የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.67K subscribers
9.62K photos
133 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
41 ቤተ ክርስቲያናት የተሳተፉበት ናሽናል ዩዝ ኮንፍረንሥ በኦክላሆማ ዩኒቨርስቲ መካሄዱ ተገለጸ።

73ኛ ብሔራዊ የወጣቶች ኮንፍረንስ ከ400 በላይ ወጣቶች እና 100 ጎልማሶች የተገኙበት ሲሆን በያዝነው የፈረንጆች አመትም በኦክላሆማ ተካሂዷል። ይህን ያህል ቁጥር ያላቸው ወጣቶች ሲሥታፉም በባለፈው አምስት አመታት ውስጥ ይሄ ከፍተኛው ቁጥር ነው።

በ16 ግዛቶች ከሚገኙ 41 ቤተ ክርስቲያኖች የተወጣጡ ወጣቶች በኮንፍራንሱ ላይ የተገኙ ሲሆን ኮንፍረንሱም አምልኮን፣ ጨዋታዎችን እንዲሁም መንፈሳዊ መዋቅር የተደረገበት ነበሩ።

የኦክላሆማ ግዛት ሴናተር የሆኑት ኒኪ ናይስ የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ፕሮግራሙን የከፈቱት ሲሆን ወጣቶች በእምነታቸው ጠንካራ እንዲሆኑና ወደ ነበሩበት ማህበረሰብ ሲመለሱም እውነተኛ ክርስቲያናዊ ማንነታቸውን እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል።

የኮንፍረንሱ ዋና ሰብሳቢ የሆኑት ራሞን ሆህሪጅ በተለያዩ ቤተ እምነቶች መካከል ጠንካራ የሆነ ግንኙነት ሊኖር እንደሚገባ ተናግረዋል።

በከሰዓት በነበሩት ፕሮግራሞች ላይ ብዙ ወጣቶች መንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲታደስ ወደ መድረክ ሲመጡ የተስተዋሉ ሲሆን “ወጣት እንዴት ልቡን ይጠብቃል?” የተሰኘው ዝማሬ በተደጋጋሜ እንደተዘመረ ተገልጿል።

መረጃውን ከክርስቲያን ክሮኒክልስ ድረ ገጽ አገኘነው።

ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ አማኑኤል ዴቢሶ
7
በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ከቀደምት አገልጋዮች አንዱ የሆኑት ፓሰተር ፍቃዱ ኦፍጋ ከዚህ አለም ድካም አረፉ።

በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን ከቀደምት አገልጋዮች አንዱ የሆኑት እና በቀጠና ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስትያን ሲያገለግሉ የነበሩት ፓሰተር ፍቃዱ ኦፍጋ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል።

መጋቢ ፍቃዱ ግማሽ ክፍለ ዘመን የዘለቀው አገልግሎታቸው የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤ/ክ ከምስረታዋ ጀምሮ አስከ ዛሬ ድረስ በጸሎት ፤ በወንጌል ሰባኪነት ፤ በመጋቢነት በማግልገል ከብዙዎች ጋር ስለወንጌል ዋጋ የከፈሉ የወንጌል አርበኛ ነበሩ።

ነሐሴ 12፣ 2017 ዓ.ም የአስክሬን ሽኝት ስነስርዓት በቀጣና ሁለት ሙሉ ወንጌል አጥቢያ ቤተክርስትያን የተከናወነ ሲሆን የቀብር ስነ ስርዓቱም በዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን መካነ መቃብር ተከናውኗል።

ኢቫንጃሊካል ቴሌቪዥን በመጋቢ ፍቃዱ ዜና እረፍት የተሰማውን ሃዘን እየገለጸ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።
5🙏3
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ክልሎች ጠቅላላ ጉባኤዎቻቸውን አካሄዱ።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የወንጂና አካባቢው ጊዜያዊ ክልል፣ አዋሽ ሸለቆ ክልል፣ የደቡብና ሰሜን አዳማ ክልሎች እንዲሁም የምስራቅ ኢትዮጵያ ክልል ከነሃሴ 9-11/2017 ዓ.ም የክልል ጠቅላላ ጉባኤዎችን አካሂደዋል።

በክልሎቹ በተካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ከዋናው ቢሮ በተወከሉ ኃላፊዎች በ2016 ዓ.ም በተሻሻለው ውስጠ ደንብ ላይ ገለጻ ሲደረግ የ2017 ዓ.ም ሪፖርትና የ2018 ዓ.ም እቅድ በክልሎቹ ዋና ጸሐፊዎች ቀርቧል። እንዲሁም የክልል ዋና ጸሐፊና አስተዳደር መሪዎች ምርጫ ተከናውኗል።

መረጃው የመሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው።
11
ዛሬ ነሐሴ 15/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ አንድነት በክርስቶስ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት 7ተኛ ጠቃላላ ጉባኤውን ጥሪ የተደረገላቸው ተጋባዥ የክብር እንግዶች ፣ የካውንስሉ አመራሮች ፣ የአብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዚደንቶች እንዲሁም የህብረቱ አባላት በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ በጉዲና ቱምሳ ሁለንታናዊ የስልጠና ማዕከል አካሂዷል።

መርሃ ግብሩን ፓስተር አስፋው በጸሎት ካስጀመሩ በኋላ አምልኮተ እግዚአብሔር ተከናውኗል። በመቀጠልም በሲዳማ ክልል ወንጌል ለዓለም ፍጥረታት ቤተ ክርስቲያን ባለ ራዕይ እና ፕሬዚደንት እንዲሁም የእምነት አባት የሆኑት ሐዋሪያ ዳኒሶ ሉምቤ በሲዳመኛ ቋንቋ መልዕክታቸው አስተላልፈው ኅብረቱን ባርከዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ምክትል ፕሬዚደንት የሆኑት ሐዋሪያ ዩሃንስ ግርማ የእግዚአብሔር ቃል አካፍለዋል።


የኢትዮጵያ አንድነት በክርስቶስ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያን ኅብረት ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ስራ አስፈጻሚ አመራር ሐዋሪያ እዩኤል አብርሃም ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የመክፈቻ ንግግግር አድርገዋል። በመቀጠልም የኅብረቱ ፕሬዚደንት ታምሩ ዋቸጎ እንዲሁም የህብረት ጠቅላይ ጸሐፊ ሐዋሪያ ተሰማ ሀብተወልድ ለህብረቱ አባላት እና ተጋባዝ እንግዶች የእንኳን ደህና መጣችሁ እንዲሁም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመቀጠልም የህብረቱ ምክትል ፕሬዚደንት ዶክተር አማኑኤል አብርሃም የተገኙ የክብር እንግዶችን ለህብረቱ አባላት መልዕክት እንዲያስተላልፉ ጋብዘዋል።

የኅብረቱ ዋና ሰብሳቢ እና የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ስራ አስፈጻሚ አመራር የሆኑት ሐዋሪያ እዩኤል አብርሃም በንግግራቸው ለተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም ለህብረቱ አካላት እንኳን አደርሳችሁ ብለው በዛሬው ጉባኤ ኅብረቱ ለ5 አመታት የሚጠቀምበትን ስትራቴጂ ካለፉት ሪፖርቶች በመነሳት እንዳጸደቁ እንዲሁም ለሁለት አመታት የተስሩቱ የክንውን ሪፖርት እንደሚቀርብ ተናግረው እግዚአብሄር እንዲሁም የተገኙ የክብር እንግዶችን አመስግነዋል።

የህብረቱ ምክትል ፕሬዚድንት የሆኑት ዶከተር አማኑኤል አብርሃም የዛሬውን ጉባኤ አስመልክቶ ኅብረቱ እየሰራ ስለሚገኝባቸው ዘርፎች ተናግረው በዝግጅቱ ላይ የተገኙ አካላትን አመስግነዋል።

የኅብረቱ ጠቅላይ ጸሃፊ የሆንቱ ሐዋሪያው ተሰማ ሀብተወልድ በእለቱ ትልልቅ ውሳኔዎችን እንዳሳለፉ ተናግረዋል።
1