የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል ECGBC
9.7K subscribers
9.14K photos
131 videos
1 file
1.55K links
ይህ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውስንል የቴሌግራም ቻናል ነው።

"ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ፤ እነሆ፤ መልካም ነው፤ እነሆም፤ ያማረ ነው።
Download Telegram
ኢንተርዲኖሚኒሸናል የስነ መለኮት ኮሌጅ ለ12ኛ ዙር ክርስቲያናዊ ማማከር በሚል ርዕሰ ስልጠና እየተሰጠ ነው ።


ኢንተርዲኖሚኒሸናል የስነ መለኮት ኮሌጅ ለ12ኛ ዙር የማማከር አገልግሎት ስልጠና የሰጠ ሲሆን በ2017 ብቻ ለ3ኛ ዙር እየተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህ ሰልጠና ላይ ከኢትዮጵያና ከኤርትራ የመጡ ከ150 በላይ ለሆኑ ለቤተክርስቲያን መሪዎች፣ መጋቢያን እና ለማማከር አገልጋዮች ከሐምሌ16-18 ቀን 2017 ዓ.ም በተቀባ ቃል ቤተክርስቲያን ስልጠናውን በመውሰድ ላይ ናቸው።

ከወጪ ሀገር በመጡት ለ32 አመት በማማከርና በሚሽን ላይ በሚሰሩት በዶ/ር ራቪ ዳንኤል ስልጠናው እየተሰጠ ነው።

የኮሌጁ ደይሬክተር ዶ/ር ታምራት ወርቁ ይህን ስልጠና ለየት የሚያደርገው ክርስቲያናዊ ማማከር ፣ማማከር ምንድነወ ፣በተለይም በቤተክርስቲያን ምን የማማከር ጉደዮች አሉ? በሚሉ አሳቦች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተናግረዋል።ዳይሬክተሩ አክለውም ስልጠናው በቀጣይነትም የሚቀጥል እንደሆነም ገልፀዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች ለኢሻኒጀሊካል ቴለቪዥን እንደተናገሩት ለግል ሕይወታቸውና በቤተክርስቲያን ውስጥ ላላቸው አገልግሎት ሰዎችን ለማገዝ ጠቃሚ የሆነ ስልጠና እንደሆነ አንስተዋል።

ኢንተርዲኖሚኔሽናል ቲዮሎጂካል ኮሌጅ በኢሻንጀሊካል ኢንተርዲኖሚኔሸናል እንተርናሽናል ሚኒስትሪ ስር የሚሰራ ኮሌጅ ሲሆን ሚኒስትሪው በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል በመመዝገብ አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ ተቋም ነው።

ለኢቫንጀሊካል ቲቪ ፡ ቤተልሔም ደረጄ