቸው እና ትልቅ ተስፋ የሚጣልባቸው መኾናቸውን ተናግረዋል።
ኃላፊዋ አክለውም በስነ-ምግር የታነፀ፣ ከሱስ የፀዳ እና ራዕይ ያለው ትውልድ ለማፍራት የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ከባለድርሻ አካት ጋር ሀሉ አብሮ ይሠራል ብለዋል።
ሥልጠናውን በንግግር የከፈቱት የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሥራ አሰፈጻሚ አባል እና የሴቶችና የወጣቶች ዘርፍ ተጠሪ ሸይኽ አብዱልሐሚድ አሕመድ የወጣትነት ተልዕኮን ብርቱነት አስመልክተው ቁርኣንና ሐዲስን ዋቢ ያደረገ ምክራቸውን ለግሰዋል።
"ወጣትነታችሁን አላህን በማላቅ፣ የራሳችሁንና የወላጆችን ሐቅ በመወጣት፣ በታታሪነት እና በስነ-ምግባር ለመወጣት ጥረት ማድረግ ይጠበቅባችኋል ሲሉ አደራ ብለዋል።
በሥልጠናው መርኃግብር ላይ በእንግድነት የተገኙት የአገር አቀፉ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዚደንት ዑስታዝ ሐይደር ከድር አብዱልቃድር ወጣትነትን አስመልክቶ ከእስልምና አኳያ ሰፋ ያለ ትምህርታዊ ንግግር አቅርበዋል።
ሙስሊም ወጣቶች እንደ ማኅበረሰብም ሆነ እንደ አገር ሚናችን የጎላ እንዲሆን ኃላፊነትን ለመሸከም ራሳችንን ማዘጋጀት ይገባናል ብለዋል።
ወጣቶች በችግር ጊዜ በግንባር ቀደምነት ተሰልፈን ዋጋ እንደምንከፍለው ሁሉ በመዋቅሮችም ውስጥ በንቃትና በብቃት ኃላፊነት የመሸከም ሚናችንን የማላቅ፣ ተቋማችንን ከፍ የማድረግ እና የለውጥ ሠራዊት መሆን ይገባናል ሲሉ የሥልጠና ተሳታፊውን አነቃቅተዋል።
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ ወጣት ሙሐመድ አሕመድ በበኩሉ ሊጉ ከተመሠረተ ጀምሮ የከተማውን ወጣቶች በማደራጀትና በማንቃት ሰፊ ሥራ መሥራቱን ተናግሯል።
ወጣትነት ለትልቅ ኃላፊነት የሚታጩበት መሠረት በመሆኑ የከተማውን የወጣት ሊግ አመራር አቅም ለማሳደግ ይህን መሰል የስነ-ምግባር ሥልጠና ትልቅ ግብዓት የሚገኝበት መሆኑን ተናግረዋል።
በሥልጠናው ላይ በዶክተር ዱረቲ ቃሲም "የዘመኑ የወጣቶች ፈተና" በሚል ርዕስ ጽሑፍ የቀረበ ሲኾን፣ ወጣቶች ለሱስ ተጋላጭ የሚሆኑበት ገፊ ምክንያት፣ የባህሪ ለውጥ፣ የዕድገት ሂደት፣ ማኅበራዊና ስነ ልቦናዊ ጫና መሠረት ያደረጉ ሳይንሳዊ የግንዛቤ ማብራሪያዎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በዑስታዝ አሕመድ ሙስጠፋ "ስነ-ምግባር በሁለቱ ዓለም፣ ለማኅበረሰባዊ ግንባታ - እስላማዊ ዕይታ" በሚል ርዕስ ስነ-ምግባር ለማኅበረሰብ ግንባታ ያለውን እሴት ከግለሰባዊ፣ ቤተሰባዊ እና ከሀገራዊ ኃላፊነት አኳያ አሳታፊ የሆነ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ከሱስ የፀዳ ትውልድ እና ጤናማ ማኅበረሰብ ለመፍጠር ለወጣቶችና ለሴቶች ትኩረት በማድረግ መሰል ሥልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ተነግሯል።
••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት።
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc13
Telegram
Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት